es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 525 suscriptores, ocupando la posición 8 336 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 179 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 525 suscriptores.

Según los últimos datos del 07 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 5, y en las últimas 24 horas de -2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 28.59%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.03% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 440 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 489 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 08 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 525
Suscriptores
-224 horas
-57 días
+530 días
Archivo de publicaciones
የአዘዞ - ጭልጋ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ እየተፋጠነ ነው ……………….////…………………… በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ማዕከላዊ ጎንደር ዞን እየተገነባ የሚገኘው የአዘዞ - ጭልጋ ባለ 230/33 ኪ. ቮ. የኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ አንድ አዲስ ባለ 230/33 ኪ. ቮ. ከፍተኛ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና 40 ኪ ሜ. ርዝመት ያለው የባለ 230 ኪ. ቮ. የኃይል መስመር ዝርጋታን ያጠቃልላል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው የሳይት ተቆጣጣሪ መሃንዲስ አቶ አድማሱ ኃይሌ እንደገለፁት የጭልጋ ባለ 230/33 ኪ.ቮ. ማከፋፈያ ጣቢያ የተለያዩ የሲቪል እና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎች ከሐምሌ 2011 ዓ.ም. እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ እንደ አቶ አድማሱ ገለጻ በማከፋፈያ ጣቢያው እስከ አሁን የኤሌክትሮ መካኒካልና የብረታ ብረት ተከላና ለኤሌክትሪክ ገመዶች ቀበራ የሚውል ግንባታ ስራዎች ተጠናቀዋል፡፡ የመቆጣጠሪያ ቤት፣ የሰራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የጥበቃ ቤት ግንባታና የፍሳሽ ማስወገጃ ግንባታዎች የማጠናቀቂያ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በቀጣይም የጠጠር ንጣፍ፣ የውስጥ አጥር፣ የሲዊችያርድ ግንባታ እና የሁለት ባለ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመር ተከላ ስራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው እንደሚከናወኑ መሃንዲሱ ጠቁመዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው አጠቃላይ አፈጻጸም 63 በመቶ ደርሷል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከነባሩ የአዘዞ ባለ 230/66/33/15 ኪ ቮ. የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ አዲስ እስከሚገነባው የጭልጋ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ የሚዘረጋው የ40 ኪ.ሜ ባለ 230 ኪ. ቮ. ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታም እየተፋጠነ ነው፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታው የሳይት ተቆጣጣሪ መሃንዲስ አቶ ሃብታሙ ኃይሉ እንደተናገሩት ለመስመር ዝርጋታው 105 ማማዎች ይተተከላሉ፡፡ ከዚህ ውስጥ ደግሞ የ22 ምሶሶ መትከያ የመሰረት ግንባታ የተጠናቀቀ ሲሆን 50 የምሶሶ ማቆሚያ የጉድጓድ ቁፋሮ ስራም እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ግንቦት 2012 ዓ.ም. የተጀመረው የመስመር ዝርጋታ ስራ አጠቃላይ አፈጻጸም 10 በመቶ ላይ ይገኛል፡፡ የአዘዞ - ጭልጋ - ፊንጫ 2ኛ - ሻምፑ - መቱ - ማሻ 230/33 ኪ.ቮ. ፕሮጀክት ዋና ማናጀር አቶ ግርማ ዘለቀ እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታውን እና የመስመር ዝርጋታ ስራውን ለማጠናቀቅ ከ281 ሚሊየን ብር በላይ በጀት ተመድቦለታል፡፡ ፋይናንሱም ሙሉ ለሙሉ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር የሚሸፈን መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ሥራውን ለመጨርስ 18 ወራት የተያዘለት ሲሆን ግንባታውን ሲኖ ሃይድሮ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ኩባኒያ ሲያከናውን በአማካሪነት ደግሞ ኢ. ኤል. ሲ. ELC የተባለ የጣሊያን ኩባኒያ እየተሳተፉበት ይገኛሉ፡፡ ስድስት ባለ 33 ኪ. ቮ. ወጪ መስመር ያሉት ይህ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በጭልጋና አካባቢው የነበረውን ሰፊ የኃይል አቅርቦት ችግር ይፈታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከአዲስ አበባ በ780 ኪ.ሜ. ርቀት ላይ በጭልጋ ወረዳ በአንጓባ ቡላድጌ ቀበሌ የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈጻጸሙ 36 በመቶ ደርሷል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 20 ቀን 2012 ዓ.ም.

ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል …………………..//////………………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2012 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ የ
ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል …………………..//////………………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2012 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡ በ2012 በጀት ዓመት ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ እና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ6 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከ6 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ መሰብሰብ ተችሏል፡፡ መምሪያው እንዳስታወቀው አፈፃፀሙ የእቅዱን 102 ነጥብ 2 በመቶ እንዲሁም በገንዘብ ከእቅዱ የ143 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር ብልጫ አሳይቷል፡፡ ከገቢው ውስጥ 6 ቢሊዮን ብሩ የተሰበሰበው ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከቀረበ ጅምላ የኃይል ሽያጭ፣ 607 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብሩ ከከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች፣ 44 ነጥብ 36 ሚሊዮን ብር ለኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር ከቀረበ የኃይል ሽያጭ እንዲሁም 69 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብሩ ኢትዮ ቴሌኮም ከተጠቀመበት የፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ የተሰበሰበ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 19 ቀን 2012 ዓ.ም.

ተጠግነው አገልግሎት የሚሰጡ ንብረቶችን በመለየት ወደ ስራ የማስገባት ስራ እየተከናወነ ነው …………………..//////………………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን ከማስወገድ በተጓጋኝ ተጠግነው አገልግሎት የሚሰጡትን ንብረቶች በመለየት ወደ ስራ የማስገባት ስራ እያከናወነ መሆኑን የተቋሙ ንብረት አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ስራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ ዳዲ እንደገለፁት ንብረቱ ተጠግኖ የሚሰጠውን አገልግሎትና የጥገና ወጪውን ከግምት ውስጥ ለማስገባት በየስራ ክፍሉ የልየታ ተግባራት እየተከናወኑ ነው፡፡ በተቋሙ የንብረት አያያዝና አስተዳደር ላይ የሚስተዋለውን ክፍተት ለመሙላትም በቴክኖሎጂ የታገዘ የንብረት ማደራጀት ስራ መጀመሩንም ስራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡ ንብረቶችን ለማደራጀት እና ለማስተዳደር የንብረት ዋጋ ክለሳ እና ወቅቱ የሚጠይቀውን የተቋም ሀብት ዕቅድ ስርዓት (Enterprise Resource planning system) የመዘርጋት ስራ በመሰራት ላይ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 19 ቀን 2012 ዓ.ም.

አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በማስወገድ ከ33 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰበሰበ …………………..//////………………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት የማይሰጡ የተለያዩ ንብረቶችን በማስወገድ በ2012 በጀት ዓመት 33 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን የተቋሙ ንብረት አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ስራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ ዳዲ እንደገለፁት ገቢው የተገኘው አገልግሎት የማይሰጡ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች፣ አልሙኒየም፣ መዳብ፣ የተለያዩ የዕቃ ማሸጊያ ጣውላዎች፣ ያገለገሉ የተሸከርካሪ ጎማዎች እና የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን በማስወገድ ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ አገልግሎት የማይሰጡ ንብረቶችን በማስወገድ 20 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 33 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ይህም ከእቅዱ የ66 በመቶ ብልጫ እንዳለው እና ከ2011 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ149 በመቶ ብልጫ እንዳሳየ ነው አቶ ታደሰ የገለጹት፡፡ ቀደም ሲል ያገለገሉ ንብረቶች ሽያጭ ሲከናወን የነበረው በመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ሲሆን የመንግስት ንብረት አስተዳደር መመሪያ ቁጥር 9/2003 መሰረት በማድረግ ተቋሙ ባወጣው የንብረት አስተዳደር እና አወጋገድ መመሪያ መሰረት የንብረት ማስወገድ ስራው በተቋሙ እየተከናወነ እንደሚገኝ ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ ታደሰ ገለፃ የስራ ክፍሎች እንዲወገድላቸው የሚያቀርቡት ጥያቄ በተቋቋመው የንብረት አስወጋጅ ኮሚቴ ታይቶ ንብረቶቹ በሚገኙበት አካባቢ ተመሳሳይ ንብረቶች የሚሸጡበትን ዋጋና የመንግስት ንብረት ማስወገድ አጄንሲ ያወጣውን መነሻ የጨረታ ዋጋ ታሳቢ በማድረግ በግልጽ ጨረታ ሽያጩ ይከናወናል፡፡ በአሁኑ ወቅትም አገልግሎት የማይሰጡ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች፣ አልሙኒየም፣ ጣውላዎች፣ አሮጌ የቤት ክዳን ቆርቆሮዎች፣ ባህርዛፍ፣ በርሜሎች፣ ያገለገሉ ጎማዎች እና ተሸከርካሪዎችን ለማስወገድ እየተሰራ መሆኑን አቶ ታደሰ ተናግረዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለነበረዉ የገቢ አሰባሰብ እድገት የተቋሙ አመራር ጥንካሬ እና በአሁኑ ወቅት ንብረት የማስወገድ ስልጣን ለተቋሙ መሰጠቱ በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡ በሌላ በኩል ንብረቶች በህጋዊ መንገድ በጨረታ በሚወገድበት ወቅት በአንዳንድ አካባቢዎች ንብረቶቹ እንዳይነሱ የመከልከል፣ ወደ ጣቢያዎች ግቢ በህገወጥ መንገድ በመግባት ቋሚ ንብረቶችን የመውሰድና ቤት የመስራት እንዲሁም የሰራተኞች መኖሪያ ቤትን ለመንጠቅ የሚደረጉ ሙከራዎች ቢሮው እያጋጠሙት ያሉ ተግዳሮቶች መሆናቸውን አቶ ታደሰ ጠቁመዋል፡፡ ችግሮችን ለመፍታትም ከክልል የፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመሰራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 18 ቀን 2012 ዓ.ም.

ሁሉም ተቋራጭ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ተባለ ........................///////.................. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሊት
ሁሉም ተቋራጭ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ሊወጣ ይገባል ተባለ ........................///////.................. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሊት በታቀደው መሰረት እንዲከናወን ሁሉም ተቋራጮች ተናበው እንዲሰሩ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አብርሃም በላይ አሳሰቡ። ዶ/ር አብርሃም የግድቡን ሥራዎች ከተመለከቱ በኋላ ከተቋራጮች ጋር ሲወያዩ እንደተናገሩት ተናቦ በመስራት የታሰበውን ውጤት ለማምጣት ሁሉም ሊረባረብ ይገባል። በመሆኑም የቅድመ ኃይል ማመጨት ሥራውንና የሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌቱን በዕቅዱ መሰረት ለማጠናቀቅ ሁሉም ተቋራጭ የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት አለበት ብለዋል። ተቋራጮቹ ዓመቱን ሙሉ 24 ሰዓት በመስራትና በመናበብ እንዲሁም ግብዐታቸውን በማቀናጀት በወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እንዲፈፅሙ መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን ዶ/ር አብርሃም አረገግጠዋል። ተቋራጮቹም የሚሰሯቸውን ስራዎችና የጊዜ ሰሌዳቸውን በማቅረብ ውይይት ተካሂዶበት ግብረመልስ ተሰጥቷቸዋል። በየወሩ በመገናኘት አፈፃፀሞችን ለመገምገም ቀጠሮ ይዘዋል። ነሐሴ 17 ቀን 2012 ዓ/ም

ለታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሠራተኞችና የፀጥታ አካላት 40 ሰንጋዎች በስጦታ ተበረከተ .....................//////............. የአማራና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሳነ መ
ለታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሠራተኞችና የፀጥታ አካላት 40 ሰንጋዎች በስጦታ ተበረከተ .....................//////............. የአማራና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሠራተኞችንና የፀጥታ አካላትን በስፍራው በመገኘት አበረታቱ። የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጉ አካላት በሙሉ ርዕሳነ መስተዳድሮቹ ያላቸውን አድናቆት በመግለፅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ተመስገን ጥሩነህ እንደተናገሩት የአባይ ተፋሰስን ለመጠበቅ ክልሉ በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ላይ በንቃት ተሳትፎ አድርጓል። ለግድቡ ግንባታም እስካሁን ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሊቱ በስኬት በመጠናቀቁም የአማራ ክልል ህዝብና መንግስት መደሰቱን ተናግረዋል። የክልሉ ድጋፍም እስከ ግድቡ ፍፃሜ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። የቤኑሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን በበኩላቸው ለውጡን በየጊዜው ሲከታተሉ መቆየታቸውን ጠቅሰው የመጀመሪያ ዙር ሙሊቱ ትልቅ ትርጉም አለው ብለዋል። ይህንን ስኬት ከአማራ ክልል አቻቸው ጋር በመጎብኘት የፕሮጀክቱን ሠራተኞች ለማበረታታት በስፍራው መገኘታቸውን ተናግረዋል። ከርዕሳነ መስተዳድሮቹ ጋር ግድቡን የጎበኙትና በአባይ መነሻ ሰከላ የተወለዱት ባለሀብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ ለፕሮጀክቱ ሠራተኞች፣ ግድቡን ቀን ከሌት ለሚጠብቁ ለመከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስ አባላት አጋርነታቸውን ለመግለፅ 40 ሰንጋዎች በስጦታ አበርክተዋል። አቶ በላይነህ ክንዴ እስካሁን ድረስ ከ33 ሚሊየን ብር በላይ ቦንድ በመግዛት የሚታወቁ ሀገር ወዳድ ባለሀብት ሲሆኑ ለሀገሬ ሀብቴን ብቻ ሳይሆን ነፍሴን ጭምር እሰጣለው በሚል አገላለፃቸው ይታወቃሉ።

ከወላይታ ሶዶ-አዲስ አበባ የተዘረጋው ሁለተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር አገልግሎት መስጠት ጀመረ …………….////……………….. ከወላይታ ሶዶ-አዲስ አበባ የተዘረጋው ሁለተኛ የኤሌክትሪክ
ከወላይታ ሶዶ-አዲስ አበባ የተዘረጋው ሁለተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር አገልግሎት መስጠት ጀመረ …………….////……………….. ከወላይታ ሶዶ-አዲስ አበባ የተዘረጋው ሁለተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር በነባሩ የጊቤ III- ወላይታ ሶዶ- አዲስ አበባ ታወር ወይም ማማ ላይ በተጨማሪ የተዘረጋ መሆኑን የ400 ኪ.ቮ ፕሮጀክት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ መሐመድ ሽኩር ተናግረዋል፡፡ በፕሮጀክቱ በዋናነት የኤሌክትሪክ ኮንዳክተር እና ኢንሱሌተር ዝርጋታ እንዲሁም የተለያዩ መሳሪያዎች ገጠማ መከናወኑን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የተዘረጋው ሁለተኛ መስመር በነባሩ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ይስተዋል የነበረውን የኃይል መጨናነቅ በማስቀረት አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያግዛል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ 400 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ኃይል የመሸከም አቅም ያለው እና 260 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ሲሆን ግንባታውን ለማከናወን 7 ነጥብ 8 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና 43 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ ተደርጎበታል፡፡ የፕሮጀክቱን ግንባታ የቻይናው ሻንጋይ ኤሌክትሪክ ኩባንያ ያከናወነው ሲሆን የዚህ ፕሮጀክት አካል የሆነው የጊቤ III- ወላይታ ሶዶ ሁለተኛ መስመር ዝርጋታ ለማከናወን በሂደት ላይ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 15 ቀን 2012 ዓ.ም.

ከሌሎች ምንጮች ስለኛ - ከኢፕድ የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ግድብ ግንባታ 35 በመቶ ደረሰ ……………………////…………… የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ግድብ ግንባታ 35 ነጥብ አንድ በመቶ መድረሱን የው
ከሌሎች ምንጮች ስለኛ - ከኢፕድ የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ግድብ ግንባታ 35 በመቶ ደረሰ ……………………////…………… የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ግድብ ግንባታ 35 ነጥብ አንድ በመቶ መድረሱን የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ። የሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ የኮይሻን ግድብ ግንባታ በተመለከተ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ እስከ ነሐሴ 2012 ዓ.ም ድረስ አፈጻጸሙ 35 ነጥብ አንድ በመቶ ደርሷል። ሁለት ሺህ 160 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የኮይሻ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ በሚፈለገው የግንባታ ፍጥነት እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል። የግድቡን ግንባታ በአምስት ዓመት ተኩል ለማጠናቀቅ ውል የተገባ መሆኑን አማካሪው አስታውሰው በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ ለማጠናቀቅ በመንግስት በኩልም አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዩሮ ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የኮይሻ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት የሲቪል ስራውን ሳሊኒ በስራ ተቋራጭነት እየገነባው ይገኛል፡፡ እንደ አቶ ሞቱማ ገለፃ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት 92 በመቶ የሚሆነው ከውሃ የሚገኝ ሲሆን ይህንን ድርሻ ወደ 70 በመቶ ዝቅ ለማድረግ ከተለያዩ ታዳሽ የኃይል ምንጮች ለማሰባጠር እየተሰራ ይገኛል፡፡ መንግስት የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማስፋትና ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጉትን ኃይል ለማሟላት የኮይሻን የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫና የታላቁን የህዳሴ ግድብ ጨምሮ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተገነቡ ይገኛሉ፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/?modal=admin_todo_tour ነሐሴ 15 ቀን 2012 ዓ.ም.

ዲ.ኬ.ቲ ኢትዮጵያ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት የኮሮና መከላከያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ …………../////……………. ዲ.ኬ.ቲ ኢትዮጵያ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ሠራተኞች የሚውል ግምታቸው ከ430 ሽህ ብር በላይ የሆኑ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል፣ ሳኒታይዘር እና ሌሎች ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ፡፡ በርክክብ ሥነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ እንደገለፁት ዲ.ኬ.ቲ ኢትዮጵያ ከግድቡ ግንባታ ጀምሮ እስካሁን ድረስ ፕሮጀክቱ ላይ ለሚሰሩ ሰራተኞች የኤች አይ ቪ ኤድስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በመስራት የፋይናንስ፣ የቴክኒክና የቁሳቁስ ድጋፍ እያደረገ ነው፡፡ ዲ.ኬ.ቲ ኢትዮጵያ ከኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠር ሥራዎች በተጨማሪ ወቅታዊ ለሆነው የኮሮና ቫይረስ የመከላከያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉ በወረርሽኙ ምክንያት የፕሮጀክቱ ሥራ ተፅዕኖ እንዳይገጥመው አስጸዋፅኦ እንደሚያደርግ ገልፀዋል፡፡ “ወደ ፊትም አብረን ሰርተን ግድቡን እውን እናደርጋለን” ብለዋል፡፡ የ ዲ.ኬ.ቲ ኢትዮጵያ ተወካይ ወ/ሮ የኔነሽ ታረቀኝ በበኩላቸው ድርጅቱ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ራሳቸውን ከኤች አይ ቪ- ኤድስ እንዲጠብቁ ሰፊ ሥራ መሰራቱን አስታውሰዋል፡፡ ቀደም ሲል አብሮ ለመስራት የተጀመረውን ስምምነት በማደስና በማጠናከር በቀጣይም አብሮ ለመሥራት መታሰቡንም ገልፀዋል፡፡ 12/12/12

ተቋሙ የፕሮጀክቶችን ማማከርና የዲዛይን ዝግጅት አቅሙ እያደገ መጥቷል ………………../////………………… የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችንና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን በራስ ኃይል የማማከር አቅሙ እያደገ መምጣቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጅነሪንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ ገለፁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት ተቋሙ ከ66 እስከ 500 ኪሎ ቮልት ያሉትን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የማማከር ስራን ላለፉት 20 ዓመታት ሲያከናዉን ቆይቷል፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ አቅሙን በማሳደግ በአሁኑ ሰዓት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ግንባታ የማማከር ስራ በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አቶ አንዱዓለም ተናግረዋል፡፡ የኢንጅነሪንግ ቢሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በማመንጫ ጣቢያዎች ላይ በራስ ኃይል የማማከር ስራን ያከናወነው የአባ-ሳሙኤል የዉሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የዕድሳት ስራን ሲሰራ እንደነበር ያስታወሱት አቶ አንዱዓለም ተቋሙ በአሁኑ ሰዓት የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን የማመከር ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ የኢንጂነሪንግ ቢሮው በአዲስ አበባ ቀላል ባቡርና ኢትዮ -ጂቡቲ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ፕሮጀክት እንዲሁም የታላቁ ህዳሴ ግድብ - ደዴሳ - ሆለታ ባለ 500 እና 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክት ጨምሮ እስከ አሁን በሃገሪቱ ተገንብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ በሚገኙት በርካታ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ላይ በማማከር ስራ ላይ እየተሳተፈ ነው ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አንዱዓለም ገለፃ ተቋሙ በባለቤትነት ከሚያከናዉናቸው ፕሮጀክቶች በተጨማሪ በግል አልሚዎች የሚከናወኑ ፕሮጀክቶችን በማማከር ለተቋሙ ገቢ በማስገኘት ላይ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ተቋሙ ከ25 በላይ የሚሆኑ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር፣ ማከፋፈያ ጣቢያ እና ሌሎች ፕሮጀክቶችን በራስ ኃይል የማማከር ስራዎች በማከናወን ላይ እንደሚገኝም አቶ አንዱዓለም ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ አንዱዓለም ገለፃ ለአብዛኛው ፕሮጀክቶች አማካሪዎች የሚቀጠረው ከውጭ ሃገር በውጪ ምንዛሬ ነበር፡፡ ይሁንና ተቋሙ በራስ ኃይል የፕሮጀክቶችን የማማከር ስራ ማከናወኑ ለአማካሪ ቅጥር የሚወጣውን የውጭ ምንዛሪ በከፍተኛ ደረጃ ከማስቀረት በተጓዳኝ የዉጪ አማካሪ ለመቅጠር በሚደረገው ሂደት የሚፈጠረውን መጓተት በማስቀረት ፕሮጀክቶች በመርሃ ግብራቸው እንዲጀመሩ እና ጥራታቸውን ጠብቀው እንዲከናወኑ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል፡፡ የተቋሙ ኢንጅነሪንግ ቢሮ ከማማከር አገልግሎቱ የሚገኘዉን ልምድ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም በሃገር ውስጥና ከሃገር ዉጪ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን በብቃት በማማከር ለተቋሙ ተጨማሪ ገቢ ለማምጣት ብሎም ለሃገር ተጨማሪ የዉጪ ምንዛሪ ምንጭ ለማስገኘት እየሰራ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡ 268 ሰራተኞችን በመያዝ የፕሮጀክቶችን ግንባታ የማማከር ስራ በማከናወን ላይ የሚገኘው ቢሮው እንደ እንጦጦ እና አንድነት ፓርክ በመሳሰሉ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ላይ የተለያዩ ሙያዊ ድጋፎችን በማድረግ የራሱን አሻራ ማሳረፍ ችሏል ነው ያሉት ሥራ አስፈፃሚው፡፡ ተቋሙ በራስ ኃይል ፕሮጀክቶችን ከማማከር በተጨማሪ የዲዛይን ስራዎችን ማከናወን በመቻሉ ለአዋሽ-ወልዲያ የባቡር መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክት ዲዛይን ክለሳ ስራ ሊያወጣው የነበረውን 22 ሚሊዮን ዶላር ማዳን መቻሉን ነው ሰራ አስፈፃሚው የተናገሩት፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ከ10 በላይ የሚሆኑ የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ዲዛይን ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ለስራው የሚያግዙ ዘመናዊ የቴክኖሎጅ መሳሪያዎች አቅርቦት እጥረት፣ የሰራተኛውን አቅም የሚያሳድጉ ስልጠናዎች አለመመቻቸት እና የባለሙያ እጥረት የማማከር ስራዎችን በተፈለገው መልኩ ለማከናወን ተግዳሮት መሆናቸውንና የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡ 12/12/12

የግድቡ የሲቪል ሥራ አጠቃላይ አፈፃፀም 88 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል ………………///…….. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሲቪል ሥራዎች አጠቃላይ አፈፃፀም 88 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ ዋ
የግድቡ የሲቪል ሥራ አጠቃላይ አፈፃፀም 88 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል ………………///…….. የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሲቪል ሥራዎች አጠቃላይ አፈፃፀም 88 ነጥብ 5 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ ገለጹ። ስራ አስኪያጁ እንደገለጹት አብዛኛው ስራው የተጠናቀቀውን የኮርቻ ግድብ ግንባታ ጨምሮ የዋናው ግድብ ሥራ፣ የጎርፍ ማስተንፈሻና የኃይል ማመንጫ ቤቶች ግንባታን የሚያጠቃልለው የግድቡ የሲቪል ሥራ አጠቃላይ አፈፃፀም 88 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል፡፡ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራዎች 46 በመቶ፣ የብረታ ብረት ሥራዎች ደግሞ 33 በመቶ ላይ በመድረሳቸው አጠቃላይ የግንባታ ፕሮጀክቱን ሥራ 75 በመቶ ላይ መድረሱን ኢንጂነር ክፍሌ አስታውቀዋል፡፡ ነሐሴ 09 ቀን 2012 ዓ.ም.

photo content

በ2012 በጀት ዓመት ከ15 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ተችሏል ………….///////…………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2012 በጀት ዓመት 15,192 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ በጽ/ቤቱ የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ቴክኒካል ድጋፍ እና አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ሰናይ ገ/ጊዮርጊስ እንዳስታወቁት በበጀት ዓመቱ 16,165 ነጥብ 48 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ዕቅድ ተይዞ 15,192 ነጥብ 11 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ተችሏል፡፡ አፈፃፀሙም የእቅዱ 94 በመቶ እንደተሳካ ያሳያል ነው ያሉት አቶ ሰናይ፡፡ እንደ አቶ ሰናይ ገለፃ በበጀት ዓመቱ የተጠበቀውን ያህል የኃይል ጥያቄ አለመቅረቡ እና የደንበኞች የሌሊት የኃይል አጠቃቀም ዝቅተኛ መሆኑ ለእቅዱ አለመሳካት ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛል፡፡ የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ወደ ኦፕሬሽን አለመግባቱ፣ የገናሌ ዳዋ 3ኛ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በታቀደው ጊዜ ኃይል ማመንጨት አለመቻሉ እና ለጣቢያዎች የመለዋወጫ ዕቃ ባለመሟላቱ በጥገና ችግር የቆሙ የማመንጫ ዩኒቶች መኖራቸው ለእቅዱ አለመሳካት ተጨማሪ ምክንያቶች መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ በሃገሪቱ የኃይል እጥረት አለመከሰቱንም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ማመንጨት የተቻለው ኃይል ከ2011 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻፃፀር የ9.5 በመቶ ጭማሪ መኖሩን አቶ ሰናይ ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በሃገሪቱ 21 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚገኙ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ጣና በለስ፣ ግልገል ግቤ I፣ ግቤ II፣ መልካ ዋከና፣ ጢስ ዓባይ II፣ ቆቃ ፣ አዋሽ 2፣ አመርቲ ነሼ እና ረጲ የደረቅ ቆሻሻ ጣቢያ ከታቀደላቸዉ በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻላቸው ተጠቁሟል፡፡ አንዳንድ ጣቢያዎች ያመነጫሉ የተባለውን ኃይል በተለያዩ ምክንያቶች ማመንጨት ባይችሉም ጊቤ 3፣ ጣና በለስ እና ጊቤ 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በበጀት ዓመቱ ማመንጨት ከተቻለው ከፍተኛውን ኃይል ድርሻ ያበረከቱ ጣቢያዎች መሆናቸውን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡ በጣቢያዎች ላይ መደበኛ የኦፕሬሽን ሥራ ሳይስተጓጎል ከጣቢያ እስከ ብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ድረስ የኦፕሬሽን ሥራውን ማዘመን የሚያስችሉ ተግባራት ሲከናወኑ እንደነበርም ተገልጿል፡፡ እንደ አቶ ሰናይ ገለፃ የኦፕሬሽን ስራዉን ሁልጊዜ አስተማማኝ ለማድረግ የዩኒቶች መደበኛ ዓመታዊና ልዩ ልዩ ጥገና በተጨማሪ የመሳሪያዎች ጥገና የብልሽት ቅድመ መከላከል የፍተሻ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ በግድቦች ላይ አስተማማኝ ውሃ እንዲኖርና የውሃ እጥረት እንዳይከሰት ለማድረግ የዕለት ተዕለት የግድቦች የውሃ አስተዳደር ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ሲሰራ እንደነበርና በዚህም ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን አቶ ሰናይ ተናግረዋል፡፡ በግድቦች አካባቢ ከሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር መልካም ግንኙነት እንዲኖር ለማድረግም በተለያየ ጊዜ የሚያነሷቸውን የተለያዩ የልማት ጥያቄዎችን የሚመልሱ የተለያዩ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በ2013 በጀት ዓመት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ደንበኞች አገልግሎት የሚውል 17,307 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት እቅድ መያዙን ከጀኔሬሽን ኦፕሬሽን ስራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ በበጀት ዓመቱ የጣቢያዎችን ዩኒቶች ሥራ ሊያስቆሙ የሚችሉ የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ላይ እና የጣቢያዎችን የኦፕሬሽን፣ ጥገናና ፍተሻ ሥራዎች ላይ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡ ነሐሴ 08 ቀን 2012 ዓ.ም.

የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ ውሃ ሲለቀቅ የሚያሳይ ቪዲዮ

የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ ውሃ መለቀቅ ተጀመረ …………………/////………………………….. የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በክረምቱ ዝናብ እየሞላ በመምጣቱ ውሃ መለቀቅ ተጀምሯል፡፡
የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ ውሃ መለቀቅ ተጀመረ …………………/////………………………….. የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በክረምቱ ዝናብ እየሞላ በመምጣቱ ውሃ መለቀቅ ተጀምሯል፡፡ ከግድቡ በየደረጃው የሚለቀቀው ዉሃ በታችኛው ተፋስስ ላይ ቅፅበታዊ ጎርፍ እንዳይከሰት ለመቆጣጠር ነው፡፡ ወደ ግድቡ የሚገባውን ውሃ ሁሉ እንደመጣ ላለመልቀቅና የተመጠነ የውሃ ፍሰት እንዲኖር በማድረግ ሊያጋጥም የሚችለውን ጉዳት ለማስቀረት ከአደጋ መከላከልና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽንና ከደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ጋር በመሆን በተፋሰሱ የታችኛው ክፍል የተለያዩ ስራዎች ሲሰሩና መልዕክቶች ሲተላለፉ ቆይተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ግድቡ በተከታታይ በቀን በአማካይ 40 ሳ.ሜ. ከፍታ ያለው ውሃ እየያዘ በመሆኑ በመካከለኛ ከፍታ ላይ የሚገኙ የግድቡን ውሃ ማስተንፈሻዎች በመክፈት ትላንት ከእኩለ ቀን ጀምሮ ለስድስት ሰዓታት በሰከንድ ወደ 2ሺህ ሜትር ኪዩብ ውሃ መልቀቅ ተጀምሯል፡፡ ዛሬም በተመሳሳይ ውሃ የመልቀቅ ሂደቱ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ወደግድቡ የሚገባውን ውሃ ታሳቢ ያደረገ ተጨማሪ ውሃ ሊለቀቅ ስለሚችል አሁንም በኦሞ ጊቤ የታችኛው ተፋሰስ የሚገኙ ነዋሪዎች ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንዲችሉ የአካባቢው አመራሮች ተገቢውን መልዕክት እንድታስተላልፉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጥሪውን ያቀርባል፡፡ ነሐሴ 06 ቀን 2012 ዓ.ም.

የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ የ2012 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ገመገሙ …………………../////………………. የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ የ2012 በጀት ዓመት
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ የ2012 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ገመገሙ …………………../////………………. የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማቱ የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የ2013 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ተወያዩ፡፡ በውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር በተካሄደው የአፈፃፀም ግምገማና የዕቅድ ውይይት ላይ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በተጨማሪ የውሃ ልማት ኮሚሽን፣ የውሃ ልማት ፈንድ ጽ/ቤት፣ የኢትዮጵያ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት፣ የመስኖ ልማት ኮሚሽን፣ የተፋሰሶች ልማት ባለስልጣን፣ የብሔራዊ ሜትርዎሎጂ ኤጄንሲ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለስልጣን እና የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሕዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት መሥሪያ ቤቶች እቅድ አፈጻጸምና የ2013 በጀት ዓመት እቅዶች ቀርበው ግምገማና ውይይት ተካሂዷል፡፡ የግምገማና ውይይት መድረኩን የመሩት የውሃ፣መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ባለፈው በጀት ዓመት በዘርፉ የተከናወኑ ሥራዎችን በዝርዝር ከገለጹ በኋላ ከሕዝቡ ፍላጎት አንጻር በቀጣዩ ጊዜ ተግቶ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ የታላቁ ሕዳሴ ግድብን በሚመለከት በቀጣይ ዓመት ኃይል ማመንጨት እንደሚጀመር፣ የአስራ አንድ ተርባይኖች ተከላ እንደሚከናወንና ሁለተኛው ዓመት የውሃ ሙሊት ለማከናወን ሥራዎች እንደሚሠሩ ጠቁመዋል፡፡ ከህዳሴው ግድብ ግንባታ ጎን ለጎንም ወደፊት ግድቡ ሲጠናቀቅ በልዩ ልዩ ዘርፎች ሊሠሩ ስለሚገባቸውም ጉዳዮች በመንግሥት ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ እንደሆነ መናገራቸውን ከሚኒስቴሩ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ችግኝ እንዲያፈሉ ይደረጋል- በተቋሙ የጄኔሬሽን ኦፕሬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ አንዳርጌ እሸቴ .....................///...............
ከቀጣይ ዓመት ጀምሮ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ችግኝ እንዲያፈሉ ይደረጋል- በተቋሙ የጄኔሬሽን ኦፕሬሽን ስራ አስፈፃሚ አቶ አንዳርጌ እሸቴ .....................///................. በጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የሠራተኞች መኖሪያ ካምፕ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡ በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ላይ የተሳተፉት የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዳር እሸቴ እንደተናገሩት በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ስራ የሀገሪቱን የውሃ ሀብት በማሻሻል ረገድ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ የአርንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ በአፈር መሸርሸር ምክንያት ደለል ወደ ውሃ ኃይል ማመንጫ ግድቦች እንዳይገባ በማድረግ ጣቢያዎቹ ለበርካታ ዓመታት እንዲቆዩ ያግዛል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ አንዳርጌ ገለፃ በእያንዳንዱ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከ1000 በላይ ችግኞች ለመትከል እቅድ ተይዞ እየተሰራ ነው፡፡ በቀጣይ ዓመትም በሁሉም ማመንጫ ጣቢያዎች ኃይል ሀገር በቀል ችግኞችን ለማፍላት እቅድ መያዙን አቶ አንዳርጌ ገልፀዋል፡፡ ይህም ለአካባቢው ስነ- ምህዳር ተስማሚ የሆነ ችግኝ ለመትከል ያግዛል ነው ያሉት፡፡ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ላይ ከዚህ በፊት ችግኝ የመትከል ስራ ሲከናወን የነበረ ቢሆንም በመንከባከብ ስራው ላይ ግን ክፍተት በመኖሩ የተተከሉ ችግኞች እንዲጸድቁ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ነው የተናገሩት፡፡ በማመንጫ ጣቢያ ሠራተኞች ከሚከናወን የችግኝ ተከላ ስራ በተጨማሪ በአንዳንድ ጣቢያዎች አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ የአረንጓዴ አሻራ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም አስታውቀዋል፡፡

አዎ ዓባይ የእኔም፣የአንተም፣ የአንቺም፣ የእኛም የሁላችም ነው!! ኢትዮጵያ በተለያዩ የተፈጥሮ ሀብቶች የተቸረች ውብ ሀገር ብትሆንም ለበርካታ ዘመናት በራሷ የተፈጥሮ ሀብት ከመልማትና ከመጠቀም ይልቅ የበይ ተመልካች ሆና በድህነት አረንቋ ውስጥ እንድትኖር የተፈረደባት መሆኑን በድፍረት መጥቀስ ይቻላል፡፡ የቅኝ ገዥ ሃገራት ከ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ በዓባይ ወንዝ ላይ ዋነኛ ተጠቃሚ ለመሆን ከፍተኛ ጉጉት ያሳደሩ በመሆኑ ከጉያዋ ፈልቆ በሚፈሰው ሃብት ላይ አንዲት ብርጭቆ ውሃ እንዳትጠቀምና እንዳትለማ የሚያደርግ የተጠቃሚነት መብቷን የጣሰና የከለከለ በቅኝ ግዢ አስገዳጅ ውሎች አማካኝነት ባላመነችበትና ባልተሳተፈችበት ጉዳይ በወንዙ ላይ ተጠቃሚ እንዳትሆን ሲደረግ እንደነበር በማስረጃነት ማንሳት ይቻላል፡፡ በተለይ በወንዙ ላይ የተደረጉ ስምምነቶችን ስንመለከት የግብጽና የሱዳንን ስም ይያዝ እንጂ በዋናነት የቅኝ ገዢዎች የእጅ አዙር ተጠቃሚነትን ታላሚ ያደረገ መሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ይህም ሲባል የቅኝ ገዥ ሃገራት በናይል ወንዝ ዙሪያ ሲያከናውኑዋቸው የነበሩት ስምምነቶች የራሳቸውን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ከማጎልበት የመነጨ እንጂ ለቅኝ ተገዥ ሃገራት ጥቅም ሲባል የተደረገ አይደለም፡፡ ግብፅና ሱዳን የእንግሊዝ ቅኝ ተገዢ ሃገራት ቢሆኑም በወንዙ ላይ ያላቸውን ተጠቃሚነት ስንመለከት ከፍተኛውን ድርሻ እንግሊዝ ከቅኝ ግዛት በኋላ ደግሞ ግብፅ ቀጥሎ ሱዳን ብቻ እንደነበሩ ስንመለከት ተካሄዱ የተባሉት ስምምነቶች ሁሉ ምን ያህል አግላይና ከልካይ እንደነበሩ ከመጠቆሙም በላይ ኢትዮጵያ በራሷ የተፈጥሮ ሀብት እንዳትጠቀምና እንዳትለማ ይደረግ የነበረውን ሴራ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡ ለዚህም እንደማሳያ በዓባይ ወንዝና ገባሮቹ ላይ እ.ኤ.አ ከ1891 እስከ 1959 ድረስ የተከናወኑ የተለያዩ ስምምነቶችን ማንሳት ይቻላል፡፡ እ.ኤ.አ በ1891 በጣልያንና በእንግሊዝ የተደረገው ስምምነት ይዘትም ጣልያን ኤርትራን በያዘችበት ወቅት በአትባራ ወይም ተከዜ ወንዝ ላይ የግብፅን ጥቅም ላለመንካት ሲባል ግድብ እንደማትሰራ ከእንግሊዝ ጋር የተዋዋለችበት መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ሌላው በ1901 ከደቡባዊ አስመራ ተነስቶ አትባራ ወንዝን የሚገብርና በመጨረሻም ወደ ዓባይ የሚቀላቀል ጋሽ/መረብ ወንዝን በማስመልከት በእንግሊዝና በጣልያን መካከል የተከናወነ ሲሆን ይዘቱም ኤርትራ በመልካም የጉርብትና መርህ ላይ ተመስርታ በወንዙ ላይ የመጠቀም መብት እንዳላት እውቅና የሚሰጥ በመሆኑ ከሌሎች የቅኝ ገዢዎች ስምምነቶች በተሻለ ሁኔታ ፍትሀዊና የአሁኗ ኤርትራን መብት የማይጎዳ ነው ተብሎ ይታሰባል፡፡ እ.ኤ.አ በ1902 የሱዳን ቅኝ ገዥ በነበረችው በእንግሊዝ እና በኢትዮጵያ መካከል የተከናወነ ስምምነት እንደነበር ይጠቀሳል፡፡ በዚህ ስምምነት ላይ ኢትዮጵያ ሙሉ ለሙሉ ውሃውን የሚያስቀር ግድብ መስራት እንደማትችል ይጥቀስ እንጅ ውሃውን ገድባ መጠቀም እንደማትችል የሚገልፅ አይደለም፡፡ በዚህ ስምምነት ላይ ግብፆች እንደሚያነሱት እርባና ቢስ ክርክር ሳይሆን የስምምነቱ ይዘት የሚለው ውሃውን ይዞ ማስቀረት (Arrest or Block) ማድረግ ወይም ሙሉ በሙሉ ማስቆም እንደማይቻል እንጂ ከማንኛውም የተጠቃሚነት ዓይነት የሚከለክል ስምምነት አለመሆኑ እሙን ነው፡፡ ይህም አሁን ሃገሪቱ እየተከተለችው ላለው ፍትሃዊና ምክንያታዊ ተጠቃሚነትን የሚያጎላ ስምምነት ነው ማለት ይቻላል፡፡ በተጨማሪም የ1906 የቤልጂየም እና የእንግሊዝ ስምምነት ማንሳት ይቻላል፡፡ በዚህ ስምነት ላይ ቤልጂየም (ኮንጎን በመወከል) እና በእንግሊዝ መካከል የተከናወነ ሲሆን የኮንጎ መንግስት ከሰምሊኪ ወይም ከልሳንጎ ወንዝ ወደ አልበርት ሀይቅ የሚወርደውን ውሀ ከሱዳን መንግስት ጋር ሳይስማማ ውሀውን የሚቀንስ ስራ ለመስራት ለማንም ፈቃድ እንዳይሰጥ የሚል ነበር፡፡ ሌላው በ1929 በእንግሊዝ እና በግብፅ መካካል የተከናወነውን ስምምነት ስንመለከት ደግሞ ሱዳንን የተወሰነ ድርሻ ብቻ እንዲሰጣት በማድረግ ግብጽና እንግሊዝ ብቻቸውን የናይል ወንዝ ተጠቃሚ እንደሆኑ በተለይም ግብፅ በናይል ወንዝ ላይ በብቸኝነት የመወሰንና ድምፅን በድምፅ የመሻር ስልጣን (Veto Power) እንዳላትና ካለምንም ጣልቃ ገብነት የሚቀጥል መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ በ1959 የተደረገው የግብጽና የሱዳን ስምምነትን ስንመለከትም በዋናነት የናይል ውሃ የግብጽ እንደሆነ እውቅና የሚሰጥ ስምምነት ነበር ማለት ይቻላል፡፡ ይህም ሲባል 55.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ለግብጽ፣ 18.5 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ ለሱዳን በመስጠት ቀሪው 10 ቢሊዮን ኩቢክ ሜትር ደግሞ የአከባቢው የኢኮሎጂካዊ ሚዛን ለመጠበቅ ወደ እንዲተን በመስማማት ኢትዮጵያ አንዲት ብርጭቆ ውኃ እንኳን የምትጠቀምበት መብት ያላገኘችበት አስገራሚና አሳዛኝ ውል ነበር፡፡ ይህ ስምምነት ሌሎች ተፋሰስ ሀገራትን ያገለለና ፍፁም የሁለትዮሽ ውል ስለነበር በኢትዮጵያ በኩል ተቀባይነት እንደሌለው ተደጋግሞ ተገልጿል፡፡ እንግዲህ በዚህ የፍርደ ገምድል ስምምነት መሰረት ኢትዮጵያ በራሷ የተፈጥሮ ሀብት መልማት እንዳትችልና እንዳትጠቀም የተለያዩ ጫናዎችና እገዳዎች ቢደረግም ይህን የዘመናት ቁጭት በራስ አቅም ገንብቶ እውን ለማድረግ ቆርጦ የተነሳው የአሁኑ ትውልድ ቀደም ሲል ይደረጉ የነበሩ ክልከላዎችና እገዳዎች ሳይበግሩት በራስ የገንዘብ አቅምና ጉልበት እንዲሁም እውቀት የግድብ ስራውን ከጀመረ እነሆ ዘጠኝ ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ እስካሁን በነበረው ሂደት ምንም አንኳን ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ያጋጠሙት ቢሆንም ያሰበውንና የጀመረውን ነገር ከዳር ሳያደርስ መተኛት የማይወደው ይህ ትውልድ ፈተናዎቹን ተቋቁሞ የዘመናት ቁጭቱን በደስታ ቀይሮ ድሃ እያሉ ለተሳለቁበትና የልማት ጥሙን ለመወጣት የድል ብስራት ዜናውን ‹‹ሀ›› ብሎ ማሰማት ጀምሯል፡፡ ታሪክን መስራት ከአባቱ የወረሰው ይህ ትውልድ የአደራ ቃሉን በብርቱ ለመወጣትና ታሪክ ሠሪነቱን ዳግም በዓለም አደባባይ ለማስመስከር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ህያው ምስክር እንደሚሆን የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ በተለይም ቀጣዩ ትውልድ የአባይን የዘመናት ቁጭት እንዳይወርስ ‹‹ቁጭት በእኔ ይብቃ›› በሚል ከፍተኛ ወኔ አባይን በሃገሩ ዋል አደር ብሎ ለሚሰነብትበት ማረፊያ ጎጆ ቀልሶ አባይን እንደሰው ‹‹ቤት ለእንግዳ›› ብሎ ‹‹እንቦሳ እሰር›› ሊባል ከጫፍ መድረሱ ዛሬም እንደጥንቱ ታሪክ ሠሪ ትውልድ ስለመሆኑ አንዱ ማሳያ ነው፡፡ በመጨረሻም ለባዕዳን ሃገር የዘመናት ሲሳይ የነበረው የአባይ ውሃን ከ‹‹ዓባይ ዓባይ ያገር ሲሳይ›› የቁጭት እንጉርጉሮ ወደ ‹‹ዓባይ ዓባይ የእኛም ሲሳይ›› የድል ዜማነት ለመቀየር የተተባበረ ክንዳችን ዓባይ ላይ ለማሳረፍ የሚከለክለን አንዳችም ነገር የለምና ዛሬም እንደትናንቱ በምንችለው ነገር ሁሉ ድጋፋችን አጠናክረን በመቀጠል አዲስ ታሪክ ለመፃፍ እንነሳ በማለት ጽሁፌን በዚሁ እቋጫሁ፡፡ አዎ ዓባይ የእኔም፣ የአንተም፣ የአንቺም፣ የእኛም በአጠቃላይ የሁላችንም ነው!!፡፡ እንደጀምርነው እንጨርሰዋለን !!

photo content

ከግድቡ የሚለቀቀዉ ዉሃ ድንገተኛ የጎርፍ መጥለቅለቅ እንዳይከሰት ለመቆጣጠር ያግዛል ............./////................... የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ እየሞላ በመምጣቱ ውሃ በየደረጃው ለመልቀቅ የሚያስችል የሙከራ ስራ ተከናውኗል፡፡ ከግድቡ የሚለቀቀው ዉሃ ወደፊት በታችኛው ተፋሰስ ላይ ጎርፍ እንዳይከሰት ለመቆጣጠር እና ውሃውን በተመጠነ መልኩ በመልቀቅ በክረምቱ መጨረሻ ላይ ግድቡ ሙሉ እንዲሆን ለማድረግ በማስፈለጉ እንደሆነ የጣቢያው ስራ አስኪያጅ አቶ ሃብታሙ ሰሙ ገልፀዋል፡፡ ውሃ ከግድቡ በየደረጃው እንዲለቀቅ መደረጉ በተፋሰሱ ውስጥ የጎርፍ መቆጣጠር ስራ ለማከናወን እንደሚያግዝም ጠቁመዋል፡፡ ግድብ የመጣውን ጎርፍ ሁሉ እንደመጣ ላለመልቀቅና የተመጠነ የውሃ ፍሰት እንዲኖር ለማድረግም በየጊዜው እየተቆጣጠሩ መልቀቅ ክረምቱ ሲጠነክር ሊከሰት የሚችለውን ጎርፍ ለመቆጣጠር እንደሚያግዝ አስረድተዋል፡፡ እንደ አቶ ሃብታሙ ገለፃ ግድቡ መያዝ ከሚችለው 15 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ውሃ ውስጥ 12 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ውሃ የያዘ ሲሆን በሴኮንድ በአማካኝ 800 ሜትር ኪዩብ ውሃ ለመልቀቅ እቅድ ተይዟል፡፡ ግድቡ ባለፈው ዓመት ህዳር ወር ከባህር ጠለል በላይ 882 ሜትር ላይ በመድረስ ከፍተኛ ውሃ መያዝ የቻለ ቢሆንም አሁን ላይ ግን ከዚህ መጠን ጋር ተመሳሳይ ውሃ መያዙን ተናግረዋል፡፡ ይህም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከሦስት ወር አስቀድሞ ከባህር ጠለል በላይ 892 ሜትር ላይ በመድረስ ሊሞላ እንደሚችል ያመለክታል፡፡ ውሃው ከአሁኑ ካልተለቀቀ ነሐሴ 4 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ሙሉ በሙሉ ሊሞላ እንደሚችልም ስራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ ግድቡ አሁን ሳይለቀቅ ቆይቶ ከሞላ በኋላ የሚለቀቅ ከሆነ ከላይኛው የጊቤ ተፋሰስ የሚመጣውን ጎርፍ ሁሉ ለመልቀቅ ስለሚያስገድድ በታችኛው ተፋሰስ ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ ሊያስከትል ይችላል ብለዋል፡፡ ይሁንና የግድቡ ውሃ በየቀኑ እየጨመረ ስለሚሄድ ውሃ የመልቀቅ ሂደቱን ቀስ በቀስ መጥኖ በማከናወን ከግድቡ በታችኛው ተፋሰስ በሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ አደጋ እንዳያስከትል እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ ግድቡ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ውሃ ሲለቅ የመጀመሪያው ሲሆን የውሃ መልቀቅ ሂደቱ እስከመቼ ሊቆይ እንደሚችል የታወቀ ነገር የለም፡፡ ሐምሌ 29 ቀን 2012 ዓ.ም