es
Feedback
AIRDROP ROOM

AIRDROP ROOM

Ir al canal en Telegram
2 485
Suscriptores
Sin datos24 horas
-157 días
-5230 días
Archivo de publicaciones
የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሠራተኞችን ለማመስገን ያለመ የሙዚቃ ኮንሰርት ሊዘጋጅ ነው! ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሚገነባበት ቦታ ላይ በግድቡ ግንባታ ሥራ እየተሳተፉ ያሉ ሠራተኞችን ለማመስገን ያለመ
የሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሠራተኞችን ለማመስገን ያለመ የሙዚቃ ኮንሰርት ሊዘጋጅ ነው! ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሚገነባበት ቦታ ላይ በግድቡ ግንባታ ሥራ እየተሳተፉ ያሉ ሠራተኞችን ለማመስገን ያለመ የሙዚቃ ኮንሰርት ለማቅረብ መታሰቡን ኢዜአ አስነብቧል። በኮንሰርቱም የኪነጥበብ ባለሙያዎች ሀገራዊ ጥበብን የወከለ ሥራ በማቅረብ በሕዳሴው የግንባታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ ያሉትን ያመሰግኑበታል የተባለ ሲሆን የሚቀርብበት ጊዜ ወደፊት በኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ሁኔታ ላይ ተመስርቶ የሚወሰን መሆኑ ነው የተገለጸው። @ethiocheck

ኢዜማ መግለጫ እንዳይሰጥ ተከለከለ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ ነሐሴ 22/2012 በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሔዱ የመሬት ወረራዎችን እና ኢ-ፍትሀዊ የሆነ የመኖሪያ ቤቶችን
ኢዜማ መግለጫ እንዳይሰጥ ተከለከለ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ዛሬ ነሐሴ 22/2012 በአዲስ አበባ ከተማ የሚካሔዱ የመሬት ወረራዎችን እና ኢ-ፍትሀዊ የሆነ የመኖሪያ ቤቶችን ክፍፍል በሚመለከት በራስ ሆቴል ሊሰጥ የነበረው መግለጫ በፖሊስ ተበትኗል። የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ናትናኤል ፈለቀ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት ከቀናት በፊት ስለ ስለ ስብሰባው ለሰላም ሚኒስቴር ከዚህ ቀደም እንደሚደረገው ሁሉ በደብዳቤ ያሳወቁ ቢሆንም ዛሬ ነሐሴ 22/2012 በራስ ሆቴል ሊሰጥ ነበረው መግለቻ ግን የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ስለ መግለቻው መረጃ የለኝም በሚል መግለጫው እንዳይካሔድ መከልከሉ ታውቋል። ምንጭ : አዲስማለዳ @ethiocheck

ስድሳ የሚሆኑ የታጠቁ የትግራይ የልዩ ኃይል አባላት ወደ አማራ ክልል መግባታቸውን የአማራ ክልል ሲያስታውቅ የትግራይ ክልል በበኩሉ ጉዳዩን "ተረት ተረት ነው" በማለት አጣጥሎታል። የአማራ ክልል የመ
ስድሳ የሚሆኑ የታጠቁ የትግራይ የልዩ ኃይል አባላት ወደ አማራ ክልል መግባታቸውን የአማራ ክልል ሲያስታውቅ የትግራይ ክልል በበኩሉ ጉዳዩን "ተረት ተረት ነው" በማለት አጣጥሎታል። የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ከትግራይ ክልል ልዩ ኃይል አባላት ወደ አማራ ክልል እየመጡ መሆኑን ጠቅሰው 60 የሚሆኑ የታጠቁ የልዩ ኃይል አባላት ወደ ክልሉ ከነትጥቃቸው መግባታቸውን አስታውቀዋል። እነዚህ ኃይሎች ከወልቃይትም ከራያ አካባቢ፣ አማራ የሆኑና እና አብዛኛዎቹ ደግሞ የትግራይ ተወላጆች መሆናቸውን ጠቅሰው አባላቱን ተቀብለው ትጥቅ በማስፈታት በአንድ ካምፕ ማስቀመጣቸውንም ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። ወደ አማራ ክልል የኮበለሉ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል አባላት አሉ ስለመባሉ በቢቢሲ የተጠየቁት የትግራይ የክልል የሕዝብና መንግሥት ግንኙነት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሐዱሽ ካህሱ፤ "ይህ የበሬ ወለደ ንግግር ካልሆነ በስተቀር እውነት አይደለም" ብለዋል። "ምናልባት ከአማራ ክልል ወደ ትግራይ ነው እየሄደ ያለው የሚለውን እነርሱ ይመልሱ እንጂ፤ ከትግራይ ወደ አማራ ክልል የሚሄድ የለም" ብለዋል። በሌላ በኩል አቶ ግዛቸው "የማንነት እና ወሰን ጥያቄን የአማራ ክልላዊ መንግሥት ትቶታል የሚለው ትክክል አይደለም" ያሉት አቶ ግዛቸው፤ የክልሉ መንግሥት የሕዝቡን ጥያቄዎች እያነሳ መሆኑን ጠቁመው የማንነት እና ወሰን፣ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት፣ የሕገ መንግሥት መሻሻል፣ ሃቀኛ ፌደራሊዝም ትግበራ እና ሌሎችም አቋም የተያዘባቸው መሆናቸውን አስረድተዋል። @ethiocheck

#BreakingNews ፎሬይን ፖሊሲ መፅሄት ማምሻውን እንደዘገበው የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዎ ሀገሪቱ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ በከፊል እንድታቆም ፍቃዳቸውን ሰጥተዋል ብሏል።
#BreakingNews ፎሬይን ፖሊሲ መፅሄት ማምሻውን እንደዘገበው የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዎ ሀገሪቱ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ በከፊል እንድታቆም ፍቃዳቸውን ሰጥተዋል ብሏል። ይህም የትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳንን በህዳሴ ግድብ ዙርያ ለማወያየት የጀመረው እንቅስቃሴ በኢትዮጵያ ተቃውሞ ገጥሞት መቆሙን ተከትሎ የመጣ ነው ብሏል። ፖምፔዎ ፍቃዳቸውን ያኖሩበት ይህ ውሳኔ በዚህ ሳምንት እንደተወሰነ መፅሄቱ ገልፆ በዚህም አሜሪካ ለኢትዮጵያ ከምታደርገው ድጋፍ ውስጥ 130 ሚልዮን ዶላሩን ልትቆርጥ አስባለች ብሏል። ለፀጥታ እና ደህንነት፣ ለፀረ-ሽብር እንቅስቃሴ፣ ለወታደራዊ ስልጠና፣ ለሰዎች ዝውውር ቁጥጥር እና ሌሎች ልማት ስራዎች የሚውሉ ድጋፎች ሊቋረጡ ከሚችሉት ውስጥ ተካተዋል ተብሏል። በሌላ በኩል ዘገባው አስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፎች እንዲሁም የጤና እርዳታዎች አይቋረጡም ብሎ የኮንግረስ ምንጮቹን ጠቅሶ ፅፏል። ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ: https://foreignpolicy.com/2020/08/27/trump-africa-gerd-dam-us-halts-foreign-assistance-funding-ethiopia-over-dam-dispute-egypt-sudan/ @ethiocheck

የሚኒሶታ ሴናተር ሁለት ዜጎቼን ኢትዮጵያ ትፍታልኝ ስትል ለስቴት ዲፓርትመንት ማመልከቻ አስገባች ጃዋር መሀመድን ጨምሮ ኢትዮጵያ ሁለት የአሜሪካ ዜጎችን አስራብኛለች ስለዚህ ዜጎቻችን እንዲፈቱ ሰትል
የሚኒሶታ ሴናተር ሁለት ዜጎቼን ኢትዮጵያ ትፍታልኝ ስትል ለስቴት ዲፓርትመንት ማመልከቻ አስገባች ጃዋር መሀመድን ጨምሮ ኢትዮጵያ ሁለት የአሜሪካ ዜጎችን አስራብኛለች ስለዚህ ዜጎቻችን እንዲፈቱ ሰትል የሚኒሶታ ሴናተር ለስቴት ዲፓርትመንት ማመልከቻ አስገብታለች። በተነሳው ሁከት ውስጥ በኢትዮጵያ የታሰሩት ጃዋር መሀመድ እና ሚሻ ቺሪ የተባሉ ሁለት የሚኒሶታ ነዋሪዎች ናቸው። FOX 9 በኢትዮጵያ የተፈጠረው አለመረጋጋት እንደቀጠለ ቢሆንም ሁለቱ የሚኒቶኒያ ሴኒተሮች የሚኒሶታ ነዋሪ የሆኑት እስረኞች መፈታት አለባቸወል የሚል ደብዳቤ ወደ አሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ልከዋል። ሁለቱ ጓደኞች ከጥቂት ዓመታት በፊት በሚኒሶታ የጀመሩትን የኦሮሞ ሚዲያ አውታር (OMN) ለማስፋት ወደ ኢትዮጵያ ሄደው ነበር፡፡ በዚያን ጊዜ በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ከፍተኛ ተስፋ ነበራቸው ፣ አሁን ግን ለእነሱ ሁሉም ነገር ተለውጦባቸዋል ሲል Fox 9 ዘግቦል ። Via Fox 9 @ethiocheck

ኢትዮ ቴሌኮም! የዋጋ ቅናሽ የተደረገባቸው ነባር አገልግሎቶች ፦ • በሞባይል ዳታ ጥቅልአገልግሎት እስከ 35 በመቶ ቅናሽ • በሞባይል ድምፅ ጥቅልአገልግሎት እስከ 29 በመቶ ቅናሽ • የሞባይል ድምፅ
ኢትዮ ቴሌኮም! የዋጋ ቅናሽ  የተደረገባቸው ነባር አገልግሎቶች ፦ • በሞባይል ዳታ ጥቅልአገልግሎት እስከ 35 በመቶ ቅናሽ • በሞባይል ድምፅ ጥቅልአገልግሎት እስከ 29 በመቶ ቅናሽ • የሞባይል ድምፅ እና ዳታ ጥምርአገልግሎት እስከ 28 በመቶ ቅናሽ • በፕሪሚየም ያልተገደበ የድምፅ ጥቅልአገልግሎት እስከ 21 በመቶ ቅናሽ •በፕሪሚየም ያልተገደበ የዳታ ጥቅል አገልግሎት እስከ 21 በመቶ ቅናሽ • በፕሪሚየም ያልተገደበ የድምፅ እና ዳታ ጥቅልአገልግሎት እስከ 20 በመቶ ቅናሽ • በፕሪሚየም ፕላስ ያልተገደበ ጥቅልአገልግሎት እስከ 16 በመቶ ቅናሽ እንዲሁም • በሳተላይት አገልግሎት (VSAT) ላይ እስከ 61 በመቶ የሚደርስ ቅናሽ ተደርጓል፡፡ አዲስ የቀረቡ አገልግሎቶች ፦ • My Ethiotelየሞባይል መተግብሪያ • Ethio eCareዌብ ፖርታል • የሞባይል ጥቅል ክሬዲት አገልግሎት • የድህረ ክፍያ የሞባይል ኮንትራት ፕላን • ኢትዮ አቫያ ስፔስ ኢንተርፕራይዝ ኮላቦሬሽን ሶልዩሽን • በጤና ይቆዩ የሞባይል ጥቅል እስከ 59 በመቶ ቅናሽ • አደይ አበባየሞባይል ጥቅል እስከ 53 በመቶ ቅናሽ • መልካም ማለዳ የሞባይል ጥቅል አገልግሎት እስከ 33 በመቶ ቅናሽ • በዓለም አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ላይ አዲስ የቀረቡ የዓለም አቀፍ የወጪ ጥሪ ጥቅል አገልግሎት ፦ • የዓለም አቀፍ የወጪ ጥሪ ጥቅል አገልግሎት • ዓለም አቀፍ የገቢ ጥሪ ለሚቀበሉ ደንበኞች የቀረበ የሞባይል አገልግሎት ጥቅል ስጦታ • በዓለም አቀፍ አየር ሰዓት አገልግሎት ላይ የተደረገ 100% የአየር ሰዓት ስጦታ @ethiocheck

ችሎት! እነአቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ ስምንት (8) ተጠርጣሪዎች ቀሪ የዐቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክር ለመስማት የተቀጠረ ቢሆንም ከ4ኛ እስከ 9ኛ ያሉ ተጠርጣሪዎች የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ውጤ
ችሎት! እነአቶ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ ስምንት (8) ተጠርጣሪዎች ቀሪ የዐቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክር ለመስማት የተቀጠረ ቢሆንም ከ4ኛ እስከ 9ኛ ያሉ ተጠርጣሪዎች የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ውጤት ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዪት ስላልመጣ ለነሃሴ 22 ቀን ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥታል። በዛሬው ችሎት የተገኙት አቶ ጃዋር መሀመድ ውጭ ሀገር ከሚገኙት ልጃቸው እና ባለቤታቸው ጋር በቪዲዮ ኮንፈረንስ አንድ ጊዜ ብቻ መገናኘታቸውን በመግለፅ በድጋሚ እንዲገናኙ እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። ፍርድ ቤቱም በዚህ እና በተነሱ ሌሎች አቤቱታዎች ላይ በቀጣይ ቀጠሮ ትዕዛዝ እሰጥበታለሁ ብሏል። Via Tarietk Adugna (ኤፍ ቢ ሲ) @ethiocheck

የእነ ጃዋር መሐመድን የቀዳሚ ምርመራ መዝገብ የሚመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፤ የ6 ተጠርጣሪዎችን የኮሮና ምርመራ ለመጠበቅ እና ተጠርጣሪዎች ባቀረቧቸው አቤቱታዎች ላይ ትዕዛዝ ለመ
የእነ ጃዋር መሐመድን የቀዳሚ ምርመራ መዝገብ የሚመለከተው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፤ የ6 ተጠርጣሪዎችን የኮሮና ምርመራ ለመጠበቅ እና ተጠርጣሪዎች ባቀረቧቸው አቤቱታዎች ላይ ትዕዛዝ ለመስጠት ለአርብ ነሐሴ 22 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጠ። [Ethiopia Insider]ethiocheck @ethiocheck

መንግስት ፍትህን እስከመጨረሻው እንዲያሰፍን ቤተ ክርስቲያኒቷ አሳሰበች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የተፈጸሙ ጥቃቶችን አስመልክቶ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫን ሰጥታለች። ጥቃቱ በተቀነባበረ መንገድ የተፈጸመ መሆኑን አረጋግጫለሁ ያለችው ቤተክርስቲያኒቷ "የመንግሥትን መዋቅር ተገን ያደረጉ የእምነት እና የብሄር ጽንፈኞች አስቀድመው ከተደራጁ ኃይሎች ጋር በመቀናጀት የፈጸሙት ስልታዊ እና አረመኔያዊ ጥቃት" ኦርቶዶክሳውያን ምእመናንን ዒላማ አድርጎ መፈጸሙ ተረጋግጧል ብላለች። የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች ተቀነባብረው የተፈጸሙ ጥቃቶች 67 የቤተ እምነቱ ተከታዮች መገደላቸውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አስታውቃለች። የደረሰውን ጉዳት የሚያጠና ዐቢይ ኮሚቴ ተቋቁሞ ጥቃቶቹ የተፈጸሙባቸውን አካባቢዎች የመለየት፣ ተጎጂዎችን የማጽናናት እና መረጃ የማሰባሰብ ሲሰራ እንደነበርም ነው ያስታወቀችው። ኮሚቴው ባሰባሰበው መረጃ ከሰኔ 22 እስከ 24 በነበሩት 3 ተከታታይ ቀናት በተፈጸመው ጥቃት ከ67 በላይ ምዕመናን በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን፣ 38 ከባድ እና 29 ቀላል የአካል ጉዳቶች መድረሳቸውንም አረጋግጧል። ከ7 ሺ በላይ ምዕመናን ከመፈናቀል ባሻገል ለከባድ ስነልቦናዊ እና አዕምሯዊ ቀውስ መዳረጋቸውንም የገለጸም ሲሆን ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙንም በመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ አረጋግጧል። ተጎጂዎችን በአፋጣኝ ባሉበት ለመርዳትና በዘላቂነት ለማቋቋም የሚያስችል አዲስ ስልት ቀይሶ እየተንቀሳቀሰ እንደሚገኝም ነው ያስታወቀው። መንግስት በአስቸኳይ በህይወት የመኖርና ሃብት የማፍራትን ሰብዓዊ እና የዜግነት መብቶች በማስከበር የደህንነትና የኑሮ ዋስትናን እንዲያረጋግጥ የጠየቀችው ቤተክርስቲያኒቷም አጥፊዎች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ፍትህ እስከመጨረሻው እንዲያሰፍን፣በጥቃቱ ምንም ዓይነት ተሳትፎ ሳይኖራቸው የታሰሩ ኦርቶዶክሳውያን እንዲፈቱ እና ከአሁን በፊትም የተፈጸሙ ተመሳሳይ ጥቃቶች ተጣርተው ለህዝብ እንዲያቀርቡ አሳስባለች። አርቲስት ሃጫሉ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ/ም በአዲስ አበባ ገላን ኮንዶሚኒየም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መገደሉ የሚታወስ ነው። @ethiocheck

የኢንተርኔት ጥቅል አገልግሎት ላይ እስከ 35 በመቶ ቅናሽ ተደረገ እንዲሁም በቤትዎ ይቆዮ የጥቅል አገልግሎትም 59 በመቶ ቅናሽ ተደርጓል። የድምፅ ጥቅል አገልግሎት ላይም የ29 በመቶ ቅናሽ የጠደረገ
የኢንተርኔት ጥቅል አገልግሎት ላይ እስከ 35 በመቶ ቅናሽ ተደረገ እንዲሁም በቤትዎ ይቆዮ የጥቅል አገልግሎትም 59 በመቶ ቅናሽ ተደርጓል። የድምፅ ጥቅል አገልግሎት ላይም የ29 በመቶ ቅናሽ የጠደረገ ሲሆን አገልግሎቱም ከነገ ነሐሴ 21/2012 ጀምሮ በስራ ላይ ይውላል። @ethiocheck

በሀገራችን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ40ሺ በልጧል። ከ700 የሚልቁት ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል።በዓለምም ደግሞ ከ23.6 ሚሊየን የሚበልጡት በቫይረስ ተይዘው 813 ሺ የሚልቁት ለሞት
በሀገራችን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ40ሺ በልጧል። ከ700 የሚልቁት ደግሞ ህይወታቸውን አጥተዋል።በዓለምም ደግሞ ከ23.6 ሚሊየን የሚበልጡት በቫይረስ ተይዘው 813 ሺ የሚልቁት ለሞት ተዳርገዋል። እባክዎ ይጠንቀቁ። #ማስኮን ያድርጉ #እጆን በአግባቡና በሳሙና ይታጠቡ #ርቀቶን ይጠብቁ #ሌሎች የህክምና ባለሞያዎች የሚላቸውን የጥንቃቄ መንገዶችን መከተሎን አይርሱ ! መልካም ቀን!! @ethiocheck

ከድምጻዊ ሀጫሉ ግድያ ጋር በተያያዘ በተፈጠረ ሁከት 67 ምዕመናን እንደተገደሉባት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አስታወቀች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተፈጠረው ሁ
ከድምጻዊ ሀጫሉ ግድያ ጋር በተያያዘ በተፈጠረ ሁከት 67 ምዕመናን እንደተገደሉባት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አስታወቀች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተፈጠረው ሁከት ምክንያት ተጎድተዋል ወደ ተባሉ አካባቢዎች ተሰማርታ ምልከታ ካካሄደች በኋላ በአዲስ አበባ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት መግለጫ በመስጠት ላይ ትገኛለች። ቤተ ክርስቲያኗ በዚህ ጊዜ እንዳለችው ከድምጻዊ ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በኦሮሚያ ፣ በሐረሪ እና በድሬዳዋ ከተማ አስተዳድር በተፈጠረ ሁከት 67 ምዕመናን ሲገደሉ ከ7 ሺህ በላይ ሰዎች ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል። በአጠቀላይም ሁከቱን መነሻ በማድረግ ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የምዕመናን ንብረት መውደሙም በመግለጫው ላይ ተገልጿል። በኦሮሚያ ክልል፣በድሬዳዋ ከተማ አስተዳድር እና በሌሎች አካባቢዎች ምዕመናን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድለዋል፣ እንደ ሰውም አስክሬናቸው በክብር አልተቀበረም ፣ ሴቶች በባለቤታቸው፣በወንድምና በአባታቸው ፊት መደፈራቸው በምልከታ መረጋገጡ በመግለጫው ላይ ተገልጿል። #EthioFM @ethiocheck

በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ ምስክሮች የመሰማት ሂደት ላይ ነገ ውሳኔ ሊሰጥ ነው በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ ስር በተጠረጠሩ 14 ግለሰቦች ላይ የቅድመ ምርመራ ምስክሮችን እያደመጠ የሚገኘው የፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት የአራዳ ምድብ ተረኛ ወንጀል ችሎት ይሰማል ተብሎ ከሚጠበቀው 15 ምስክሮች ውስጥ ሶስቱን በሁለት ቀጠሮ ሰምቷል። ቀሪ ምስክሮችን ለመስማት “በኮሮና ቫይረስ የተያዙት ድነው እስኪመለሱ ይዘግይ ወይም ይቀጥል” በሚለው ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤቱ ነገ ረቡዕ ከሰአት ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ዝርዝር ዝገባውን ለማንበብ ይህን ማገናኛ (ሊንክ) ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2020/1759/ @ethiocheck

ኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር እና የግድቡን ጉዳዮች በንግግር ብቻ ለመፍታት ተስማሙ! ሱዳንና ኢትዮጵያ የቆዩ የጋራ ችግር መፍቻ ዘዴዎችን በመጠቀም በመካከላቸው ያሉ የድንበር እና ከሕዳሴ ግድብ ጋር
ኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር እና የግድቡን ጉዳዮች በንግግር ብቻ ለመፍታት ተስማሙ! ሱዳንና ኢትዮጵያ የቆዩ የጋራ ችግር መፍቻ ዘዴዎችን በመጠቀም በመካከላቸው ያሉ የድንበር እና ከሕዳሴ ግድብ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችንም በውይይት ብቻ ለመፍታትም ከስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ ከአሜሪካ ‘ሽብርተኝነትን የሚደግፉ ሀገራት ዝርዝር መዝገብ’ ዉስጥ የሱዳን ስም እንዲሰረዝ ኢትዮጵያ ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥልም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አረጋግጠዋል፡፡ የህዳሴ ግድቡን በተመለከተ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የሚከናወነው የሶስትዮሽ ድርድር ዉጤታማ እንዲሆን በመተማመን ላይ የተመሰረተው ዉይይት እንዲቀጥል ሁለቱ ጠቅላይ ሚኒስትሮች እና ካቢኔዎቻቸው ተስማምተዋል፡፡ Readmore https://telegra.ph/AlAin-08-25 @ethiocheck

በአርቲስት ሀጫሉ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ከበደ ገመቹ ዛሬ ለ4ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርቧል! በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ከበደ ገመቹ ዛሬ ለአራተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርቧል
በአርቲስት ሀጫሉ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ከበደ ገመቹ ዛሬ ለ4ኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርቧል! በአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ የግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ከበደ ገመቹ ዛሬ ለአራተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርቧል። በዚህ ወቅትም በተጠርጣሪ እጅ ላይ የተገኘው የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ በብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ኤጀንሲ መመርመሩን መርማሪ ፓሊስ ገልጿል። ተጠርጣሪው ከበደ ገመቹ በበኩሉ በአስተርጓሚ በኩል በሰጠው አስተያየት ከተያዘ ከአንድ ወር ከ16 ቀን በላይ እንደሆነው ጠቅሶ አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ የተገደለበት ሽጉጥ የኔ አይደለም ሲል ፍርድ ቤቱ ዋስትና እንዲፈቅድለት ጠይቋል። መርማሪ ፖሊስም ሽጉጡ የተጠርጣሪው መሆኑን ለችሎቱ አብራርቷል፤ በግድያው ወቅት በቦታው እንደነበር ጠቅሷል። ጉዳዩን የተከታተለው ችሎቱ ለፖሊስ የምርመራ ውጤት ትንተና ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልገዋል ሲል የ10 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ፈቅዷል። ምንጭ፡- FBC/ ታሪክ አዱኛ @ethiocheck

ትምህርት ሚኒስቴር የቀጣይ ዓመት የትምህርት ምዝገባ ከነሃሴ 20/2012 ዓ/ም ጀምሮ መካሄድ እንደሚጀምር አሳወቀ! ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶች የቀጣይ አመት የትምህርት ምዝገባን ከነሃሴ 20
ትምህርት ሚኒስቴር የቀጣይ ዓመት የትምህርት ምዝገባ ከነሃሴ 20/2012 ዓ/ም ጀምሮ መካሄድ እንደሚጀምር አሳወቀ! ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶች የቀጣይ አመት የትምህርት ምዝገባን ከነሃሴ 20 ጀምረው ማካሄድ ይችላሉ ብሏል። ትምህርት ቤቶች ምዝገባውን ሲያካሂዱ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በዓለም የጤና ድርጅትና በጤና ሚኒስቴር የተቀመጡ መከላከያዎችን በሚገባ በመተግበር መሆን እንዳለበት ማሳሰቢያ ተሰጥቷል። ትምህርት የሚጀመርበት ቀን በቀጣይ እንደሚወሰንና ይፋ እንደሚደረግ ተገልጿል። አካላዊ ርቀት ጠብቆ ለማስተማር እንዲሁም የንፅህና መጠበቂያዎችን ከማዘጋጀት እና ሌሎች የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከላከያ ተግባራትን ተግባራዊ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት የሚደረግባቸው ተግባራት እንደሆኑ ተነግሯል። በምን አይነት መልኩ ትምህርት መጀመር እንዳለበት የተለያዩ አማራጮችን ለማመላከት ሰፊ ውይይት እየተደረገባቸው ሲሆን ውሳኔ ሲያገኝ ይፋ ይደረጋል ተብሏል። የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ጊዜን በተመለከተ ሚኒስቴሩ በቅርብ የሚያሳውቅ ሲሆን ተማሪዎች ራሳቸውን እያዘጋጁ እንዲቆዩ ማሳሰቢያ ተሠጥቷል። @ethiocheck

አቶ ደጀኔ እና ጋዜጠኛ ጉዮ በዋስ ከእስር እንዲወጡ ተወሰነ! የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራር የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ
አቶ ደጀኔ እና ጋዜጠኛ ጉዮ በዋስ ከእስር እንዲወጡ ተወሰነ! የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) አመራር የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ እና አብረዋቸው በአንድ መዝገብ ችሎት የቀረቡ ሁለት ተጠርጣሪዎች በ10 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ዛሬ ብይን ሰጠ። በሌላ መዝገብ ዛሬ ችሎት ፊት የቀረበው የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ (OMN) ጋዜጠኛ ጉዮ ዋሪዮ በተመሳሳይ የዋስትና የገንዘብ መጠን ከእስር እንዲወጣ በይኗል። @ethiocheck

#UPDATE በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ላይ የግድያ ሙከራ ተደርጎ ከሸፏል ይህንን ጉዳይም የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አበረ አዳሙን 'ሚዛን ቴሌቪዥን' ለተባ
#UPDATE በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ላይ የግድያ ሙከራ ተደርጎ ከሸፏል ይህንን ጉዳይም የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አበረ አዳሙን 'ሚዛን ቴሌቪዥን' ለተባለ ሚዲያ ተናግረዋል እየተባለ ሲናፈስ ነበር። በኢትዮጵያ ዜና/መረጃዎች እያጣራ ይፋ እያደረገ የሚገኘው 'ኢትዮጵያ ቼክ ፕሮጀክት' አቶ አበረ በስልክ አነጋግሯቸው "ይህ ፍፁም ስህተት የሆነ ወሬ ነው ፣ አሁን ላይ በክልሉ ምንም አይነት የፀጥታ መደፍረስም ሆነ የተባለው አይነት ችግር አልተከሰተም" ብለዋል። ሚዛን ቴሌቭዥን የተባለ የዩትዩብ ገፅ ላይ በስልክ ገብተው ተጠርጣሪዎች እንደተያዙ የሚያወሩት እርሳቸው እንደሆኑ ሲጠየቁ "ግዜውን አላስታውስም፣በፍፁም ግን የቅርብ ግዜ አይደለም" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። @ethiocheck

ለህዳሴው ግድብ ሰራተኞች ማበረታቻ የሚሆን 40 የበሬ ሰንጋ ስጦታ ተበረከተ! የአማራና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን እየጎበኙ ነው። የአማራ ክልል ርእ
ለህዳሴው ግድብ ሰራተኞች ማበረታቻ የሚሆን 40 የበሬ ሰንጋ ስጦታ ተበረከተ! የአማራና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን እየጎበኙ ነው። የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር ተመሥገን ጥሩነህ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን እየጎበኙ ነው። በቅርቡ ለግድቡ ግንባታ ድጋፍ 33 ሚሊዮን ብር ቦንድ የገዙት ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴም ለፕሮጀክቱ ሰራተኞች ማበረታቻ የሚሆን 40 የበሬ ሰንጋ ስጦታ አበርክተዋል። - #አብመድ @ethiocheck

በአንዴ 28 ሜትር ኪዩብ አረም ማረምና መሸከም የሚችል ማሽን ባህርዳር ገባ! ተቀማጭነቱ በአሜሪካ የሆነው ዓለማቀፉ ጣናን መልሶ ማቋቋም ማህበር በአሜሪካና በእንግሊዝ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን በማስተባ
በአንዴ 28 ሜትር ኪዩብ አረም ማረምና መሸከም የሚችል ማሽን ባህርዳር ገባ! ተቀማጭነቱ በአሜሪካ የሆነው ዓለማቀፉ ጣናን መልሶ ማቋቋም ማህበር በአሜሪካና በእንግሊዝ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን በማስተባበር በ5.8 ሚሊዮን ብር የገዛውን የእንቦጭ ማጨጃ ማሽን ዛሬ ባሀር ዳር መግባቱን ጣና አዋርድ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል:: ማሽኑ በአንዴ 28 ሜትር ኪዩብ አረም በአንዴ ማረምና መሸከም የሚችል ሲሆን 75 የፈረስ ጉልበትም አለው፡፡ ማህበሩ ከዚህ ቀደም የተለያዩ ድጋፎች ሲያደርግ መቆየቱም ይታወሳል፡፡ ዓለማቀፉ ጣናን መልሶ ማቋቋም ማህበር በውጭ ሃገር በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ-ኢትዮጵያዊያን የተመሰረተ የበጎ አድራጎት ማህበር ነው። የማህበሩ አባላትም በነጻ ለሃገራቸው ድጋፍ ለማድረግ የተሰባሰቡ በአካባቢ ጥበቃና ውሃ አያያዝ ዙርያ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው በጎ ፍቃደኞችን ያካተተ ነው። @ethiocheck