es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 539 suscriptores, ocupando la posición 8 340 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 161 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 539 suscriptores.

Según los últimos datos del 28 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 1, y en las últimas 24 horas de -4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 24.98%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.34% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 882 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 539 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 8.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 29 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 539
Suscriptores
-424 horas
-147 días
+130 días
Archivo de publicaciones
photo content
+9

ሁለቱ ተቋማት በስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ ………///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮ - ጅቡቲ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን አመራሮች በተቋማቱ የጋራ ጉዳዮች ላይ የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል። ውይይቱ በሁለቱ ተቋማት መካከል የመግባቢያ ስምምነት ከተፈረመ በኋላ የታዩ ለውጦችና መፈታት ያለባቸው ቀሪ ጉዳዮች ላይ ለመምከርና ልምድ ለመለዋወጥ ያለመ ነው። የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ የመግባቢያ ስምምነቱ ከተፈረመና በቅርበት መስራት ከተጀመረ በኋላ የባቡር የኃይል አቅርቦት መሻሻሉን ተናግረዋል። በክፍያ አሰባሰብና በታሪፍ፣ በኢነርጂ ሜትሮች ገጠማና አጋርነት በመፍጠር ረገድ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ አንስተዋል። ስትራቴጂክ አጋርነትን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን  ልምዶችን በመውሰድ የመሰረተ ልማት ስርቆትን በጋራ መከላከል በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተቋሙ በጋራ መስራት ይፈልጋል ብለዋል። የኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብዲ ዘነበ በበኩላቸው ስርቆት፣ የንብረት ውድመትና የመስመሩ በእንስሳት መዘጋት የባቡር እንቅስቃሴውን እንደሚያስተጓጉል ገልፀዋል። ይህን ችግር ለመቅረፍ ተቋማቸው የፖለቲካና የማህበረሰብ መሪዎችን ከማሳተፍ አንስቶ ከፀጥታ አካላት ጋር ተቀራርቦ የሚሰራ ተቋማዊ አደረጃጀት መፍጠሩን ተናግረዋል። የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራም በተጓዳኝ እየተከናወነ ስለመሆኑም አብራርተዋል። የሁለቱም ተቋማት አመራሮች በተነሱት ጉዳዮች ላይ አስተያየት ሰጥተዋል። በውይይቱ ማጠናቀቂያ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ  እንደተናገሩት የመሰረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል በጋራ መስራት ያስፈልጋል። የኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ችግሩን ለመፍታት ያከናወናቸውን ሥራዎች ከተቋሙ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማዛመድ ለመስራት ልምድ የወሰድንበት ነው ብለዋል። ግንዛቤ በመፍጠር፣ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ በማድረግና የመንግስት መዋቅሩን በማሳተፍ በጋራ መስራት ከተቻለ ለውጥ ሊመጣ እንደሚችል ገልፀዋል። ከውይይቱ በኋላ አመራሮቹ የተቋሙን የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ጎብኝተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

በጣቢያው የተከናወኑት የፍተሻና ጥገና ሥራዎች ከዕቅድ በላይ ኃይል ለማምረት አስችሏል ………///……. በአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የክትትል፣ ፍተሻና የጥገና ሥራዎች በአግባቡ በመከናወናቸውና የተሻለ የንፋስ ፍጥነት በመኖሩ ጣቢያው ከዕቅድ በላይ ኃይል ማምረቱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ መለሰ ሲሎ እንዳስታወቁት ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት 220 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ለማመንጨት አቅዶ 223 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት በማመንጨት ከዕቅድ በላይ አሳክቷል፡፡ የተመረተው ኃይል ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ቅናሽ ቢያሳይም በስድስት ወራት ለማምረት ከታቀደው አንጻር ግን የ3 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት ብልጫ እንዳለው ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት በጣቢያው የተለያዩ የጥገና ሥራዎች መከናወናቸውን የጠቀሱት አቶ መለሰ ሁሉም መደበኛና ድንገተኛ ጥገናዎች በራስ አቅም መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ከ82 በላይ የንፋስ ተርባይንና ጀነሬተሮች ላይ ከተከናወነው የጥገና ሥራ በተጨማሪ በ230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ፣ በዩኒት ትራንስፎርመሮች እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት ማስተላለፊያ መስመር ላይ የክትትልና ፍተሻ ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡ በጣቢያው የብሬከር ችግር ሲከሰት በአጭር ጊዜ ጠግኖ ወደ ሥራ ማስገባት የሚችል ብቁ የጥገና ባለሙያ መኖሩንም ነው ሥራ አስኪያጁ የጠቆሙት፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 06 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም በሜዲካል ዶክተር የስራ መደብ ባለሙያዎችን በቋሚነት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው ጥር 02 ቀን 2016 ዓ.ም የተሰጠውን ፈተና መውሰዳችሁ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በተ.ቁ 1 ስማቸው የተገለጸው አመልካች ከየካቲት 06 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው ዋናው መ/ቤት የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀርበው የቅጥር ፎርም እንዲሞሉ እናሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 06 ቀን 2016 ዓ.ም

...

...

...

photo content

ውሳኔ ካገኙ የፍትሐብሔር ክርክሮች ከ229 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ………///…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፌዴራልና በክልል ፍርድ ቤቶች ክርክር ካካሄደባቸው የፍትሐብሔር መዝገቦች 229 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ማዳን መቻሉን የተቋሙ የህግ መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ እንዳታወቁት ባለፉት 6 ወራት በተለያየ ደረጃ ያሉ 329 የፍትሐብሔር፣ የወንጀል እና የሥራ ክርክር መዝገቦች ላይ በፌዴራልና በክልል ፍርድ ቤቶች ክርክር እና ክትትል ተደርጓል፡፡ ክርክር ሲካሄድባቸው ከቆዩት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር የገንዘብ መጠን ያላቸው 190 የፍትሐብሔር ጉዳይ የክስ መዝገቦች ውስጥ በ45ቱ ላይ ውሳኔ መሰጠቱን ገልፀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ውሳኔ ከተሰጠባቸው የፍትሐብሔር መዝገቦች መካከል 13ቱ ሙሉ በሙሉ፣ አራቱ በአመዛኙ፣ ሦስት መዝገቦች ደግሞ በከፊል ለተቋሙ በማስወሰን 229 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ማዳን ተችሏል፡፡ ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ ቀሪ 25 መዝገቦች እንደገና እንዲታዩ ቀጥሎ ላለው ፍርድ ቤት ይግባኝ መባሉን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል፡፡ መምሪያው ከያዛቸው 67 የሥራ ክርክር መዝገቦች መካከል በግማሽ ዓመቱ በ28 መዝገቦች ላይ ውሳኔ ሲሰጥ 22 መዝገቦች ሙሉ በሙሉ ለተቋሙ፤ 5 መዝገቦች ደግሞ ለከሳሾች መወሰኑን ነው አቶ መርክነህ የተናገሩት፡፡ ለከሳሾች በተወሰኑ የሥራ ክርክር መዝገቦች ላይ እንደሁኔታቸው ይገባኝ የቀረበባቸው ጉዳዮች መኖራቸውን ጠቁመዋል፡፡ ከፍትሐብሔርና የሥራ ክርክር መዝገቦች በተጨማሪ 72 የወንጀል መዝገቦች ላይ ክትትል ተደርጓል ያሉት ዳይሬክተሩ በስድስት መዝገቦች በቀረቡ ተከሳሾች ላይ የገንዘብ ቅጣትና እስከ ስድስት ዓመት የሚደርስ ፅኑ እስራት መተላለፉንም አስታውቀዋል፡፡ አቶ መርክነህ እንዳሉት የወንጀል ክስ መዝገቦቹ በተቋሙ ንብረት ላይ በተፈፀሙ የመሰረተ ልማት ስርቆት እና የእምነት ማጉደል ተግባራት ላይ ያተኮሩ ናቸው፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

ባለፉት ስድስት ወራት ከ 9 ሺህ ስድስት መቶ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኢነርጂ ተመርቷል ……….///………. በ2016 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት 9 ሺህ 627 ነጥብ 4 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ መመረቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማመንዎች ኦፐሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የዕቅድ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ሽፈራው እንዳስታወቁት በ2016 የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት 10 ሺህ 788 ነጥብ 39 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማምረት ታቅዶ 89 ነጥብ 2 በመቶውን ማሳካት ተችሏል፡፡ የኢነርጂ ምርቱ ከዕቅዱ አንፃር ቅናሽ ቢያሳይም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ምርት ጋር ሲነጻፀር የ11 ነጥብ 6 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን ሥራ አስኪያጇ ጠቁመዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የታቀደውን ኃይል ለማምረት ከሞላ ጎደል ዝግጁ ቢሆኑም በኃይል ተጠቃሚዎች በኩል የታቀደውን ያህል ባለመጠቀማቸው ምክንያት አፈፃፀሙ መቀነሱን ተናግረዋል፡፡ በግማሽ ዓመቱ ማምረት ከተቻለው ውስጥ 9 ሺህ 247 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 96 ነጥብ 1 በመቶ ከውሃ፣ 3 መቶ 46 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 3 ነጥብ 6 በመቶ ከነፋስ እና 33 ነጥብ 1 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም 0 ነጥብ 3 በመቶ ከተርማል የተመረተ መሆኑን ሥራ አስኪያጇ አስረድተዋል፡፡ እንደ ወ/ሮ ጥሩወርቅ ገለፃ ህዳሴ፣ ገናሌ ዳዋ፣ መልከ ዋከና፣ አመርቲ ነሼ፣ አዋሽ 3ኛ እና ቆቃ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲሁም፣ አዳማ 1 እና አዳማ 2 የንፋስ ማመንጫ ጣቢያዎች ከዕቅድ በላይ ያመነጩ ሲሆን ጣና በለስ እና ፊንጫ ማመንጫ ጣቢያዎች ደግሞ በአንፃሩ ዝቅተኛ አፈፃፀም የነበራቸው ጣቢያዎች ናቸው፡፡ ግልገል ጊቤ I፣ II እና III ማመንጫ ጣቢያዎች ደግሞ የዕቅዳቸውን ከ90 በመቶ በላይ ማሳካት ከቻሉ ጣቢያዎች መካከል ተጠቃሾች እንደሆኑም አንስተዋል፡፡ በስድስት ወራት ውስጥ ከተመረተው ኃይል ጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ34 ነጥብ 8 በመቶ ትልቁን ድርሻ ሲያበረክት በሁለት ዩኒት ኃይል እያመረተ የሚገኘው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ደግሞ በ9 ነጥብ 1 በመቶ ተከታዩን ድርሻ እንደሚወስድ ነው የተናገሩት፡፡ የጣቢያዎች ኃይል የማመንጨት ዝግጁነት አፈፃፀም 96 በመቶ እንደነበር ያነሱት ሥራ አስኪያጇ በስድስቱ ወራት የተመዘገበው ከፍተኛው የኃይል ጭነት 3 ሺህ 523 ነጥብ 36 ሜጋ ዋት እንደነበር ጠቅሰዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የታቀደውን ኢነርጂ ለማሳካት በቀጣይ ወራት ሙሉ የማመንጨት አቅምን መጠቀም የሚያስችሉ ሥራዎች እንደሚከናወኑ አስገንዝበዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 05 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይድ ኬር አድሚኒስትሬቲቭ አሲስታንት 1ኛ የስራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ታህሳስ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሁፍ እና የቃል ፈተና (ኢንተርቪው) በተመሳሳይ ቀን ስለሚሰጥ ይህንን አውቃችሁ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 04 ቀን 2016 ዓ.ም

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይድ ኬር አድሚኒስትሬቲቭ አሲስታንት 1ኛ የስራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ታህሳስ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቻይድ ኬር አድሚኒስትሬቲቭ አሲስታንት 1ኛ የስራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ታህሳስ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች የካቲት 7 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት ማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሁፍ እና የቃል ፈተና (ኢንተርቪው) በተመሳሳይ ቀን ስለሚሰጥ ይህንን አውቃችሁ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 04 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

photo content
+9

የሀገራችንን ሀብቶች በአግባቡ ለመጠቀም ለሰላም ትኩረት መስጠት ይገባል - የተቋሙ ሠራተኞች ...///... ኢትዮጵያ ያሏትን ፀጋዎች ወደ ምንዳ መለወጥ እንድትችል ለሰላም ትኩረት መስጠት እንደሚገባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ገለፁ። የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች  ከዕዳ ወደ ምንዳ" በሚል መሪ ሃሳብ በተቋሙ አዳራሽ ውይይት አካሒደዋል። በውይይቱ ላይ ሰነድ ያቀረቡት በተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ አስቸጋሪ ፈተናዎችን በመጋፈጥ አንድነቷን አስጠብቃለች። ሀገር በቀል የሆኑ የኢኮኖሚ ፖሊሲ በማመንጨት ወደ ትግበራ መገባቱንም ነው አቶ ደመረ የገለፁት። ኢትዮጵያ ሊለማ የሚችል የኢነርጂ፣ ማዕድን፣  ውሃ እና መሬት ያላት መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስፈፃሚው ይህን እምቅ ፀጋ ወደ ሀብት ለመቀየር የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባ አብራርተዋል። ዓለም አቀፋዊ ክስተቶች፣ የሥራና ፈጠራ ባህል አነስተኛ መሆን እንዲሁም የፍላጎትና አቅርቦት አለመጣጣም የኑሮ ውድነት ፈተናዎች መሆናቸውንም አቶ ደመረ ተናግረዋል። በውይይቱ ላይ ሃሳባቸውን ያነሱት ተሳታፊዎች እንዳሉት ተቋሙ የሀገር ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ነው። የተቋሙ ሠራተኞች በሁሉም አካባቢዎች ተንቀሳቅሰው ሥራቸውን ማከናወን በሚችሉበት ሁኔታ ላይ የሚታዩ ስጋቶችን ማስወገድ እንደሚገባም ነው ያነሱት። ዜጎች ይበልጥ በሚያስተሳስሯቸው የወል ማንነቶች ላይ በመስራት የጋራ አንድነትን ማጠናከር እንደሚያስፈልግም ነው የጠቆሙት። የተሳሳቱ ትርክቶች ለተሳሳቱ ውጤቶች ምክንያት እየሆኑ በመምጣታቸው የጋራ ትርክት በመፍጠር ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አንስተዋል። በውይይቱ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት በተቋሙ የኢንጅነሪንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ውድነህ የማነ እንደገለፁት  ኢትዮጵያን ለማሳደግ የሚገጥሙንን ችግሮች በጋራ መቅረፍ ይገባል። አባቶቻችን ነፃ የሆነች ሀገር ቢያስረክቡንም የኢኮኖሚ ነፃነታችንን ለማረጋገጥ ትውልዱ መስራት ይኖርበታል ብለዋል። በውይይቱ ላይ የማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ውይይቱ ለምንፈልገው ሰላምና ዕድገት አስተዋፅኦው የጎላ ነው። እንደ ሀገር ያሉንን ፀጋዎች ወደ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የተሻለች ኢትዮጵያን ማስረከብ ይጠበቅብናል ብለዋል። እንደ አቶ አሸብር ገለፃ አሉታዊ ሃሳቦችን ወደ ጎን በመተው እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን በቀና መንፈስ መመልከት ይገባል። ተቋሙ ሀገራዊ እንደመሆኑ መጠን የሰላም እጦት በሚከናወኑ የፕሮጀክትና የኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ ችግር እንዳያስከትል ሁሉም የሰላም ዘብ መሆን እንደሚገባው ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል። የተቋሙ ሥራ አመራር ከሠራተኛው የሚነሱ ጥያቄዎችን በአፋጣኝ ለመመለስ እየሰራ እንደሚገኝም ነው አቶ አሸብር የገለፁት። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”         የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     የካቲት 01 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6