es
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Ir al canal en Telegram
2 485
Suscriptores
Sin datos24 horas
-157 días
-5230 días
Archivo de publicaciones
#ታላቅ_ቅናሽ ታላቅ ቅናሽ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ብሩክ ቡና (BROOK COFFEE) ብሩክ ቡና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ አለምአቀፍ ደረጃውን ጠብቆ በDXN Ethiooia አማካኝነት የኢትዮጵያ አንደኛ ደረጃ ቡና የአለማችን የእፅዋቶች ሁሉ ንጉስ ቀይ እንጉዳይ ( Ganoderma ) ከተባለው ህርብ (እፅዋት ) ጋር በማዋሀድ ለመጀመርያ ግዜ ለአለም አበርክቶልናል። ቀይ እንጉዳይ ማለት ከ 400 በላይ የምግብነት እን የህክምና ጠቀሜታ ያለቸው ንጥረነገሮችን በውስጡ የያዘ ድንቅ እፅዋት ነው ። የብሩክ ቡና ጥቅሞች፦ ፩ የደም ዝውውርን ያፋጥናል ። ፪ በሰውነታችን ውስጥ ያሉ የተለያዩ መርዛማ አሰሮችን ያፀዳልናል (በተለያዩ የሰውነታችን የቋሻሻ ማስወገጃዋች አማካኝነት ያስወግድልናል ። ፫ ለአይምሯችን ሀይል እና ብርታትን ይሰጣል ። ፬ አላስፈላጊ ውፍረትን ለመቀነስ ይረዳል ። ፭ የሰውነታችንን የበሽታ የመከላከል አቅምን ያጎለብታል ። ፮ የጨጓራ እና የምግብ አለመፈጨት ችግርን ያስወግድልናል። ፯ ለስኳር ህመምን ለመቀነስ ይረዳል። ፰ የካርዲዮቫስኩላር (የልብ እና የደም ቧንቧ )ጤናን ለመደገፍ ይረዳል። ፱ አላስፈላጊ ጭንቀትን ለማስወገድ ይረዳል ። 250 ግራም=200 ብር 500 ግራም = 400 ብር በብዛት ለሚገዙ ቅናሽ ይኖረናል 0910159791 @dxnproductethiopia inbox 👉 @gezahegnofficial

የኢፌዲሪ የሀገር መከለከያ ሰራዊት በእዩ ጩፋ ላይ ክስ ሊመሰርት መሆኑን አስታወቀ! በቅርቡ እዩ ጩፋ የተባለ ግለሰብ በሐይማኖት ስም እየተከተሉኝ ነው ያላቸውን ግለሰቦች ክብር ባልጠበቀ መልኩ ከነዩኒፎርማቸው በቪዲዮና ፎቶ ቀርፆ በአደባባይ እንዲሰራጭ አድርጓል። ይህ የሰራዊቱን ስምና ታማኝነት በማሳጣት ለግል ፍላጎትና ጥቅም በማን አለብኝነትና ኃላፊነት በጎደለው አኳኋን ለፈፀመው ድርጊት መከላከያ በህግ ለመጠየቅ መዘጋጀቱን የሰራዊቱ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮሎኔል ጌትነት አዳነ አስታውቀዋል። ጥቂት የሰራዊታችን አባላትም ይህን ፍላጎት ለማሟላት የሁሉም ኢትዮጵያውያን መለያ የሆነውን ወታደራዊ የደንብ ልብስ ለብሰው ተሳታፊ የሆኑ እንደነበሩ ተረጋግጧል ያሉት ኮሎኔሉ፤ ተሳታፊዎቹም በመከላከያ ወታደራዊ ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ተይዘውና ታስረው ጉዳያቸውን ወደ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ለማቅረብ የማጣራት ስራ እየተሰራ ይገኛል ተብሏል። በዚህ አይነት ጥፋት ከዚህ ቀደምም በተለያዩ የእምነት ተቋማት የተገኙ አባላት ላይ የእርምት እርምጃ ተወስዶ እንደነበረ ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል። ወደፊትም ፣ ማንኛውም የሰራዊት አባል የየትኛውም እምነት ተከታይ ቢሆን በእንደዚህ አይነት ተግባር ውስጥ ተሳትፎ ከተገኘ ተጠያቂ ይሆናል ብለዋል ። የእምነት ተቋማትና መላው ህዝብ የመከላከያ ሰራዊቱን ዩኒፎርሙን ለብሶ በእምነት ተቋማት፣ በህዝቡ ዘንድ ነውር በተባሉ የመጠጥ ፣ የሱስ ፣ የቁማር ወዘተ ቦታዎች የሰራዊት አባልም ሆነ አስመሳይ ዩኒፎርም ለባሽ ሲመለከት እንዲጠቁም ጥሪ አቅርበዋል። "ሰራዊታችን ፣ በጋብቻና በቀብር ጊዜ ፣ በእምነት ቦታዎች ክብሩን በጠበቀ መልኩ የሚከወኑ ስርዓቶች መኖራቸውና ሰራዊቱም እምነት ካለው ህዝብ የወጣ በመሆኑ ፣ በየግሉ ሐይማኖት ያለው መሆኑ ሊታወቅ ይገባል። በኛ በኩል በህጋችን የተፈቀዱና የተከለከሉ ጉዳዮችን በውስጣችን የማስረፅ ስራም ይሰራል" ብለዋል። @ethiocheck

#ታላቅ_ቅናሽ ታላቅ ቅናሽ 🔥🔥🔥🔥🔥🔥 ብሩክ ቡና (BROOK COFFEE) ብሩክ ቡና በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ አለምአቀፍ ደረጃውን ጠብቆ በDXN Ethiooia አማካኝነት የኢትዮጵያ አንደኛ ደረጃ ቡና የአለማችን የእፅዋቶች ሁሉ ንጉስ ቀይ እንጉዳይ ( Ganoderma ) ከተባለው ህርብ (እፅዋት ) ጋር በማዋሀድ ለመጀመርያ ግዜ ለአለም አበርክቶልናል። ቀይ እንጉዳይ ማለት ከ 400 በላይ የምግብነት እን የህክምና ጠቀሜታ ያለቸው ንጥረነገሮችን በውስጡ የያዘ ድንቅ እፅዋት ነው ። የብሩክ ቡና ጥቅሞች፦ ፩ የደም ዝውውርን ያፋጥናል ። ፪ በሰውነታችን ውስጥ ያሉ የተለያዩ መርዛማ አሰሮችን ያፀዳልናል (በተለያዩ የሰውነታችን የቋሻሻ ማስወገጃዋች አማካኝነት ያስወግድልናል ። ፫ ለአይምሯችን ሀይል እና ብርታትን ይሰጣል ። ፬ አላስፈላጊ ውፍረትን ለመቀነስ ይረዳል ። ፭ የሰውነታችንን የበሽታ የመከላከል አቅምን ያጎለብታል ። ፮ የጨጓራ እና የምግብ አለመፈጨት ችግርን ያስወግድልናል። ፯ ለስኳር ህመምን ለመቀነስ ይረዳል። ፰ የካርዲዮቫስኩላር (የልብ እና የደም ቧንቧ )ጤናን ለመደገፍ ይረዳል። ፱ አላስፈላጊ ጭንቀትን ለማስወገድ ይረዳል ። 250 ግራም=200 ብር 500 ግራም = 400 ብር በብዛት ለሚገዙ ቅናሽ ይኖረናል 0910159791 @dxnproductethiopia inbox 👉 @gezahegnofficial

በአዲስ አበባ ለፀጥታ ስጋት አጠራጣሪ ለሆኑ ጉዳዮች ጥቆማ መስጫ ስልክ ቁጥሮች ፦ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ህብረተሰቡ ማንኛውም ለፀጥታ ስጋት አጠራጣሪ የሆኑ ጉዳዮችን በሚመለከትበት ወቅት ከታች በተዘ
በአዲስ አበባ ለፀጥታ ስጋት አጠራጣሪ ለሆኑ ጉዳዮች ጥቆማ መስጫ ስልክ ቁጥሮች ፦ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ህብረተሰቡ ማንኛውም ለፀጥታ ስጋት አጠራጣሪ የሆኑ ጉዳዮችን በሚመለከትበት ወቅት ከታች በተዘረዘሩት የስልክ ቁጥሮች አማካኝነት ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል። - ልደታ ክፍለ ከተማ - 0118578492 - ቂርቆስ ክፍለ ከተማ- 0118578501 - አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ - 0118578499 - ቦሌ ክፍለ ከተማ - 0118578509 - የካ ክፍለ ከተማ - 0118578491 - ቃለቲ ክፍለ ከተማ - 0118578507 - ላፍቶ ክፍለ ከተማ - 0118578503 - ጉለሌ ክፍለ ከተማ - 0118578505 - አራዳ ክፍለ ከተማ - 0118578511 - ኮልፌ ክፍለ ከተማ - 0118578508 ሀገር አቀፍ የ24 ሰዓት መረጃ መቀበያ ፦ - 0115526302 - 816, 987 - 0115526303 - 0115524077 - 0115543678 - 0115543681 #SHARE #ሼር @ethiocheck

በእነ አቶ ጃዋር የህክምና ጉዳይ፤ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር እና የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ ተሰጠ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከእነ አቶ ጃዋር መሐመድ የህክምና ጉዳይ ጋር በተያያዘ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር እና የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ችሎት ፊት ቀርበው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ዛሬ ትዕዛዙን የሰጠው በተከሳሽ ጠበቆች የቀረበለትን አቤቱታ ከመረመረ በኋላ ነው። የተከሳሽ ጠበቆች አቤቱታ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጸረ ሽብር እና የሕገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት፤ “የፍርድ ቤቱ ውሳኔ እንዳይከበር ሚና ነበራቸው” ያላቸውን የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ተወካዮችን ከዚህ ቀደም በነበረው ውሎው አስጠርቶ ጠይቋል። ተከሳሾች ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ ላይ ባሉበት ወቅት፤ የነበሩበት ተሽከርካሪ “በመንገድ ላይ ታግቶ እንዲቆም አድርገዋል” የተባሉ ኃላፊ ደግሞ ለዛሬ ረቡዕ መጋቢት 22፤ 2013 እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። የችሎቱን ትዕዛዝ ተቀብለው ዛሬ ችሎት ፊት የቀረቡት የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል አዛዥ ኢንስፔክተር መገርሳ ገሙ በዕለቱ የሆነውን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። እነ አቶ ጃዋር ወደ ላንድ ማርክ ሆስፒታል ሲወሰዱ አጅበዋቸው እንደበር የጠቀሱት አዛዡ፤ አፍሪካ ህብረት አካባቢ ሲደርሱ ተከሳሾቹ ያሉበት ተሽከርካሪ እንዲቆም በስልክ ትዕዛዝ እንደተላለፈላቸው ተናግረዋል። ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/2766/

አጭር መረጃ ስለተሻሻለው የንግድ ህግ ፦ By : Haileyesus Seyume ላለፉት 62 ዓመታት ያህል በስራ ላይ የነበረው የንግድ ህግ ዛሬ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተሻሽለ ፀድቋል። - የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከሌሎች አዋጆች በተለየ እስከ 3 ወር ጊዜ ተወስዶ ተወያይቶ ነው ዛሬ ያፀደቀው - 825 አንቀፆች ማሻሻያ ተደርጎባቸዋል፤ - የተሻሻለው አዋጅ ወቅቱን እና ቴክኖሎጂን ታሳቢ ያደረገ ነው ፤ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ተሳፍቶ ለምታደርገው ጥረት የሚያቀል ነው። - ማንኛውም ሰው ወደ ንግድ ስርዓት ለመግባት ይቸገርበት የነበረውን ረጅም አሰራር የሚያሳጥር ነው። - የተሻሻለው ህግ የሚመለከተው የንግድ ስራን ብቻ ሲሆን የባንክ እና ሂሳብ ጉዳይ የሚመለከተው ከነበረው የንግድ አወጅ እንዲወጣ ተደርጎ ለብቻው እንዲታይ ተደርጓል። - ማንኛውም ግለሰብ እና ድርጅት ባለው ካፒታል በንግድ ስርዓቱ ውስጥ ለመሳተፍ በፈለገበት ወቅት ሃሳቡን አቅርቦ በፈለገው ሞያ ላይ መሳተፍ ይችላል፤ ነገር በህግ የተከለከሉትን አይመለከትም። - ማኛውም ሁለት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በህብረት ስራ ማህበራት መስርተው በንግድ ላይ መሳተፍ ይችሉ ነበር ነገር ግን በግለሰብ ደረጃ ማህበር መመስረት አይቻልም ይህ እንዲቀር ተደርጎ ማንኛውም ግለሰብ ብቻውን ሆኖ የንግድ ህብረት ስራ ማህበር መስርቶ በንግድ ውስጥ እንዲንቀሳቀስ መብት ይሰጣል። - የውጭ ባለሃብቶች በሀገር ውስጥ በተለያዩ የስራ መስኮች እንዲሰማሩ የሚያመቻችበት ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል። - ከዚህ ቀደም ትናንሽ የሚባሉ ስራዎች (1ና 2 ሰው ተሳትፎ የሚሰራባቸው) በንግድ ስርዓት ውስጥ እንዲየልፉ ይገደዳሉ በዚህም ከትንሽ ተነስተው ወደ ትልቅ ደረጃ ለመድረስ የሚየስቡ ነጋዴዎች በስርዓቱ ምክንያት ከስራው ሲወጡ ነበር ይህን ለመቅረፍ በአዲሱ አዋጅ ትናንሽ ስራዎች ነጋዴ ተብለው እንዳይመዘገቡ እና ያለ ንግድ ፍቃድ ስራቸውን እንዲሰሩ የሚፈቅድ ነው ፤ በአዋጁ ላይ አንድ ወይም ሁለት ብሎ በቁጥር ተቀምጧል። ለምሳሌ ፦ - እርሻ እና ከብት ማርባት - የደን ልማት - የእደጥበብ ስራዎችም በነጋዴ የሚለው ውስጥ እንዳይካተቱ ተደርገዋል። ነገር ግን ካፒታል ያላቸው ወይም ተጨማሪ ስራቸውን ለመስራት የሚያስችል ከሆነ በዚህ ውስጥ አይስተናገዱም ፥ ካፒታላቸው ምን ያህል ነው የሚለው በቀጣይ በሚወጣ ዝርዝር የህግ አዋጅ የሚካተት ነው። - ዛሬ ተሻሽሎ የፀደቀው አዋጅ ለ30 ዓመታት ስራ ላይ ይውላል ተብሎ የሚጠበቅ አዋጅ ነው። @ethiocheck

ኢዜማ ከየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢ በላቀ ችግር የገጠመው በኦሮሚያ ክልል ነው- ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ፓርቲ ከየትኛውም የሀገሪቱ አካባቢ በላቀ ብዙ ችግር የገጠመው በኦሮሚያ ክልል መሆኑን መሪው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ። በክልሉ ያሉ የፓርቲው አባላት መታሰር፣ መሰደድ እና የጽህፈት ቤቶች መዘጋት ባለፉት ሁለት ወራት ይበልጥ ተባብሷል ብለዋል። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ይህን ያሉት ፓርቲያቸው በአዳማ ከተማ ዛሬ እሁድ ረፋዱን በጠራው የምርጫ ቅስቀሳ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ነው። “በየትኛውም አካባቢ በፍጹም የማይጠበቁ ነገሮች የምንሰማው ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ነው” የሚሉት የኢዜማ መሪ፤ በክልሉ በመንግስት አስተዳደርም ሆነ በብልጽግና ውስጥ ያሉ አመራሮች የሚያስፈራቸው ምን እንደሆነ እንደማይገባቸው ለመርሃ ግብሩ ታዳሚያን ገልጸዋል። በፓርቲያቸው ላይ ችግር በደረሰ ቁጥር የኦሮሚያ መስተዳድር ሰዎችን እና የክልሉ የብልጽግና ፓርቲ አመራሮችን እንደሚያነጋግሩ የጠቀሱት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ የባለስልጣናቱን ግፊት ተጠቅመው አባሎቻቸውን እንደሚያስፈቱ አስረድተዋል። “ለምንድነው ይሄ የሚሆነው?” ሲሉም የፓርቲው መሪ ጠይቀዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ከእናት ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት፤ ዶ/ር ሰይፈሥላሴ አያሌው ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ (ክፍል 2) ● “ኢትዮጵያ ባለፉት 45 ዓመታት በ‘እኛ’ እና በ ‘እነርሱ’ ተከፋፍላለች። ይህንን የመከፋፈል ነገር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ማብቂያ ልናበጅለት ይገባል ብለን ነው የተነሳነው።” ● “ብሔር እና ብሔረሰቦች የሚለውን ትርጉሙን ማናችንም አናውቀውም። ማነው ብሔር? ማነው ብሔረሰብ? - አናውቀውም” ● “ኢትዮጵያውያን፤ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ ህዝቦች አይደለንም። አንድ ህዝብ ነን። 110 ሚሊዮን የተለያየ ቋንቋ ተናጋሪ አንድ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው ያለን።” ● “ሀገራችን የቀደመ ማንነቷን መልሳ ማግኘት አለባት። ወደ ቀደመ ማንነቷ ለመመለስ ኢትዮጵያዊ ማንነቷን መፈለግ መቻል አለባት። ስለዚህ ታሪኳን፣ ወጓን፣ ባህሏን፣ ልማዷን፣ ሃይማኖቷን፣ በደንብ አድርገን እነኚህን ነገሮች መመለስ መቻል አለብን። ‘ይህንን ጠብቀን ማቆየት አለብን ስንል ወደምን ያመጣናል?’ ወደ conservative ነገር ያመጣናል።” ● “አሁን ሀገራችን ፓርላሜንታዊ ስርዓት ነው የምትከተለው። ያ ስርዓት ባለፉት 30 ዓመታት በተመለከትነው ሀገርን ወደተሻለ ነገር ሊያመጣ አልቻለም። እየሄድን ያለነው የጎሳ ፖለቲካን ተከትለን በተቻለ መጠን ማቻቻል ነው።” ● “ኢትዮጵያ ውስጥ ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት መኖር አለበት ስንል ፓርላማውም መኖር አለበት- እንደ ህግ አውጪ አካል። ግን ሙሉ ስልጣን ያለው ፕሬዝዳንት እንዲሆን ያስፈልጋል። ምንልባትም ዛሬ ኢትዮጵያ ከተተበተበችበት የጎሳ ፖለቲካ ሊያላቅቃት የሚችለው ፕሬዝዳንታዊ ስርዓት ነው ብለን የምናስበው።” ● እናት ፓርቲ ሕገ መንግስቱን ማሻሻል “ግንባር ቀደም ስራው ነው የሚሆነው።”

ቪዲዮ፦ ቃለ ምልልስ ከእናት ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ጋር በመጪው ግንቦት ወር መጨረሻ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ ምርጫ በርካታ ዕጩዎችን ካስመዘገቡ ፓርቲዎች ተርታ አንድ እምብዛም ስሙ የማይሰማ ፓርቲ መገኘቱ ከሰሞኑ መነጋገሪያ ሆኗል። “እናት” የሚል መጠሪያ ያለው ይህ ሀገር አቀፍ ፓርቲ የእውቅና ሰርተፍኬት ባገኘ በአንድ ወር ውስጥ “እንዴት በርካታ ዕጩዎችን ማስመዝገብ ቻለ? አባላቶቹስ እነማን ናቸው? ” ስንል የፓርቲውን ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሰይፈሥላሴ አያሌውን ጠይቀናል። ምክትል ፕሬዝዳንቱ ከ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ለቀረበላቸው፤ “ፓርቲው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አደረጃጀቶችን ተጠቅሟልን?” ለሚለው ጥያቄም ምላሽ ሰጥተዋል። ፓርቲያቸው በሚወዳደርባቸው ቦታዎች ድምጽ ካገኘ፤ ገዢውን ፓርቲ ጨምሮ ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር የጥምር መንግስት በመመስረት ጉዳይ ላይ ያለውን አቋምም አብራርተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ኦፌኮ እና ኦነግ በዘንድሮው ምርጫ ባንሳተፍም ሰላማዊ ትግላችንን እንቀጥላለን አሉ። መንግስት በፓርቲያቸው ላይ የሚያደርገውን ማዋከብ እና እስር እስካላቆመ ድረስ በምርጫው ለመሳተፍ እንደማይሞክሩ ኦነግና ኦፌኮ ተናግረዋል። በስድስተኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ የሚወዳደሩ የእጩዎች ምዝገባ ከየካቲት 08 እስከ 21 ድረስ ተካሄዶ ባሳለፍነው ቅዳሜ መጠናቀቁ ይታወሳል። ይሁን እንጂ ቦርዱ የእጩዎች ምዝገባ ሂደትን በመገምገም የምርጫ ክልል ቢሮዎች ለመከፈት በመዘግየታቸው፣ የትራንስፓርት መጓተት የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች ላይ የምዝገባ ቀንን በማራዘሙ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ ምክንያቶች እጩዎችን ለመመዝገብ ችግር ስላጋጠመን ይራዘምልን ብለው መጠያቃቸውን ተከትሎ ለአራት ተከታታይ ቀናት አራዝሚያለሁ ሲል አስታውቋል፡፡ በዚህ የመጀመሪያ ዙር እጩዎችን ካላስመዘገቡ ተፎካካሪ ፓርቲዎች ውስጥ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ና የኦሮሞ ፌደራሊስ ኮንግረንስ (ኦፌኮ) ይገኙበታል ፡፡ ኢትዮ ኤፍ ኤም በጉዳዩ ላይ ፖርቲዎቹ ምን እንደሰሩ ጠይቋል፡፡ የኦፌኮ ተቀዳሚ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ቀናቱ ቢጨመሩም ባይጨመርም ለውጥ አይመጣም ብለዋል፡፡ መንግስት የጠየቅናቸውን ነገሮች ከግምት እስካላስገባ ድረስ ምን ይዘን ነው የምንገባው ብለው ጠይቀዋል ፡፡ "እጩዎቻችን በእስር ላይ ሆነው ፤ ቢሮዎቻችንም ቢሆኑ ሆን ተብሎ እየተዘጉ መወዳዳር አንችልም" ሲሉም ፕሮፌሰር መረራ ተናግረዋል፡፡ ከበርካታ ዓመታት የትጥቅ ትግል በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ ለመወዳደር የተዘጋጀው ኦነግ ፤ በአባሎቹ ላይ የእስር እና የእንግልት ዘመቻው እንደቀጠለ ተናግሯል፡፡ ምንም ለውጥ ባለመኖሩ የተነሳም በዚህ ምርጫ ላይ ለመሳተፍ ከእኔ ይልቅ መንግስት ወሳኝ ሆኗል ብሏል ኦነግ፡፡ በ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ ከፍተኛ ግምት ከሚሰጣቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ የነበረው ኦነግ በውስጣዊ ችግሮቹ እና በፓርቲ አመራሮች እስር ታጅቦ ምርጫውን ሲጠብቅ እንደነበር ተናግሯል፡፡ በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው ኦነግ ቃላ ቀባይ የሆኑት አቶ በቴ ኡርጌሳ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት በኦሮሚያ ክልል ከፍተኛ እስርን ጨምሮ ጽህፈት ቤቶቻችን ተዘግተው አልቀዋል ብለውናል፡፡ ሁኔታው ገዢው ፖርቲ ብቻውን ለመወዳር መወሰኑን አሳይቷል ይላሉ አቶ በቴ፡፡ ኦነግ በመንግሥት ይደርስብኛል በሚለው ጫናና በአመራሮቹ መካከል የተፈጠረው ቅራኔ በምርጫ ተሳትፎው ላይ ተጽዕኖ እንዳሳደረበትም ተናግሯል፡፡ የፓርቲው ቃል አቀባይ አቶ በቴ በዚህ ምርጫ ባንሳተፍም ሰላማዊ ትግላችን ግን ይቀጥላል ብለዋል ፡፡ ምርጫ አንዱ የትግል መንገድ እንጂ ብቸኛ አይደለም የሚሉት ቃል አቀባዩ መሳሪያችንን ጥለን ወደ ሀገር የገባነው በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ነው ብለዋል ፡፡ ይህንንም እያደረግን ነው የሚሉት አቶ በቴ ደጋፊዎቻችንም ሆኑ አባሎቻችን ይህንን ተገንዝበው ሰላማዊ ትግሉን እንዲቀጥሉ አድርገናልም ብለዋል። የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ምክትል ቢሮ ሀላፊው አቶ ግዛቸው ጋቢሳ በበኩላቸው ፓርቲዎቹ እያሰሙ ያሉት ቅሬት ትክክል አለመሆኑን ተናግረዋል። በክልሉ የተዘጋ የማንኛውም ፓርቲ ጽህፈት ቤትም ሆነ አባል የለም የሚሉት አቶ ግዛቸው ህግ ከተጣሰ ግን የብልጽግና አመራር እና አባላትን ጨምሮ ማንኛውም ግለሰብ በህግ ይጠየቃል ብለዋል። በክልሉ ቅሬታ ካላቸው ፓርቲዎች በተጨማሪ ሌሎች ፓርቲዎች የምርጫ ዝግጅታቸውን በማካሄድ ላይ እንደሆኑም አቶ ግዛቸው ተናግረዋል። @ethiocheck

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የሀረሪ ክልል ርእሰ መስተዳድር መቀሌ ገቡ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ እና የሀረሪ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኦሪዲን በድሪ
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የሀረሪ ክልል ርእሰ መስተዳድር መቀሌ ገቡ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ እና የሀረሪ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኦሪዲን በድሪ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ መቀሌ ገቡ። የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ እና የሀረሪ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ኦሪዲን በድሪን የያዘው ልኡካን ወደ መቀሌ ያቀኑት በህግ ማስከበሩ ሂደት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ነው፡፡ ልኡካኑ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋ እና የካቢኔያቸው አባላት፣ የመቀሌ ከተማ የአገር ሽማግሌዎች እንዲሁም የኃይማኖት አባቶች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ በሁለቱም የመንግስት አመራሮች የሚመራው ልኡክ በቆይታው ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራሮች ጋር ይወያያል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ @ethiocheck

TIKVAH-MAGAZINE, [23.02.21 01:26] [In reply to TIKVAH-MAGAZINE] [ Photo ] በምሥራቅ ወለጋ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል አርሶ አደሮችን ትጥቅ እያስፈታ መሆኑ ተገለጸ (በአዲስ ማለዳ ጋዜጣ የቀረበ ) በአሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋ ዞን የኦሮሚያ ልዩ ኀይል የአካባቢውን ማኅበረሰብ እና አርሶ አደሮችን ትጥቅ እያስፈታ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች መግለጻቸውን ለአዲስ ማለዳ አስነብቧል። የክልሉ ልዩ ኀይል ማኅበረሰቡን ትጥቅ ማስፈታት የጀመረው ባሳለፍነው ሳምንት መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ለአዲስ ማለዳ የጠቆሙ ሲሆን፣ ልዩ ሀይሉ ማኅበረሰቡ እራሱን ከኦነግ ሸኔ ጥቃት የሚጠብቅበትን መሳሪያ በግድ እያስፈታ በማለት ቅሬታ እንደፈጠረባቸው ተናግረዋል። ልዩ ሀይሉ ትጥቅ ለማስፈታት ወደ ማኅበረሰቡ ዘልቆ በገባበትም ሁኔታ በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ሰባት አርሶ አደሮች በልዩ ሀይሉ በተተኮሰ ጥይት ሕይወታቸውን እንዳጡ አዲስ ማለዳ ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል ሲል አስነብቧል። የኦሮሚያ ክልል መንግሥት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጌታቸው ባልቻ በአካባቢው ግጭቶች መኖራቸውን ለአዲስ ማለዳ በሰጡት ምላሽ አረጋግጠዋል። በዚህም የሰው ሕይወት እንደጠፋ ኃላፊው አምነዋል። ይሁን አንጅ የክልሉ ልዩ ሀይል ከማኅበረሰቡ ጋር መጋጨቱን መረጃ አልደረሰኝም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። የትጥቅ ማስፈታት ተግባሩን በተመለከተም ሕጋዊ ያለሆነ ትጥቅ ካለ ሕግ የማስከበር ሥራ በልዩ ሀይሉ ሊሰራ ይችላል ብለዋል። Readmore https://telegra.ph/አዲስ-ማለዳ-02-23 PHOTO: ፋይል @ethiocheck

ጁንታው በዋሻ ውስጥ ሆኖ የትግራይን ህዝብ ለማደናገር የሚያደርገው ጥረት እንደማይሳካ የአገር መከላከያ ሰራዊት ገለፀ! ጁንታው በዋሻ ውስጥ ሆኖ የትግራይን ህዝብ ለማደናገር የሚያደርገው ጥረት እንደማ
ጁንታው በዋሻ ውስጥ ሆኖ የትግራይን ህዝብ ለማደናገር የሚያደርገው ጥረት እንደማይሳካ የአገር መከላከያ ሰራዊት ገለፀ! ጁንታው በዋሻ ውስጥ ሆኖ የትግራይን ህዝብ ለማደናገር የሚያደርገው ጥረት እንደማይሳካ የአገር መከላከያ ሰራዊት ገለፀ። የአገር መከላከያ ሰራዊትን ስም በማጥፋት ህዝብን ብዥታ ውስጥ ለመክተት የሚንቀሳቀሱ መገናኛ ብዙሃንን በህግ እንደሚጠይቅም አስታውቋል። የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ተሰማ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለኢዜአ መግለጫ ሰጥተዋል። Via ENA @ethiocheck

#UpdateEthiopiaElection የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ የካቲት 03 የምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር ይፋ አድርጓል። በአጠቃላይ 49,407 የምርጫ ጣቢያዎች ለ6ተኛው ጠቅላላ ምርጫ አገልግሎት የሚሰጡ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን ሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች በአንድ PDF ፋይል ከላይ ተያይዟል። ምርጫ ጣቢያዎቹ ፦ በአዲስ አበባ ከተማ - 1,848 በሲዳማ ክልል - 2,247 ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል - 699 አፋር ክልል- 1,432 አማራ ክልል- 12,199 ድሬዳዋ ከተማ- 305 ጋምቤላ ክልል- 431 ሃረሪ ክልል- 285 ኦሮሚያ ክልል- 17,623 ደ/ብ/ብ/ህ ክልል- 8,281 ሶማሌ ክልል- 4,057 @ethiocheck

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ትምህርት ለማስተማር በሁለት ዙር ዕውቅና ለተሰጣቸው ሲቪል ማኅበራት ሠርተፊኬትና ተያያዥ ሠነዶችን መስጠት ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ትምህርት ለሚያስተምሩ ሲቪል ማኅበራት ዕውቅና ለመስጠት ባወጣው ጥሪ መሠረት ማመልከቻ ያስገቡትን ሲቪል ማኅበራት በመገምገምና ማመሟላት ያለባቸውን ቀሪ ሠነዶች በመጠየቅ በጥር 13 ቀን 2013 ዓ.ም. የመጀመሪያን ዙር ለ24 ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ዕውቅና መስጠቱ ይታወቃል። ቦርዱ በተጠቀሰው ቀን የሁለተኛ ዙር ዕውቅና ሂደት እንደተጠናቀቀ የተጨማሪ ማኅበራትን ዕውቅና ይፋ እንደሚያደርግ በገልጸው መሠረት ሁለተኛ ዙር ዕውቅና የተሰጣቸውን ማኅበራት ዝርዝር እንደሚከተለው ይፋ አድርጓል። 1. ሁሉን ዐቀፍ ራዕይ ለዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ-Inclusive Vision for Democratic Ethiopia 2. ሆፕ ፎር ዴቨሎፕመንት-Hope for Development Association 3. ምሥራቃዊ የዕድገት ፋና የበጎ አድራጎት ማኅበር-Eastern Development Initiative (EDI) 4. ሴንተር ፎር ኮሚኒቲ ደቨሎፕመንት-Center for Community Development (CEFCOD) 5. ሪሊፍ ኤንድ ሰስቴይነብል ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን-Relief and Sustainable Development Organization 6. ሪሰረክሽን ኤንድ ላይፍ ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን-Resurrection and Life Development Organization 7. ነርቸር ኤጁኬሽን ኤንድ ዴቨሎፕመንት-Nurture Education and Development 8. አሊያንስ ፎር ፒስ ኤንድ ዴቨሎፕመንት-Alliance for Peace and Development 9. አድቮኬትስ ኢትዮጵያ-Advocates Ethiopia 10. ኢትዮጵያዊ ተነሳሽነት ለሰብዓዊ መብቶች-Ethiopian Initiative for Human Rights 11. ኢንተግሬትድ ኮሚዩኒቲ ኢጁኬሽን ኤንድ ዴቨሎፕመንት አሶሴሽን-Integrated Community Education and Development 12. ኮሚዩኒቲ ሰስቴይነብል ዴቨሎፕመንት ኤይድ ኦርጋናይዜሽን-Community Sustainable Development Aid Organization 13. የሰላምና ልማት ማዕከል-Peace and Development center 14. የአርብቶ አደር ሴቶችና ልማት ድርጅት-Women and Pastoralist Youth Development Organization (WA-PYDO) 15. የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች ማኅበር-Addis Ababa City Women Association 16. አፍሮ ኢትዮጵያ ኢንቴግሬትድ ዴቨሎፕመንት አሶሲየሽን-Afro Ethiopia Integrated Development (AID) 17. የኢትዮጵያ ወጣቶች ፌዴሬሽን-Ethiopian Youth Federation 18. የኢትዮጵያ የሴቶች ፌዴሬሽን/Ethiopian Women's federation 19. የክርስቲያን በጎ አድራጎትና ልማት ማኅበራት ሕብረት-Consortium of Christian relief and Development Association 20. የደቡብ ክልል መምህራን ማኅበር ጽ/ቤት-South region Teachers Association Officer 21. ደሊጀንስ ፎር ሂዩማን ራይት ፕሮቴክሽን-Diligence for Human rights protection 22. ጉሩሙ ዴቨሎፕመንት አሶሴሽን-Gurmuu Development Association 23. ጣምራ ሶሻል ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን-Tamra for Social Development Organization 24. ጥላሁነን የበጎ አድራጎት ማኅበር-Tilahunen Charity Association 25. ጥረት ኮሚዩኒቲ ኢምፓወርመንት ፎር ቸንጅ አሶሴሽን-Tiret Community Empowerment for Change Association 26. ፍሪ ሶሳይቲ ፎር ሰስቴኔብል ዴቬሎፕመንት-Free Society for Sustainable Development (FSfSD) 27. ፕሮ - ዴቨለፕመንት ኔትዎርክ-Pro Development Network 28. ፕሮግረስ ኢንተግሬትድ ኮሚዩኒቲ ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን-Progress Integrated Community Development 29. ሪፍት ቫሊ ችልድረን ኤንድ ዊሜን ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን- Rift Valley Children and Women Development 30. ሪዲም ዘ ጀኔሮሽን- Redeem the Generation 31. ምዕራፍ ሁለገብ የከተማ ልማት ድርጅት- Miraf Hulegeb Yeketama Limat Dirgit 32. ኦርጋናይዜሽን ፎር ገርልስ አደልትስ ኤንድ አድቮኬሲ- Organization for Girls, Adults and Advocacy 33. ቪዥን ኢትዩጲያ ኮንግረስ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት- Vision Ethiopia Congress for Democracy 35. ሻሎም ሂዩማኒቴሪያን ዴቨሎፕመንት አሶሴሽን- Shalom Humanitarian development Association 36. ማዘር ኤንድ ዴቨሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን- Mother and Children Development Organization 37. ብራይት ቪዥን ፎር ኮሚዩኒቲ- Bright Vison for Community 38. የኢትዮጲያ ወጣቶች ሰላም እና ብልፅግና ተልዕኮ- Ethiopia Youth Peace and Prosperous Mission 39. ጎግአቦሮ ልማት ማኅበር- Gogaboro Development Association 40. ኢኒሽየቲቭ አፍሪካ-Initiative Africa 41. ሰፈር - ኢትዮጵያ-Safer – Ethiopia ከዚህ ቀደም በመጀመሪያ ዙር ዕውቅና የተሰጣችሁ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶችን ጨምሮ ከላይ ስማችሁ የተዘረዘረ ሁለተኛ ዙር ዕውቅና ያገኛችሁ የሲቪል ማኅበራት፤ ለ6ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ት/ት ለማስተማር አስፈላጊውን ቅድመ ሁኔታ ስላሟላችሁ ከሰኞ የካቲት 1 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋናው መሥሪያ ቤት ቢሮ ቁጥር 107 እየመጣችሁ ሠርተፍኬት እና ሌሎች ሠነዶችን እንድትወስዱ ባቀረብነው ጥሪ መሠረት ሠርተፊኬትና ተያያዥ ሠነዶች መስጠቱን በይፋ መጀመራችንን ልናሳውቅ እንወዳለን። Via የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ @ethiocheck

ኦነግ በምርጫው ለመሳተፍ እየተፍጨርጨርኩ ነው አለ! የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ በውስጣዊ የፖርቲ ቀውስ የተነሳ በ6 ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ለመሳተፍ አጣብቂኝ ውስጥ መውደቁን ለኢትዮ ኤፍ ኤም አሳውቋል፡፡ የፖርቲው ቃላቀባይ አቶ ቀጀላ መርዳሳ ምርጫ ቦርድ ፖርቲው የገጠመውን ችግር ለመቅረፍ አሰቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን እንዲያደርግ ጥብቅ ማሳሰቢያ ቢሰጥም በተቀዳሚ ሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ እንቢተኛነት ማድረግ እንዳልቻለና እና ልመና ላይ መሆኑን ነግረውናል፡፡ ውዝግቡ ከተፈጠረ ወዲህም ምርጫ ቦርድ ጋር በስመ ሊቀመንበርነት የግንባሩ ተወካይ ናቸው በሚል ግንኙነት ስላላቸው ፈጽሞ የጋራ ውሳኔና መመሪያ እየሰጡም ፤እየተቀበልንም አይደለም ነው የሚሉት አቶ ቀጀላ፡፡ እኛ ምርጫ ቦርድ ችግሮን ተገንዝቦ በአፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጠን እና ወደ ምርጫ ዝግጅቱ እንድንገባ እየጠየቅን ነው ይላሉ፡፡ አሊያም ግን ምርጫ ውስጥ የማይሳተፍ ፖርቲ ጥቅሙ ምን ሊሆን ይችላል ሲሉም ይጠይቃሉ፡፡ በዚህ አይነት ከሄድንም የእርሳቸው ስብስብ በምርጫው ለመሳተፍ አይችልም ምክንያቱም ህጋዊ አይደለም ባይ ናቸው ፡፡ የእኛ ጥያቄ ምርጫ ቦርድ ከእርሳቸው ጋር የሚያደርገውን ግንኙንት እንዲያጤነውና መፍትሔ እንዲሰጠን ነው ምክንያቱም ይህ ነገር አግባብነትም ሆነ ፍትሐዊ አይደለም ነው የሚሉት አቶ ቀጀላ፡፡ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሄድ የግድ መሆኑን የሚያነሱት አቶ ቀጀላ አሁን ድርጅታዊ ቀውስ ውስጥ ስላለን ወደ ምርጫው መግባት አንችልም ከባድ ብለው፡፡ ችግሮ እስኪፈታ ምርጫ ቦርድ በልዩ ሆኔታ ቀናትን ገፋ እንዲያደርግልን እንጠይቃለን ፡፡ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ምርጫውን መካፈል ከባድ ሊሆን እንደሚችል ነው ያነሱት፡፡ Via ethio fm

ሱዳን የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ ውሃ ሙሌት ከዚህ በላይ የሚቀጥል ከሆነ በብሄራዊ ደህንነቴ ላይ የተሰነዘረ ጥቃት ይሆናል አለች ሱዳን የታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የዉሃ ሙሌት ከዚህ በላይ ከቀጠለ ሂደቱ በብሄራዊ ደህንነቴ ላይ የተደቀነ አደጋ ይሆናል፤ሂደቱም ስጋት ይፈጥርብኛል ስትል አስታውቃለች። የሱዳን የመስኖና የውሃ ሀብት ሚኒስትር ያስር አባስ በትላንትናው እለት እንዳስታወቁት ኢትዮጲያ ከካርቱምና ካይሮ ጋር ስምምነት ሳይደረስ ውሃ ለመሙላት እንቅስቃሴ ልታደርግ ትችላለች የሚል ስጋት በሱዳን ከኩል እንዳለ ተናግረዋል። በቀጣዩ ሀምሌ ወር ኢትዮጲያ የግድቡን የውሃ ሙሌት የምታካሂድ ከሆነ በሱዳን ላይ የተቃጣ ብሄራዊ የደህንነት አደጋ ይሆናል ሲሉ ያስር አባስ ተናግረዋል። ከአሶሴትድ ፕሬስ ጋር ቆይታ ያደረጉት ያስር አባስ ሲናገሩ የውሃ ሙሌቱ የሚካሄድ ከሆነ በማዕከላዊ ሱዳን ከሚኖረው ህዝብ 50 በመቶ ያህሉ ለአደጋ ይዳረጋል፤የመስኖና የኃይል ፕሮጀክት ክፉኛ ይጎዳል ብለዋል። በዚሁ ዙርያ በኢትዮጵያ ወገን የተሰጠ መግለጫ ግን የለም።ኢትዮጲያ የምትገነባው የታላቁ የህዳሴ ግድብ ለፍትሃዊ የልማት ተጠቃሚነት ሲሆን ሱዳን በየዓመቱ የሚፈትናትን የጎርፍ ስጋትን የሚቀንስም ይሆናል። አባስ በትላንትናው እለት ሀገራቱን በማደራደር ረገድ አሜሪካ፣የአውሮጳ ህብረትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንዲሳተፉ ጠይቀዋል። የአባስ ይህንን መሰሉ የማስጠንቀቂያ ንግግር ኢትዮጲያና ሱዳን በድንበር ውዝግብ ውስጥ ባሉበት በዚህ ወቅት መሆኑ ውጥረት የሚያባብስ ሊሆን ይችላል። @ethiocheck

“የካቲት የአድዋ ወር" "የካቲት የአድዋ ወር" በሚል የ125ኛው የአድዋ ድል በዓል የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ዛሬ የካቲት 1 ቀን 2013 ዓ.ም በዳግማዊ ሚኒሊክ አደባባይ በፌደራል ፖሊስ ማርች ባንድ
“የካቲት የአድዋ ወር" "የካቲት የአድዋ ወር" በሚል የ125ኛው የአድዋ ድል በዓል የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ዛሬ የካቲት 1 ቀን 2013 ዓ.ም በዳግማዊ ሚኒሊክ አደባባይ በፌደራል ፖሊስ ማርች ባንድ ታጅቦ ተከናውኗል። መርሃ-ግብሩን ያስጀመሩት በባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚንስትር ዲኤታ ክብርት ወ/ሮ ብዙነሽ መሰረት ለመገናኛ ብዙሃን ስለ መርሃ ግብሩ መልእክት አስተላልፈዋል። የካቲት የአድዋ ወር ሆኖ እንዲዘከር መወሰኑን ከባህልና ቱሪዝም ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። @ethiocheck

አኗር መስጅድ አካባቢ ባለ ስፍራ በደረሰ የእሳት ቃጠሎ ከ20 በላይ መኖሪያ ቤቶች ተቃጠሉ በአዲስ አበባ ልዩ ስፍራው ልዩ ስሙ ስሜ ሜዳ (ንጉስ ሚካኤል ሆቴል አካባቢ ) ባለ አኗር መስጅድ አካባቢ በሚገኝ ስፍራ ዛሬ ጥር 29,2013 ቀን ስድስት ሰአት ምክንያቱ ባልታወቀ የእሳት አደጋ ከ20 በላይ መኖሪያ ቤቶች መቃጠላቸውን ፊደል ፖስት ከስፍራው የደረሰ መረጃ ያሳያል። የከተማው እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ስለተፈጠረው የአደጋ ውድመትና መንስኤ ዝርርዝር መረጃ ባይሰጥም እሳቱ በቁጥጥር ስር መዋሉን ለፊደል ፖሰት ገልፇል ። Via fidel post @ethiocheck

በትግራይ ክልል የወደሙ ዩኒቨርሲቲዎች እድሳት ተደርጎላቸው ስራ ሊጀምሩ ይገባል … የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት:: የምክር ቤቱ የሰው ሃብትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርን የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ገምግሟል። ሚኒስትሩ ዶክተር ሳሙኤል ሁርቃቶ የመስሪያ ቤቱንና ተጠሪ ተቋማቱን እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። በሪፖርቱ የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ጥራት ልማት እንዲሁም የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍን የማጠናከር ተግባራት መከናወናቸው ተገልጿል። በሳይንስ ልማት ረገድ አገሪቷ የበለጸገ ኢኮኖሚ እንዲኖራት የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን ማከናወንና ኮቪድ-19 በትምህርት ስርዓቱ ላይ ተጽእኖ እንዳያሳድር በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዙ የመከላከል ስራዎች መሰራታቸው ተብራርቷል። በትምህርት ልማትም በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በኢኖቬሽን፣ በሂሳብና በሰው ሃብት ዘርፎችና ደረጃውን የጠበቀ የምርምር ማዕከላት የማስፋፋት ስራ መሰራቱም ተገልጿል። በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍ የኮቪድ መከሰትን ተከትሎ ችግር ፈቺና ወጪ ቆጣቢ የሆኑ የምርምር ውጤቶችን ተግባራዊ ማድረግ በስፋት መሰራቱን ሚኒስትሩ ገልፀዋል። @ethiocheck