cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Ramz Tube (Ibn Suleyman)

"የተሰበረ ልባቸውን ጠግኑ፤ ስሜታቸውን ጠብቁ፤ ቃላት ምረጡ፤ ድርጊታችሁን አለስልሱ፤ መልካም ትድድርን አትርሱ፤ ማንንም አታቁስሉ፤ በንፅህና በቀናነት ኑሩ። ይህ የነቢያት መንገድ፣ የመልካሞች መንገድ ነው።" for any coment @ibn_suleyman01 & @Adham_Tube_inbox_bot ✍............🌺🌺🌺..............☘☘

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
502
Suscriptores
Sin datos24 horas
-17 días
-1130 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ምን ይናፍቅሃል አትሉኝም ? ያች የድሮዋ ነፍሴ ናት የምትናፍቀኝ። አሁንማ ደክሞኛል ትንሹ ፈተና ሁሉ በቀላሉ ይጥለኛል። ጌታዬ ሆይ እኔ መጥፎ ነኝ። ከለላህ አይራቀኝ። እኔን ለኔ አትተወኝ። ©Abx @Ibn_Suleyman
Mostrar todo...
Ramz Tube (Ibn Suleyman)

"የተሰበረ ልባቸውን ጠግኑ፤ ስሜታቸውን ጠብቁ፤ ቃላት ምረጡ፤ ድርጊታችሁን አለስልሱ፤ መልካም ትድድርን አትርሱ፤ ማንንም አታቁስሉ፤ በንፅህና በቀናነት ኑሩ። ይህ የነቢያት መንገድ፣ የመልካሞች መንገድ ነው።" for any coment @ibn_suleyman01 & @Adham_Tube_inbox_bot ✍............🌺🌺🌺..............☘☘

😢 1
Repost from "ኡማ ቲቪ " Tv
በኮዬ ፈጬ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት "ጆሮ ከሚያሳይ ሂጃብ" ውጪ ምንም አይነት ኢስላማዊ አለባበስ ለብሶ ለፈተና መቀመጥ መከልከሉ ተገለፀ! .. ... በሸገር ሲቲ ኮዬ ፈጬ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በቀጣይ ሀምሌ ወር ላይ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍለ ዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና በተመለከተ ከተማሪ ወላጆች ጋር ስብሰባ ማድረጉ የተገለፀ ሲሆን በስብሰባው ወቅትም በተለይ ከሙስሊም ተማሪዎች ጋር በተያያዘ "ጆሮ ከሚያሳይ ሂጃብ ውጭ" ምንም አይነት ኢስላማዊ አለባበስ ለብሶ ለፈተና መቀመጥ አይችሉም በማለት ውሳኔ ማሳለፉን በስብሰባው ተሳታፊ የነበሩ የተማሪ ወላጆች ለሀሩን ሚዲያ ገልጸዋል። . እንደወላጆቹ ገለፀ ውሳኔው የመጣው ከፌዴራል ትምህርት ሚኒስቴር ነው መባላቸውን ተናግረው በዚህ ምክንያት አስራሁለት አመት ሙሉ የለፉ ልጆቻችን ምን እንደምናደርግ ግራ ገብቶናል ብለዋል።አዲስ የወጣው ገና ልፀደቀው የትምህርት ሚኒስቴር መመሪያ "አንቀፅ 6፡ የፊት መሸፈኛን ገልጦ የአንድን ሰው ፊት ለሴት ፈታኝ ወይም ለማንኛውም ሴት የፈተና ተቆጣጣሪ እና በወንድ ፈታሽ ወይም ለፈተና ጣቢያ ኋላፊው/ አስተዳዳሪው የፈተና በር ላይ የተሸፈነውን የተፈታኝ ተማሪ ፊት ማንነት እንዲያውቅ ፈቃደኛ መሆን አለበት"የሚል ሲሆን ነገር ግን ከዚህ በተቃራኒው ጆሮ ከሚያሳይ ሂጃብ ውጪ ያሉ ኢስላማዊ አለባበስ መከልከላቸውን ነው የተማሪዎቹ ወላጆች የገለፁት። . በጉዳዩ ዙሪያ የሸገር መጅሊስ እንዲሁም የኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ መጅሊስን ሀሩን ሚዲያ ያነጋገረ ሲሆን "ችግሩን ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶችን ማድረጋቸውን ገልፀው ነገር ግን ከአቅማችን በላይ ነው ብለዋል።ሀሩን ሚዲያ ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ የኮዬ ፈጬ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርን ለማነጋገር የሞከረ ቢሆንም ምላሽ ሳይሰጡ ቀርተዋል።
Mostrar todo...
2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
አስቸኳይ አስቸኳይ የወንድማችን የየቲሞች አጋዥ የሆነው ወንድማችን ዘይኑ መኪና አሁን 11:15 ላይ ከስራ ቦታ ከሆነው አዲስ ሰፈር አስኮ አፍናን ካፌ በር ላይ በሌቦች ተወስዶብናል የታርጋ ቁጥር አአ 29921 ኮድ 3 ሲልቨር ከለር ዶልፊን አይናማው 0911958452/0911715649 መረጃወችን ለወዳጄ ዘመድ ሼር ያርጉ! የቴሌግራም ቻናላችን ከስር በሊንኩ ይቀላቀሉ👇 https://t.me/+UAKV32q7U2HKzEMf
Mostrar todo...
ኢና ሊላሂ ወዒና ኢለይሂ ራጂዑን የውዱ ኡስታዛችን ኡስታዝ አቡበክር  ባለቤት ሃናን ወላጅ አባት የሆኑት ሐጂ መሀመድ አባዱራ ወደ አኼራ አልፈዋል: ስርአተ ቀብራቸውም  በጅማ ከተማ የሚፈፀም ይሆናል:: አላህ ይዘንላቸው
Mostrar todo...
😭 3👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
ዕለቱን በታሪክ የዛሬ 18 አመት በዛሬዋ እለት ማለትም ሰኔ 25 ቀን 2006 የአልቃሳም ብርጌድ እና አል ናስር ሳላህ አልዲን ብርጌድ በዋሻዎች ዉስጥ ድንበር ተሻግረው ባካሄዱት አስገራሚ ዘመቻ አሸባሪውን ጊላድ ሻሊትን ድንበር ላይ እያለ ከታንኩ ውስጥ በቁጥጥር ስር ማዋል ችለዋል። አል-ቃሳም ብርጌድ አሸባሪውን ከ5 ዓመታት በላይ በማቆየት 1,027 የፍልስጤም እስረኞች በአንድ አሸባሪ ምትክ የተፈቱበትን ታሪካዊ የእስረኞች ልውውጥ ስምምነት በማድረግ በጥቅምት 18 ቀን 2011 ከእስራኤል ጋር በተደረገው ስምምነት ጊላድ ሻሊትን ለቀቀው። በዛኔው ታሪካዊ ድል ከተፈቱት የፍልስጤም እስረኞች መካከል ኮማንደር የህያ ሲንዋርን ጨምሮ 208ቱ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው የሚገኙ ነበሩ። መሀመድ @Palestine_quds
Mostrar todo...
👍 2
🥰 3
Photo unavailableShow in Telegram
«ይህች ዐለም ልክ እንደ ተራራ ናት። ድምፅህ በአንተ ላይ የተመሠረተ ነው። በመልካም ድምፅ ስትጮህ በመልካሙ ይመልስልሀል... በመጥፎ ድምፅ ስትጮህ ራሱን መጥፎውን ደግሞ ያሠማሀል። ዱንያም እንዲህ ናት አንድ ሠው ስላንተ መጥፎ ቢናገርም አንተ ስለ እርሱ መልካም ተናገር ... አለምን ትለውጥ ዘንዳ ቀልብህን ቀይር»✨🦋 ሠይዲ ሸምስ አት-ተብሪዝ https://t.me/Strong_iman
Mostrar todo...
👍 3🥰 1
🌹 ሳንፈልጋቸው ቀርበውን ስንፈልጋቸው ከሚርቁን ቅስም ሰባሪና አስመሳይ ሰዎች አላህ ይጠብቀን። 🖊💝
Mostrar todo...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
⌛3 ቀን ብቻ ቀረ!⌛ ኢስላምን ለመተግበር ህግጋቱን ማወቅ አስፈላጊ ነው። የኢስላማዊ ህግጋት ጥናት ዘርፍ ፊቅህ ይባላል። ታዋቂ ከሆኑ የፊቅህ መዝሀቦች (አስተሳሰብ ትምህርት ቤቶች) መሀከል የሆነው ፊቅህ አሻፊዒያ የመጀመሪያ ኪታብ የሆነችውን ሰፊነቱ ነጃ መማር ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ብዙ ምሁራን መስክረዋል። ሰፊነቱ ነጃ ማለት የመዳኛይቱ መርከብ ማለት ሲሆን በአምልኮ ተግባራቶቻችን ስኬታማ ሆነን እንድን ዘንድ ሁነኛ ሚና ያላት ኪታብ ነች። በሀገራችንም የሀይማኖት ትምህርት ጀማሪዎች የሸሪዓ እውቀትን የሚጀምሩባት ኪታብ ነች። በኪታቧ አንድ ሙስሊም ሊያከናውናቸው የሚገቡ መሰረታዊ አምልኳዊ ተግባራት ህግጋት በግሩም ሁኔታ ቀርበዋል። እርስዎም ሀይማኖታዊ ግዴታዎትን በእውቀት ላይ ተመስርተው ያከናውኑ ዘንድ ለማገዝ አልገዛሊ አካዳሚ ይህን አድል አመቻችቶላችኋል። የትምህርት አሰጣጡ ሙሉ በሙሉ በኦንላየን የቀጥታ ስርጭት (LIVE) ሲሆን በተጨማሪም ለትምህርት አሰጣጥ ሂደቱ ውጤታማነት አጋዥ የሆኑ የትምህርት ግብአቶችን ያገኛሉ። ትምህርቱ የሚጀምረው ጁን 22/2024 ወይም ሰኔ 15/2016 ዓ ል ሲሆን ለተከታታይ 12 ሳምንታት ዘወትር ቀዳሜ ማታ 2:30–3:15 በቀጥታ ስርጭት ይተላለፋል። በትምህርቱ ማጠናቀቂያም ፈተና የሚኖር ይሆናል። በስኬት የሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ሰርተፍኬት የሚያገኙ ሲሆን ወደቀጣይ ምዕራፍ በመሸጋገር የእውቀት አድማሳቸውን የሚያሰፉበት እድል ተመቻችቷል። ያለን ቦታ ውስን በመሆኑ ዛሬውኑ ተመዝግበው ቦታዎትን ይያዙ። ለመመዝገብ ከስር ያለውን ሊንክ ይጫኑ https://forms.gle/35MjjTBNxhkyiBH66 ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም @algazaliacademyadmin ወይም በዋትስአፕ https://wa.me/251984109507 ያናግሩን
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.