933
Suscriptores
+124 horas
+27 días
+430 días
Archivo de publicaciones
933
🩸...... በእነዚህ ታወቂ !!
👇👇
🔘 አንደበትሽን በጥበብ በመክፈት አስተውለሽም በመናገር ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 ስርዓት ባለው አለባበስ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 ለተቸገሩት ለሚለምንሽም #በድብቅ መልካምን በማድረግ ካለሽ ላይም በመለገስ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 በጨዋነትሽ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 በቁጥብነት በእርጋታነት ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 ራስን በመግዛትሽ ያለኝ ይበቃኛል በማለትሽ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 በትህትና ዝቅ በማለትሽ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 ከአለም ጋር ባለመተባበርሽ ክፉውን ሁሉ በመቃወምሽ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 የመፈጠርሽ አላማ ገብቶሽ ደግሞም ሴትነት ገብቶሽ እንደ እግዚአብሔር ቃል በመመላለስ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 በይቅርታና ተሸንፎ በማሸነፍ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 በቅድስናሽ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
🔘 በፊሪያ እግዚአብሔር በመመላለስሽ ሰዎች ይወቁሽ 🙋♀
⚠️ እሷ ይህ ነው ባህሪዋ 👆 በመባል መታወቅ መልካም ነው የእግዚአብሔርም ትልቁ #ደስታ ነው። ልክ እንደዘመኑ ራሳቸውን እንደጣሉ🤦♀ ለገንዘብ ለዝና ዋጋቸውን ያወረዱ እንደፈለጉ መልበስ፣ መናገር፣ መዝናናት መኖርን ምርጫቸው ባደረጉ ሴቶች #አትቅኚ❌ በእነዚህ ነገር መታወቅ ነገው #ሞት ስለሆነ #አጭር ጊዜ አንደቀረሽ አውቀሽ ለእግዚአብሔር #ደስታ ኑሪ‼️
✒️ ደካማው ቦና 🐅
@onlyforjesus1
Share 👉 @lebamsetoch
933
♦️ የውዶች ሁሉ ውድ ነሽ… 😲
👇👇
🔺 የወርቁ፣ የነሃሱና ብሩ አልፎም የከበሩት መዓድናት💰 በሚመዘኑበት ሚዛን ላይ የሌለሽ ከእነርሱ ጋርም የማትስተካከዪ "የውዶች ሁሉ ውድ ነሽ"👍
🔺 ቅድስናን የተጫመትሽ፣ ክርስቶስን በልብሽ ያነገስሽ🙋 በሰው ዘንድ ተመን የማይወጣልሽ እንቁና የተለየሽ ውብ ልባም ሴት ነሽ❤️
🔺 እንደ ዛፍ ቅጠል ቶሎ የልብሽ መልክ የማይጠወልግ ውብና ውድ ነሽ👍
🔺 አስተዋይ የሆንሽ ክርስቶስ የልቤ የሚልሽ አንቺዋ ልባም ሆይ ውድና ውድ ነሽ 😲
🔹 ምነኛ ውድ ነሽ 😲
👇👇
አይንን ከሚስበው
ከብርና ከወርቅ
ብልጭልጭ ከሆነው
ከአልማዙ ይልቅ
እንቁ ይሁን ገንዘቡ
የማይጠጋጋሽ
አንቺ ልባም ሴት ሆይ
ምነኛ ውድ ነሽ 😲
✒️ ቦና
🔺" ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል። "
(መጽሐፈ ምሳሌ 31:10)
ለአስተያየት @onlyforjesus1
@lebamsetoch
933
🩸ዋጋሽን ታውቂ ኖሯል!? 🙋♀
👇👇
#ማንነታቸውን በገንዘብ በዕንቁ የለወጡ ራሳቸውንም #ለድርድር በድፍረት በአደባባይ ያስቀመጡ ከገንዘብ #በታች አድርገው ራሳቸውን የቆጠሩ በዚህ ዘመን ጥቂት አይደሉም 🤔
#አቋምና መልካቸውን በመደገፍ ተሽሎ ለመጣው #እንደጨረታ ራሳቸውን ለጊዜው ቢሆንም የሚሰጡም ዋጋቸውን ውድነታቸውን #ያላወቁ በዚህ ዘመን ውስን አይደሉም 🤔
🔘አስተውይ👇
"ከገንዘብ በላይ ዋጋ እንዳለው ያላወቀ ሰው ገንዘብ ይገዛዋል!!" 🐅
"ማንነታችሁን ባላወቃችሁት ልክ ለማይጠቅማችሁ ነገር ተገዢ ልትሆኑ ትገደዳላችሁ!!" 🐅
🔘 ዋጋ አለሽ ከገንዘብና ዕንቁ የሚበልጥ ማንነታቸውን በረሱ በኃጢአት መንገድ ላይ ካሉቱ ሚዛን ላይ ራስሽን አታስቀምጪ 👉 "#ማንነት በገንዘብ #ለውጥ ውስጥ #ሞት ነውና ያለው"⚠️
👉#ምክንያታቸው እየደረደሩ ማንነትን በገንዘብ ለውጠው #የተለወጡ መስለው ልብሽን ሊሰርቁት ቢፈልጉ.. 👉#የብሉን ንጉስ ይዘው ከአንቺ በላይ ኑሮ የሚኖሩ በሚስሉ... 👉ቢጠጡ ቢለብሱ በቅንጦት ቢኖሩ... "ሕይወት አጭር ናት" ተዝናንቶ #ማለፍ ነው ቢሉ ይህ ልብሽን #አያስደንግጠው ማንነትን መርሳት ያመጣው #የውድቀት አስተሳሰብ ነውና!!
"አዎን የስጋውን መሻት ለሚፈፅም ሕይወት አጭር ናት እግዚአብሔር መፍራት ግን እስመጨረሻው ቀጣይ ናት!!"🐅
አንቺ ግን 👉 1⃣ በዚህ ክፉ ዘመን ፅኚ በውድ ዋጋ ሕይወትሽም ለክርስቶስ እንደተሸጠ እወቂ 2⃣ ከምክንያቶችሽ በላይ እግዚአብሔርን ተመልከቺ በችግር ውስጥም ሆነሽ 3⃣ ክፉውን ተቃወሚ እግዚያብሔር ፍሪ በመንገዱም ተመላለሺ በሰማይም በምድርም በረከት ይሆንልሻልና🙏
" ውድ ነሽ ከሚያልፈው የምታልፊ!!" 🐅
✒️ ደካማው ቦና 🐅
Share👉 @lebamsetoch
933
🩸"ውሳኔ ማለት…"🤔
👇👇
🔹#ውሳኔ ማለት #ነገን አሻቅበን የምናይበት ራሳችንንም🤔 የምንመዝንበት ለሕይወታችን አንዱ #ዋነኛ ነገር ሲሆን በአንድ ቃል ስገልፀው👉 "ውሳኔ ማለት ነገ ማለት ነው!!"
🔹ከዛሬ ወደ መልካም ነገ መሸጋጋሪያ መሰላል አልያም ድልድይ ማነው ብትሉኝ ውሳኔ ነው እላችዋለው🤔
#ቆራጥና #በጎ የሆውን ነገር #ዛሬ ለሕይወቱ የወሰነ ያ ሰው ነገው ፍሬያማ ነው🍇 አንድን ነገር ስትወስኚ ሁል ጊዜም #ሁለቴ አስቢ🙋♀ አንዳንድ ጊዜ መልካም ውሳኔ #የመሰሉ ውሳኔዎች ናቸውና ከመስመር የሚያስወጡሽ ስትወስኚ #ንቁና ብልህ ሁኚ። በብዙ የሰዎች #ጩሀት ብቻ ሳይሆን ከዛም እልፍ ብለሽ ነገርሽን #ተመልክተሽ ወስኚ ደግሞ የውሳኔ ተቃራኒ #ይሉኝታን አስወግጂ ፅኑ ሁኚ💪
የሰው #መልካም ምክር ስሚ🙋♀ #በተሳሳተ #የአስተሳሰብና የሕይወት መንገድ ላይ ቆመሽ ላንቺው ብሎ ለሚያወራሽ ሰው #ልብ ስጪ ተመለሰሺም ቶሎ ወስነሽም ከዛ ነገር ፈቀቅ በይ🙏 "ከመልካምም መልካም #ይመረጣልና አስተውይም!!" ለመልካም ውሳኔ ሁሌ ንቁ ፈጣንም ሁኚ ያ ጉዳይ ስር ከሰደደ የሚገድልሽ ነውና ስትዘገይም እንዳዛው🤷♂
ልባም ሴት የውሳኔ ሴት ናት። ታዲያ ነገሽን ለመስራት ዛሬ የነገ ግብዓት ከሆኑት የሕይወት መርሆች ማከከል 👉 "ውሳኔን" ተከተይ🙏 ልብ በይ ቆም ብለሽም ሁሌም ያለሽበትን መንገድ ተመልከቺ።
"ውሳኔ ማለት ነገ ማለት ነው"!🐆
ደካማው ቦና 🐆
ለአስተያየት @onlyforjesus1
Share @lebamsetoch
933
🩸ላይቀር ሳይመሽ!!
👇👇
👉 የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ አንድ #ቀን ዛሬ የተመካሽበት ውበት መልክ #ይረግፋል 🤦♀
👉 #የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ዛሬ የኮራሽበት ገላ አቋም/ ቁመና አይሰነብትም አንድ ቀን #ይከዳሻል 🤦♀
👉 ዛሬ #እንዳሻሽ ልትሆኚ ያደረገሽ ወጣትነት #ጉብዝና ቢሆን እንኳ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ምኩዝ #ከመመርኮዝ አታመልጪም 🤦♀
"ከብርቱ የወጣትነት ጊዜ ባሻገር ነገ እርጅና አለ!!" 🐅
"ቆሞ የሚጠብቅ ወጣትነት የለም!!"🐅
🔘 ዛሬ እንደ #ቀልድ እድሜና ጊዜ የፈጀ ነገ #በእርጅና ወራት #ከፀፀት ውጪ መልካም #ትዝታ የለውም። በጉብዝና ጊዜ #ያልተደረገ በከዘራው ጊዜ አይመጣም።
"በከዘራ ሩጫ የለም!!" 🐅
🔘 በጉብዝናው ወራት ለእግዚአብሔር #ያልኖረ #ያልሆነም ጉልበት ሲደክምም ምንም እንኳ መኖር ቢችልም ምን ዋጋ አለው #ያን ጊዜ ማድረግ በሚችለው ልክ አያደርግም🤷♂
🔘 ነገ ኖራለው አይባል ነገር🤔 ምን ይታወቀል ለነገ ያደረ ሊበላሽ እንደሚችል‼️ በጊዜው መጠቀም ያ ሁሌም የተሻለው መልካም ሃሳብ።
⚠️ ውበት/ መልክ እንደ ጠዋት ጤዛ ሰንባች ካልሆነ!? የተመኩበት አቋም ጉልበት ነገ ከዘራ ሊደግፈው ካልቀረ!? ከፀፀት ለመትረፍ ዛሬ #ሳይመሽ እግዚአብሔርን ወደ ማሰብ መመለሱ ሳይሻል አይቀርም ትላላችሁ🤔⁉️
"ሩጫ ቀን ሳለ ነው ከመሸ ማን ያውቃል!!"
✒️ ደካማው ቦና 🐅
ለአስተያየት👉 @onlyforjesus1
Share👉 @lebamsetoch
933
🩸ዲና!! 🤦♀
👇👇
በመፅሐፍ ቅዱስ በኦሪት ዘፍጥረት ምዕ 34 ላይ የያዕቆብ ሴት ልጅ ስለሆነት ዲና አሳዛኝ ሁነት ይነግረናል። ተገዳ #ስለመደፈሯ ከዚያም የተነሳ ወንድሞቿ ስላደረጉት የተንኮል ተግባር አልፎም የተፈጠሩ ነገሮችን ይነግረናል። ታዲያ እኔም ከዲና ሕይወት አንድ የተማርኩትንና ከቀረልኝ ነገር ይህን ልላችሁ ወደድኩ👇
🔘 "አንድ ቀን የዚያን አገር ሴቶች #ለማየት ወጣች" ይህ የነገር ሁሉ ጅማሬ ነበር👇
#ወጥቶ ከማየት 👀 በፊት👉 #በልብ #በአእምሮ #በጆሮ የሚገቡ እነዚያ ነገሮች ለመልካምም ይሁን ለክፉ ድርጊት እጅግ ወሳኝ ቦታ አላቸው። ዲና በምን #ምክንያት እነዚያን ሴቶች ለማየት እንደወጣች ባናውቅም ግን🤔 1⃣ የቤቱ ብቸኛ ሴት ልጅ እንደመሆኗ ምናልባት ሴት ጓደኞች ለማፍራት⁉️ 2⃣ ምናልባት የዚያን ሃገር #ባህል #አለባበስ #ውሎ #ድባቡ #ማሕበራዊ ኑሮን ለማየት⁉️ምክንያቷ ይህ ይሁን ምንም ሕይወቷ ላይ ትልቅ #ዋጋ እንዳስከፈላት እንመለከታለን።ለራስ ብቻ ሳይሆን ለቤተሰብ ለአገር የሚተርፍ እዳ። 🤦♀
🔘 ልብ በሉ ምክንያታችሁ👉 #እድሜ፣ #እምነት ማጣት፣ #ብቸኝነት፣ #መገፋት፣ #የኑሮ ሁኔታ፣ #ዘና ማለት ነፃነት መፈለግ፣ #ስጋን ደስ ማሰኘት ብቻ ምንም ይሁን ምክንያታችሁ #እግዚአብሔር ካልሆነ የትኛውም ድርጊታችሁ ዋጋ ሊያስከፍላችሁ የግድ ነው። 🤦♀
1⃣ ዲና "አንድ ቀን" ነው የወጣችሁ ያቺ #አንድ ቀን ለመደፈሯ ብሎም ለተፈጠረው አሳዛኝና አሳፋሪ ተግባር መንስኤ ሆነ።👉 ጠላት #በአንድ ቀንም ዋጋ ያስከፍላል #እያባበለም ዋጋ ያስከፍላል።⚠️
2⃣ ድንገት ብድግ ብላችሁ ስሜታችሁ እንደመረራችሁ እንዳትወስኑ። ሁኔታዎችን ሁሉ ከእግዚአብሔር አንጻር ተመልከቱ። 🙏
3⃣ ሁኔታዎችን #ለመርሳትና #ለመሸሸግ አለምን ምርጫ መጠለያም አታድርጓት #በአሸዋ ላይ የተመሰረተች ናትና።
4⃣ #የተሻለ ህይወት እንዳለ አድርጎ ጠላት የሚያሳያችሁ #ሊያርዲችሁ ነው።
⚠️ ለጊዜው ነሮው #ባይጥማችሁም ግራ ቢገባችሁም ግን👉 ከእግዚአብሔር ጋር ሆኖ በችግር #ማለፍ ይሻላል።
"ወደ አለም አይመተጥም፤ ከአለም ዘንድም ተስፋ የለም!!" 🐅
✒️ ደካማው ቦና 🐅
ለአስተያየት👉 @onlyforjesus1
Share👉 @lebamsetoch
933
🩸ሴት ሆይ 🗣
👇👇
1⃣ ከአልማዝና እንቁ ሁሉ😲 ውድ አልፎም የበላይ ሆነሽ ስለምን ገንዘብና ወርቅ ያታላልሻል ስለምንስ ወርደሽ ትገኛለሽ⁉️
2⃣ በሴትነትሽ በክብርም በመፈጠርሽ ብቻ ልትኮሪና🙋 ዘና ብለሽ መኖር ሲገባሽ ስለምን👉 ራስሽን የበታች አድርጎ መቁጠር አስፈለገ 🤷♂❓
3⃣ አለባበስሽ ቅድስናሽ👍 መሆኑን ዘንግተሽ ይልቅስ ስለምንስ ሰውነትሽን/ ገላሽን አደባባይ ላይ መግለጥ ተገቢ ሆኖ ተገኘ⁉️🤔
4⃣ ብልህ፣ አዋቂ፣ ጭምት፣ ኩሩ ሴት ሆነሽ ሳለ የቀረበሽ ወንድ ሁሉ ለምን ያታልልሻል😡❓
5⃣ ከአመፃው አለም መለየትና በቅኑ መንገድም መጓዝ ሲገባሽ እንዴት🤷♂ አልባሌ ቦታ ተገኝተሽና ዋጋሽን ዝቅ ታደርጊያለሽ🤔⁉️
6⃣ ውበት እግዚአብሔርን መፍራት ሆኖ ሳለ ስለምን በመዋቢያ ምርቶች ላይ #እምነትሽን ትጥያለሽ⁉️
"ውድ ነሽና እንደ ውድ ሁኚ!!"
✒️ ደካማው ቦና 🐅
ለአስተያየት👉 @onlyforjesus1 / 0942305601
Share👉 @lebamsetoch
@lebamsetoch
933
⚠️ አጭር ምክር!!👂
🔘 በፈገግታ ተቀበይ 🙋♀
👇👇
#ሰው በእርሷ ሕይወት ላይ #ዋጋ ብሎም #ስፍራ እንዳለው #የተረዳች ያቺ ሴት እንዴት ያለች እድለኛ ትሆን‼️ ከራሷ አልፋ ለሌላው በረከት ናትና ።
በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ ብታልፍ የሰው ጉዳይ #ግድ ስለሚላት🤔 ከራሷ ነገር ወጥታ #በፈገግታ ልብን #ትመልሳለችና። ያቺ ልባም ሴት በመከራ እየተጓዘች እንኳ ፊቷን ሰው ላይ አትጥልም በፈገግታ ተቀብላ በመፍትሄ ትሸኘዋች። 🙋♀
ልብ በይ 👉 ሰው ወደ አንቺ ሲወጣ አስቀድመሽ በደስታ ፈገግ ብለሽ ተቀበይው ፊት አትንሺው ለዛ ሰው #ያቺ ፈገግታ ሕይወቱ ላይ ምን ለውጥ እንደሚያመጣ አታውቂምና‼️
በአንድ ፈገግታ #ያዘነ ሊፅናና፣ #ሸክም ያለው ቀሎት የሚሰማውን ሊያወራ ይችላል🤷♀። ለሰው ጊዜና ቦታ ይኑርሽ ለአንዲት ነፍስ ግድ ካለለሽ የግል ሩጫሽ ነገ ይጥልሻል😳።ከራስ ጊዜ ቀንሶ ዋጋም ቢሆን ከፍሎ ለሰው ጊዜ መስጠት እንዴት መልካም ነው።
በምንም ሁኔታ ውስጥ ሁኚ ሰውን በፈገግታ ተቀበይ ፊትሽን አታጨማጂው። 👉 #የበደለሽ ሰው እንኳ ቢሆን ምከሪው #ጥፋቱን ንገሪው እንጂ በዝምታ ብቻ አትለፊው ትጎጃለሽና።
⚠️ ታዲያ አስተውይ #በፈገግታ ተቀበይ ማለት #ባህሪ አትለይ ወይም #አትመርምሪ ማለት አይደለም ለሕይወትሽ የማይበጀውን #ትቆርጫለሽ። ግን ፈገግ ብለሽ ሰው አስተናግጂ ተቀበይም ፊትን አትንሺ። 🙏
ሁሉም ለራሱ እየተሯሯጠ ባለበት በዚህ ዘመን ለሰው ፈገግ ማለት ሰውን መቀበል በረከት ነው። ፈገግ ማለት መገልፈጥ አልያም ማፌዝ አይደለም🤔 ሰውን #ለመስማት #ደስታን ለማካፈል #መልካሙን መንገድ ለመጠቆም ለማጽናናት #ዝግጁ መሆን ማለት ነው። 🙏
⚠️ ይበልጥ ደግሞ ፍሬ እንድታፈሪ በእግዚአብሔር ቃል እውቀት ራስሽን ሙይ🙏
✒️ ደካማው ቦና 🐅
ለአስተያየት👉 @onlyforjesus1 / 0942305601
Share 👉 @lebamsetoch
933
🔘 "በሰው ተስፋ የማይቆርጥ ጌታ አለና ተስፋ አለሽ!!"
👉 14 እግዚአብሔር በቃሎቹ የታመነ ነው፥ በሥራውም ሁሉ ጻድቅ ነው፤ እግዚአብሔር የተፍገመገሙትን ሁሉ ይደግፋቸዋል፥ የወደቁትንም ያነሣቸዋል።
'መዝሙረ ዳዊት 145:14'
@lebamsetoch
933
🔘 "በሰው ተስፋ የማይቆርጥ ጌታ አለና ተስፋ አለሽ!!"
👉 14 እግዚአብሔር በቃሎቹ የታመነ ነው፥ በሥራውም ሁሉ ጻድቅ ነው፤ እግዚአብሔር የተፍገመገሙትን ሁሉ ይደግፋቸዋል፥ የወደቁትንም ያነሣቸዋል።
'መዝሙረ ዳዊት 145:14'
@lebamsetoch
933
8 ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።
9 በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።
'1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1:8-9'
@lebamsetoch
933
🔘 አይኖችሽ ወዳዩት ሁሉ ልብሽ ብሎም እግሮችሽ እንዳይሮጡ አጥብቆ የሚጠብቅሽ 👇
👉 34 እንዳስተውል አድርገኝ፥ ሕግህንም እፈልጋለሁ፤ በፍጹም ልቤም እጠብቀዋለሁ።
'መዝሙረ ዳዊት 119'
🔘 ከድካም ከውድቀት ማግስት ብርታትና መነሳት እንዳለ የሚጠቁምሽ 👇
👉14 እግዚአብሔር በቃሎቹ የታመነ ነው፥ በሥራውም ሁሉ ጻድቅ ነው፤ እግዚአብሔር የተፍገመገሙትን ሁሉ ይደግፋቸዋል፥ የወደቁትንም ያነሣቸዋል።
'መዝሙረ ዳዊት 145:'
🔘 እንዴት እንደ ልባም ሴት ሆነሽ መመላለስ እንዳለብሽ ሹክ የሚልሽ 👇
👉መፅሐፈ ምሳሌ ምዕ 31: 10-31
🔘 ምን ያክል ውድ እንደሆንሽ የሚነግርሽ 👇
👉10 ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል። 'መጽሐፈ ምሳሌ 31'
🔘 የቷ ሴት እንደምትመሰገን ምን ስራዏቿም መልካምን እንደሚከፍላት አልፎም ውበት ማለት ምን ማለት እንደሆነ የሚያሳስብሽ 👇
👉30 ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች። 'መጽሐፈ ምሳሌ 31'
🔘 በምን መንገድ አንደበትሽን መክፈት እንዳለብሽ የሚጠቁምሽ 👇
👉13 አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ።
'መዝሙረ ዳዊት 34:'
🔘 ራስን መግዛት ሰውነትሽም የራስሽ እንዳልሆነ በስጋሽም የፈጠረሽን ጌታ ልታከብሪ እንደሚገባ የሚያስተምርሽ 👇
👉19-20 ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
'1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:19-20'
🔘 አለባበስሽ ቅድስና እንደሆነ የሚያስገነዝብሽ 👇
👉ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ።
'1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:4'
🔘 ሰነፍ ሴት እንዳትሆኚ የሚመክርሽ 👇
👉1 ብልሃተኛ ሴት ቤትዋን ትሠራለች፤ ሰነፍ ሴት ግን በእጅዋ ታፈርሰዋለች። 'መጽሐፈ ምሳሌ 14:'
🔘 ባልሽ የቤቱ ራስ እንደሆነ ልታከብሪው ልትታዘዢው እንደሚጠባ በረከትም ፍሬም በዚያ መንገድ እንደሆነ ይሀው የሚልሽ 👇
👉እንዲሁም፥ እናንተ ሚስቶች ሆይ፥ ከባሎቻችሁ አንዳንዱ ለትምህርት የማይታዘዙ ቢኖሩ፥ በፍርሃት ያለውን ንጹሑን ኑሮአችሁን እየተመለከቱ ያለ ትምህርት በሚስቶቻቸው ኑሮ እንዲገኙ ተገዙላቸው።
'1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3:1-2'
⚠️ ትህትና በክብር ዝቅ ባለበት በዚህ ዘመን እግዚአብሔር የሚፈልጋት አይነት ያቺን ትሁት ልባም ሴት እንድትሆኚ የሚመክርሽ 👇
🔘ህያው የእግዚአብሔር ቅዱሱ ቃል ነውና አንቺ ሴት 👇
🔘 ራስሽን በእግዚአብሔር ቃል እውቀት ሙይ አእምሮሽና ልብሽ👉 #እረፍት #ደስታ #ቀናውንም መንገድ ይከተላሉና
በዘመናዊነት በስልጣኔ #ዋጋዋን የረሳች ያቺን ወደ ሞት የምትመራ አይነት #ሰነፍ ሴት ከመሆን እግዚአብሔር ይጠብቃችሁ ዘንድ ይህ ለእናንተ መልካም ምኞቴ ነው🙏
⚠️ #እንደጊዜው #እንደፋሽኑ #እንደሁኔታው ሳይሆን መኖርስ እንደ #እግዚአብሔር ቃል 🙏
✒️ ደካማው ቦና 🐅
ለአስተያየት 👉 @onlyforjesus1
Share 👉 @lebamsetoch
933
♦️ ሴቶችም… 👇
👇👇
1⃣ የተከበሩ 🙏
🔺 አንቺ👉 ክብር ያለሽ ሴት ነሽ👍 ማለትም ተራ አይደለሽም❌ ነገር ግን ሰውም እግዚያብሄርም የሚያከብርሽ በሰራሽው ስራ ነው🤷♂ ስለዚህ ክብር እንዳለሽ አውቀሽ መኖር ያንቺ ድርሻ ነው በተራ😳 ነገር ውስጥ የምታልፊና ቀለሽም የምትገኚ ከሆነ ችግሩ ከአንቺ😔 ነው "ክብር ያለሽ ሴት ነሽ አትቅለይ"💪
2⃣ ሐሜተኞች ያልሆኑ ❌
ከንፈርሽ የተፈጠረው👉" መልካምን ወሬ ለማውራትና ለመናገር ነው እንጂ🤔 በሐሜት ክፋ ሃሳብን ሰው ላይ ለመዝራት አይደለም🙅♂" ጓደኛሽን በጀርባ የምታሚ አትሁኚ ይሄ ያንቺ ባህሪ አይደለም😔 ይልቁኑ የጠሉሽን የሰደቡሽን ክፋትንም ያደረጉብሽን😡 በከንፈርሽ ብቻ ሳይሆን ከልብሽ መርቂ እግዚያብሄር በዚህ ደስ ይሰኛልና🙏
3⃣ ልከኞች 💁
በልክና በመጠኑ የምትኖሪ ሁኚ🙏 ብዙም ከፍ አትበይ ደግሞም አትውረጂ የምታደርጊውን ሁኑ ማስተዋልን እየተመረኮዥሽ ከውኚ😲 በጣም ከፍ ካልሽ ጌታን ልትፈታተኚ ዝቅም ካልሽ ልታጉረመርሚ😡 ስለምትችይ "በመጠኑ ኑሪ"🙏
" እኛ ግን ከቀን ስለ ሆንን፥ የእምነትንና የፍቅርን ጥሩር የመዳንንም ተስፋ እንደ ራስ ቁር እየለበስን በመጠን እንኑር፤"
1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 5:8
4⃣ በነገር ሁሉ የታመኑ🙋
ተስፋ እንድትቆርጪ አልተፈቀደልሽም❌ ይልቁኑ በእምነት እንድትበረቺ ግን ስልጣን ተሰጥቶሻል😍 ስለዚህ በምንም ሁኔታ ውስጥ ብታልፊ እምነትሽን አትጪ "እምነተሽ የነገሽ መሰረት ነውና"🙏
ከላይ👆 ያሉትን አራቱን መስፈርቶች እንደ ልባም ሴት ልታሟዪ🤷♂ የግድ ነው በረከትሽ ያለው በእነዚህ ውስጥ ነውና🙏
✒️ ደካማው ቦና 🐅
share 👉 @lebamsetoch
933
🔘 #የማይጠወልግ፣ #የማይጣል ፣ #የማይሰለች የእድሜ ልክ ውበት እግዚአብሔርን #መፍራት ነውና አንቺ ሴት እግዚአብሔር መፍራት ውበትሽ አድርጊ🙏
" ውበት ሐሰት ነው፥ ደም ግባትም ከንቱ ነው፤ እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች። "
(መጽሐፈ ምሳሌ 31:30)
ለአስተያየት 👉 @onlyforjesus1
Share 👉 @lebamsetoch
933
🔘 የቱንም ያክል ዋጋ ቢያስከፍላችሁ እግዚአብሔር ካወራችሁ ነገር ፈቀቅ አትበሉ በራሳችሁም መንገድ ለመሄድ አትፈልጉ ያ ውድቀት ነውና 😔
🔘 ጌታን እየተከተላችሁ አይዞአችሁ አትቀደሙም 🙏
🔘 ከእግዚአብሔር ሃሳብ አትተላለፉ አቋራጭ አትመልከቱ እርሱ ስለእናንተ የሚያስብ አምላክ ነውና 🙋♂
🔘 አዎን እግዚአብሔርን የተከተለ ወድቆ አያውቅም ዘግይቶም አያውቅም🤷♂
🔘 በጎውን የጌታ ለመቅደም አትሩጡ❌ መጨረሻው ድካም ነውና
18 በለሱን የጠበቀ ፍሬዋን ይበላል፥ ጌታውንም የሚጠብቅ ይከብራል።
'መጽሐፈ ምሳሌ 27:18'
⚠️ አስቀድሙት ተከተሉትም👇
5 መንገድህን ለእግዚአብሔር አደራ ስጥ፥ በእርሱም ታመን፥ እርሱም ያደርግልሃል።
'መዝሙረ ዳዊት 37:5'
✒️ ደካማው ቦና 🐅
ለአስተያየት👉 @onlyforjesus1
Share👉 @lebamsetoch
933
🩸አዎን እስካልሞታችሁ ድረስ የመኖር የመነሳት የመመለስ ተስፋ አላችሁ 🙋♂
🩸አዎን በምሕረት ከተፍገመገሙበት መቆም ከወደቁበት መበርታት አለ 🙋♂
🩸አዎን ከትላንት የተሻለ ነገ አለ አስቀያሚውን ትላንት የምትበቀሉበት 🙋♂
🩸አዎን በለቅሶ ብቻ የማያበቃ በብዙ ሳቅ የተሞላ ነገ አለ 🙋♂
👉 #ድቅቅ ብላችኃል አዎን #መጠንከር ትችላላችሁ በራሳችሁ ላይ ተስፋ #ቆርጣችኃል አዎን ተስፋ ማድረግ ትችላላችሁ #በሕይወት አይደላችሁ🤷♂!? ታዲያ ተስፋችሁን ማን #ነጠቀ⁉️
👉 አይዞአችሁ በምህረት የሚቀጠል ሕይወት አለ ያልተበላሸ ተስፋ ያለው ነገ 🙏
✒️ ደካማው ቦና 🐅
ለአስተያየት👉 @onlyforjesus1
Share👉 @lebamsetoch
933
⚠️ ⚠️
🔘 ራስን ማጥፋት አማራጭ አይደለም ራስን ከማጥፋት ጀርባ ደህና ነገር የለምና‼️
አዎን ሰው በብዙ ነገር ያልፋል ምድር ላይም ሰልፉ እግጅ ብርቱ ነው።👉 #ማጣት፣ #መካድ መረሳት፣ #ብቸኝነት፣ አለመሳካት #ተስፋ መቁረጥ፣ #በጨለማ መኖር ግራ መጋባት፣ #ህመም በሽታ፣ የስጋ ድካም #ራስን መጥላት ከነዚህም ያለፋ ጉዳዮች ብዙውን ሰው ራሱን ወደ #የማይመልሰው ሞት ሊመራው እንደ #በቂ ምክንያት ይወሰዳሉ ። 🤔
አዎን ምክንያቱን #እግዚአብሔር ያላደረጋ ሰው ራሱን ሊያጠፋ ይህ በቂ ምክንያቱ ነው🤷♂
🔘ጥያቄ 👉 ጉዳዩ የዘላለም ሞት ጉዳይ ሆኖ ሳለ ታዲያ እንዴት ራስን ማጥፋት #እረፍት ይሆናል🤔⁉️
⚠️ በሞት ብቻ #የሚያበቃ ሕይወት የለም በዘላላምና በሞት ሕይወት ዳግም #የሚቀጥል እንጂ። ስለዚህ ከምርጫ አታስገቡ ራስን ማጥፋት ይህ #ከሰይጣን ነው ተቃወሙት❌
13 ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል።
'1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 10:13'
አይዞዎችሁ በርቱ ምርጫችሁን የዘላለም ሕይወት አድርጉ በዚያ ነውና እረፍት ያለው🙋♂። ምክንያታችሁን ጌታ አድርጉ ራሳችሁን #ማየት ስትጀምሩ ጌታን #ተመልከቱ ያኔ ክፉ ሃሳብ ሁሉ ይጠፋልና🙏
🔘ተስፋ አለ 👉 #ለመኖር #ለመቀጠል #ለመነሳት #ለመሄድ #ለመሮጥ #ተስፋ ለማድረግ። ራስን ለማጥፋን በቂ የመሰለው ምክንያት ብታስቡት #ምናልባት ጥላችሁት የምትሄዱ #እግዚአብሔርን ብታዩበት የሚጠፋ ነው።
⚠️ ይህ የዘላለም ሕይወት ጉዳይ ነው‼️
ክፉውን ተቃወሙት❌ደግሞም እላለው " ከትውልድ አእምሮ ላይ ዘላለም ሞትን ያመጣልና ራስን የማጥፋት የሰይጣን ሃሳብ በኢየሱስ ስም የተነሳ ይሁን " 🙏
# አይዞአችሁ ተስፋ አለ‼️
✒️ ደካማው ቦና 🐅
ለአስተያየት👉 @onlyforjesus1 / 0942305601
Share👉 @lebamsetoch
933
10 ልባም ሴትን ማን ሊያገኛት ይችላል? ዋጋዋ ከቀይ ዕንቍ እጅግ ይበልጣል።
'መጽሐፈ ምሳሌ 31:10'
🔹አንቺ ብቻ በእግዚአብሔር መንገድ ሂጂ እንጂ 👉 በረከት ነሽ ደግሞም ምንጭ ግራ ለተጋቡ ለብዞዎች ደራሽ ፣ ለባልሽ ኩራት፣ ፍሬያማ ትውልድን የምታፈሪ፣ በሰማዩም በምድሩም የምትባረኪ ሴት ላትሆኚ የሚከለክልሽ ፈፅሞ የለም🤷♂ ብቻ አንቺ በእግዜሩ መንገድ በቅድስና ሂጂ ወደ ጌታም ተመለሺ። " ሴት ሁኚ!! "
✒️ ደካማው ቦና 🐅
ለአስተያየት @onlyforjesus1
Share @lebamsetoch
@lebamsetoch
