es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 528 suscriptores, ocupando la posición 8 328 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 176 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 528 suscriptores.

Según los últimos datos del 06 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 6, y en las últimas 24 horas de -3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 27.84%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.05% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 323 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 492 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 07 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 528
Suscriptores
-324 horas
-97 días
+630 días
Archivo de publicaciones
photo content

የተቋሙን ገቢ ለማሳደግ እና ወጪውን ለመቀነስ በትኩረት እየተሰራ ነው ……………….////………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ገቢውን ቀጣይነት ባለው መልኩ ለማሳደግ እና ወጪውን ለመቀነስ የተለያዩ አማራጮችን ነድፎ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከፕሮጀክቶች አዋጭነት ጥናት ጀምሮ እስከ ኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ድረስ እንዲሁም በደጋፊ የስራ ሂደቶች ወጪዎችን በመቀነስ እና አዳዲስ የገቢ ምንጮችን በጥናት ላይ ተመስርቶ በመለየት ተግባራዊ ለማድረግ አማካሪ ድርጅት ተቀጥሮ እየሰራ ላይ ይገኛል፡፡ በአማካሪ ድርጅቱ የተጀመረው ስራ የተቋሙን ገቢ ለማሳደግ እና ወጪውን ለመቀነስ ከፍተኛ ሚና ሊጫወት የሚችል ሲሆን ጥናቱን በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ የተቋሙን ወጪ ለመቀነስ እና ገቢውን ለማሳደግ ሁሉም የተቋሙ ሠራተኛና አመራር የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል ለተለያዩ ጉዳዮች የሚወጣውን ወጪ በመቀነስና ብክነትን በማዳን እንዲሁም በየክፍሉ የሚገኙ መልካም አጋጣሚዎችን ወደ ገቢ በመቀየር ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ መስከረም 28 / 2013 ዓ.ም.

በፕሮጀክቱ ንብረቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ ዳርጎታል ……………..////…………………. የኢትዮ- ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀ
በፕሮጀክቱ ንብረቶች ላይ እየተፈፀመ ያለው ስርቆት ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ ዳርጎታል ……………..////…………………. የኢትዮ- ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀሙበት እንደሚገኝ የኢትዮ - ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ አስተባባሪ ገለፁ፡፡ አስተባባሪው አቶ ሰይፉ ፈይሳ እንደገለፁት በኢትዮጵያ በኩል የሚገነባው የ433 ኪሎ ሜትር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል፡፡ ይሁን እንጅ በወላይታ ዞን አንዳንድ አካባቢዎች በማስተላለፊያ መስመሩ ሽቦዎች እና የምሰሶ ብረቶች ላይ በተደጋጋሚ የስርቆት ወንጀሎች እየተፈፀመበት ይገኛል ብለዋል፡፡ ይህም ተቋሙን ለተጨማሪ ወጪ በመዳረግ ከ34 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራም እንዳደረሰበት ነው ያስታወቁት፡፡ ኪሳራው የደረሰው በስርቆቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰበትን የማስተላለፊያ መስመሩን አካላት በአዲስ ለመተካትና ለመቀየር፣ እንዲሁም ለመበየድ፣ ለዕቃ ግዥ እና ለምሶሶ (Tower) ቅየራ ተጨማሪ ወጪ በመውጣቱ ነው፡፡ የማስተላለፊያ መስመሩ 994 ምሶሶች ያሉት ሲሆን በተፈፀመው ስርቆት ጉዳት ከደረሰባቸው ምሶሶዎች መካከል አንዱን ሙሉ በሙሉ መቀየሩን አስተባባሪው ተናግረዋል፡፡ የግንባታ ሰራው በ2008 ዓ. ም የተጀመረው የኢትዮ- ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ከ183 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric/ መስከረም 27 2013 ዓ.ም.

photo content
+1

በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የቆጣሪ ገጠማ ሥራ በመከናወን ላይ ነው ……………///…………….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የቆጣሪ ገጠማ ስራ በማከናወን ላይ መሆኑን በተቋሙ የስማርት ሜትር ፕሮጀክት ቢሮ ስራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጇ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ እንደገለጹት ተቋሙ 130 በሚሆኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የቆጣሪ ገጠማ ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የቆጣሪዎቹ መገጠም የተቋሙ ደንበኞች ለተጠቀሙት ኃይል ትክክለኛውን ክፍያ እንዲከፍሉ ለማድረግ እንደሚያግዝ ስራ አስኪያጇ አስታውቀዋል፡፡ ይህም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዚህ ቀደም በ40/60 የክፍፍል ስምምነት መሰረት የሚገኘውን ክፍያ በማስቀረት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወጣውን ኃይል ቆጥሮ በማስከፈል የተቋሙን ገቢ ለማሳደግ ይጠቅማል ብለዋል፡፡ እንደ ወ/ሮ ሐይማኖት ገለፃ የቆጣሪ ገጠማ ስራው የኃይል ብክነትን ለመለየት እና አስፈላጊውን የማስተካከያ እርምጃ ለመውሰድም ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡ በመገጠም ላይ የሚገኙት ቆጣሪዎች በእንግሊዝ ሀገር የተመረቱ “CEWE Prometer 100” የተባሉ ሲሆን የገጠማ ስራውንም “Siemens Proprietary Limited” የተባለ ድርጅት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ድርጅቱ 1 ሺ 476 ቆጣሪዎችን እንዲያቀርብ ስምምነት ላይ መደረሱን የጠቀሱት ወ/ሮ ሐይማኖት ከዚህ ውስጥ 1 ሺ 226 ቆጣሪዎች በጣቢዎች ላይ የሚገጠሙ ሲሆን ቀሪ 250 ቆጣሪዎች ደግሞ ለመጠባበቂያነት የሚያገለግሉ ናቸው ብለዋል፡፡ በጣቢያዎች ላይ ለመግጠም ከታሰቡ ቆጣሪዎች መካከል ይህ መረጃ እስከተጠናቀረበት ድረስ በ42 ጣቢያዎች ላይ 353 ቆጣሪዎች ተገጥመው የሙከራና የፍተሻ ስራ በመከናወን ላይ ነው፡፡ እንደ ስራ አስኪያጇ ገለፃ በእያንዳንዱ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚገጠመው የቆጣሪ ብዛት እንደ ጣቢያው ወጪ መስመር ብዛት የሚወሰን ይሆናል፡፡ የቆጣሪዎች ተከላ የዲዛይን፣ የማምረት እና የማጓጓዝ ስራው በ2012 በጀት ዓመት የተገባደደ መሆኑን ያነሱት ወ/ሮ ሐይማኖት እስከ ታህሳስ 2013 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ የገጠማ ስራውን ለማጠናቀቅ እቅድ መያዙን ተናግረዋል፡፡ በቆጣሪ ገጠማ ስራው ላይ ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ ባለሞያዎች እንዲሳተፉ መደረጉን የተናገሩት ስራ አስኪያጇ ይህም በቀጣይ ለሚከናወኑ የቆጣሪ ገጠማ ስራዎች በራስ አቅም ለመስራት የሚያስችል ልምድ ለማግኘት ታስቦ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡ በ130 ጣቢያዎች ላይ ለሚከናወነው የቆጣሪ ገጠማ አጠቃላይ ስራ የአቅርቦት፣ የተከላ፣ የፍተሻና ሙከራ ስራዎች ለማከናወን በዓለም ባንክ የሚሸፈን ከ25 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ብር እና ከ2 ነጥብ 17 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካ ዶላር በጀት ተይዞለታል፡፡

ሚኒስትሩ የታላቁ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ ******************* የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከዓለምአቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች
+3
ሚኒስትሩ የታላቁ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ ******************* የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከዓለምአቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ፡፡ ኃላፊዎቹ ስለግድቡና ስለግንባታው ሂደት በሚኒስትሩ ገለፃ ተደርጎላቸው ግንባታውን እየተዘዋወሩ ተመልክተዋል። ከጉብኝቱ በኋላም በግድቡ ግዝፈትና በግንባታው ሂደት ውስብስብነት መደነቃቸውን ኃላፊዎቹ ለሚኒስትሩ ገልፀውላቸዋል። በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንዲሁም የተቋሙ የኃይል ማመንጫዎች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሰፋ ንጉሴ ተገኝተዋል። በኢትዮጵያውያን የገንዘብ ድጋፍ በመገንባት ላይ የሚገኘው የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አጠቃላይ አፈፃፀም 76 ነጥብ 3 በመቶ ላይ ደርሷል። መስከረም 24 ቀን 2013 ዓ/ም

ሚኒስትሩ የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ *********************** የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ዋና
+6
ሚኒስትሩ የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታን ጎበኙ *********************** የውሃ፣መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ከተመድ የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ዋና ጸሃፊ ከቬራ ሶንግዌ ጋር በመሆን የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታንና በሥራ ላይ የሚገኘውን ጊቤ ሶስት የውሃ ኃይል ማመንጫን ጎበኙ፡፡ ጉብኝቱ ኢትዮጵያ ያሏትን የውሃ ሃብቶች ለዘላቂ እድገትና ለዜጎች ህይወት መሻሻል እንዴት በአግባቡ እየተጠቀመች እንደሆነ ለማየት አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡ “በኦሞ ወንዝ ላይ የተለያዩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጋችን በተመሳሳይ ሌሎች ወንዞቻችንንም እንዴት በአግባቡ መጠቀም እንደምንችል ማሳያ ነው ብለዋል” ሚኒስትሩ፡፡ ጊቤ ሶስት የውሃ ኃይል ማመንጫ በአሁኑ ሰዓት 1870 ሜጋ ዋት ሃይል የማመንጨት አቅም ያለው ላይ ሲሆን አሁን ግንባታው 39 በመቶ የደረሰው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ደግሞ ሲጠናቀቅ ደግሞ 2160 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል እንደሚያመነጭ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ “የኮይሻና የሕዳሴ ግድቦች ሲጠናቀቁ አሁን ያለውን የኤሌክትሪክ ኃይል ምርት በ170% በማሳደግ በ2022 ሙሉ በሙሉ ለዜጎች ኃይል ለማቅረብ በምናደርገው ጥረት ላይ ትልቁን ሚና ይጫወታሉ” ማለታቸውን የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፓሬሽን ዘግቧል። በጉብኝቱ ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ተገኝተዋል። መስከረም 24 ቀን 2013 ዓ/ም

photo content

photo content

የወላይታ ሶዶ የኮንቨርተር ጣቢያ የሙከራ (commissioning) ስራ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል .........................///......................... የወላይታ ሶዶ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የሙከራ ስራ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡ በፕሮጀክቱ የሰብስቴሽን ኢንቻርጅ ባለሙያው አቶ ሃብታሙ ግርማ እንደገለፁት የኮንቨርተር ጣቢያውን የግንባታ ስራ በማጠናቀቅ በአሁኑ ወቅት የሙከራ ስራው በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ከወላይታ ሶዶ ከተማ 7 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ እየተገነባ የሚገኘውን የኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የሙከራ ስራ በቅርቡ በማጠናቀቅ የፍተሻ ስራውን ለመጀመር እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ እንደሚገኝም አቶ ሃብታሙ ገልፀዋል፡፡ እንደ አቶ ሃብታሙ ገለፃ የሙከራ ስራው ከስራ ተቋራጩ፣ ከአማካሪ ድርጅቱ እንዲሁም ከተቋሙ የተለያዩ የስራ ክፍሎች በተውጣጡ ባለሙያዎች በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የኮንቨርተር ጣቢያው ከወላይታ ሶዶ ነባሩ የማከፋፈያ ጣቢያ የወጡ አራት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመሮች እንዳሉት ነው ባለሙያዉ የጠቆሙት፡፡ ጣቢያው በዲዛይን፣ በቴክኖሎጂ እና በአይነቱ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው እንደሆነ ያነሱት አቶ ሃብታሙ ይህም ቀጥተኛ ዥረት (Directe current) መሆኑ እና 12 ኮንቨርተር ትራንስፎርመሮች የተገጠሙለት በመሆኑ ከሌሎች ማከፋፈያ ጣቢያዎች ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡ ይህ ባለ 500 ኪሎ ቮሎት የኮንቨርተር ጣቢያ ሁለት ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ማስተላለፊያ መስመር የማሻገር አቅም ያለው እንደሆነም ነው ባለሙያው ያብራሩት። የፕሮጀክቱ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ኬንያን ጨምሮ ታንዛኒያን እና ሌሎች የአፍሪካ ሃገራትን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎም ይጠበቃል፡፡ የኢትዮ- ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና የኮንቨርተር ጣቢያ መገንባት የክፍለ-አህጉራዊ የኃይል ትስስርን ከማጠናከሩም ባሻገር የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሬ ለማሳደግ ያግዛልም ተብሏል፡፡ የፕሮጀክቱን የግንባታ ስራ ሲመንስ የተሰኘ የጀርመን ኩባንያ በማከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን በማማከር ስራው ላይ ደግሞ ትራክ ቤል የተሰኘ ኩባንያ ተሳትፎበታል፡፡ በኢትዮጵያ በኩል በመገንባት ላይ የሚገኘው የኢትዮ -ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር እና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት የግንባታ ስራ ቢጠናቀቅም ወደ አገልግሎት ለማስገባት የዚህ ፕሮጀክት አካል የሆነውንና በኬኒያ መንግስት በኩል እየተገነባ የሚገኘውን ፕሮጀክት መጠናቀቅ ይጠብቃል ነው የተባለው፡፡ የኮንቨርተር ጣቢያው ከዓለም ባንክና ከአፍሪካ ልማት በብድር በተገኘ ከ285 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት በመከናወን ላይ የሚገኝ መሆኑን ከፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ ከዚህ ውስጥም 243 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላሩ በዓለም ባንክ እንዲሁም ቀሪው ከ42 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላዩ ደግሞ በአፍሪካ ልማት ባንክ የሚሸፈን ነው ተብሏል፡፡ የኮንቨርተር ጣቢያው የግንባታ ስራ በ2009 ዓ.ም በይፋ መጀመሩ ይታወሳል፡፡

photo content

photo content
+1

የቢሾፍቱ፣ ዱከም እና ሞጆ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እየተከናወነ ነው ...................///............... የቢሾፍቱ ባለ 400/230/15፣ የዱከም ባለ 230/15 እና የሞጆ ባለ 230/15 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሽመልስ አብዲሳን ጨምሮ የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንዲሁም አባ ገዳዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

photo content

የቱለፋ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ ለምርቃት ዝግጁ ሆነ ..................///................... በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሀገረማርያም ወረዳ የተገነባው የቱለፋ ባለ 132/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው መጠናቀቁንና አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የመካከለኛ ሪጅን ትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ዳይሬክተር አቶ አበባው ያለው እንዳስታወቁት የማከፋፈያ ጣቢያው መጠናቀቅ በቱለፋ ከተማ እና በዙሪያው በሚገኙ ከተሞች ይስተዋል የነበረውን የኃይል መቆራረጥ ከማስቀረቱም በተጨማሪ በአካባቢው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል ብለዋል፡፡ ግንባታው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ የሆነው ይህ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 63 ሜጋ ዋት አቅም መሸከም የሚችል ኤ.አይ.ኤስ ብሬከር ሲስተም (Air Insulated System) የተገጠመለትም ነው ተብሏል፡፡ አቶ አበባው እንዳሉት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው አራት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ያሉት ሲሆን አቅማቸውም 63/23/40 ሜጋ ቮልት አምፒር ነው፡፡ ከነባሩ የደብረ-ብርሃን - ለገጣፎ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር ላይ መስመር በመዘርጋት ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ጋር ማገናኘት ተችሏል ብለዋል። በአሁኑ ሰዓት በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ባለ 33 ኪሎ ቮልት መስመር ብቻ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝም ነው ኃላፊው የጠቆሙት፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያውን የገነባው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን (የራስ ኃይል) ሲሆን ግንባታውን ለመጨረስ ከ4 ነጥብ 8 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ወጪ ተደርጎበታል፡፡ ፕሮጀክቱን በማማከርም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የትራንስሚሽን ኢንጂነሪንግ ቢሮ ተሳትፎ አድርጓል፡፡

ጤና ሚኒስቴር ለፕሮጀክቱ ግብዐትና ሌሎች አስፈላጊ ድጋፎችን አደርጋለው አለ ......................../////................. የጤና ሚኒስቴር በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ኮሮናን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዝ አስታወቀ። የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ኤባ አባተ፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትርና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር አብርሃም በላይ እንዲሁም የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች በፕሮጀክት ሳይቱ ላይ ኮሮናን ለመከላከል እየተሰራ ያለውን ስራ ገምግመዋል። የህዳሴ ግድብ የሀገራችን ብልጽግና የሚረጋገጥበት ታላቅ ፕሮጀክት በመሆኑና በተያዘው ዓመት ለማሳካት የታለመው የሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌትና የቅድሚያ ኤሌክትሪክ ማመንጨት እቅድ በኮቪድ ምክንያት እንዳይስተጓጎል ለፕሮጀክቱ ቅድሚያ በመስጠት በግብዐትና ሌሎች አስፈላጊ ድጋፎችን በማድረግ ከተቋሙ ጋር በጋራ ለመስራት ቃል ገብተዋል። ይህን የሚከታተልና የሚያስፈጽም ከጤና ሚኒስቴር፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ጤና ቢሮና ከህዳሴ ፕሮጀክት የተውጣጣ ኮሚቴ በማዋቀር የተጀመረውን የኮሮና መከላከል ስራ በተጠናከረ መልኩ የሚከታተል ግብረ ኃይል እንደሚቋቋም ሚኒስትሯ ገልፀዋል። ቫይረሱን ለመከላከል የሚሰራው ስራ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የስራ ኃላፊዎቹ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። መስከረም 16ቀን 2013 ዓ/ም

በዱከም እና በሞጆ የተገነቡት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ሊመረቁ ነው …………………./////……………….. ለዱከም እና ለሞጆ ከተሞችና እና አካባቢያቸው እንዲሁም በዙሪያቸው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች የኃይ
በዱከም እና በሞጆ የተገነቡት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ሊመረቁ ነው …………………./////……………….. ለዱከም እና ለሞጆ ከተሞችና እና አካባቢያቸው እንዲሁም በዙሪያቸው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች የኃይል ፍላጎት ምላሽ የሚሰጡ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ተጠናቀቀ፡፡ ከአዲስ አበባ በ30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በዱከም ከተማ የተገነባው ባለ 230/15 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ፣ የፍተሻ እና የሙከራ ስራ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል፡፡ ከአዲሱ የቢሾፍቱ 400/230/15 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ተነስቶ እስከ ዱከም ማከፋፈያ ድረስ 16 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ጥንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታም ተከናውኗል፡፡ በሞጆ ከተማ የተገነባው ባለ 230/15 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያም በተመሳሳይ የግንባታ፣ የፍተሻ እና የሙከራ ስራው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል፡፡ ሁለቱም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጥንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር እና አስር ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ያሏቸው ሲሆን ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች ተተክለውላቸዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ከጊንጪና ቢሾፍቱ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ጋር በአንድነት በቅርቡ ይመረቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም.

የኃይል ሽያጭ ስምምነት ተደረገ ………………..////………………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል ሽያጭ ስምምነት አደረጉ፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ
የኃይል ሽያጭ ስምምነት ተደረገ ………………..////………………… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል ሽያጭ ስምምነት አደረጉ፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የኢትየጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈረው ተሊላ ተፈራርመዋል፡፡ ትናንት በተካሄደው የፊርማ ሥነ-ስርዐት ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ስምምነቱ ተቋማቱ በተሻለ መንገድ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡና የጋራ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል፡፡ ተቋማቱ በኃይል ኔትወርክ የተገናኙ እንደመሆናቸው ስምምነቱ ያላቸውን ቅንጅትና ትብብር የበለጠ ለማጠናከር እና የስራ አፈጻጸማቸውን ለማሻሻል የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈረው ተሊላ በበኩላቸው መስሪያ ቤቶቹ የተሰጣቸውን ኃላፊነት በህግ በተወሰነው አግባብና በስምምነታቸው መሰረት እንዲወጡ እንደሚያስችላቸው ነው ተናግረዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማርኬቲንግ እና ገበያ ልማት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ታምራት እንደተናገሩት ስምምነቱ የሁለቱ ተቋማትን የኤሌክትሪክ ግብይት በህግ አግባብ ለማከናወን ያስችላቸዋል፡፡ በተቋማቱ መካከል ቀደም ሲል የነበረው የኤሌክትሪክ ግብይት በ40/60 ሽያጭ ስምምነት ላይ የተመሰረተ ሲሆን የአሁኑ ስምምነት ግን የቀድሞውን አሰራር በመለወጥ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሚገጠም ቆጣሪ ንባብ ላይ ተመስርቶ የሚከናወን ይሆናል፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric መስከረም 13 ቀን 2013 ዓ.ም.

የጊንጪ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ …………………../////…………….. ላርሰን ኤንድ ቱብሮ በተባለ የህንድ ኩባንያ የተገነባው የጊንጪ ባለ 230/15 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪ
የጊንጪ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ …………………../////…………….. ላርሰን ኤንድ ቱብሮ በተባለ የህንድ ኩባንያ የተገነባው የጊንጪ ባለ 230/15 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነ፡፡ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳዊት ገ/እግዝአብሔር እንዳስታወቁት የማከፋፈያ ጣቢያው መጠናቀቅ በጊንጭና በዙሪያው የሚገኙ ከተሞችን የኃይል መቆራረጥ ከማስቀረቱም በተጨማሪ ወደ ፊት አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል የሚያገኘው ከገፈርሳ - ጌዲዮን ከተዘረጋው ባለ 230 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ሲሆን ሁለት ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች ተተክለውለታል፡፡ ጣቢያው ሁለት ጥንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ እና 10 ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ በ2008 ዓ.ም የተጀመረው ይህ ፕሮጀክት አጠቃላይ ወጪው 67 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ የፌስ ቡክ ገፃችንን በመወዳጀት ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ https://www.facebook.com/Ethioelectric መስከረም 13 ቀን 2013 ዓ.ም.

photo content
+2