2 485
Suscriptores
Sin datos24 horas
-157 días
-5230 días
Archivo de publicaciones
2 485
እናት ፓርቲ፤ ዶ/ር ሰይፈ ሥላሴ አያሌውን ፕሬዝዳንት አድርጎ መረጠ
እናት ፓርቲ፤ ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩትን ዶ/ር ሰይፈ ሥላሴ አያሌውን ፕሬዝዳንት፤ የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑትን ጥሩማር አባተን ደግሞ ምክትል ፕሬዝዳንት አድርጎ መረጠ። ፓርቲው ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 30፤ 2015 ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤው፤ የተሻሻለውን የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ፣ አደረጃጀቱን የሚወስነውን ሰነድ እና የአምስት ዓመት ዕቅድም አጽድቋል።
ለስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ ከፍተኛ ዕጩዎችን በማቅረብ በሶስተኛ ደረጃ ተቀምጦ የነበረው እናት ፓርቲ፤ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ሊያካሄድ የነበረው ከአንድ ወር ገደማ በፊት የካቲት መጨረሻ ላይ ነበር። በአዲስ አበባ አራት ኪሎ አካባቢ በሚገኘው የቅድስት ስላሴ ዩኒቨርሲቲ አዳራሽ ሊካሄድ የነበረው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ፤ “ከበላይ አካል መጣ” በተባለ ትዕዛዝ ምክንያት መከልከሉ ይታወሳል።
ትላንት በተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ፤ እናት ፓርቲን በፕሬዝዳንትነት እንዲመሩ የተመረጡት ዶ/ር ሰይፈ ሥላሴ የፖለቲካ ተሳትፏቸውን የጀመሩት በዚሁ ፓርቲ ውስጥ ነው። ከመጀመሪያ እስከ ዶክትሬት ዲግሪያቸውን በኢኮኖሚክስ ትምህርት ዘርፍ በሩስያ የተከታተሉት ዶ/ር ሰይፈ ስላሴ፤ አብዛኛውን የስራ ጊዜያቸውን ያሳለፉት በመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ ነው።
ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10556/
@EthiopiaInsiderNews
2 485
“ከወቅታዊ ሁኔታ አንጻር የሚነሳው ጥያቄ ትክክል ቢሆንም፤ በሀገር ደረጃ የተወሰነው ውሳኔ የሚጠቅም ነው” – ዶ/ር ይልቃል ከፋለ
የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላትን “በፌደራል እና በክልል የጸጥታ ተቋማት ማደራጀትን” አስመልክቶ በተላለፈው ውሳኔ ላይ የሚነሳው ጥያቄ “ከወቅታዊ ሁኔታ አንጻር ትክክል ቢሆንም፤ በሀገር ደረጃ የተወሰነው ውሳኔ የሚጠቅም ነው” ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ተናገሩ። ይህን ውሳኔ በተመለከተ በተሰራጨ “አጥፊ ፕሮፖጋንዳ” ምክንያት፤ የተወሰኑ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት ከካምፖቻቸው በመውጣት ወደ ከተሞች እና ወደ የቤተሰቦቻቸው መሄዳቸውንም ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸዋል።
ዶ/ር ይልቃል ይህን ያሉት የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታን በተመለከተ ለክልሉ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 1፤ 2015 በሰጡት መግለጫ ነው። “የአማራ ክልል ልዩ ኃይልን በተለየ መንገድ የሚጎዳ ነገር እና ውሳኔ ለብቻው አልተደረገም። ወጥ እና ሀገራዊ ውሳኔ ነው የተደረገው። በሁሉም ክልል የሚፈጸም ነው። ለቀጣይ ሀገር ግንባታም የሚጠቅም፣ አብሮነትን የሚያሳድግ ነው ብለን እናምናለን” ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በዛሬው መግለጫቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሆኖም የአማራ ክልል ከሌላው ክልል ተነጥሎ፤ “ጥያቄ የሚያነሳበት መንገድ ምንድነው የሚለው በደንብ መታየት አለበት” ብለዋል። “ከወቅታዊ ሁኔታ አንጻር የሚነሳው ጥያቄ ትክክል ቢሆንም፤ በሀገር ደረጃ አፈጻጸሙ መሄድ ያለበት እና የሚጠቅም መሆኑን ደግሞ በውል መገንዘብ ይገባናል። ስለሆነም ከዚህ ችግር በመተባበር፣ በመወያየት እና ችግርን እና ቅሬታን በሰላምና በውይይት በመፍታት መውጣት እንችላለን” ሲሉ ዶ/ር ይልቃል ተስፋቸውን ገልጸዋል።
ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10551/
2 485
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በክልል ልዩ ኃይሎች ላይ የተላለፈው ውሳኔ፤ “ዋጋ ተከፍሎም ቢሆን ተግባራዊ ይደረጋል” አሉ
የክልል ልዩ ኃይሎችን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማካተቱ ውሳኔ፤ “ዋጋ ተከፍሎም ቢሆን” ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አስታወቁ። ይህ ውሳኔ ተግባራዊ እንዳይደረግ “ሆን ብለው የአፍራሽነት ሚና በሚጫወቱ” አካላት ላይ፤ “ተገቢው የህግ ማስከበር እርምጃ” እንደሚወሰድ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስጠንቅቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህን ያሉት የክልል ልዩ ኃይሎችን በሚመለከት በመንግስት የተላለፈውን ውሳኔ በተመለከተ ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 1፤ 2015 በይፋዊ የፌስ ቡክ ገጻቸው በተሰራጨ መግለጫቸው ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ መግለጫቸው፤ ተቃውሞ ከሚያነሱ አካላት ውስጥ የተወሰኑት ጉዳዩን በደንብ ካለመረዳት የሚያደርጉት መሆኑን ገልጸዋል። ቀሪዎቹ አካላት ግን ሆን ብለው ውሳኔውን ለማደናቀፍ የሚሰሩ ናቸው ሲሉ ከስሰዋል።
“ ‘የዚህ ወይም የዚያ ክልል ልዩ ኃይል ብቻውን ትጥቅ ሊፈታ ነው፤ የዚህኛው ክልል ይቆይ ተብሏል፤ ይሄን ወይም ያንን ሕዝብ ለመጉዳት የተደረገ ነው’ የሚሉ ውዥንብሮችን የሚነዙ አካላት ገሚሶቹ ባለማወቅ ሲሆን፤ የተቀሩት ዓላማቸው ሕዝብ ከማበጣበጥ የዘለለ አይደለም” ብለዋል አብይ።
“ጥቂት የማይባሉት ‘የክልል ልዩ ኃይል መፍረስ አለበት’ ብለው ሲጽፉና ሲሞግቱ የከረሙ ናቸው፤ ጠለቅ ብለን ብንፈትሻቸው፥ ይሁን ሲሏቸው አይሁን፣ አይሁን ሲሏቸው ይሁን የማለት ልማድ የተጠናወታቸው ሆነው እናገኛቸዋለን” ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመግለጫቸው ተችተዋል። አብይ “የአፍራሽነት ሚና” አላቸው ባሏቸው አካላት መንግስታቸው ሊወስደው ስላሰበው እርምጃም በመግለጫቸው ጥቆማ ሰጥተዋል።
2 485
በደጀን ከተማ በተቃውሞ መንገድ በመዘጋቱ፤ የሀገር አቋራጭ ትራንስፖርት አገልግሎት ተቋረጠ
ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር ከተማ የሚስደው መንገድ ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ ደጀን ከተማ ላይ በመዘጋቱ፤ የሀገር አቋራጭ ትራንስፖርት አገልግሎት መቋረጡን የከተማይቱ አስተዳደር ኃላፊዎች እና ነዋሪዎች ተናገሩ። በደጀን ከተማ በዛሬው ዕለት የንግድ እንቅስቃሴ መቆሙ እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መዘጋታቸውም ተገልጿል።
በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ወደምትገኘው ደጀን ከተማ የሚያስገባው መንገድ የተዘጋው፤ “የክልሉ ልዩ ኃይል መበተንን በሚቃወሙ ነዋሪዎች” እንደሆነ የከተማዋ የሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጌ ዘውዱ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። የደጀን ከተማ ወጣቶች ተቃውሟቸውን ማሰማት የጀመሩት ከትላንት አርብ ከሰዓት ጀምሮ መሆኑን ኃላፊው ገልጸዋል።
ከቀኑ አስር ሰዓት ገደማ ላይ ተቃውሞ የሚያሰሙ ነዋሪዎች፤ ወደ ከተማዋ የሚያስገባው መንገድ ላይ ድንጋይ በማስቀመጥ የተሽከርካሪዎች ፍሰት እንዲቆም ማድረጋቸውን ኃላፊው አስታውቀዋል። የከተማዋ ኮሚዩኒኬሽን ቡድን መሪ አቶ ሞኙ ሆዴ አሳየ በበኩላቸው፤ ከደጀን ከተማ መግቢያ በተጨማሪ በከተማው የሚያልፈው መንገድ መዘጋቱንም አስረድተዋል።
ዝርዝሩን ለማንበብ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10539/
@EthiopiaInsiderNews
2 485
በወለንጪቲ ከተማ አቅራቢያ 15 አሽከርካሪዎች ባልታወቁ ታጣቂዎች መታገታቸው ተገለጸ
⚫ አምስቱ አሽከርካሪዎች ከቆይታ በኋላ ተለቅቀዋል ተብሏል
በኦሮሚያ ክልል ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ከአዋሽ ወደ ወለንጪቲ ከተማ ሲጓዙ የነበሩ 15 አሽከርካሪዎች በታጣቂዎች መታገታቸውን እና አምስቱ በተስኋላ መለቀቃቸውን የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሰሪዎች ፌዴሬሽን አስታወቀ። የቀሩትን አሽከርካሪዎች ለማስለቀቅ የጸጥታ አካላት “ኦፕሬሽን” መጀመራቸውን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ገልጿል።
የኢትዮጵያ ትራንስፖርት አሰሪዎች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ብርሃኔ ዘሩ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” እንደገለጹት፤ አሽከርካሪዎቹ ባልታወቁ ታጣቂዎች የታገቱት ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ መጋቢት 26፤ 2015 በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ቦሰት ወረዳ ውስጥ በምትገኘው ወለንጪቲ ከተማ አቅራቢያ ነው፡፡ ከአዲስ አበባ በ117 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ወለንጪቲ ከተማ አቅራቢያ የታገቱት አሽከርካሪዎች፤ ማዳበሪያ እና ስኳር እያጓጓዙ እንደነበር የጠቆሙት አቶ ብርሃኔ፤ “የተወሰነው” ጭነት በታጣቂዎቹ መዘረፉን ተናግረዋል።
ታጣቂዎቹ አሽከርካሪዎቹን ወዳልታወቀ ቦታ መውሰዳቸውን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ ተሽከርካሪዎቹ ከእገታው በኋላም በቦታው ቆመው መቆየታቸውን አስረድተዋል። በአሽከርካሪዎቹ ላይ እገታ መፈጸሙን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ያረጋገጡት የኢትዮጵያ የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማህበር አስተባባሪ አቶ አብዱራሂም መሀመድ፤ ተሽከርካሪዎቹ ዛሬ ከእገታው ቦታ መነሳታቸውን ተናግረዋል፡፡
የተሽከርካሪዎቹ ባለንብረቶች የባለቤትነት ማረጋገጫቸውን በማሳየት ከቦታው እንዲነሱ ማድረጋቸውንም አክለዋል፡፡ አቶ ብርሃኔ በበኩላቸው ከትላንት በስቲያ ከታገቱት ውስጥ አምስቱ የኦሮሚያ ክልል የመንግስት የልማት ድርጅት የሆነው ገዳ ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ማህበር አሽከርካሪዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ እነዚህ አሽከርካሪዎች ከቆይታ በኋላ መለቀቃቸውን፤ ይሁንና በምን አይነት መንገድ እንደተለቀቁ እስካሁን መረጃ እንዳላገኙ አክለዋል።
* * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/10485/
[ፎቶ፦ ከ “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ፋይል የተወሰደ]
@ethiopianinsider1
2 485
በአዲስ አበባ ከተማ ባሉ ትምህርት ቤቶች የኦሮምኛ ቋንቋ በተጨማሪነት መሰጠት ተጀመረ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር በሚተዳደሩ ትምህርት ቤቶች፤ የኦሮምኛ ቋንቋ ትምህርት ካለፈው ሳምንት ጀምሮ መሰጠት ተጀመረ። የከተማይቱ ትምህርት ቢሮ የተጨማሪ ቋንቋ ትምህርቱን የሚሰጡ 2,600 ገደማ መምህራንን ለመቅጠር በሂደት ላይ መሆኑን አስታውቋል።
የብዝኃ ቋንቋ ስርዓተ ትምህርት በአዲስ አበባ በሚገኙ የመጀመሪያ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መተግበር የተጀመረው፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ባለፈው ጥር ወር ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነው። በዚህ ውሳኔ መሰረት በአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በሚሰጥባቸው ትምህርት ቤቶች ኦሮምኛ በሁለተኛ ቋንቋነት እንዲሰጥ ይደረጋል።
የአፍ መፍቻቸው ኦሮምኛ ለሆነ እና በዚሁ ቋንቋ ለሚማሩ ተማሪዎች ደግሞ፤ አማርኛን እንደ ተጨማሪ ቋንቋ እንዲወስዱ ካቢኔው ወስኖ ነበር። የኮተቤ ዩኒቨርስቲ ያካሄደውን ጥናት መሰረት በማድረግ እንደተላለፈ የተገለጸው ይህ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ውሳኔ፤ የአረብኛ እና ፈረንሳይኛ ቋንቋ ትምህርት ለዘጠነኛ እና አስረኛ ክፍል ተማሪዎች በምርጫቸው መሰረት እንዲሰጥ መወሰኑም በወቅቱ ተገልጿል።
ይህንን መሰረት በማድረግ የሀገር ውስጥ ተጨማሪ ቋንቋዎች ከሶስተኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች፤ አሁን ከተጀመረው የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት ጀምሮ እንዲሰጥ መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አድማሱ ደቻሳ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል። በአዲስ አበባ ከተማ ካሉት 786 የግል እና የመንግስት ትምህርት ቤቶች ውስጥ፤ 625 ያህሉ የኦሮምኛ ቋንቋን በተጨማሪነት ማስተማር መጀመራቸውንም አቶ አድማሱ ገልጸዋል።
* ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ:- https://ethiopiainsider.com/2023/9806/
@ethiopianinsider1
2 485
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የሚያቀርቧቸውን የአስፈጻሚ አካላትን ሹመት ለማጽደቅ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ ማክሰኞ ስብሰባ ሊያደርግ ነው። ሁለት የፓርላማ አባላት የነገው አጀንዳ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚያቀርቧቸውን ተሿሚዎች ሹመት ማጽደቅ” መሆኑን የሚገልጽ መልዕክት እንደደረሳቸው ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናግረዋል።
የተወካዮች ምክር ቤት ለመገናኛ ብዙሃን ዛሬ ባሰራጨው መረጃም ነገ ከቀኑ 7:30 ጀምሮ በሚካሄድ ስብሰባ ፓርላማው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የቀረቡ ሹመቶችን መርምሮ እንደሚያጸድቅ አስታውቋል። አንድ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የፓርላማ አባል፤ በምክር ቤቱ ጽህፈት ቤት በኩል የተላለፈው መልዕክት “ማንም የምክር ቤት አባል እንዳይቀር” የሚል ማሳሰቢያ መያዙን አክለዋል።
አራት የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ካቢኔ አባላት ከትላንት በስቲያ ቅዳሜ ከኃላፊነት መነሳታቸው ይታወሳል። ከኃላፊነት ተነስተው “በክብር ሽኝት” እንደተደረገላቸው የተገለጹት ሚኒስትሮች፤ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስተሯ ዳግማዊት ሞገስ፣ የማዕድን ሚኒስትሩ ታከለ ኡማ እና የግብርና ሚኒስትሩ ኡመር ሁሴን ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትሩ አቶ ተፈሪ ፍቅሬ ናቸው።
ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ ከሶስት ሳምንት በፊት ሹመት ከሰጧቸው አስራ አራት አምባሳደሮች መካከል አቶ ኡመር ሁሴን እና አቶ ተፈሪ ፍቅሬ ይገኙበታል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@ethiopianinsider1
2 485
መስከረም አበራ “በጥላቻ ንግግር” እና “በሐሰተኛ መረጃ ስርጭት” ክስ ተመሰረተባት
የፌደራል ዐቃቤ ህግ የ“ኢትዮ ንቃት” የዩ-ቲዩብ መገናኛ ብዙኃን መስራች እና ባለቤት በሆነችው መስከረም አበራ እና አምሀ ደገፋ በተባሉ የስራ ባልደረባዋ ላይ “በጥላቻ ንግግር” እና “በሐሰተኛ መረጃ ስርጭት” ሁለት ክሶች መሰረተ። ክሱ የቀረበለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፤ መስከረም ክሷን በውጭ ሆና እንድትከታተል የ50 ሺህ ብር ዋስትና ፈቅዷል።
ዐቃቤ ህግ ዛሬ ሐሙስ ታህሳስ 27፤ 2015 በዋለው ችሎት፤ በመስከረም ላይ ክስ የመሰረተው በባለቤትነት በምታስተዳድረው “ኢትዮ ንቃት” የዩቲዩብ መገናኛ ብዙኃን ባስተላለፈቻቸው ፕሮግራሞች መሆኑን አስረድቷል። መስከረምን ወክለው በችሎት የተገኙት ሁለት ጠበቆች “ክሱ አሁን ነው የደረሰን ዝርዝር ክርክር ለማቅረብ ጊዜ ያስፈልገናል” በሚል የዋስትና ክርክር ማንሳታቸውን ጠበቃዋ ሄኖክ አክሊሉ ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይር” ተናግረዋል።
ጠበቆቹ በክስ መዝገቡ ላይ ምስክሮች አለመጠቀሳቸውን በማንሳት፤ ደንበኛቸው “በዋስትና ብትወጣ ልታበላሸው እና ችግር ልትፈጥርበት የምትችለው ማስረጃ አለመኖሩን” ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም ተከሳሿ “ቋሚ አድራሻ ያላት እና በዋስትና ብትወጣ ግዴታዋን አክብራ የምትቀርብ” መሆኑን በመጥቀስ ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብቷ እንዲጠብቅላት ጠይቀዋል።
* * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2023/9267/
2 485
በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች 8.3 ሚሊዮን ሰዎች እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ
የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በተደረገባቸው የትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች 8.35 ሚሊዮን ሰዎች የእለት ደራሽ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ከሶስቱ ክልሎች ከፍተኛ የእርዳታ ጠባቂ ቁጥር ያለበት ትግራይ ክልል ሲሆን በክልሉ ውስጥ 5.2 ሚሊዮን ሰዎች የእለት ደራሽ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡
የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ይህንን ያስታወቀው ዛሬ አርብ ታህሳስ 21፣ 2015 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው፡፡ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም እንዳስታወቁት ከፍተኛ የእርዳታ ፈላጊ ቁጥር ባለበት ትግራይ ክልል በሁሉም ዞኖች የእለት ደራሽ እርዳታ ጠባቂዎች አሉ፡፡ በክልሉ ለአንድ ወር የሚያስፈልገው የምግብ እርዳታ መጠን 88,179 ሜትሪክ ቶን መሆኑን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል፡፡
በአማራ ክልል እርዳታ በሚፈልጉት ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ ሰሜን ጎንደር እና ሰሜን ወሎ ዞኖች 2.4 ሚሊዮን ሰዎች የዕለት ደራሽ እርዳታ ጠባቂ ናቸው ተብሏል፡፡ በተመሳሳይ በሶስት ዞኖች ውስጥ ያሉ ነዋሪዎች እርዳታ ፈላጊ በሆኑበት በአፋር ክልል የተረጂዎች ቁጥር ከ715 ሺህ በላይ እንደሆነ ኮሚሽነሩ በመግለጫው ላይ ተናግረዋል፡፡ (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
* * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/9224/
2 485
የፎቶ ዘገባ፡- መቐለ ከተማ ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ታህሳስ 19 የስልክ አገልግሎት ማግኘቷ ይታወሳል፡፡ ትላንት ሐሙስ ደግሞ ኢንተርኔት በከፊል በተወሰኑ ቦታዎች ላይ መስራት መጀመሩ ይታወሳል፡፡ እሱን ተከትሎ በመቐለ ከተማ ሮማናት አደባባይይ አካባቢ የሚገኙ የሞባይል ስልክ መሸጫ ሱቆች ዛሬ ተጨናንቀው ታይተዋል፡፡ በርካታ ሰዎች አዳዲስ ሞባይል ስልክ ሲገዙ እና የተበላሹትን ሲያስጠግኑ ነበር፡፡
በተጨማሪም ከዚህ በፊት በከተማይቱ ሳይሸጡ ተቀምጠው የነበሩ ባለ10፣ ባለ15 እና ባለ100 ብር የሞባይል ካርዶች መንገድ ላይ ሲሸጡ ተስተውለዋል፡፡ ነገር ግን ካርዶቹ ላይ ያለው ስውር ቁጥር ተፍቆ ሲሞላ “አይሰራም” የሚል ቅሬታ ከተጠቃሚዎች ሲደመጥ ነበር፡፡ (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@Ethiopianinsider1
2 485
በትግራይ ክልል መዲና መቐለ ከተማ ከዛሬ ከሐሙስ ታህሳስ 20 ከሰዓት ጀምሮ በአንዳንድ አከባቢዎች የኢንተርኔት አገልግሎት መስራት መጀመሩን “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” በስፍራው ከሚገኙ የዐይን እማኞች አረጋግጣለች፡፡ (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@Ethiopianinsider1
2 485
የሲሚንቶ የፋብሪካ በር አማካይ የመሸጫ ዋጋ ከ590 ብር ወደ 758 ብር ጨመረ
ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ከመስከረም መጀመሪያ አንስቶ ተግባራዊ ሲደረግ የነበረው የሲሚንቶ የፋብሪካ መሸጫ ዋጋ ላይ ማሻሻያ አድርጓል፡፡ ከትላንትና ጀምሮ ለፋብሪካዎች ተሰራጭቷል የተባለው የዋጋ ማሻሻያ ከ506 ብር እስከ 683 ብር የነበረውን የአንድ ኩንታል ሲሚንቶ የፋብሪካ በር ዋጋ ከ750 ብር እስከ 795 ብር አድርሷል፡፡
በአዲሱ ዋጋ ላይ ከፍተኛው የፋብሪካ መሸጫ ዋጋ የተወሰነለት ዳንጎቴ ሲሚንቶ ከነበረበት 549 ብር ወደ 795 ብር እንዲያድግ ተደርጓል፡፡ ደርባ ሲሚንቶ 761 ብር፣ ሙገር ሲሚንቶ 755 ብር፣ ናሽናል ሲሚንቶ ደግሞ 765 ብር የፋብሪካ መሸጫ ዋጋ ተቆርጦላቸዋል፡፡ ፓዮኒር፣ ኢትዮ እና ኢስት ሲሚንቶዎች በአንጻሩ 753 ብር ሆነዋል፡፡
መስከረም ላይ የዋጋ ትመና ያልተደረገት ኢንቺኒ ሲሚንቶ 750 ብር ተወስኖለታል፡፡ ሀበሻ ሲሚንቶ 754 ብር፣ ኩዩ ሲሚንቶ 752 ብር እንዲሁም ካፒታል ሲሚንቶ 751 ብር የፋብሪካ ዋጋቸው እንዲሆን ተደርጓል፡፡ በአራት ወራት ውስጥ በድጋሚ የተወሰነው የፋብሪካ በር መሸጫ ዋጋ ቀድሞ በአማካይ 590 ብር ሲሸጥ የነበረውን ሲሚንቶ በአማካይ 758 ብር እንዲደርስ አድርጎታል፡፡
አስራ እንዱ የሲሚንቶ አምራች ፋብሪካዎች በአንጻሩ ይወሰንልን ብለው አቅርበው የነበረው ዋጋ በአማካይ 1014 ብር እንደነበር ንግድ ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ እንደ ሚኒስቴሩ መረጃ ከፍተኛ ዋጋ እንዲወሰንለት ያቀረበው ፓዮኒር ሲሚንቶ ነው፡፡ ፋብሪካው አንድ ኩንታል ሲሚንቶ የፋብሪካ በር መሸጫ ዋጋ 1783 ብር እንዲሆንለት ጠይቆ ነበር፡፡ ፓዮኒር አሁን የተወሰነለት ዋጋ ከጠየቀው በ1030 ብር ያነሰ ነው፡፡
ኢንቺኒ ሲሚንቶ ደግሞ 1298 ብር የፋብሪካ በር መሸጫ ዋጋ አስገብቶ 750 ብር እንዲሸጥ ተወስኖለታል፡፡ ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ዛሬ ይፋ ያደረገው ይህ የፋብሪካ በር መሸጫ ዋጋ፤ ለስድስት ወራት የሚቆይ እንደሆነ አስታውቋል፡፡ (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
2 485
በኦሮሚያ ክልል በአምስት ወራት ውስጥ ብቻ “በብዙ መቶዎች የሚገመቱ” ሰዎች በታጣቂዎች እንደተገደሉ ኢሰመኮ አስታወቀ
በኦሮሚያ ክልል ውስጥ በሚገኙ አስር ዞኖች ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች፤ ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ “በብዙ መቶዎች የሚገመቱ” ሰዎችን “በአሰቃቂ ሁኔታ” መግደላቸውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታወቀ። በእነዚህ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች “አይነት እና ቁጥር” ጨምሯል ያለው ኮሚሽኑ፤ የታጣቂዎቹ ጉዳይም “የመወሳሰብ አዝማሚያ” ማሳየቱን ገልጿል።
ኢሰመኮ ይህንን ያለው፤ በኦሮሚያ ክልል የሚፈጸሙ ጥቃቶችን እና ተያይዞ የተከተሉ “መጠነ ሰፊ ሰብአዊ ቀውሶችን” አስመልክቶ ዛሬ ረቡዕ ህዳር 28፤ 2015 ባወጣው መግለጫ ነው። በኦሮሚያ ክልል ጥቃት የሚፈጸምባቸው አካባቢዎች ስፋት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን የጠቆመው ኮሚሽኑ፤ ባለፉት አምስት ወራት ብቻ በ54 አካባቢዎች ግጭቶች መመዝገቡን አትቷል።
በመንግስታዊው የሰብዓዊ መብት ተቋም ዝርዝር መሰረት፤ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ አራት የወለጋ እና ሶስት የሸዋ ዞኖች ግጭቶች ተከስተዋል። በአርሲ፣ በኢሉ አባቦር እና በቡኖ በደሌ ዞኖች የሚገኙ አካባቢዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ ግጭቶች እንደነበሩ ኮሚሽኑ ገልጿል።
በተጠቀሱት አካባቢዎች ውስጥ የሚከሰቱት አብዛኛዎቹ ጥቃቶች “ሆን ተብሎ ሲቪል ሰዎችን ኢላማ ያደረጉ” መሆናቸውን ኢሰመኮ ዛሬ ባወጣው ባለ አምስት ገጽ መግለጫ ላይ አመልክቷል። አብዛኞቹ ጥቃቶች “ብሔርን መሰረት ያደረጉ ናቸው” ያለው ኮሚሽኑ፤ “በተወሰኑ ሁኔታዎች የፖለቲካ አመለካከትን” መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች እንደሚፈጸሙም አክሏል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@ethiopianinsider1
2 485
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ፓርላማውም ጭምር አጀንዳ ሊቀርጽለት እንደማይችል አሳሰበ
ከአንድ ዓመት ገደማ በፊት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአዋጅ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን፤ ፓርላማውም ቢሆን አጀንዳዎች እንዲቀርጽለት እንደማይፈልግ አስታወቀ። አጀንዳ የማሰባሰብ እና የመቅረጽ ኃላፊነት በአዋጅ የተሰጠው ለኮሚሽኑ ብቻ መሆኑንም ገልጿል።
በአስራ አንድ ኮሚሽነሮች የሚመራው ኮሚሽን ይህን ያስታወቀው፤ የስራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ዛሬ ረቡዕ ህዳር 21፤ 2015 ባቀረበበት ወቅት ነው። በሱሉልታ ከተማ በሚገኘው የአፍሪካ አመራር ልህቀት ማዕከል በተካሄደው በዛሬው ስብስባ፤ ኮሚሽኑ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት በዋና ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን አርዓያ አማካኝነት ቀርበዋል።
ከዋና ኮሚሽነሩ ሪፖርት በኋላ፤ የፓርላማ አባላቱ ያሏቸውን ጥያቄዎች እና አስተያየቶቻቸውን ሰንዝረዋል። በፓርላማ አባላቱ መካከል ከቀረቡ አስተያየቶች መካከል፤ የሀገራዊ ምክክሩ አጀንዳዎች ምን መምሰል እንዳለባቸው ጥቆማ ያቀረቡባቸው ይገኙበታል።
የፓርላማ አባላቱ ይህን መሰል አስተያየት፤ በዛሬው ስብስባ በተገኙ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች ተቃውሞ ገጥሞታል። ከኮሚሽነሮቹ አንዱ የሆኑት አቶ መላኩ ወልደማሪያም “ዛሬ የተገናኘነው ሪፖርት ለማቅረብ እንጂ አጀንዳ ለመሰብሰብ አይደለም” ብለዋል። “አጀንዳ set እንዲደረግልን አንፈልግም። እሱን በጣም በጥብቅ ነው የምንቃወመው” ሲሉ ጠንከር ባሉ ቃላት ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
* * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8791/
@Ethiopianinsider1
2 485
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከዚህ ቀደም በፓርላማ ቀርበው ስለዳኞች እና ፍትህ አካላት “ሌብነት” ያደረጉትን ንግግር አስታውሰው፤ ጉዳዩን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎችን ለፓርላማ አባላቱ አጋርተዋል። አብይ ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ በፓርላማ ባደረጉት ንግግር “አንደኛ ደረጃ ሌቦች፤ ዳኞች ናቸው” ማለታቸው በዳኞች ዘንድ ቅሬታን ፈጥሮ ነበር። አብይ በዛሬው ንግግራቸውም ዳኞችን በተመለከተ ተመሳሳይ ገለጻ ተጠቅመዋል።
“ሌብነት አለ ሲባል ዝም ብሎ ሳይሆን፤ በቴሌግራም ‘ግሩፕ’ ከፍተው ጉቦ የሚቀባበሉ ዳኞች አሉ” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወንጅለዋል። አርበኛ ለመሆን ደግሞ ‘እንትናን ፈታሁ፤ እንትናን አሰርኩ’ እያሉ የሚቀላቅሏቸው ጨዋታዎች አሉ። እንደዚህ አይነት ቀልድ ጥሩ አይደለም” ሲሉ አብይ በ”ሌብነት” ተዘፍቀዋል ላሏቸው ዳኞች ጠንከር ያለ መልዕክት አስተላልፈዋል። የፍትህ ስርዓቱ መሻሻል ካለበት “ጊዜው አሁን ነው” ሲሉም ተናግረዋል።
* * ዝርዝር ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8627/
@Ethiopianinsider1
2 485
የሙስና ወንጀሎችን የተመለከቱ ጥቆማዎች የሚቀርቡባቸው ቢሮዎች እና ስልክ ቁጥሮች መዘጋጀታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከ “ሌብነት” ጋር የተያያዙ ጥቆማዎች የሚቀርቡባቸው ቢሮዎች እና የስልክ ቁጥሮች በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሌብነትን በተመለከተ ሀገራዊ ኮሚቴ ተቋቁሞ ጥናት እየተደረገ መሆኑን ዛሬ ማክሰኞ ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው የፓርላማ ውሏቸው “ሌብነት በጣም አታካች ነገር ሆኗል። በተለይ የገጠመንን ሀገራዊ ፈተና፣ የገጠመንን ሀገራዊ ችግር እንደ ዕድል የወሰዱ ሰዎች፤ ቀይ መስመር ያልነውን ሌብነት ቀይ ምንጣፍ አድርገውታል” ሲሉ ተደምጠዋል።
በጉዳዩ ላይ በካቢኔ እና በስራ አስፈጻሚ ደረጃ ውይይት እንደተደረገበት ያነሱት አብይ፤ “ሀገራዊ ኮሚቴ አቋቁመን ጥናት እያጠናን እንገኛለን። በሁለት ሶስት ቀን ውስጥ ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን” ብለዋል። “ለዚህ ዓላማ ብቻ የተዘጋጁ ቢሮዎች አሉ፤ ስልኮች አሉ። መረጃ፣ ሰነድ በማቀበል፤ ቢያንስ ባናጠፋ እንኳን ሌብነትን አንገት እንድናስደፋ በጋራ እንስራ” ሲሉ ህዝቡ ጥቆማዎችን እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ‘ፋይል በእግሩ አይሄድም’ የሚል ቋንቋ፤ common ቋንቋ ነው። ፋይል በእጅ ብቻ ነው የሚሄደው፤ በእግሩ አይሄድም። ሌብነት ልምምዱ ብቻ ሳይሆን እንደ መብት መወሰዱ፤ አደገኛ ነገር ነው” ሲሉ የሁኔታውን አሳሳቢነት ለፓርላማ አባላት አስረድተዋል። “ይህን ነገር መፍትሄ ካላበጀን፤ ‘እድገታችንን ይጎዳል’ የሚለውን ማሰብ ጠቃሚ ነው” ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
* * ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8627/
@Ethiopianinsider1
2 485
በዛሬው የፓርላማ ውሎ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ከህወሓት ጋር ያደረገውን ድርድር በተመለከተ የተወካዮች ምክር ቤት አባላት በርከት ያሉ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለጥያቄው በሰጡት ምላሽ፤ “የማያልቅ ጦርነት ውሃ በወንፊት ነው። ዝም ብሎ እየተዋጉ መኖር አይቻልም” ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የሰላም መጥፎ የጦርነት ጥሩ የለውም። ሰላም ሁሌም ጥሩ ነው። ጦርነት፤ ሁሌም እያሸነፍክም ቢሆን መጥፎ ነው። ምክንያቱም ሰው ትገድላለህ፤ ዶላር ትተኩሳለህ። ዶላር እየተፋህ እና ሰው እየገደልክ የሚገኝ ጥቅም እና ጥሩ ነገር የለም” ሲሉም ተደምጠዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@Ethiopianinsider1
2 485
በአዲስ አበባ በ500 ቢሊዮን ብር “ሳተላይት ሲቲ” እንደሚገነባ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአዲስ አበባ ከተማ ከ400 እስከ 500 ቢሊዮን ብር በሆነ ወጪ “ሳተላይት ሲቲ” እንደሚገነባ ተናገሩ። “ጫካ ሃውስ” የሚል ስያሜ ያለው ይህ ፕሮጀክት፤ ቢያንስ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ገቢ ያስገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ለተወካዮች ምክር ቤት አባላት ዛሬ ማክሰኞ ህዳር 6፤ 2015 በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በሰጡት ማብራሪያ ነው። አብይ የ“ጫካ ሃውስ” ፕሮጀክት ጉዳይን ያነሱት፤ ከሰሞኑ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ በ49 ቢሊዮን ብር ቤተ መንግስት እየገነቡ ነው” በሚል የተሰራጩ ዘገባዎችን በመጥቀስ ነው።
“ልንገነባ ያሰብንው ‘የጫካ ሃውስ’ ይባላል። ልንገነባ ያሰብንው ለኢትዮጵያ፣ ለአፍሪካ ኩራት የሚሆን ‘ሳተላይት ሲቲ’ ነው። ልንገነባ ያሰብንው የኢትዮጵያን ቤት ነው” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)
@Ethiopianinsider1
2 485
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ስለ ወልቃይት ምን አሉ?
🔴 “ወልቃይትን በሚመለከት የሚነገሩ ሽረባዎች፣ ሴራዎች፣ conspiracies ብዙ እሰማለሁ። የኢትዮጵያ መንግስት በእነዚህ ሽረባዎች ውስጥ እጁ የለበትም። የወልቃይት ህዝብ እንዲገነዘብ የምንፈልገው፤ የሚወራው፣ የሚናፈሰው አሉባልታ ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት እጁ የለበትም።”
🔴 “እኛ ደቡብ አፍሪካ የሄድንው ወልቃይት ወደ አማራ ይሁን ወደ ትግራይ ይሁን የሚለውን ለመወሰን አይደለም። የፕሪቶሪያው ‘ሰሚትም’ ይኸን ለመወሰን ስልጣን የለውም። ምን አገባው እና ነው የኢትዮጵያን መሬት እዚያ ሂድ እዚህ ሂድ የሚለው? እኛ እዚያ የሄድንው እንዴት ሰላም አምጥተን በንግግር ችግሮቻችንን እንፍታ ለማለት ነው። ለምን ወልቃይት ተስቦ እዚያ ውስጥ እንደሚገባ አላውቅም።”
🔴 “ወልቃይት ብቻ አይደለም፤ ሰሜን ሸዋ ላይ ኦሮሚያ እና አማራ ጥያቄ አላቸው። እሱም ደቡብ አፍሪካ ይሂድ? ሲዳማ እና ወላይታ፤ ብላቴ ላይ ጥያቄ አላቸው። እሱም ደቡብ አፍሪካ ይሂድ? ቦታው አይደለም። የተስማማነው በኢትዮጵያ ህግ እና ስርዓት ይፈጸም ነው።”
🔴 “ከህገ መንግስት በፊት ነው የተወሰደው፤ በጉልበት ነው የተወሰደው” ላሉት፤ የእኔ ፍላጎት ያ ስህተት እንዳይደገም ነው። ዛሬ እኔ በጉልበት፤ ነገ ታገሰ በጉልበት ከሆነ ዘላቂ ሰላም አያመጣም። ወልቃይት ብንፈልግም ባንፈልግም የተወላገደ አማርኛ፣ የተወላገደ ትግርኛ የሚናገር፤ የሁለቱ ህዝቦች ድልድይ የሆነ ህዝብ ነው። ሁለቱንም ቋንቋ የሚናገር የተጋባ የተዋለደ ህዝብ ነው። ‘ወልቃይቴነቱን ነው አትንኩብኝ’ ያለው እንጂ ከእንግዲህ በኋላ ትግራይ ከሚባል ጋራ አልገናኝም፤ አልነጋገርም አላለም። ቢልም አይችልም።”
🔴 “ይህን በህግ እና በስርዓት ብንፈጽም ለወልቃይት ይጠቅማል። ለአማራ ይጠቅማል። ለትግራይ ይጠቅማል። የሚጎዳው ነገር የለም። በህግ እና ስርዓት እንፈጽም የሚለውን ነገር ከብዙ ተንኮል ጋር ማያያዝም አስፈላጊ አይደለም። እዚያ አካባቢ ጥያቄ ረዘም ላለ ጊዜ ነበረ። ከዚህ ቀደም ኮሚሽን ያቋቋምነው ለዚያ ብለን ነው። አሁንም ያኔም የነበረን አቋም በህግ አግባብ በምክክር በውይይት ይፈታ የሚል ነው።”
🔴 “ከአማራ ወገን ላለፉት 30 ዓመታት ብዙ ወልቃይቴዎች ሲፈናቀሉ፤ ሲሰደዱ ኖረዋል። እነሱ በሌሉበት ህዝበ ውሳኔ ቢባል፤ የተመናመነ ህዝብ ነው እና እንጎዳለን። በትግራይ በኩል አሁን በተፈጠረው ግጭት ብዙ ሰው ወጥቷል። ስለወጣ አሁን ባለው ቢወሰድ አማራ ክልል አድቫንቴንጅ ይወስዳል የሚሉ ስሞታዎች ይሰማሉ። ወልቃይቴ፤ ወልቃይቴ ነው፤ ይታወቃል። ከአድዋም የሄደ፤ ከደብረ ማርቆስም የሄደ ሰው ሊኖር ይችላል። ግን ወልቃይቴ ይታወቃል። አትላንታም ይኑር፣ አውስትራሊያም ይኑር፣ ጅማም ይኑር፤ ስለዚያ ቦታ ሀሳብ እንዲሰጥ ዕድል ካልተሰጠው በስተቀረ ዘላቂ ሰላም አያመጣም።”
🔴 “ጉዳዩ ወደዚያ ስለሄደ፣ ወደዚህ ስለመጣ ሳይሆን፤ ያ ህዝብ የራሱን ዕጣ ፈንታ እንዲወስን፤ ዲሞክራሲያዊ ዕድል እንዲያገኝ ማድረግ ከቻልን ብቻ ነው መፍትሔ የሚመጣው። እነዚያን ችግሮች በሚቀርፍ መንገድ እንደሚሰራ ተስፋ አደርጋለሁ። ጊዜ የወሰድነው፤ ጊዜ የጠበቅነው ለዚያ ነው።“
🔴 “ከህገ መንግስት በፊት ህወሓት በግድ ስለወሰደ አሁን እኛ ደግሞ በግድ ወስደን፤ እዚያ ዘመኑን በሙሉ ወታደር ልናቆም አንችልም። በስምምነት ካልሆነ በወታደር ነው የሚሆነው። በወታደር ከሆነ ዘላቂ አይሆንም። ጊዜ ይፈታዋል። አሁን ያለን ሰዎች ስናረጅ፣ ስንደክም፤ ልክ አሁን የተፈጠረው ይፈጠራል።“
[በ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የተጠናቀረ። ይህ ዘገባ ተጨማሪ መረጃዎች ታክለውበታል]
* * ለተጨማሪ፦ https://ethiopiainsider.com/2022/8639/
