cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ማዕደ ሰማይ

#በፀጋ ነው #ፀጋው ብቻ #የታደገን ከዓለም ጡጫ። #በፀጋ የዳነ #ያለፀጋ አይፅፍም #ያዳነው እያለ #የዳነው አይነግስም፤ #ባለፀጋው #ባይኖር #እኔም ችዬ አልኖርም። እንዳለው እንድኖር ጸጋ አለ የሚያኖር። http://t.me/ElgraceBot ለአስተያየቶ በዚህ 👇 ይላኩልኝ። @Surtsega @Surafeltsegamets

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
787
Suscriptores
Sin datos24 horas
-67 días
-830 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

#ያ_ዘመን_ሲጠባ 🔎🔎 ሞቶ መኖር እየቻለ ኖሮ ለመሞት አዳም ተቻኮለ። ጉድ እኮ ነው ወገን ማስተዋል ከራቀን 📌📌 🔐 ‼️ ⓢⓤⓡⓐⓕⓔⓛ            ━━━━⊱✿⊰━━━━━ 👉👉 @elgraceministry 👈👈 👉👉 @elgraceministry 👈👈
Mostrar todo...
2
Photo unavailableShow in Telegram
#እግዚአብሔር_ይመስገን!! ስለ ዶክተር ማሙሻ ተጨንቃችሁ የነበራችሁ፣ የጸለያችሁ፣ የጠየቃችሁ፣ የደወላችሁ፣ ፍቅራችሁን የገለጻችሁ ወዳጆቻችን ተባረኩ ፥ ይኸው እግዚአብሔር ጸሎታችንን ሰምቷልና እናመሰግነው ዘንድ ይገባናል። የምትችሉ ሁሉ ለእግዚአብሔር ሰው ስላደረገው መልካም ነገር በቦታው በመገኘት #እግዚአብሔርን እናመስግን። ━━━━⊱✿⊰━━━━━ @gtmmbetsega  @elgraceministry @Elgracebot        @surtsega          @surafeltsegamets
Mostrar todo...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
Photo unavailableShow in Telegram
ኢየሱስ #ጌታ(ያህዌህ) ነው። እርሱ (ድንቁ የአብ (ኤሎሄ) ስጦታ) ለዘላለም አባት ለፍጥረታት ሁሉ አስገኚያቸው፤ ፈጣሪያቸው ሰማይና ሰራዊቱ የሚሰግዱለት ምድርና አራዊቱ ሚንቀጠቀጡለት ንፋሳትና ባህሩ የሚታዘዙለት ከአብርሃም በፊት የነበረ እግዚአብሔር (ያህዌህ) እርሱ በጠባብ ደረት በአጭር ቁምጣ ከድንግል ማርያም በመወለድ ወደ ምድር ሰው ሆኖ የመጣ ግን ከዛ ዕለት ያልጀመረ ኧረ ኢየሱስ ንጉስ፣ መድሃኒት፣ ጌታ እና ክርስቶስ ነው። ዘላለም የማይሻር ታላቅ እውነት፤ ኢየሱስ የዓለምን ሁሉ ኃጢዓት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ (የታረደው በግ) እንዲሁም የይሁዳ አንበሳ (ማህተሙን የፈታ) ጌታ መሆኑ ነው። ለመላው የንጉስ ካህናት መልካም የንጉስ ልደት በዓል ይሁንልን።          @━━━━⊱✿⊰━━━━━ @      👉👉 @elgraceministry 👈👈      👉👉 @elgraceministry 👈👈
Mostrar todo...
1
Photo unavailableShow in Telegram
⛸⛸ #የነፍሴ_ደዋሪ ⛸⛸ ምራዊ ሳቃችን፥ ምታስፈነድቀን፤ ህያው ተስፋችን፥ የምትናፍቀን፤ በደሳሳ ጎጆ፥ ሙላተ ማድጋ፤ በነጠፈ ተስፋ፥ ብርቱ ባለጠጋ፤ የሻገተውን፥ ፈጽሞ አለምላሚ፤ የተቆረጠውን፥ እንደአዲስ ገጣሚ፤ ከጥንት ጥንትን መስራች፥ ከዘላለም ዘላለምን ሰሪ፤ የህይወትን ትርጉም፥ የህይወትን ፍቺ፥ ብቻውን ቀማሪ፤ የሰማይ እና የምድር ደዋሪ፤ እውነተኛው ፈገግታችን፤ ሀዘን የለሹ ደስታችን፤ ምራዊ ሳቃችን፥ ምታስፈነድቀን፤ ህያው ተስፋችን፥ የምትናፍቀን፤ መቼ ነው መምጣትህ? መቼ ነው ምጻትህ? መችም እንደጥንቱ በረት አትወርድም፤ ዳግም ለእኛው፥ በእኛው አትዋረድም፤ ሰማይ እያወጋህ፥ ምድርም ሸሽጋህ፥ ጠባብ ደረት፤ አጭር ቁምጣ አያመጣህም። ምራዊ ሳቃችን፥ ምታስፈነድቀን፤ ህያው ተስፋችን፥ የምትናፍቀን፤ ልክ እንደሙሽሪት፥ ተጠናቃ ሙሽራዋን እንደምትጠብቅ፤ በንጽህና፥ እንደምትናፍቅ፤ መቼ ነው፥ `ምትመጣው? መች አንተን፥ እንጠብቅ? ምራዊ ሳቃችን፤ ምታስፈነድቀን ህያው ተስፋችን፤ የምትናፍቀን አሜን እንደናፈቅንህ፤ አሜን እንደራብከን፤ ሳይቀዘቅዝ ለአንተ ያለን ንጡህ ፍቅር ታጥበን ነፅተን እስክትመጣ እንጠብቅህ።              ━━━━⊱✿⊰━━━━━ @gtmmbetsega    @elgraceministry @Elgracebot           @surtsega          @surafeltsegamets
Mostrar todo...
4
Photo unavailableShow in Telegram
ሰላም እንደምን አላችሁ የሚሽን ሞቢላይዜሽን ኢትዮጵያ ቤተሰቦች! እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን ! ይህ የምናከብረው በዓል ከክብረ-በዓልነትም በላይ የእግዚአብሄር ዘላለማዊ አጀንዳ ለህዝቦቹ የተገለጠበት፣ አማኑኤል እግዚአብሄር ከእኛ ጋር ያልንበት ነው። በወንጌል ላልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች እያደረግነው ያለውን ጸሎት እንቀጥላለን ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ሳምንቱን በምድራችን ላይ በአጠቃላይ እንደአህጉር ላልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎችን ልዩ ትኩረትን በመስጠት "መወለዱን ላልሰሙት" በሚል ተከታታይ ጸሎት በእግዚአብሄር ምህረት የታሰቡ ሆነው ለጌታችን በሚቀርቡበት ስርዓተ ጸሎት እንድንሳተፍ እንጋብችዋለን! በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ ካሉት 8.00 ቢሊዮን ሰዎች 3.40 ቢሊዮን ሰዎች የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ለመስማት ዕድል ወይም ተደራሽነት በሌላቸው የሕዝብ ክፍሎች ውስጥ ይኖራሉ። በጆሹዋ ፕሮጀክት መሠረት፣ በአለም ላይ 17,446 የሚጠጉ ልዩ የሕዝብ ቡድኖች ወይም ክፍሎች አሉ፣ ከእነዚህም ውስጥ 7,248 ያልተደረሱ (ከ42 በመቶ በላይ የሚሆነው የዓለም ህዝብ)! ከእነዚህ አነስተኛ ደረጃ ላይ ከሚደርሱት ቡድኖች ውስጥ አብዛኛዎቹ (85%) በ 10/40 መስኮት ተብሎ በሚጠራው ልዮ ቦታ ውስጥ ይገኛሉ እና በእነዚህ ሰዎች መካከል ከ3% ያነሰ የሚስዮናዊነት ስራ ይሰራል። በአለማችን በወንጌል ያልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች አጠቃላይ የሕዝብ ብዛት ፡- 8.1 ቢሊዮን የሀገራት ብዛት፡- 205 አጠቃላይ የሕዝብ ክፍሎች ብዛት ፡- 17,281 ያልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች፡- 7,248 (41.9%) ባልተደረሱ የሕዝብ ክፍሎች ውስጥ ሚገኙ፡- 3.4 ቢሊዮን ያልተደረሱ የሕዝብ ክፍች በፐርሰንት፡- 42.4% አብዛኞቹ የሚገኙት ፦ በ 10/40 መስኮት (85%)
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
የተወደዳችሁ የማዕደ ሰማይ ተከታታዮች ጌታ ቢፈቅድና ብንኖር ወደሌላ የህይወት ምዕራፍ የምዘዋወርበትን ቀን አብረን እንሆን ዘንድ ግብዣዬን በታላቅ አክብሮት አቀርባለሁ። #እግዚአብሔርን_አሰብሁት #ደስ_አለኝም። @elgraceministry @elgraceministry
Mostrar todo...
7
Photo unavailableShow in Telegram
#የንቀት_ጥግ ጻድቁ አብርሃም፥ ታላቁ የእምነት አባት፤ ድንኳን በመስራት ነው፥ አለምን የናቃት። አይገርምም?🤔             ━━━━⊱✿⊰━━━━━ @gtmmbetsega     @elgraceministry @Elgracebot           @surtsega          @surafeltsegamets
Mostrar todo...
6🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
#የምሬን_ማመልክህ #ናፈቅኸኝ ላልከኝማ አምልከኝ፥ መርጠህ ከእልፍ መሃል፤ እያዜምኩ ሳዜምልህም፥ ለአንተስ ያንስብሃል። በምን ዕድል፥በምን ዕጣዬ፤ ከአንተ ቤተ ሰዎች፥ መቆጠሬ፤ ምስጋናዬን ያልቀዋል ለምላሼ ሺስ ቢሆን መች ይበቃል? በቃ አይምሽ፥ በቃ አይንጋ፤ ሺ ጊዜ ሺ ቅዱስ እያልኩህ፥ ዘላለም ይጥባ። t.me//elgraceministry
Mostrar todo...
3