es
Feedback
ነገረ ሃይማኖት

ነገረ ሃይማኖት

Ir al canal en Telegram

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን መሰረት የደረጉ ✔የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ✔የቅዱሳን አባቶቻችን ገድል ✔የኢትዮጵያ ገዳማት ታሪክ ✔መጽሐፍት ዳሰሳ ✔የነገረ ሃይማኖት ትምህርቶች...ይቀርባሉ

Mostrar más
389
Suscriptores
Sin datos24 horas
+17 días
+830 días
Archivo de publicaciones
✝ ከምን ዓይነት ነገር መላቀቅ እንዳለብህ ታዉቃለህ ?? ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ ምድራዊ ምኞት ምን ያህል አስከፊ እንደሆነና እንዴት ከዚህ ነገር ነፃ መውጣት እንዳለብን እንዲህ በማለት ይመክሩናል፦ "ወዳጄ ከምድራዊ ምኞትህ ተላቀቅ ከምን አይነት ነገር መራቅ እንዳለብህ ታውቃለህ? ከምድራዊ ፍላጎት ከመሳሰሉት ራቅ ፍፁም የመንፈስ ነፃነት እንዲኖርህ ከፈለክ ከምድራዊ ምኞቶችህ ተላቀቅ። በእርጋታና በግልጽነት ላውጋህ እጅግ አብዝተህ የምትጨነቅባቸው ልብህን የተቆጣጠሩት ታላላቅ ምድራዊ ተስፋዎች አሉህ። እነኚህም ሃሳብህን ሁሉ ይቆጣጠሩታል ብቻህን በምቶንበት ጊዜ በምናብ ይመጡብሃል በምትተኛ ጊዜ ህልምህ ሁሉ ይህ ይሆናል ልትክዳቸው የማትችለው ነገር ግን የምታውቃቸው ምድራዊ አላማዎች አሉህ። ተፈላጊነት እንዲኖርህ ትመኛለህ፣ ስልጣን እንዲኖርህና፣ ኃያል እንድትሆን፣ ዕውቅና እንዲኖርህና ስምህ ከጽንፍ እስከ አጽናፍ እንዲናኝ ትፈልጋለህ። በሀብት፣ በምድራዊ ስልጣን፣ በዕውቀት በማዕረግና በመልክ ዝነኛ የመሆን ተስፋ አለህ ፣ በመኖሪያ ቤት፣ በምግብ፣ በልብስና በሰውነት ደስታን በሚሰጡ ነገሮችም ተስፋ አለህ። ዓለም በአንተ እንጂ አንተ በዓለም እየኖርክ አይደለም። ስለዚህ አንተነትህ በዚህ ምድራዊ ተስፋ የታጠረ ነው። መንፈስህም ከስጋ ፍላጎቶች መራቅን ትመኛለች ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስ በሥጋ ላይ ይመኛልና። (ገላ.5፥17) እነዚህ ሥጋዊ ተስፋዎችና ፍላጎቶች ስኬታማ ስለማይሆኑ ግራ ትጋባለህ። ይህን በእርግጥ ቅሬታን ያመጣብሃል። እነዚህን ነገሮች ሁሉ ትናፍቃለህ ነገር ግን ናፍቆትህ አያስደስትህም። ስለዚህ ለምኞትህ ሁሉ ማስተካከያ ታበጅለት ይሆናል ምናልባትም ይጠቅሙኛል የምትላቸውን ሰዎች ማግኘት፣ በምኞትህ ዙሪያ የተጻፈ መዛግብት ማገላበጥ ትፈልግ ይሆናል በዚህም ላይ ታች ስትል ምኞትህን ለማሳካት ትታገላለህ እንዲሆን ሌላ ዘዴ ልትፈጥር ትችላለህ ይሁን እንጂ ሳይሳካልህ ቀርቶ በሃሳብና በጥረት ትታክታለህ ከዚያም ትበሳጫለህ። ከዚህ የከፋው ነገር በእነዚህ ምኞቶችና ተስፋዎች ስኬታማ አለመሆን ምክንያት ለከፋ ሕይወት መዳረግህ ነው። እንደምትሰለች አውቃለሁ አዘንኩልህ እስከመቼ ድርስ በምኞት ማዕበል ውስጥ ትኖራለህ? የምትመኘውን ባገኘህ ጊዜ ደስተኛ ትሆናለህ ይህ ደስታ ስለማያረካህ ሌላ አዲስ ደስታን እንድትመኝ ያደርግሃል። ልክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ "ከዚህ ውሃ የሚጠጣ ሁሉ እንደገና ይጠማል" (ዮሐ.4፥13 ) እንዳለው እርካታ አይኖርህም። ስለዚህ ውድ ወንድሜ ነገሩን በእርጋታ ከአንተ ጋር ለመነጋገር እፈልጋለሁ። "አለሙም ምኞቱም ያልፋል" (1ኛ ዮሐ.2፥17) ታዲያ ይህን ቃል ካወክ ለምን አለማዊ ፍላጎቶችን ለማግኘት ትታክታለህ? አንተ ልክ እንደ እኔ ለመሬት እንግዳ ነህ። ዓለም የሚያልፍበት አንተም የምትጠፋበት ጊዜ ይመጣል ልክ ከእናትህ ማህጸን ራቁትህን እንደመጣህ እንደዚሁ ራቁትህን ትመለሳለህ።(ኢዮ. 1፥21) ዓለምን ከነክብሯ ከነሀብቷና ከነስሟ ለቀሃት እንድትሄድ በመገደድ እንደ ማንኛውም ሰው ወደ መሬት ትወርዳለህ። ከዚያም ከዓለም ያገኘኽውን ደስታ ታወቂነት ወይም ምንም ይሁን ምን ሥጋህን ከሞት ሊከላከልልህ አልያም ሥጋን ከሚበሉት ትል ሊከላከልልህ አይችልም። በፍርድ ቀን ከዓለም ሀብትና ንብረት ውጭ በእግዚአብሔር ፊት ትቆማለህ። መልካም ይሁን ክፉ የሰራኸው ሥራ እንጂ የዓለም ቁሳዊ ነገር አይከተልህም። ስለዚህ ውድ ወንድሜ ምኞትህንና ተስፋህን በዓለም ላይ በማድረግ መታወክህ ለአንተ ጥሩ አይደለም ይህችን ምድር እሾህንና አሜኬላን እንዳበቀለችልህ ትዘነጋለህን!!! ከእኛ በፊት የነበሩና ምድርን ሊረግጧት የማይገባት የቅዳሳን አባቶችና እናቶች አሠራርና ፈለግ ተከተል ቅድስናቸውን ያገኙት ይህችን ዓለም በመውደድ ሳይሆን በመናቅ ነበር ሁኔታዎች ሁሉ ተመቻችተውላቸው ሳለ በዓለም ስላሉ ነገሮች ለማንኛውም ጉጉት አልነበራቸውም ። ውድ ወንድሜ አሁንም ምኞት አሉህ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና (ማቴ.6፥21) የሥጋን ምኞቶችን ስለተቆራኘ መንፈሳዊ ነገሮች በአንተ አመለካከት ዋጋቸውን ያጣሉ ይህ የክብር ጌታ እንደተፈተነው ዓይነት ፈተና ነው። (ማቴ.4፥8-9) አሁን አስተውል እነዚህን ነገሮችን ብትይዝ በጥሩ ምኞት ያላሰርካት ነፍስህን ብታጣ ጥቅሙ ምንድን ነው? ነፍስህ ነጻነትን ትሻለች። ከስጋ ምኞት ተላቀን የመንፈስ ፍሬ የሆኑትን " የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣  እምነት፣ የውሃት፣ ራስን መግዛት ነው።"(ገላ.5፥22) እንዳለው ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ እነዚህን ገንዘብ አድርገን እንድንኖር እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን!! (የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ "የመንፈስ ነጻነት "ከሚለውና በዲ/ን ደስታ ፍፁም ከተተረጎመው መጽሐፍ ላይ የተወሰደ። ምክር ወተግሳፅ እንዳቀረበው)

✝ + በሕይወት ፡ ሳለን ፡ ዋስ ፡ ያልፈለገች ፡ ነፍስ ፡ በምትሞትበት ፡ ቀን ፡ በሰማይ ፡ ዋስ ፡ አታገኝም ። ነገሩ እንዲህ ነው ፤ ብዙ እዳ ያለበት ሰው ቢኖር የሚከፍለው ባይኖረው የሚዋሰውም
✝ + በሕይወት ፡ ሳለን ፡ ዋስ ፡ ያልፈለገች ፡ ነፍስ ፡ በምትሞትበት ፡ ቀን ፡ በሰማይ ፡ ዋስ ፡ አታገኝም ። ነገሩ እንዲህ ነው ፤ ብዙ እዳ ያለበት ሰው ቢኖር የሚከፍለው ባይኖረው የሚዋሰውም ቢያጣ ወደ ፈራጅ ይወስዱታል ፤ ዳኛውም ለአሽከሩ ይሰጠዋል ፤ አሽከሩም ያስረዋል ። ለቅሶና ጦር ማፏጨት በአለበት ቦታ ይጣላል ። ዕዳውን እስኪጨርስ ድረስ አይወጣም ። እኛም በቁርጥ ፍርድ ቀን ከእግዚአብሔር አብ ፊት በደረስን ጊዜ እንደዚህ እንሆናለን ። በሕይወት ሳለን በዚህ ዓለም የሚዋሰን ካልፈለግን በሰማይ የሚዋሰን አናገኝም ። ይህም ማለት በዚህ ዓለም እንደሚቻለን ርኅራኄ ካላደረግን ፣ ድሆችን ጦም አዳሪዎችን ከረሳን በሰማይ የሚዋሰን የሚቀበለን የለም ማለት ነው ። ንስሐ ካልገባን ቸርነትን ካላደግን በሰማይ ምህረትን አናገኝም ። ድርሳነ ሚካኤል ዘጥቅምት #ተግተንእንጸልይ  #ሰዋስወብርሃን

✝ ክርስቲያን መሆን "ክርስትና ለዘለዓለም የሚተነፍሱት የሕይወት እስትንፋስ ነው አይቋረጥም። ከተቆረጠ ሕይወት ያን ጊዜ ትርጉም ታጣለች። ክርስትና ለዘለዓለም የሚያነዱት እንጂ ለተወሰነ ጊዜ ተጠቅመው የሚያዳፍኑት እሳት አይደለም። ክርስትና በየበዓላት ጊዜ ብቻ ለብሰው ኋላ ሳጥን እንደሚቆልፉበት የክት ልብስ ሳይሆን ሁልጊዜም የሚያጌጡበት የሕይወት ልብስ ነው። ክርስትና ከዳኑ በኋላ የሚሞቱት ሞት ሳይሆን ከሞቱ በኋላ የሚድኑበት ሕይወት(የጽድቅ ፍኖት) ነው።"           የመንፈሳዊ እድገት ማነቆዎች    (በ ዲ/ን ኃ/ጊዮርጊስ ተፈራ፤1993) @bahiretibebat21

✝ #አደራ_አለብኝ! የ 2016 ዓ.ም 1ኛ ዙር ጉባኤ ዓለም ዓቀፍ የግቢ ጉባኤ ምሩቃን ኅብረት ጉባኤ ቀን፡ ኅዳር 2/2016 ዓ.ም ሰዓት፡ ከ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ ጉባኤው በሁሉም ማእከላት በተመሳሳይ
✝ #አደራ_አለብኝ! የ 2016 ዓ.ም 1ኛ ዙር ጉባኤ ዓለም ዓቀፍ የግቢ ጉባኤ ምሩቃን ኅብረት ጉባኤ ቀን፡ ኅዳር 2/2016 ዓ.ም ሰዓት፡ ከ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ ጉባኤው በሁሉም ማእከላት በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት ይከናወናል። ቦታ፡ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ

✝️ "እግዚአብሔርን የምትፈሩት ሆይ፡ ዋጋችሁን እንዳታጡ እመኑት:: እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፡ የዘለዓለም በጎነቱን ምሕረቱንና ደስታውን ተስፋ አድርጉ፡፡ በዘመን የቀደሙ ሰዎችን ተመልከቱ፡ዕወቁም፡-በእግዚአብሔር አምኖ ያፈረ ማነው? እርሱን በመፍራት የታገሠና የተጣለ ማነው? ጠርቶትስ ቸል ያለው ማነው? እግዚአብሔር መሓሪ ይቅር ባይም ነውና ኀጢአትን ይቅር ይላል፡በመከራ ቀንም ያድናል" ሲራ 2:8-11

✝ "The road to hell is paved with excuses and Justifications" H.H Pope Shenouda

✝️ “ድንግል ሆይ! ባማረ በተወደደ ነገር ሁሉ መሰልኹሽ ምስጋናሽን ግን ለመፈፀም አልቻልኩም፡፡ እግዚአብሔርን ባመሰገንሁ ጊዜ ባንቺ ለስሙ ምስጋና አቀርባለሁ፤ በስምሽም ጸሎቴን በጸለይሁ ጊዜ ጸሎቴን ለልጅሽ አቀረብሁ፤ ዳግመኛም ውዳሴሽን ወደማወቅ ባህር ልዋኝ ወደድሁ፣ ወደ ክብርሽ ገናንነት ወደብ እደርስ ዘንድ ደከምሁ፣ ያንዲቷን ማእበል ሞገድ ያህል ስንኳን አላለፍሁም። ወደ ጽርሐ አርያም ጠፈር ለመድረስ የሚቻለው ማነው? ከምድር በታች ወዳለው ባሕር መሠረትስ መዋኘት ማን ይችላል? ድንግል ሆይ! ክብርሽን ገናንነትሽን ጠንቅቆ መናገር የሚቻለው ማነው?'' ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

✝ ትሕትናን ውደዷት " ትሕትናን ውደዷት ኃጢአታችሁን የምትሸፍን ናትና።ሁሉም ኃጢአት በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ቢሆንም ከኃጢአቶች ሁሉ መጥፎ የሆነው ግን የልብ ትዕቢት ነው።ራሳችሁን አዋቂ አድርጋችሁ ከፍ ከፍ አታድርጉ። ይህንን የምታደርጉ ከሆነ ጥረታችሁ ሁሉ ፍሬ አልባ ይሆናል። ይህም መርከባችሁ ባዶውን ወደ ዳርቻው እንዲደርስ ያደርገዋል።"       አባ እንጦንስ

✝ የክርስቲያን መለያው [ምልክቱ] ምንድን ነው? “የክርስቲያን መለያው [ምልክቱ] ምንድን ነው? ባልጠበቀው ሰዓት ጌታ እንደሚመጣ አስቦ በየዕለቱ በየሰዓቱ ነቅቶ መጠበቁ እና እግዚአብሔርን ደስ በሚያሰኘው መንገድ ምላሽ ለመስጠት ተዘጋጅቶ መቆሙ ነው” ቅዱስ ባስልዮስ

✝ “እንደማይሰጥ ይዘገያል” (ቅዳሴ ሠለስቱ ምዕት) ጸሎት የምንጸልይባቸው የየራሳችን ምክንያቶች አሉን፤ ጥሩ የትምህርት ውጤት፣   ጤና፣   የተሳካ ሥራ፣    መልካም ትዳር፣   ከሕይወት ፈተና መራቅ፣   መልካም ቤተሰብ፣    ልጅ፣   ለንስሓ እና ቅዱስ ቍርባን መብቃት ወዘተ… የሰው ልጅ በዘመናት ለአምላኩ ከጸለያቸው ጸሎቶች መካከል ይገኙበታል። አዳም ከጸጋ ከተራቆተ በኋላ ከገጠመው የሕሊና ሕመም (የቀደመውን ደስታ እና ሰላም ማጣት) የተነሣ፣   መንግሥተ ሰማያትን ይለምን ነበር። ሰው ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅር አገብሮት መጸለዩ እንዳለ ሆኖ፣  ትልቁ የጸሎት መነሻ ግን ማጣት ነው። የቀደመ ሰላም፣   ፍቅር፣   ትዳር፣   ልጅ፣   ጤና፣   የተስተካከለ ሕይወት በማጣት እግዚአብሔር ደጅ ለጸሎት የቆምነው እልፍ ነን። አዳም መንግሥተ ሰማያትን፣ የቀደመ ክብሩን፣ የቀደመ ሰላሙን፣ የቀደመ ጤንነቱን አጥቶ ፤ ለንስሓ እና ለጸሎት እንደቆመ ማለት ነው፤ ጸሎቱ ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶ ተሰማለት። ለመልሱ ተግባራዊነት ደግሞ 5500 ዘመንን ቆየ። እንደቆይታው ግን የማይፈጸም ይመስል ነበር። እግዚአብሔር መልሱን ለመስጠት 5500  ዘመን መቆየቱ የራሱ ምክንያት አለው! ልክ የእኛን ጸሎት መልስ ለመስጠት እንደሚዘገየው ማለት ነው። ብዙዎቻችን ከመዘግየቱ የተነሣ ተስፋ ከማጣት ጀምሮ እግዚአብሔርን እስከ መካድ እንደርሳለን[ተስፋ እንቆርጣለን]። ለአዳም 5500 ዘመን እንደቆየበት ምክንያት፣  ለኛም ጥያቄ መዘግየት ምክንያቶች ምንድናቸው የሚለውን ለማሰብ ለአዕምሯችን ዕድል አንሰጠውም። ይልቁን  የመልሱን መዘግየት እንደ መቅረት አድርገን እንገነዘባለን። ለረጅም ጊዜ ደጁ ተመላልሰን የጸለይነው ጸሎት መልስ አልባ መስሎ ይሰማናልና። እግዚአብሔር እኛ በፈልገነው ወቅት መልሱን ስላልሰጠን ተስፋ እንቆርጣለን፤ እግዚአብሔር ጨርሶ የተወን ያክል ይሰማናል። የሠለስቱ ምእት ቅዳሴ ይኽን ነገር ሲገልጥ  "እንደማይሰጥ ይዘገያል" ይለዋል እግዚአብሔርን፤ እውነት ነው እግዚአብሔር መስጠቱ ለማይቀር ይዘገያል፤ የሚዘገይበትም የራሱ ምክንያቶች አሉት። እኛም ለመረዳት መሞከር ያለብን፣ እነዚያን ምክንያቶች እንጂ መዘግየቱን እንደመቅረት መረዳት የለብንም።" @betemetsihaf

✝ "መላው ዓለምን ያስደነገጡ ታላላቅ መከራዎች ሁሉ መነሻቸው ትዕቢት ነው፡፡"    ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

✝ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር እንዴት እናሳድግ? "ሁሌ ስለ እርሱ ማሰብ፣ እርሱን መጠጋትና ከእርሱ ጋር አንድነታችንን ማጠንከር፥ ለእርሱ ያለንን ፍቅር ይጨምራል። በሥራ ላይ ሆነን፣ ምንም ፋታ በሌለ
ለእግዚአብሔር ያለንን ፍቅር እንዴት እናሳድግ? "ሁሌ ስለ እርሱ ማሰብ፣ እርሱን መጠጋትና ከእርሱ ጋር አንድነታችንን ማጠንከር፥ ለእርሱ ያለንን ፍቅር ይጨምራል። በሥራ ላይ ሆነን፣ ምንም ፋታ በሌለን ጊዜም ቢሆን፥ እርሱን እናነጋግረው። ማለትም በምናደርገው ነገር ሁሉ ወደ እርሱ እንጸልይ። በማንኛውም በምናከናውነው ድርጊታችን ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ልንጸልይ ይገባናል። ከእርሱ ጋር ባለን አብሮነት እየተደሰትን፤ የምናደርገውን ሁሉ ለእርሱና ለእርሱ ብቻ ነው እንበል፤ ተግተንም እንፈጽመው።" እማሆይ ኄራኒ

✝ "ከቤተ ክርስቲያን የሚርቁትን አጋንንት ይወስዷቸዋል።ስለሆነም ወደ ቤተ ክርስቲያን መሔድን አታቋርጡ።፣መንፈሳዊ ዋጋና ዘላለማዊ ሕይወት ታገኛላችሁ።"     መፅሐፈ ዲድስቅልያ

✝ "ወደ መሬት ወድቀን በሰገድን ጊዜ ኃጢአት እንዴት ወደ ታች ጎትታ እንደጣለችን እናስታውሳለን። ዳግመኛም ከወደቅንበት በተነሣን ጊዜ የእግዚአብሔር ጸጋ እና ምሕረት እንዴት ከመሬት እንዳነሣንና የሰማዩን ርስት እንደሰጠን እንመሰክራለን"           ቅዱስ ባስልዮስ

✝ ወደ አግዚአብሔር መቅረብ ትወዳለህን? ወንድሜ ሆይ ወደ አግዚአብሔር መቅረብ ትወዳለህን? ከሐዋርያው ከቅዱስ ጳውሎስ ጋርስ እንዲህ ማለትን ትሻለህን? "..ልሄድ ከክርስቶስ ጋር ልኖር እናፍቃለሁ።ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና።" ፊል 1:23 ይህን ለማለት ከፈለግህ ያ በሰዎች ፊት ከፍ ከፍ የምታደርገው የምታመጻድቀውና ከእግዚአብሔር ይልቅ ታመልከው ዘንድ ከጀመርከው አንተነትህ ተላቀቅ!          ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ         ( የነፍስ አርነት)

✝ "ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።" ገላትያ 6:-14 መልካም በዓል @bahiretibebat21

✝ "ክርስቲያን ማለት በሚችለው አቅም ሁሉ ክርስቶስን በሃሳብ፣ በቃልና በተግባር የሚመስል ነው።"   ቅዱስ ዮሐንስ ዘቅሊማቆስ(ዘሰዋስው) @bahiretibebat21

"..በንጹሕ ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር የመነጋገርን እድል እንድታገኝ አቀራረብህ ሁሉ ለእግዚአብሔር ክብር የሚጠነቅቅ መንፈሳዊ ፍርሃት ያለው ይሁን!! በርግጥ የአንተ ፍርሃት ባሪያ ለጌታው የሚንቀጠቀጠውን ዓይነት ፍርሃት ሳይሆን የልጅ እና የአባት ዓይነት፤ አልያም ከቅጣት በላይ ስለ ፍቅር የመጠንቀቅ ዓይነት ፍርሃት ይሁን። በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ (ጉዞ ወደ እግዚአብሔር)

✝ ''ስትጸልይ በማክበር ውስጥ መሆንን ተለማመድ፣ የልብና የሥጋ ማክበር ይኑርህ፣ የስሜቶች ሰላምም እንዲሁ። ቀስ በቀስ መዝሙራትን፣ ወንጌላትንና የዘወትር ጸሎቶችን አጥና። በሁሉም ጊዜ ውስጥ ጸሎት መጸለይን ተለማመድ፣ ስትሠራ፣ ስትራመድና ከሌሎች ሰዎች ጋር ስትቀመጥ እንኳ፣ ዘወትር ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኔ ኃጢአተኛውን ማረኝ እያልህ መጸለይን ተለማመድ። በማንኛውም ጊዜ ለሌሎች ሰዎች መጸለይን ተለማመድ፣ ለሁሉም ሰዎችም ፍቅር አሳይ፣ ለጠላቶችህና አንተን ለሚሰድቡህ ሰዎች እንድትጸልይ የሚያዝህን የእግዚአብሔር ትዕዛዝ ተለማመድና ተግባራዊ አድርግ።" ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ