es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 525 suscriptores, ocupando la posición 8 336 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 179 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 525 suscriptores.

Según los últimos datos del 07 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 5, y en las últimas 24 horas de -2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 28.59%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.03% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 440 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 489 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 08 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 525
Suscriptores
-224 horas
-57 días
+530 días
Archivo de publicaciones
የአሜሪካ የኒዉክለር አቅም፣ የሩሲያ ተምዘግዛጊ ሚሳኤሎችና የጦር ጄቶች፣ የናሳ ተመራማሪዎችና አንቱ የተባሉ ሳይንቲስቶች፣ የቻይና የቴክኖሎጂ ፈጠራ አቅም ወዘተ ...... የዜጎቻቸውን ደህነንነት ለመጠበቅና አቅም አልቻሉም፡፡ በተለይ በዓለማችን አሉ የተባሉት የቴክኖሎጂ ፈጣሪና ባለቤት የሆኑ ሃገራት መሪዎች እንደ እስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒያሚን ኔትያናሁ፣ እንደ እንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንስ ያሉት ወሸባ (quarantine) መግባት ስናይ እነዚያ ከአየር ላይ ጠላትን ይቀልባሉ የተባሉ ዘመናዊ መሳሪያዎችን (ስናይፐሮች) የታጠቁ ጠባቂዎቻቸውና አጃቢዎቻቸው ከረቂቋ የኮሮና ቫይረስ ምንም ማንም ማንንም ሊያስጥል እንደማይችል በቂ ማሳያ ነው፡፡ እንደ ጣሊያኑ ጠቅላይ ሚኒስትር በአደባባይ እንባ እየረጩ ተስፋ በመቁረጥ ፍትህ ወደ ሰማይ ሲጠይቁ ስናይ ለካ በቴክኖሎጂ መበልፀግ እና መሳሪያ መታጠቅ ትርጉም አልባ መሆኑን እናያለን፡፡ የኮሮና ቫይረስ ሃብታም - ድሃ፣ የሠለጠነ - ያልሰለጠነ፣ ቀይ - ጥር፣ ሴት - ወንድ፣ ልጅ - አዋቂ፣ የከተማ- የገጠር ሰው ሳይል መላውን የሰው ልጅ እየገደለ የሚገኝ በሽታ ነው፡፡ ስለሆነም የአንተ ወይም የአንቺ መኖር ለቤተሰብና ለሀገር እጅግ ጠቃሚ ነውና በየጊዜው ከጤና ባለሙያዎችና ከመንግስት የሚሰጡ መመሪያዎችን በመቀበልና በመተግበር ራሳችንና ቤተሰባችን ከኮሮና ወረርሽኝ እንከላከል፡፡

ዛሬ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ 6 ሰዎች ተገኙ፣ ቁጥሩ 35 ደርሷል፣ እናም አሁን አብዝተን ስለምንወዳቸው ሰዎች ሁሉ ግድ ሊለን ይገባል፣ አገርና ህዝብን እንታደግ፡፡

#etv የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት በዚህ ዓመት በመጀመር የሃይል ማመጨት ስራ ለማሰጀመር በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ https://www.facebook.com/541629952535552/posts/3203231236375397/

የኮሮና ቫይረስ ዕለታዊ ሁኔታ በኢትዮጵያ - 24/07/2012 ዓ.ም
የኮሮና ቫይረስ ዕለታዊ ሁኔታ በኢትዮጵያ - 24/07/2012 ዓ.ም

የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ለመመከት

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወቅታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። ኮሮናን እንከላከላለን ፤ ግድቡን እንጨርሳለን!!! ሙሉ መልዕክታቸውም እንደሚከተለው ቀርቧል። ውድ የሀገሬ ሕዝቦች የሕዳሴው ግድባችንን ግንባታ የጀመረበትን ዘጠነኛ ዓመት በምናከብርበት በዚህ ወሳኝ ወቅት ላይ ሁለት ጉልህ ፈተናዎች ገጥመውናል፡፡ አንደኛው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ራሱ የሕዳሴ ግድብ ግንባታችንን የተመለከተ ጉዳይ ነው፡፡ ሁላችንም እንደምናውቀው ለእኛ ለሰው ልጆች ትልቁ ጸጋችን ሕይወት ሲሆን ይሄን ድንቅ ጸጋ ሊነጥቀን የኮሮና ወረርሽኝ የእያንዳንዳችን በር እያንኳኳ ከደጃችን ቆሟል። ቫይረሱ የሚተላለፍበት መንገድ ከሰዎች ለሰዎች ንኪኪ ጋር የተገናኘ እና የሚስፋፋበትም መጠን ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ ፈጣን እየሆነ እንደመጣ በየዕለቱ የምናየው እውነታ ሆኗል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ወረርሽኙ 201 ሀገራትን አዳርሷል። ከፍተኛ ሥርጭት የተመዘገበባቸው 10 ግንባር ቀደም ሀገራት ከጠቅላላ የኮሮና ተጠቂ 80 በመቶውን ይሸፍናሉ። 90 በመቶ የሚሆነው የኮሮና ሞት የተመዘገበውም በእነዚህ ሀገራት ነው፡፡ የኮሮና የሥርጭት ፍጥነት በኢኮኖሚና በሥልጣኔ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱትን ሀገራት በከፋ ሁኔታ አዳርሷል። በሀገራችን የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር ዛሬ 26 ቢሆንም በሚቀጥሉት ሳምንታት ቁጥሩ ሊያሻቅብ ይችል ይሆናል። ምናልባትም ሞት ያጋጥመንም ይሆናል። አሁን በሽታው ከአዲስ አበባ አልፎ በክልል ከተሞችም እየታየ ነው። ለቁጥጥር እንዳያስቸግር አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች በሚኖሩባቸው መንደሮች እንዳይገባ ሁላችንም መረባረብ ይኖርብናል፡፡ በመንግሥት በኩል የጥንቃቄ ሕጎችን በጥብቅ ለማስፈጸም፣ የመከላከያና የሕክምና ቁሳቁሶችን በየቦታው ለማዳረስ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል። ትምህርት ቤትና መሥሪያ ቤቶችን ጨምሮ ሰዎች የሚበዙባቸውን ስፍራዎችን እንዲዘጉ፣ በሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርቶች የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች እንዲገደቡና ሌሎችም ተያያዥ ርምጃዎች እየተወሰዱ ናቸው። ለእነዚህም ርምጃዎች ተፈጻሚነት አስፈላጊ የሆኑ አደረጃጀቶች ተፈጥረዋል፡፡ ውድ የሀገሬ ሕዝቦች በአሁኑ ወቅት ሀገራችን ከምትጠነቀቅላቸውና በስስት ከምታያቸው ጸጋዎቿ ሁለተኛው የሕዳሴ ግድባችን ነው፡፡ የሕዳሴ ግድባችን ከዕለት ጉርሳችን ቀንሰን በተባበረ ክንድ እየገነባን እዚህ ያደረስነው ብቻ ሳይሆን የማድረግ ዐቅማችንን ያሳየንበት ትልቁ ጸጋችን ነው፡፡ ለግድባችን ከፍ ያለ ግምት የምንሰጠው አንድም የሉዓላዊነታችን ምልክት፣ ሁለትም የትሥሥራችን ገመድ በመሆኑ ጭምር ነው፡፡ የፊታችን ክረምት ግንባታው ተገባዶ የውኃ ሙሌት እንጀምራለን ። የኮሮና ወረርሽኝ በዚህ ወቅት መከሠቱ ትኩረታችንን ቀንሶ የሕዳሴ ግድብ ግንባታችን በማጓተት ቀላል የማይባል ተጽዕኖ እንደሚያሳድር ግልጽ ነው፡፡ በወረርሽኙ ምክንያት ተዘናግተን የግድብ ባለቤት የመሆን ጉዟችን ማዝገም የለበትም፡፡ እስከዛሬ አሳድገን አሳድገን ፍሬውን ለማየት የጓጓንለት ልጃችንን አሁን በተጋረጠብን አደጋ ምክንያት ፍሬውን ከማየት መገታት የለብንም፡፡ በዚህ ወቅት የኮሮና ወረርሽኝን ለመግታት የምናደርገው ትግል በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ መምታት የሚያስችለን ወሳኝ ጎዞ መሆኑ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ልብ ውስጥ መታተም አለበት ። ቤት በመቀመጥና ቶሎ ቶሎ ንጽሕናችንን በመጠበቅ የኮሮና ወረርሽኝን መከላከል በአንድ በኩል፤ የሕዳሴ ግድባችን፣ ግንባታው ተጠናቆ በቶሎ የውኃ ሙሌቱ እንዲጀመር በዐቅማችን መዋጯችንን መላክ በሌላ በኩል ከሁላችንም ይጠበቃል፡፡ በርግጥ ጊዜያችንን በሥራ ስናሳልፍ የነበርን ሰዎች ለኮሮና ሲባል ቤት ውስጥ መቀመጥ አስቸጋሪ ነው። ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ኪሳራዎችን ሊያደርስብንም ይችላል፡፡ ሆኖም ግን በሌላ መልኩ ካየነው ይሄንን አጋጣሚ ለመልካም ተግባራት ልናውለው እንችላለን፡፡ ወላጆች ለልጆቻቸው ፍቅር የሚሰጡበት፤ ባለትዳሮች ስለቀጣይ የሕይወታቸው ምዕራፍ በሰፊው የሚያቅዱበት፤ እንዲሁም ማንበብ የሚፈልጉ ሰዎች ጊዜ ወስደው እንዲያነብቡ፤ የሚጽፉ ሰዎች ጊዜ አግኝተው እንዲያሰላስሉ፣ የሚመራመሩ ሰዎች እንዲመራመሩ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል፡፡ በዚህ መልኩ ለተወሰነ ጊዜ ወደ ውጭ ከመውጣት ተቆጥበው ቤታቸው የሚያሳልፉ ዜጎቻችን ራሳቸውንና ሌሎችንም ከክፉው ወረርሽኝ ከማዳን በዘለለ፣ ወረርሽኙ አልፎ ሁሉም ነገር ሲረጋጋ ብዙ መልካም ነገሮችን ማትረፋቸው አይቀርም፡፡ ኮሮናን ለመከላከልም ሆነ ግድቡን ለማጠናቀቅ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያለ ልዩነት እንደ አንድ ሠራዊት ሆኖ በማሸነፍ ወኔ መነሣት አለበት። የኮሮና ሥርጭትን ለመግታት ከሰዎች ንክኪ ርቀታችንን በመጠበቅና ራሳችንን መግዛት እንደሚገባን ሁሉ፤ ከሌሎች ሀገራት ርዳታ ለመዳን ለግድባችን ግንባታ ቦንዳችንን መግዛት ይጠበቅብናል፡፡ የኮሮና ቫይረስ ሥርጭትን ለመግታት እንዲረዳ በሚል በተዘጋጁ የመልእክት መላኪያ ቁጥሮች አማካኝነት ጥቆማና ድጋፍ ስናደርግ በተመሳሳይ ለሕዳሴው ግድብ በ8100 ላይ A ብለን በመላክ የድጋፍ ቤተሰብነታችንን ማረጋገጣችንን እንቀጥላለን፡፡ በዚህ መልኩ በመጪው ወራት ውስጥ በዝቅተኛ የጉዳት ሰለባ ኮሮናን ከሀገራችን አጥፍተን፤ በአፋጣኝ ሕዳሴ ግድባችንን የመጀመሪያውን የውኃ ሙሌት አጠናቀን ሁላችንም ስኬታችንን ለማየት እንደምንበቃ አልጠራጠርም፡፡ በርግጥም በተባበረ ክንድ ከሠራን ኮሮናንም እንከላከላለን፤ ግድቡንም እንጨርሳለን። ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር! ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ መጋቢት 23/ 2012 ዓ.ም

አንተስ
አንተስ

የኮሮና ቫይረስ ኮቪድ-19 ወቅታዊ ሁኔታ 22/07/2012
የኮሮና ቫይረስ ኮቪድ-19 ወቅታዊ ሁኔታ 22/07/2012

ነገ ደግሞ በፈረንጆቹ አቆጣጠር April 1st ነው ... በዚህ ቀን ደግሞ ብዙ የሀሠት መረጃዎች ይለቀቃሉ... ወቅቱ ኮሮና ቫይረስ የተመለከቱ መረጃዎች በብዛት የሚወጡበት ስለሆነ መረጃዎችን ማጣራት
ነገ ደግሞ በፈረንጆቹ አቆጣጠር April 1st ነው ... በዚህ ቀን ደግሞ ብዙ የሀሠት መረጃዎች ይለቀቃሉ... ወቅቱ ኮሮና ቫይረስ የተመለከቱ መረጃዎች በብዛት የሚወጡበት ስለሆነ መረጃዎችን ማጣራት ግድ ይላል...

ራስዎን እና ቤተሰብዎን ከኮሮና ቫይረስ ለመጠበቅ እነዚህን ነገሮች ይተግብሩ! https://www.facebook.com/ethiopianpressagency/videos/626811681504161/

በሶማሌ ክልል የተገነቡት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያና ማስተላለፊያ መስመሮች ሥራ ጀመሩ በሶማሌ ክልል በቀብሪደሃር ከተማ የተገነባው የቀብሪ ደሃር ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ ጀመረ፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ የሲቪልና የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀው በትናንትናው ዕለት በይፋ ስራ መጀመሩ ታውቋል፡፡ ከጎዴ ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር እንዲገናኝ የተደረገው የቀብሪደሃር ማከፋፈያ ጣቢያ ባለ 33 ኪሎ ቮልት አምስት ወጪ መስመሮች ያሉት ሲሆን በቀብሪ ደሃር እና በዙሪያው ለሚገኙ ከተሞች በፈረቃ ይሰጥ የነበረውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ሙሉ ለሙሉ እንደሚያስቀር ታምኖበታል፡፡ የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የአካባቢውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በማነቃቃት በሃገሪቱ እየተካሄደ ያለውን ፍትሐዊ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ተደራሽነትን ለማጠናከርና አርብቶ አደሩን በመንደር በማሠባሰብ የዘርፈ ብዙ የመሠረት ልማት አውታሮች ተጠቃሚ በማድረግ የአኗኗር ዘይቤውን ለማዘመን ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡https://www.facebook.com/photo.php?fbid=209224883640628&set=pcb.209225350307248&type=3&__tn__=HH-R&eid=ARBfSJiEyFCsBb_7sorcr3OiZgfLZ8hVhj9XnPiTOoKjnkimOnLuSAPD9tGvJ7LXQqprP1336YFALHMP

በሕዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ቦታ የኮረና ቫይረስ መመርመሪያ እንዲኖር ለማድረግ እየተሰራ ነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት በሚካሄድበት ስፍራ የኮረና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ከመንግሥት አካላት ጋር በመነጋገር በግድቡ ቦታ ላይ የቫይረሱ መመርመሪያ እንዲኖር ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። የፕሮጀክቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለፁት ፤የፕሮጀክቱ ሠራተኞችን ከኮረና ቫይረስ ስርጭት ለመታደግ እየተሰራ ሲሆን፣በቫይረሱ የሚጠረጠር ሠራተኛ ከተገኘም ማቆያ ለማዘጋጀት ከመንግሥት አካላት ውይይት እየተደረገ ነው። ፕሮጀክቱ በሚካሄድበት ስፍራ መገኘት ያለባቸው ሰዎች ካሉም ምርመራ ተደርጎ እንዲገቡ እንደሚደረግ ጠቁመዋል። በግንባታው ላይ ለተሰማሩ ለሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ሀገር ለመጡ ሠራተኞች ሲባል በሚካሄደው ጥንቃቄ በፕሮጀክቱ ቦታ የሚሄድ ማንም ሰው ጤንነቱ ይረጋገጣል። በፕሮጀክቱ ሥፍራ የህክምና ባለሙያዎች መኖራቸውን የጠቀሱት ኢንጅነሩ፣ በዋናነት የሚፈለጉት ግን በወረርሽኙ ዙሪያ ሰልጥነው እንክብካቤ የሚያደርጉ እና ምርመራ አድርገው መቆጣጠር የሚችሉ ባለሙያዎች መሆናቸውን አስታውቀዋል። https://www.facebook.com/ethiopian.electrcpower.1

"እንድታስብ - አዕምሮህን እንድትፀና - ጉልበትህን እንድትወስን - ልቦናህን እንድትፈፅም - መንገድህን ፈጣሪ ይጠብቅ!!! በነገር ሁሉ ፈጣሪ ሀገራችንንና ህዝባቿን ይጠብቅ ባለን አቅም ሁሉ ተረባርበ
"እንድታስብ - አዕምሮህን እንድትፀና - ጉልበትህን እንድትወስን - ልቦናህን እንድትፈፅም - መንገድህን ፈጣሪ ይጠብቅ!!! በነገር ሁሉ ፈጣሪ ሀገራችንንና ህዝባቿን ይጠብቅ ባለን አቅም ሁሉ ተረባርበን የምንሰራ በሚጎለን ደግሞ እሱ ይሚሞላበት ይሁን" (ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር ዐብይ ለኢትዮጵያ ህዝብ ካስተላላፉት መልዕክት የተወሰደ)

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ መልዕክት የተከበራችሁ የተቋማችን ሠራተኞችና አመራሮች፤ ከሁሉ አስቀድሜ በተቋማችን ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን እና በራሴ ስም ሠላምና ጤና እመኝላችኋለሁ፡፡ ሁላችሁም እንደምታውቁት የኮሮና ቫይረስ ከተከሰተ ጀምሮ በዓለማችን ላይ ከባድ ሰብዓዊ፣ ስነልቡናዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት አስከትሏል፡፡ ዘርና ሃይማኖት፣ ዕድሜና ፆታ፣ ሀብትና ሥልጣን ሳይለይ ክቡሩን የሰው ልጆች ህይወት ቀጥፏል፤ የሀገራትንም ኢኮኖሚ አንኮታኩቷል፡፡ በኢኮኖሚ፣ በቴክኖሎጂና በጤና ስርዓታቸው የተሻለ የሚባሉ የዓለማችንን ሀገራት ሳይቀር በከፍተኛ ሁኔታ በመምታት ተቋሞቻቸውን እንዲዘጉ አስገድዷል፡፡ በሀገራችንም የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ መገኘቱ ይፋ ከሆነ በኋላ መንግስት የተለያዩ የጥንቃቄ እርምጃዎች እንዲወሰዱ በማድረግ፣ የተለያዩ እርምጃዎች እንዲወሰዱ መመሪያዎችን አስተላልፏል፡፡ በተቋማችንም የተለያዩ የጥንቃቄና የመከላከል እርምጃዎች በመተግበር ላይ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ የኮሮና ቫይረስ መስፋፋት እንደኛ ያሉ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አገልግሎት የበለጠ እንደሚፈልግ ግልፅ ነው፡፡ ተቋማችን የሚሰጠው አገልግሎት ኃይል ከመስጠት የዘለለ መሆኑን ከማንም በላይ እንደምትረዱት እምነቴ ነው፡፡ ምክንያቱም መብራት ከኃይል ምንጭነት ባለፈ በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን ከፍተኛ የጤና ስጋት ሆኖ የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከልና ስርጭቱን ባለበት ለማስቆም የሚኖረው አስተዋጽኦ በቀላሉ የሚገለጽ አይደለም፡፡ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት ተግባራዊ እንዲሆን ከሚመከሩት መንገዶች አንዱ የእጅን ንፅህና በአግባቡ መጠበቅ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ውሃና ሳሙና አልያም ሌሎች የንፅህና መጠበቂያዎች ያስፈልጋሉ፡፡ በመሆኑም የውሃ ተቋማትም ሆኑ የንፅህና ግብዐቶችን የሚያመርቱ ተቋማት አገልግሎቱን ለህዝባችን ለማቅረብ ኃይል ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡ የህክምና ተቋማትም የቫይረሱን ስርጭት ለመግታትና ታካሚዎችን ለማከም ለሚያደርጉት ጥረት ያልተቋረጠ ኃይል ማግኘት አለባቸው፡፡ ለዚህም ተቋማችን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን በቅንጅት መስራቱን አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ ስለሆነም በየደረጃው ያላችሁ የተቋማችን ሠራተኞችና አመራሮች የተጣለባችሁ ኃላፊነትና የምትሰሩት ሥራ ለደቂቃዎች እንኳ የሚቋረጥ ባለመሆኑ አስቸጋሪ ባህርይ እንዳለው በሚገባ እረዳለው፡፡ ስለሆነም ይህንን አስቸጋሪ ወቅት ከወትሮ በበለጠ ትጋት እንደምትወጡት እምነቴ ነው፡፡ ተቋማችንና ህዝባችን የጣለባችሁን ኃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት በሚመለከታቸው የመንግስት አካላት የሚሰጡትን የጥንቃቄና የመከላከል እርምጃዎች በአግባቡ በመተርጎም የራሳችሁን፣ የቤተሰባችሁን፣ የሥራ ባልደረቦቻችሁንና የህዝባችሁን ህይወት እንድትጠብቁና እንድትታደጉ የአደራ መልዕክቴን አስተላልፋለሁ፡፡ የተከበራችሁ የተቋማችን ሠራተኞችና አመራሮች፤ የኦፕሬሽን ሥራ ቀን ከሌት የማይቋረጥ፣ አስቸጋሪና ፈታኝ ሁኔታዎችን ተቋቁሞ መስራትን የግድ የሚል በመሆኑ ከእያንዳንዱ ሠራተኛ ከፍተኛ ጽናት፣ ቁርጠኝነትና መስዋዕትነትን ይጠይቃል፡፡ ተቋማችን የሚያበረክተው አገልግሎት ሀገራችን የቫይረሱን ሥርጭት ለመግታት በምታደርገው ጥረት ውስጥ ጎልቶ የሚነገር ታሪክ እንደሚሆን እምነት አለኝ፡፡ ዛሬ ላይ የምንሰራው ሥራ ነገ ላይ ህዝብና ታሪክ የሚመሰክርለት እንዲሆን ለማድረግ አቅማችን የፈቀደውን ሁሉ ማድረግ ይኖርብናል፡፡ ጥንቃቄን አስቀድመን የህዝባችን የክፉ ቀን ደራሽና አጋር መሆናችንን በተግባር እንድናስመሰክር ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡ ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ! ጤና ለህዝባችን! ጤና ለሀገራችን! አሸብር ባልቻ - ዋና ሥራ አስፈፃሚ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=207879517108498&id=100036593526350