✞ ኤፍታህ በማለዳ
📣ይህ ✞ ኤፍታህ በማለዳ የተባለው ኦርቶዶክሳዊ ዕውቀትን መማማሪያ እንዲሁም ስለሀይማኖታችን እንድናቅና "የሰው ጠላት የለኝም" በማለት ጠላታችን ዲያብሎስን በመቃወም ከክርስቶስ ጋር በመሆን ለበረከትና ለፀጋ በመትጋት መንግስትቱን ለመውረስ የምንማማርበት ነው። እግዚአብሔር ይርዳን። በተከከታታይ የማንቂያ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶችን በኤፍታህ ይጠብቁን። @Eftah_bemaleda
Mostrar másEl país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
687
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
Photo unavailableShow in Telegram
ሂዱ ንገሩ አውሩ ለዓለም ተነስቷል በዚህ የለም #መድኃኔዓለም
@Eftah_bemaleda
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቸነከረባቸዉ አምስቱ ችንካሮች (ሚስማሮች) ስም፦
#1ኛ ሳዶር
#2ኛ አላዶር
#3ኛ ዳናት
#4ኛ አዴራ
#5ኛ ሮዳስ
አምስቱ የእመቤታችን ኃዘናት፦
#1ኛ ከአምስቱ አንዱ አይሁድ እንዲገድሉክ በቤተ መቅደስ ስምዖን ትንቢት በተናገረ ጊዜ ነዉ።ሉቃ 2÷34
#2ኛ ሁለተኛዉም ሦስት ቀን በቤተ መቅደስ ባጣሁህ ጊዜ ነዉ።ሉቃ 2÷41
#3ኛ ሦስተኛዉም እጅህን እግርህን አስረዉ በጲላጦስ አደባባይ የገረፉህን ግርፋት ባሰብኩ ጊዜ ነዉ።ዮሐ19÷1
#4ኛ አራተኛዉም በዕለተ አርብ እራቆትህን ቸንክረዉ በሁለት ወንበዴዎች መካከል እንደሰቀልኩ ባሰብኩ ጊዜ ነዉ አለችዉ። ዮሐ19÷17
#5ኛ አምስተኛዉም ወደ ሐዲስ መቃብር ዉስጥ እንዳወረዱህ ባሰብኩ ጊዜ ነዉ።ዮሐ 19÷38
ጌታ እኛን ለማዳን በመስቀል ላይ በተሰቀለ ጊዜ የተፈፀሙ 7ቱ ተአምራት፦
#1ኛ ፀሐይ ጨልሟል
#2ኛ ጨረቃ ደም ሆነ
#3ኛ ከዋክብት እረገፉ
#4ኛ ዓለቶች ተሰነጠቁ
#5ኛ መቃብር ተከፈቱ
#6ኛ ሙታን ተነሱ
#7ኛ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለሁለት ተቀደደ
ሰባቱ የመስቀል ላይ ንግግሮች፦
#1ኛ አምላኬ አምላኬ ለምን ተዉከኝ።ማቴ 27÷46
#2ኛ አባት ሆይ የሚያደርጉት አያዉቁምና ይቅር በላቸዉ።
ሉቃ 23÷34
#3ኛ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር እንድትኖር በእዉነት እነግረሃለሁ።
ሉቃ 23÷43
#4ኛ እነሆ ልጅሽ አነዃት እናትህ።ዮሐ 19÷26
#5ኛ ተጠማሁ።ዮሐ 19÷28
#6ኛ አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ።ሉቃ 23÷46
#7ኛ የተፃፈ ሁሉ ደረሰ ተፈፀመ አለ።ዮሐ19÷30
የአምላካችን ቸርነትና የእመቤታችን ምልጃ አይለየን አሜን ፫
❤️ @Eftah_bemaleda
" ሕማማት መስቀል" ተብለው የሚዘከሩት አሥራ ሦስት ሲሆኑ እነዚህም፦
1. በብረት ሐብለ መጋፊያና መጋፊያው እስኪጋጠም ድረስ የኋሊት መታሰሩ
2. ከአፍንጫው ደም እስኪውጣ ድረስ 25 ጊዜ በጡጫ መመታቱ
3. 65 ጊዜ ከግንድ ማጋጨታቸው
4. 120 ጊዜ በድንጋይ ፊቱን መመታቱ
5. 365 ጊዜ በሽመል መደብደቡ
6. 80 ጊዜ ጽህሙን መነጨቱ
7. 6666 ጊዜ መገረፉ
8. አክሊለ ሦክ በራሱ ላይ መደፋቱ
9. 136 ጊዜ በምድር ላይ መውደቁ
10. ሳዶር፡ አላዶር፡ ኤዴራ፡ ዳናትና ሮዳስ በሚባሉ 5ቱ ቅንዋተ መስቀልበችንካር መቸንከሩ
11. መራራ ሐሞትን መጠጣቱ
12. መስቀሉን ተሸክሞ መንገላታቱ
13. በመስቀል መሰቀሉ ናቸው።
💛 @Eftah_bemaleda
ሕማምህን ላስብ
ከእኔ ምን አይተህ ነው
እንዴት ብትወደኝ ነው
ግርፋቴን ወስደህ አንተ የተገረፍከው
ከኔ ምን አይተህ ነው
እንዴት ብትወዳኝ ነው
እኔ እንድናገር አንተ ግን ዝም ያልከው
እንዴት ብትወደኝ ነው
ማንስ ለጠላቱ ይህን ያህል ይደክማል
እራሱንስ ለሞት አሳልፎ ይሰጣል
ያንተ ግን ይለያል
ያንተ ግን ይደንቃል
ከርስት ልትመልሰኝ የህማም ሰው ሆነሀል
ህማምህን ላስብ ሞትህን ልናገር
የከፈልክልኝን የመዳኔን ነገር
በለሷ ለምልማ በቅጠል ብታምር
ፍሬ ግን የላትም ላንተ ሚሆን ነገር
አንተ ግን ስለኔ ብዙውን ሆነሀል
እርቃንህን ተሰቅለህ እኔን አልብሰሀል
ህማምህን ላስብ ሞትህን ልናገር
የከፈልክልኝን የመዳኔን ነገር
እንዳላየ አልፎኛል ሌዋዊውም ካህኑ
አለም እንደዚህ ናት ከጨለመ ቀኑ
በዘይት ጠገንከኝ በወይንህ አከምከኝ
በያሪኮ መንገድ ቆስየ ብታየኝ
ህማምህን ላስብ ሞትህን ልናገር
የከፈልክልኝን የመዳኔን ነገር
ፍቅርህ ይበረታል ፍቅርህ ይለውጣል
ያየሁት መዳፍህ ልቤን ቀስቅሶታል
ይህ ሁሉ ለእኔ ነው መከራ ህማሙ
እንደ አዲስ ፈጥሮኛል በከበረ ደሙ
ህማምህን ላስብ ሞትህን ልናገር
የከፈልክልኝን የመዳኔን ነገር
@Eftah_bemaleda
_ሕማምህን_ላስብ_ዘማሪት_ሲስተር_ዮርዳኖስ_ምስጋናው_ቤተ_ቅኔ_Beta_QeneMP3_70K.mp36.24 MB
ያለን #አንድ ነው፤ ነገር ግን ሁሉን መሆን ይችላል!! እርሱም፦ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
❝ጴጥሮስ ግን፦ ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን #ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።❞
ሐዋርያት 3፥6
Join - @Eftah_bemaleda
Photo unavailableShow in Telegram
መጋቢት ፳፯ በዚህች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ! "ሊቃነ መላዕክት በመፍራትና በመንቀጥቀጥ ከፊቱ የሚቆሙለትን በአደባባይ አቆሙት፤ ኃጢአትን ይቅር የሚለውን ኃጥእ አሉት፤በመኳንንት በሚፈርደው በርሱ ፈረዱበት!"
Join - @Eftah_bemaleda
ማን ያምናል አሁን የእኛን መዳን
በአለም እርኩሰት ለሚያውቀን
እንዲሁ ነጻ ናችሁ ያልከን
ተባረክ ፈቅደህ የባረከን
ኑሮአችን ነበር የጨለማ
ምንቀኝ የአልምን ዜማ
ሳንጠፋ ሳንገባ ከጥልቁ
ተማርን ታይቶልን ሰንደቁ
Join - @Eftah_bemaleda
ምህረቱ ለዘላለም ነውና
ቸርነቱ ለዘላለም ነውና
እግዚአብሔርን አመሰግኑ
ከመከራ ዘመን መራመጃ ሆኖ
ልጆቹን ያወጣ በግርማው ሸፍኖ
ይጋር ሰሀዶታ የጸጥታ ወደብ
ወደ ተጨቆኑት በፍትህ የሚቀርብ
የእስራኤልን ቅዱስ አመስግኑ
መልካሙን እረኛ አመስግኑ
ለድሆች የሚፈርድ አመስግኑ
እውነተኛ ዳኛ አመስግኑ
@Eftah_bemaleda
“…እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ እናንተ ታለቅሳላችሁ ሙሾም ታወጣላችሁ፥ ዓለም ግን ደስ ይለዋል፤ እናንተም ታዝናላችሁ፥ ነገር ግን ኀዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል። ሴት በምትወልድበት ጊዜ ወራትዋ ስለ ደረሰ ታዝናለች፤ ነገር ግን ሕፃን ከወለደች በኋላ፥ ሰው በዓለም ተወልዶአልና ስለ ደስታዋ መከራዋን ኋላ አታስበውም። እንግዲህ እናንተ ደግሞ አሁን ታዝናላችሁ፤ ነገር ግን እንደ ገና አያችኋለሁ ልባችሁም ደስ ይለዋል፥ ደስታችሁንም የሚወስድባችሁ የለም።”
ዮሐ 16፥ 20-23
@Eftah_bemaleda