es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 539 suscriptores, ocupando la posición 8 340 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 161 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 539 suscriptores.

Según los últimos datos del 28 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 1, y en las últimas 24 horas de -4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 24.98%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.34% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 882 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 539 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 8.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 29 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 539
Suscriptores
-424 horas
-147 días
+130 días
Archivo de publicaciones
ለጥገና ሥራ ሲባል ነገ ከንጋቱ 11፡00 ጀምሮ ኃይል ይቋረጣል ……..///…….. ከካራቆሬ በጦር ኃይሎች ወደ ጥቁር አንበሳ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ ላይ ለሪል ስቴት ግንባታ በሚከናወን ቁፋሮ ምክንያት ጦር ኃይሎች አካባቢ ከኮካ በስተጀርባ ትናንት ጉዳት ደርሶ ኃይል ተቋርጦ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ ጉዳቱን በጊዜያዊነት ትናንት ጠግኖ የተቋረጡት መስመሮች ኃይል እንዲያገኙ የተደረገ ቢሆንም ነገ ማክሰኞ ታህሳስ 23 ቀን 2016 ዓ.ም. በምሰሶው እና በመስመሩ ላይ ተጨማሪ የጥገና ሥራ ማከናወን አስፈልጓል፡፡ በመሆኑም በሚካሄደው ጥገና ምክንያት ከጥቁር አንበሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል በሚያገኙት በአብነት፣ በሞላ ማሩ፣ በልደታ እና በአካባቢው፡፣ በተ/ሃይማኖት ቤተክርስቲያንና በአካባቢው፤ በፒያሳና በአካባቢው በከፊል፣ በሜክሲኮ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታልና በአካባቢው፣ በአምባሳደር፣ በሸራተን ሆቴልና አካባቢው ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 3፡30 ሰዓት ድረስ ድረስ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ ይቆያል፡፡ ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሜዲካል ዶክተር የሥራ መደብ ባለሙያዎችን ለመቅጠር መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም በወጣው ማስታወቂያ መሰረት መስፈርቱን አሟልታችሁ ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ጥር 02 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በአሸናፊነት ቀጥሏል ……….///……… በዘጠነኛ ሳምንት የከፍተኛ ሊግ ውድድር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ይርጋጨፌ ቡናን አንድ ለበዶ በመርታት የሊጉን መሪነት አጠናክሯል። ትናንት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ጨዋታውን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮ የተጫወተ ሲሆን ይርጋጨፌ ቡና በአንፃሩ በመከላከል እና አልፎ አልፎ በመልሶ ማጥቃት ለመጫወት ጥረት አድርጓል። የኢትዮ - ኤሌክትሪክን የማሸነፊያ ጎል ቢኒያም ካሳሁን በ55ኛው ደቂቃ ላይ ማስቆጠር ችሏል። ኢትዮ - ኤሌክትሪክ ካደረጋቸው ዘጠኝ ጨዋታዎች ሰባቱን በማሸነፍ በ21 ነጥብ እና በስምንት ንፁህ ጎል ሊጉን በመምራት ላይ ይገኛል። ኢትዮ - ኤሌክትሪክ በመጪው አርብ ታህሳስ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ከቤንች ማጂ ቡና ጋር 10ኛ ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+2

ተቋሙ ለቢት ክላስተር የዳታ ማዕከል የሰጠው የኃይል አቅርቦት ፈቃድ የለም .........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሩሲያው ቢት ክላስተር የዳታ ማዕከል ኃይል ለማቅረብ ያደረገው ሥምምነት አለመኖሩን አስታወቀ። በተቋሙ የማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ህይወት እሸቱ እንደገለፁት ለዳታ ማይኒንግ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ለማግኘት የተለያዩ ሀገራት ኩባንያዎች ጥያቄ እያቀረቡ ቢሆንም ቢት ክላስተር የዳታ ማዕከል የሚባል የሩሲያ ኩባንያ ግን ያቀረበው ምንም ዓይነት ጥያቄ የለም። በተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጪ መገናኛ ብዙሃን ኩባንያው በአዲስአበባ ቂሊንጦ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ 120 ሜጋ ዋት ኃይል የሚጠቀም የዳታ ማዕከል ግንባታ እያካሄደ ስለመሆኑ ዘገባዎችን ይዘው የወጡ ቢሆንም መረጃው ከእውነት የራቀ ነው ብለዋል። የዳታ ማይኒንግ አቅራቢ ድርጅቱ በ30 ሺህ ካሬ ሜትር ላይ ትራንስፎርመሮችን የማገናኘት ሥራ እየሰራ እንደሆነ አድርጎ ያወጣው ዘገባ የተሳሳተ መሆኑንም ነው አቶ ህይወት የተናገሩት። በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከግሪድ ኃይል የሚያገኙ እና እርስ በርስ የተሳሰሩ መሆናቸው እየታወቀ የዳታ ማዕከሉ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በቀጥታ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚያገኝ አድርጎ የተሰራው ዘገባ እውነትነት የሌለው መሆኑን ገልፀዋል። እንደ አቶ ህይወት ገለፃ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገሪቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አገልግሎት በየጊዜው በመገምገም የኃይል ፍላጎት እና አቅርቦትን ያማከሉ ሥራዎች በማከናወን ላይ ነው። የዳታ ማዕከል ኩባንያዎች የሚያቀርቧቸው የኃይል አቅርቦት ጥያቄዎች የሚመለሱት የሀገር ውስጥ የኃይል ፍላጎት ከተሟላ በኋላ መሆኑንም አረጋግጠዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 22 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

በተቋሙ ስትራቴጂ ላይ ቀጣይነት ያለው ተግባቦት ሊኖር እንደሚገባ ተገለፀ ...///... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት በሚተገብረው የስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ የሥራ መሪዎች ቀጣይነት ያለው ተግባቦት ሊኖራቸው እንደሚገባ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ አስታወቀ። የተቋሙ የሥራ መሪዎች ለቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት በሚተገበረው የግሪድ ስትራቴጂ ዕቅድ ዙሪያ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱ ላይ የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ እንደገለፁት በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የሚተገበረው የግሪድ ስትራቴጂ የተቋሙን አፈፃፀም ለማሳደግ ፋይዳው የጎላ ነው። ተቋሙ በሰው ኃይል አደረጃጀቱ፣ በኃይል ማመንጨት እና ማስተላለፍ አቅሙ እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ ሀገራት ካሉ አቻ ተቋማት ጋር ባለው የኃይል ትስስር ድርሻ ላይ ያተኮረ ገለፃ አድርገዋል። ስትራቴጂክ ዕቅዱ ፈጣን ለውጦችን እያሳየ ከመጣው የዓለምና የሀገሪቱ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማስቻል የሥራ መሪዎች ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁርጠኛ ሊሆኑ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተቋሙ የኢንቨስትመንትና ስትራቴጂ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ተሾመ እንደገለፁት ስትራቴጂክ ዕቅዱን በየደረጃው ለተቋሙ የሥራ ዘርፎችና ሠራተኞች ማውረድ ይገባል። ሰው፣ ቴክኖሎጂ እና አሰራር የተቋሙ ስትራቴጂካዊ እሳቤዎችና አቅጣጫዎች መሆናቸውንም ነው ዳይሬክተሩ የጠቆሙት። በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የሚተገበረውን የግሪድ ስትራቴጂ ለማሳካት አራት የትኩረት መስኮች፣ አራት ዕይታዎች፣ 18 ተቋማዊ ግቦችና 44 መለኪያዎች በውጤት ተኮር ሥርዓቱ  ውስጥ መካተታቸውን ተናግረዋል። የስትራቴጂክ ዕቅዱ ከመንግሥት ፖሊሲዎችና የአሠራር መመሪያዎች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ለማድረግ የውጤት ተኮር ሥርዓቱን የመከታተል፣ የመገምገም እና ቀጣይነት ያለው የድጋፍ ሥራ ማከናወን እንደሚገባም ነው አቶ ወንድወሰን የጠቀሱት። የተቋሙ የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) በበኩላቸው የሥራ መሪዎች በስትራተጂክ ዕቅዱ አፈፃፀም ላይ ያላቸውን ሚና አስመልክቶ ገለፃ አድርገዋል። ለስትራቴጂክ ዕቅዱ መሳካት ተፅዕኖ የማሳደር፣ ነባራዊውን የሥራ ሁኔታ ቀጣይነት ባለው መልኩ የመለወጥ እንዲሁም ለተቋም ግድ ያለው የሥራ መሪ መፍጠር እንደሚገባም ተናግረዋል። የሥራ መሪዎቹም በውይይቱ ላይ የተለያዩ አስተያየቶችና ጥያቄዎች አቅርበው በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። በውይይቱ ላይ የማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደገለፁት በተቋሙ ያለውን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን የተያዘውን ራዕይ ለማሳካት መስራት ይገባል። ስትራቴጂክ ዕቅዱን ተከትሎ የሚተገበረው አደረጃጀትም የሥራ መሪዎችን ከሥራ የሚያፈናቅል ሳይሆን ከምንጊዜውም በተሻለ ኃላፊነታቸውን ለመወጣት እንደሚያግዛቸው ተናግረዋል። እንደ አቶ አሸብር ገለፃ ተቋሙ የለውጥ ጎዳና ላይ በመሆኑ በለውጥ መንፈስ በዕቅድ የተያዙ ሥራዎችን ማከናወን ይገባል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 20 ቀን 2016 ዓ.ም

ብዝኃነትን መኖር!
ብዝኃነትን መኖር!

photo content
+1

photo content
+9

ተቋሙ በቀጣይ በሚተገብረው የግሪድ ስትራቴጂ ላይ ውይይት እያካሄደ ነው ......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎች ተቋሙ በቀጣይ ሦስት ዓመታት በሚተገብረው የግሪድ ስትራቴጂ ላይ በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ ውይይት ማካሄድ ጀምረዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ መድረኩን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት ውይይቱ ተቋሙ አሁን ያለበትን የአፈፃፀም ደረጃና በሚተገበረው የግሪድ ስትራቴጂ ላይ ወጥ የሆነ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው። የግሪድ ስትራቴጂውን ዕውን ለማድረግ ሁሉም የተቋሙ የሥራ መሪ በንቃትና በትብብር መስራት እንደሚጠበቅበት የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው በውይይቱ ላይ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉም ጥሪ አሳስበዋል። ተቋሙ በሚቀጥሉት ዓመታት በሰው ኃይል አደረጃጀት፣  በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፍ ፣ በኃይል ሽያጭ እንዲሁም ለግንባታ በዕቅድ የተያዙት ፕሮጀክቶች ለመተግበር ከመካከለኛና ከፍተኛ አመራሩ ምን ይጠበቃል በሚሉ ዐቢይ ጉዳዮች ላይ ገለፃ ቀርቦ ውይይት እንደሚካሄድ ከወጣው መርሃ ግብር ማወቅ ተችሏል። ለአንድ ቀን በሚቆየው የውይይት መርሃግብር ላይ በየደረጃው ያሉ የተቋሙ አመራሮች የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነቶች በላቀ አፈፃፀም እንዲወጡ የጋራ መግባባት ላይ ይደረሳል ተብሎ ይጠበቃል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 20 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

የፕሮጀክቱ ግንባታ ከ95 በመቶ በላይ ተጠናቋል ……...///…….... የቡታጅራ - ወራቤ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ አፈፃፀም ከ95 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ዐቢይ አታኩሬ እንደገለፁት የፕሮጀክቱ አብዛኛዎቹ የሲቪልና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ተጠናቀው የፍተሻና ሙከራ ሥራ ተጀምሯል። የኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታውን በተያዘው ወር አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ነው የገለፁት። እንደ አቶ ዐቢይ ገለፃ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፈርመሮች እንዲሁም አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ገቢና ስድስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። የማስፋፊያ ግንባታ ሥራዎች በነባሩ የቡታጅራ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ መከናወናቸውን ጭምር ነው ያስታወቁት። ከቡታጅራ እስከ ወራቤ እንደሚተከሉ ከሚጠበቁት 95 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ውስጥ የ94 የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ተከላ መጠናቀቁንና ቀሪውን አንድ ምሰሶ ለመትከል የሚያስችሉ ሥራዎችም መገባደዳቸውን ጠቁመዋል። ከቡታጅራ እስከ ወራቤ የኮንዳክተር ገመድ ለመዘርጋት ከታሰበው 36 ኪሎ ሜትር ውስጥ 35 ነጥብ 6 ኪሎ ሜትር ማጠናቀቅ መቻሉንም ነው አቶ አብይ የተናገሩት። የፕሮጀክቱን ግንባታ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ ዕቅድ ቢያዝም ከወሰን ማስከበር፣ ከሲሚንቶ አቅርቦት እና ከዲዛይን ሥራዎች ጋር በተያያዘ በሦስት ወራት መዘግየቱን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። እንደ አቶ ዐቢይ ገለፃ በፕሮጀክቱ የወሰን ማስከበር ሥራዎችን ለማከናወን 157 ሚሊዮን ብር የካሳ ክፍያ ተፈፅሟል። ይሁን እንጂ በመስቃን ወረዳ ቡታጅራ አካባቢ የካሳ ክፍያ የተፈፀመባቸውን የመሬት ይዞታዎች በወቅቱ የማስነሳት ሥራ ማከናወን እንዳልተቻለ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የወረዳው አስተዳደር የፕሮጀክቱን ፋይዳ በመረዳት አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጥም ጠይቀዋል። የፕሮጀክቱን የግንባታ ሥራዎች ሲኖ ሃይድሮ የተባለ የቻይና ኩባኒያ እያከናወነው ሲሆን በአማካሪነት ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኢንጅነሪንግ ቢሮ እየተሳተፈበት ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱን ግንባታ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ 10 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በጀት ወጪ የተደረገ ሲሆን የፋይናንስ ወጪውም ሙሉ በሙሉ በዓለም ባንክ መሸፈኑን ጠቅሰዋል። የቡታጅራ-ወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለወራቤ ከተማና በከተማው አቅራቢያ ለተገነባው የኢንዱስትሪ መንደር እንዲሁም በዙሪያው ለሚገኙ የስልጢ ዞን ወረዳዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ፋይዳው የጎላ መሆኑን አቶ ዐቢይ ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ ግንባታ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ የክትትልና የድጋፍ ሥራዎች ላከናወኑ የመስተዳድር አካላትም ምስጋናቸውን ሥራ አስኪያጁ አቅርበዋል። ፕሮጀክቱ ከ500 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎችም ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በድራጊስት (Druggist) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መጋቢት 02 ቀን 2015 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከታህሳስ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እናሳውቃለን ፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

የቅጥር ሁኔታ መረጃ ማስተካከያ በቻይልድ ኬር አድሚኒስትሬሽን አሲስታንት 1ኛ የሥራ መደብ ታህሳስ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ክፍት የስራ መደብ ለውጭ አመልካቾች ማስታወቂያ ያወጣን መሆኑ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ማስታወቂያው ሲወጣ የቅጥር ሁኔታው በስህተት በቋሚነት ተብሎ የወጣ ስለሆነ የቅጥር ሁኔታው በኮንትራት መሆኑን ከይቅርታ ጋር እናሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3