ገብርኤል ሀያሉ
ምድር በጨለማ፥ስትኖር በመርገም
መፈፀሚያዉ ሲደርስ፥ቃሉ የመዳኒያለም
ንፅይት ከሆነችዉ፥ከድንግል ሊወለድ
የተከመረዉን፥የአለም ሀጢያት ሊንድ
፤
ገብርኤልን ላከዉ፥ብሎ እናቴን አብስር
በክብርም ስገድ፥ዉደቅ ከእግሮቿ ስር፤
፤
አለና ፈጣሪ፥መልእክቱን ጨርሶ
የብርሀንን ፋና፥ገብርኤልን አልብሶ
የዘካርያስንም፥ብስራቱን አስታዉሶ
እንዲህ አለ አምላክ፤
ለአብሳሪዉ መለአክ፤
፤
ታዲያ ስታበስራት፥ወደጄ ገብርኤል
እንደ ዘካርያስ እንዳትደናገጥ፥ባርካት በሀይለ ልኡል፤
፤
አለዉ እግዚአብሔሄር
ለገብርኤል ሲያሳይ፥የእናቱን ክብር፤
፤
ገብርኤልም ከአምላክ፥ምስራቹን ይዞ
ከሰማይ ወረደ፥በደስታ ተጉዞ፤
፤
ከተባለችዉም፥ከማርያምም ሲደርስ
በደስ'ታዉ ብዛት፥ዉስጡ ስትላወስ
የአምላኩን እናት፥ስላየ ተደንቆ
ይስግድላት ጀመር፥ከእግሯ በታች ወድቆ።
፤
እሷም በመላእኩ፥ግራማ እየፈራች
ሚሆነዉን ሁሉ፥መመልከት ጀመረች፤
፤
ቀጠለ ገብርኤል፥በደስታ ተሞልቶ
ደስ ይበልሽ አላት፥ክንፎቹን ዘርግቶ፤
፤
ከአለም ሁሉ ሴቶች፥አንቺ ትለያለሽ
የአለሙን ብርሀን፥ጌታን ትወልጃለሽ
ስሙንም ኢየሱስ፥ብለሽ ትይዋለሽ፤
፤
አላት ገብርኤል' ለማርያም---ማር በሆነ ቃሉ
ወድቆ በመስገዱ፥ሳይነጥፍ ፀዳሉ፤
፤
በዚ ድንቅ ብስራት፥ማርያም ደነገጠች
እንዲህ በትህትና----እራሷን ዝቅ አርጋ፥መላእኩን ጠየቀች፤
፤
እንዲህ ያለ የእጅ መንሻ ይደረግልኛልን?
አምላኬስ በእኔ ዘንድ ሊወለድ እገባዋለዉን?
፤
አለች አዛኚቷ፥እራሷን አዋርዳ
በአምላኳም ፍቅር፥እሩቅ አለም ነጉዳ
፤
ሄደች. . ሄደች. . . ሄደች ---- እራቀች በሀሳቧ
፤
ንፋሳቱን አልፋ፤
ደመናን ተላልፋ፤
ማእበሉን ቀዝፋ፤
፤
ከልብ ምኞቷ፥ልትደርስ ከአምላክ እናት
ባርነትን ሽታ፥አሽከር ልትሆናት
አስባ ነበረ፥ልታገለግላት፤
፤
ገብርኤልም አይቶ፥የማርያምን ፍቅር
ቃላትን ለማዉጣት፥አፉ ቢተሳሰር
ብስራቱ ነዉ እና፥ቃሉ የእግዚአብሔሄር
እሺ ይሁንልኝ፥ብላ ተቀበለች ስለ ጌታ ክብር፤
፤
ገብርኤልም ለሷ፥ክብሩን ገለጠላት
ትሆናለች እና፥ለወልድ እግዚአር እናት፤
፤
አባ ገብርኤሌ
-------------------- --------------------
አባ ገብርኤሌ፤አንተ አባት አለም
ለኛ ስጦታ ነህ፥ብርሀን ለአለም፤
፤
ምንኛስ ድንቅ ነዉ፥የተሰጠህ ክብር
በብስራትህ ብቻ፥ምትሰራዉ ተአምር፤
የደስታችን መለአክ፥የማትመረመር፥
አረ የማትለወጥ፥ፍቅር ነህ ዘላለም፤
፤
ገብርኤሌ፤ አባ
አቤቴ ልበልህ፥አንተም በለኝ ልጄ
ምንም ፅድቅ የለኝም፥ባዶ ሆኖል እጄ፤
፤
እኔም ያሳደከኝ፥ይኸሄዉ ያንተዉ ፍሬ
አንተዉ ባስተማርከኝ፥በህይወት መምህሬ
ለማርያም" ሰግደ፥ባረከዉ ሰላምታ
እሷም ደስ እንዳላት፥ምስራቹን ሰምታ፤
፤
ለምስራች ባይሆን፥ለሷ የኔ ሰላምታ
እኔም ልሳለማት ጠላቴም ይመታ
ለክብሯ መግለጫ፥ያንተን ስም በመጥራት፥ከፊቷ ወድቄ
በገብርኤል ሰላምታ፥ስላም እላታለዉ በፍቅሯ ነጥቄ፤
፤
አባት አለም፥ዜናዊ ሀዲሱ
እናቱን እናቴን ደስታ ይገባልሻል፥ያልካት በመቅደሱ፤
ዳንኤልን ከጉድጓድ፥ከተራቡ አናብስ፥እንዳዳንክ ከነሱ፤
፤
ለሶስቱ ህፃናት፥ለፀኑት በእምነት
ፈጥነህ እንዳጠፋህ፥ሚነደዉን እሳት፤
፤
ለህፃኑ ቂርቆስ፥መከታ በመሆን
እንዳቀዘቀዝከዉ፥ዉሀ ሚፈላዉን፤
፤
ዛሬም በአንተ ረድኤት፥በረከት ተማምና
ምትኖረዉ ሀገሬን፥በሀጢያት ዘምና
፤
ዘረኞች ባፈሉት በሚፍለቀለቀዉ፥በእርኩሳን ሀሳብ
ልጆቿ አለቀዉባት፥በ ባለ ጊዜዎች፥ወደዛ ብትሳብ፥
፥
ወገን በወገኑ---ወንድም በወንድሙ፥ሲጨካከን አይተህ
ሀገሬ ኢትዮጲያ ይህን ሁሉ ነገር፥ፈልጋ እንዳልሆነ ከልብህ ተረድት
የአርባቡ አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ፥እንለምንሀለን እንድትረዳን መተህ።
-------------------------------------------------------------------------
የገጣሚዉ ፀሎተ ምርቃት
ይቺ የኔ ፀሎት፥ከታች የማሰፍራት
ከልብ ለተረዳዉ፥የሆነች ምርቃት
ቃላቷ ቢቀልም፥ሀሳቧን አክብጄ
ለአምላክ ልነግረዉ ነዉ፥ደጀ ሰላም ሄጄ ።
፤
እንግዲ ወገኔ፥ፀሎቴ እንዲያርግ
መስዋቴ እንዲሆን፥ልክ እንደ አብርሀም በግ፤
እሱም እንዲሰማኝ፥አግዘኝ በሞራል
ትንሽም ብትሆን፥ምርቃት ነችና-------ሁልህም አሜን በል፤
አሜን . . .በል ወዳጄ አሜን. . . በል
አሜን. . . በይ እህቴ አሜን . . . በይ
አረ አሜን . . . በይ እናቴ አሜን . . . በይ
ያብቃለት እርኩሰት፤
ለዘላለም ይጠፋ የፖለቲካ እሳት፤
አሜን . . . .
ሀገር ትሁን ሰላም፤
እኛንም ያኑረን፥አንድ አርጎ ዘላለም፤
አሜን . . . .
ችላ አትበሉ
ከአሜን ይቀራል
ሰዎች አሜን በሉ
አሜን . . . . .
የህፃናት ሞት ይብቃን፥
አምላከ እስራኤል በአንድነት ያንቃን፤
አሜን . . . . .
የእናት እንባ ይቁም፤
ልጇ እንዳይገደል፥ገብርኤል ከፊት ቁም፤
አሜን . . . . .
በሰዉ እጅ ከመጥፋት፤
ፈጣሪ ያድነን ሞቶ ከመገኘት፤
አሜን . . . . . .
ይሄ ደሞ ለእኔና እኔን ለሚመስሉ ብቸኛ ሰዎች ነዉ
አምሳዮች አሜን በሉ ትልቅ ምርቃት ነዉ
አሜን . . . . . . .
ሳይግባቡ ከመጋባት፤
ፈጣሪ ይሰዉረን፤
ተግባብቶ ከመፋታት፤
አሜን . . . . . . .
ከዘረኛ ሰዉ ራስ፥
አምላክ ይጠብቀን
ከአመፀኛ ምላስ፤
፤
ሰዉረን አምላክ ሆይ
ፍቅርና ምረትህ፥በምድር ላይ ይታይ
አሜን. . .አሜን በሉ አሜን
አዎ ከምናየዉ፥ከምንሰማዉ፥ካለዉ ነገር ሁሉ
ከክፉ ያድነን ከአምላክ ዬስታርቀን ገብርኤል ሀያሉ።
በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁልህ ስፍራም ይመራህ ዘንድ
እነሆ እኔ መላእክት በፊትህ እሰዳለሁ ዘጸ 2 3 : 2 0
እንኳን ለአርባብ አለቃዉ ለቅዱስ ገብርኤል በአል በሰላም አደረሳቹ እመቤቴ ማርያምን ደስታ ያበሰረ መላክ የሀገራችንን መከራ የሚያጠፋበትን የደስታ ብስራት ያምጣል አሜን።
ወስብኸት ለእግዚአብሔር።
✍አብሰጠኝ ዘ-ማርያም
18/04/2015