es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 691 suscriptores, ocupando la posición 8 014 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 155 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 691 suscriptores.

Según los últimos datos del 29 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 137, y en las últimas 24 horas de 5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 34.17%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 17.11% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 362 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 685 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 30 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 691
Suscriptores
+524 horas
+77 días
+13730 días
Archivo de publicaciones
photo content

ማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን ለማስተናገድ ዝግጁ ነው ‎…....///…….. ‎የጅግጅጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑ
+6
ማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን ለማስተናገድ ዝግጁ ነው ‎…....///…….. ‎የጅግጅጋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ የኃይል ጥያቄዎችን ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ‎ ‎ሥራ አስኪያጁ አቶ ደምለው እሸቱ እንደገለጹት ‎በማከፋፈያ ጣቢያው ላይ ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ በተከናወኑ የአቅም ማሳደግና የማዘመን ሥራዎች አሁን ላይ የጅጅጋ ከተማና አካባቢው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኙ ነው። ጣቢያው እስከ 60 ሜጋ ዋት ኃይል የማቅረብ አቅም ቢኖረውም በአሁኑ ወቅት ለደንበኞች እየቀረበ ያለው የኃይል መጠን 30 ሜጋ ዋት ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፈያ-ጣቢያው-ተጨማሪ-የኃይል-ጥያቄ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

ማስታወቂያ ......///....... የጄንደርና ሶሻል አፌርስ ኤክስፐርት V (Gender and Social Affairs Expert V) የጄንደርና ሶሻል አፌርስ ኤክስፐርት V (Gender and So
ማስታወቂያ ......///....... የጄንደርና ሶሻል አፌርስ ኤክስፐርት V (Gender and Social Affairs Expert V) የጄንደርና ሶሻል አፌርስ ኤክስፐርት V (Gender and Social Affairs Expert V) የሥራ መደብ የተመዘገባችሁ አመልካቾች የትምህርት ማስረጃችሁን እና የሥራ ልምዳችሁን በኢሜይል አድራሻ tsbprojectresourceproject@gmail.com እንድትልኩ እናሳስባለን። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ምንጭ ጥገኝነትን መቀነስ! ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት በውሃ ኃይል (Hydro-power) ላይ ጥገኛ ሆና ቆይታለች። ይሁንና የኃይል ስብጥሩን ለማስፋት የተለያዩ ሥራዎች በመሰራት ላይ ናቸው፡፡
የኃይል ምንጭ ጥገኝነትን መቀነስ! ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት በውሃ ኃይል (Hydro-power) ላይ ጥገኛ ሆና ቆይታለች። ይሁንና የኃይል ስብጥሩን ለማስፋት የተለያዩ ሥራዎች በመሰራት ላይ ናቸው፡፡ በቀጣይ ዓመታ ይተገበራሉ ተብለው በዕቅድ ከተያዙት መካከል የንፋስና የፀሐይ ኃይልን በስፋት ማካተቷ የአቅርቦት አስተማማኝነትን (Power Supply Reliability) ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑ ታምኖበታል፡፡ በመሆኑም የኃይል ምንጭ ጥገኝነት (Over-reliance on Hydropower) መቀነስ የሚኖሩትን አራት ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታዎች ቀጥለን እንመለከታለን። የአየር ንብረት ለውጥንና ድርቅን መቋቋም (Climate Resilience) የውሃ ኃይል ማመንጫዎች የዝናብ መጠን ሲቀንስ እና የግድቦች ውሃ የመያዝ አቅም ሲቀንስ የማመንጨት አቅማቸው በከፍተኛ መጠን ይቀንሳል። ስለሆነም እንደ ንፋስና ፀሐይ ባሉ ሌሎች ታዳሽ የኃይል ምንጮች ላይ ኢንቨስት ማድረጓ የሚከተሉትን ጥቅሞች ይሰጣል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ምንጭ-ጥገኝነትን-መቀነስ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ አገልገሎት መስጠት ጀመረ ….....///…….. በባህር ዳር ከተማ የተገነባው የባለ 230 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ አገልግሎ
+2
የተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ አገልገሎት መስጠት ጀመረ ….....///…….. በባህር ዳር ከተማ የተገነባው የባለ 230 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ተሻገር እንደገለፁት በከተማዋ አንድ ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ የሚገኝ ቢሆንም እያደገ የመጣውን የነዋሪውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ጥያቄ የሚመልስ አልነበረም፡፡ ነባሩ የባህር ዳር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለከተማዋና አካባቢው ኢንዱስትሪዎች 125 ሜጋ ዋት ኃይል እያቀረበ መሆኑን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ ሆኖም ጣቢያው ኃይል የመጫን አቅሙ በመሙላቱ ምክንያት ተጨማሪ ጥያቄዎችን ማስተናገድ የማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን አስታውሰዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተንቀሳቃሽ-ማከፋፈያ-ጣቢያው-ግንባታ-ተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም

🇪🇹 የኢትዮጵያ ኢነርጂ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ - ዘመናዊ፣ ፍትሐዊና ዘላቂ የፖሊሲ ማዕቀፍ! ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት አስርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየውን የኢነርጂ ፖሊሲ በመከለስ፣ ሀገራዊና ዓ
🇪🇹 የኢትዮጵያ ኢነርጂ ዘርፍ አዲስ ምዕራፍ - ዘመናዊ፣ ፍትሐዊና ዘላቂ የፖሊሲ ማዕቀፍ! ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት አስርት ዓመታት በሥራ ላይ የቆየውን የኢነርጂ ፖሊሲ በመከለስ፣ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያገናዘበ አዲስ ረቂቅ ፖሊሲ ለውይይት ቀርቧል። ይህ ፖሊሲ ኢትዮጵያን የአህጉሪቱ የኃይል ማማ ለማድረግ የተያዘውን ራዕይ ለማሳካት የሚያስችል ዋነኛ ምሰሶ ነው። 🇪🇹⚡️ በፖሊሲው ትኩረት የተደረገባቸው ጉዳዮች፡- የኢነርጂ ስብጥርን ማመጣጠን (Energy Mix) 💡 ከውኃ ኃይል (Hydro) ባለፈ የንፋስ፣ የፀሐይ፣ የጂኦተርማልና የባዮ-ጋዝ አማራጮችን በስፋት በማካተት በተወሰኑ የኃይል ምንጮች ላይ ያለንን ጥገኝነት በመቀነስ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ማድረግ፤ 🌅 ኃይል ላይ የተመሠረተ ልማት ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ፀጋ በመጠቀም 100% አረንጓዴና ታዳሽ የሆነ የኃይል ልማትን ማረጋገጥ የፖሊሲው ዋነኛ ግብ ነው። በመሆኑም የፖሊሲው ትኩረት የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የምናደርገውን ጥረት መደገፍ ነው፡፡ 🌅 የኢነርጂ ተደራሽነትና ፍትሐዊነት ኃይል ለሁሉም ለማዳረስና በከተማም ሆነ በገጠር የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎች የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የሚያስችሉ የቴክኖሎጂና የፋይናንስ አማራጮችን ያመቻቻል። ይህም የዜጎችን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻልና ለኢንዱስትሪ ልማት መፋጠን ቁልፍ ሚና ይጫወታል። 🌅 የግል ዘርፉን ተሳትፎ ማሳደግ በዘርፉ የሚታዩ የአቅርቦት ውስንነቶችን ለመቅረፍና ግዙፍ የኢነርጂ ፕሮጀክቶችን በገንዘብና በቴክኖሎጂ ለመደገፍ የግል ባለሀብቶች (IPPs) በስፋት የሚሳተፉበት ግልጽ አሠራር እንዲዘረጋ ማድረግ፤ ይህ አዲስ የፖሊሲ ማሻሻያ ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና የምታደርገውን ጉዞ የሚያፋጥን "የኢነርጂ ነዳጅ" እንደሚሆን ይታመናል።

በጣቢያው የኃይል አቅርቦትን ለማሻሻል የሚያስችል ሁለተኛ ዙር የአቅም ማሳደግ ሥራ እየተከናወነ ነው ……..///…..… በምዕራብ አርሲ ዞን እና በአካባቢው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍ
+5
በጣቢያው የኃይል አቅርቦትን ለማሻሻል የሚያስችል ሁለተኛ ዙር የአቅም ማሳደግ ሥራ እየተከናወነ ነው ……..///…..… በምዕራብ አርሲ ዞን እና በአካባቢው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለማርካት በሻሸመኔ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሁለተኛ ዙር የአቅም ማሳደግ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ምህረቱ ግዛው እንደገለፁት ጣቢያው ከ1966 ዓ.ም. ጀምሮ አገልግሎት ሲሰጡ የቆዩ መቆጣጠሪያዎችን በዘመናዊ የጂ.አይ.ኤስ ብሬከሮች በመቀየር አስተማማኝና ያልተቆራረጠ ኃይል ለማቅረብ እየተሰራ ነው። ቀደም ሲል በማከፋፈያ ጣቢያው የነበሩት የ33 እና 15 ኪሎ ቮልት መቆጣጠሪያ ብሬከሮች በዘመናዊ የጂ.አይ.ኤስ ብሬከሮች ተቀይረው አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ሥራ አስኪያጁ አስታውሰዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በጣቢያው-የኃይል-አቅርቦትን-ለማሻሻል-የ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም

🇪🇹💡 የሰባት ዓመታት የኃይል ዘርፍ ጉዞ፦ ከእጥፍ በላይ ዕድገትና የ100% ታዳሽ ኃይል ድል! ከ2011 ጀምሮ በነበሩት ባለፉት ሰባት ዓመታት በሀገራችን የኃይል ማመንጨትና መሠረተ-ልማት ግንባታ ላይ የተመዘገበው ውጤት እጅግ አስደናቂ ተብሎ ሊገለጽ የሚችል ነው። አሐዞች እንደሚነግሩን ዘርፉ በየዓመቱ በአማካይ የ10% እድገት በማስመዝገብ ላይ ይገኛል። ⚡️ ዋና ዋና የስኬት አመልካቾች (2011 እስከ 2017) 💡 የኃይል ምርት መጠን፦ ከ15.3 ቴራዋት ሰዓት (TWh) ወደ 29.5 ቴራዋት ሰዓት በእጥፍ አድጓል። 💡 የማመንጨት አቅም፦ ከ4,500 ሜጋ ዋት (MW) ተነስቶ አሁን 9,760 ሜጋ ዋት ደርሷል። 💡 አጠቃላይ ዓመታዊ ገቢ፦ ከነበረበት 10 ቢሊዮን ብር ወደ 75.4 ቢሊዮን ብር አድጓል። 💡 የውጭ ምንዛሬ ገቢ፦ ከቀጣናዊ የኃይል ሽያጭና ከቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የሚገኘው ገቢ ከ100 ሚሊዮን ዶላር በታች የነበረ ሲሆን አሁን 338.7 ሚሊዮን ዶላር ደርሷል። 🇪🇹💡 ኢትዮጵያን በዓለም ልዩ የሚያደርጋት ምንድነው? ሀገራችን አጠቃላይ የኃይል ምንጯን 100 በመቶ ወደ ታዳሽ ኃይል (Renewable Energy) ያሸጋገረች ጥቂት ከሚባሉ የዓለም ሀገራት ተርታ መሰለፏ ትልቅ ኩራት ነው። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፦ 💡 17 የውኃ ኃይል ማመንጫዎችን፤ 💡 5 የንፋስ ኃይል ማመንጫዎችን፤ 💡 1 የጂኦተርማል (የከርሰ ምድር እንፋሎት) እና 💡 1 ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል የሚያመነጭ ጣቢያን ያስተዳድራል። 🏗⚡️ የመሠረተ-ልማት አውታራችን ስፋት፦ ከተለያዩ የኃይል ማመንጫዎች የተመረተው የኃይል ምርት 15,857 ኪሎ ሜትር የሰርኪዩት ርዝመት ባላቸው የማስተላለፊያ መስመሮችና የተለያየ የቮልቴጅ መጠን ባላቸው 148 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች (Substations) ባሉት ዘመናዊ የግሪድ ኔትወርክ ለተጠቃሚዎች እየደረሰ ይገኛል። 💡🇪🇹 የኢትዮጵያ ብርሃን ለቀጣናውም ትርፍ የሚሆን ብርታት እየሆነ ነው! 💡🇪🇹

photo content

ፕሮጀክቱ የግብርና ማቀነባበሪያ ፓርኩን ወደ ሙሉ የማምረት አቅም ያሸጋግረዋል …….///….… የገንደ አርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለቡልቡላ
+5
ፕሮጀክቱ የግብርና ማቀነባበሪያ ፓርኩን ወደ ሙሉ የማምረት አቅም ያሸጋግረዋል …….///….… የገንደ አርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከ40 ሜጋ ዋት በላይ ኤሌክትሪክ እንደሚያቀርብ የፓርኩ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ገቢታ ኢረጎ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው መጠናቀቅ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኩን ወደ ሙሉ የማምረት አቅም ለማሸጋገርና ለኢንቨስትመንት መፋጠን ወሳኝ ሚና ይጫወታል። ፓርኩ ካረፈበት 271 ሄክታር መሬት ውስጥ 136 ሄክታሩ ለኢንዱስትሪዎች ልማት የሚውል መሆኑን ጠቁመው ይህንኑ ግዙፍ የልማት ቀጠና ለማንቀሳቀስ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚያስፈልገው ነው ያብራሩት። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱ-የግብርና-ማቀነባበሪያ-ፓርኩን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ የኢነርጂ ፖሊሲ ሊከለስ ነው ........///........ ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የቆየውን የኢነርጂ ፖሊሲ የሚከልስ ረቂቅ ፖሊሲ ለውይይት ቀረበ። በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አቅ
+3
የኢትዮጵያ የኢነርጂ ፖሊሲ ሊከለስ ነው ........///........ ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የቆየውን የኢነርጂ ፖሊሲ የሚከልስ ረቂቅ ፖሊሲ ለውይይት ቀረበ። በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አቅራቢነት በተዘጋጀው የረቂቅ ፖሊሲ ውይይት ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ተሳትፈዋል። ኢትዮጵያ ስትጠቀምበት የቆየችው የኢነርጂ ፖሊሲ አሁን ካለው የሀገሪቱና የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣም ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ በሥራ ላይ ያለውን  ፖሊሲ መከለስ እንዳስፈለገ ተነስቷል። በረቂቅ ፓሊሲው ላይ ስድስት ዐበይት ጉዳዮች የተካተቱ ሲሆኑ ሙያዊ ድጋፍ በመስጠትና በማማከር የሀገር ውስጥ እና ከሌሎች ሀገራት የተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኢትዮጵያ-የኢነርጂ-ፖሊሲ-ሊከለስ-ነው&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

በሁለቱ ዞኖች ላይ ተቋርጦ የቆየው ኃይል ዳግም ተመልሷል ......///....... በአባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አቅራቢያ አንድ የእንጨት ምሰሶ በመውደቁ ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ኤሌክትሪክ ዳግም መመለሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንዳስታወቁት ወደ ማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል በሚያደርሰው አንድ ገቢ የእንጨት ምሰሶ መስመር ላይ ችግር በመፈጠሩ ምክንያት በዳውሮ እና ኮንታ ዞኖች ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል፡፡ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታም ቀደም ሲል ስድስት የእንጨት ምሰሶዎችን ይጠቀም የነበረውን መስመር በአንድ አዲስ የእንጨት ምሰሶ አማካኝነት በአቅራቢያው ከሚገኝ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ጋር በማገናኘት ኤሌክትሪክ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ጌታሁን ገለፃ የተበጣጠሱ የኤሌክትሪክ ሽቦዎች እና የተበላሹ የኮንዳክተር ሽቦ ማያያዣዎችን በመቀየር በአካባቢው ሊደርሱ የሚችሉ አደጋዎችን መከላከል ተችሏል፡፡ አሁን ላይ በዞኖቹ ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ መመለስ ተችሏል ያሉት ሥራ አስኪያጁ በጥገና ሥራው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ ለነበሩ የጥገና ባለሙያዎች እንዲሁም ችግሩ እስኪፈታ ድረስ በትግዕስት ለጠበቁ ደንበኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

🇪🇹 የኢነርጂ ዘርፍ ሪፎርም - ከተቋማዊ ዕዳ ወደ ፋይናንስ ጥንካሬ! 🇪🇹 የሀገራችን የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆነው የኃይል ዘርፍ፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ታሪካዊ የሚባል የሪፎርም እና የፋይናንስ ማሻሻያ እርምጃዎችን አከናውኗል። ከተከናወኑት የሪፎርም ሥራዎች መካከል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቀነስ ረገድ የተከናወኑ ሥራዎች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ 🔍 ከሪፎርሙ በፊት የነበረው ተግዳሮት ምን ነበር? ከ2010 ዓ.ም በፊት የኃይል ዘርፉ በከፍተኛ የንግድ ብድር ዕዳ የተዘፈቀ ነበር፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሂሳብ መዝገብ የዕዳና የካፒታል ጥምርታ (Debt-to-equity ratio) ከፍተኛ ልዩነት እንዳለው የሚያሳይ ነበር። ይህ ዕዳ ተቋሙን ለፋይናንስ ሥጋት ከመዳረግ ባለፈ ብድርም ሆነ የግል የኃይል አምራቾችን (IPPs) ለመሳብ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል። 🇪🇹 🚀 የተወሰዱ ታሪካዊ የማሻሻያ እርምጃዎች፦ 1. የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (HGER)  ማክሮ ኢኮኖሚውን ለማረጋጋትና የኢነርጂ ዘርፉን የፋይናንስ ዘላቂነት ለማረጋገጥ የተቀረጸ ስልታዊ አጀንዳ ነው። 2. የዕዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን (LAMC)  የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ዕዳ "ለመውሰድ" መንግሥት ባቋቋመው የዕዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን (LAMC) አማካይነት የተቋሙ የሂሳብ መዝገብ (Balance sheet) መልሶ እንዲስተካከል ተደርጓል። 3. የዕዳ ስረዛና የካፒታል እድገት  በ2016 ዓ.ም ብቻ ወደ 217 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዕዳ ከተቋሙ የሂሳብ መዝገብ እንዲሰረዝ ተደርጓል። ይህም የተቋሙን የተከፈለ ካፒታል ከ319 ቢሊዮን ወደ 589 ቢሊዮን ብር በማሳደግ በሁለት እጥፍ እንዲጨምር አድርጓል። 4. አስደናቂ የዕዳ ቅናሽ  በመንግሥት ጣልቃ ገብነት የተቋሙ አጠቃላይ የፋይናንስ ዕዳ በ2015 ዓ.ም መጨረሻ ከነበረበት 355 ቢሊዮን ብር በ2016 ዓ.ም መጨረሻ ወደ 128 ቢሊዮን ብር ዝቅ እንዲል ተደርጓል። 💡 የዚህ ለውጥ ፋይዳ ምንድነው? የተቋሙ የፋይናንስ ጤንነት መመለስ ተቋሙ የብድር ተዓማኒነቱን መልሶ እንዲያገኝ አድርጎታል። ከኪሳራ ወደ ትርፋማነት እንዲሸጋገርም አድርጓል፡፡ በዚህም እንደ ዓለም ባንክ ካሉ ተቋማት ጋር እንደ "ASCENT" ባሉ ግዙፍና አዳዲስ ንጹሕ የኃይል ተደራሽነት መርሀ ግብሮች ላይ ለመሳተፍ በር ከፍቶለታል። የኢትዮጵያን የኃይል ተደራሽነት ለማሳድና የሀገራችንን የኢንዱስትሪ ሽግግር ለማፋጠን ጠንካራና በፋይናንስ የዳበረ የኃይል ተቋም መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው!

photo content

በሪጅኑ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም የማከናወን ልምምድ እያደገ ነው፤ ‎.....///…... የጥገናና የማስፋፊያ ሥራዎችን በሪጅኑ አቅም የማከናወን ልምምድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን በኢትዮጵ
+7
በሪጅኑ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም የማከናወን ልምምድ እያደገ ነው፤ ‎.....///…... የጥገናና የማስፋፊያ ሥራዎችን በሪጅኑ አቅም የማከናወን ልምምድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ 2 ሪጅን ገለጸ። ‎ ‎በሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቁ ሙሉ እንደገለጹት ምስራቅ 2 ሪጅን አምስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እንዲሁም 719 ኪሎ ሜትር ርዝመትና 1 ሺህ 643 ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ያሉት የማስተላለፊያ መስመሮችን ያስተዳድራል። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በሁሉም ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የቅድመ መከላከል፣ ድንገተኛና በዕቅድ ላይ የተመሠረቱ የጥገና የፍተሻ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በሪጅኑ-የጥገና-ሥራዎችን-በራስ-አቅም-የ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም

🌋 ከጥልቁ ምድር የሚገኝ የማይነጥፍ የኃይል በረከት - የከርሰ ምድር እንፋሎት (Geothermal)! 🇪🇹⚡️ ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ውስጥ በመገኘቷ ከፍተኛ የከርሰ ምድር እንፋሎት ወይም የጂኦተርማል ኃይል እምቅ አቅም ካላቸው ጥቂት ሀገራት አንዷ ናት። ይህንን በመጠቀም ረገድ እንደ ሀገር የአሉቶ ላንጋኖ የጂኦተርማል ፕሮጀክት እንደ ዓይን ከፋች ፕሮጀክት ተደርጎ የሚወሰድ ቢሆንም በዘርፉ ብዙ መስራት እንዳለብን የሚያሳይ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ በአሉቶ እስከ 70 ሜጋ ዋት ለማመንጨት የማስፋፊያ ፕሮጀክት እየተከናወነ ሲሆን እንደ ቱሉ ሞዬ እና ኮርቤቲ ባለ ሳይቶች የግል አልሚዎች በዘርፉ ለመሰማራት የተለያዩ ሥራዎችን በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ⚙️ የኃይል አመራረት ሂደቱ እንዴት ነው? የጂኦተርማል ኃይል አመራረት ሂደት ተፈጥሮንና ቴክኖሎጂን አቀናጅቶ የሚሠራ አስደናቂ ሂደት ነው፡፡ ዋና ዋና ሂደቶቹም፡- 1. ቁፋሮ፦  በመጀመሪያ ጥልቅ የሆኑ ጉድጓዶች (Wells) እስከ ሦስት ሺህ ሜትር ድረስ ወደ መሬት ውስጥ ይቆፈራሉ። 2. የእንፋሎት መውጣት፦  ከመሬት በታች ያለው ከፍተኛ ሙቀት በውስጥ ያለውን ውሃ ወደ ትኩስ እንፋሎት ይቀይረዋል። ይህ ከፍተኛ ግፊት ያለው እንፋሎት በትቦዎች አማካይነት ወደ ላይ ይወጣል። 3. ተርባይን ማሽከርከር፦  ወደ ላይ የወጣው እንፋሎት ግዙፍ ተርባይኖችን በከፍተኛ ፍጥነት ያሽከረክራል። 4. ኤሌክትሪክ ማመንጨት፦  ተርባይኑ ሲሽከረከር ከጄነሬተር ጋር በመገናኘት ሜካኒካዊ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ይቀይራል። 5. መልሶ መጠቀም፦  ጥቅም ላይ የዋለው እንፋሎት ተመልሶ ወደ ውኃነት እንዲቀየር ተደርጎ ወደ መሬት ውስጥ ተመልሶ በመርፌ (Injection) መልክ ይገባል፤ ይህም ሂደቱ ተደጋጋሚና ቀጣይነት እንዲኖረው ያደርጋል። 🌟 የጂኦተርማል ኃይል ዋና ዋና ጥቅሞች፦ 🌋 ከአየር ንብረት ጋር አለመለዋወጡና አስተማማኝነቱ (Reliability)፦  እንደ ውኃ ግድቦች በዝናብ እጥረት፣ ወይም እንደ ፀሐይና ነፋስ በአየር ሁኔታ አይቀያየርም። በቀን 24 ሰዓት፣ በዓመት 365 ቀናት ያለ ማቋረጥ ኃይል ይሰጣል። 🌋 ታዳሽና ንጹሕ ኃይል መሆኑ፦  ምንም ዓይነት ተረፈ ምርት ወይም በካይ ጋዝ ስለማያመነጭ ለአካባቢ ጥበቃና ለ"አረንጓዴ ኢኮኖሚ" ግንባታ ተመራጭ ነው። 🌋 ዘላቂና የማይነጥፍ የኃይል ምንጭ መሆኑ፦  የከርሰ ምድር እንፋሎት ሁልጊዜም ያለ በመሆኑ ለዘመናት አገልግሎት የሚሰጥ ዘላቂ የኃይል ምንጭ ነው። 🌋 አነስተኛ ቦታ የሚፈልግ መሆኑ፦  ከውኃ ግድቦች ወይም ከሶላር ፓርኮች አንጻር ሲታይ በጣም አነስተኛ በሆነ የቆዳ ስፋት ላይ ሰፊ ኃይል ማመንጨት ይቻላል። ሀገራችን በአሉቶ ላንጋኖ፣ በቱሉ ሞዬ እና በኮርቤቲ አካባቢዎች የጀመረቻቸው የጂኦተርማል ፍለጋና የማልማት ፕሮጀክቶች እውን ሲሆኑ የኃይል አቅርቦታችንን ይበልጥ አስተማማኝ እንደሚያደርጉት ይታመናል። የኢትዮጵያ ብርሃን ከምድር ጥልቀት እስከ ሰማይ ከፍታ ይበራል!

photo content
+1

የተቋሙ የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል እውቅና ተሰጠው …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሴት ሠራተኞቹ ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር ያቋቋመው የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል
+2
የተቋሙ የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል እውቅና ተሰጠው …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሴት ሠራተኞቹ ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር ያቋቋመው የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል “የሞዴል ማዕከል” እውቅና ማግኘቱን በተቋሙ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ አስታወቁ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንዳስታወቁት የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከሉ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እውቅና ከተሰጣቸው ሰባት ሞዴል የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከላት መካከል ግንባር ቀደም ሆኗል፡፡ የማዕከሉ ከባቢያዊ ሁኔታ፣ የህጻናት መመገቢያ፣ መኝታና፣ መጫወቻ ክፍሎች ስፋት፣ የመጸዳጃና የመታጠቢያ ክፍሎች ሁኔታ እና የህጻናት ቅበላ መስፈርት እንዲሁም የሞግዚትና የህጻናት ንጽጽር ተቋማቱ የተወዳደሩባቸው መስፈርቶች እንደነበሩ ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙ-የህጻናት-ማቆያና-መንከባከቢያ-ማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም