es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 537 suscriptores, ocupando la posición 8 357 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 176 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 537 suscriptores.

Según los últimos datos del 01 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 22, y en las últimas 24 horas de 4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.24%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.50% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 921 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 563 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 537
Suscriptores
+424 horas
-357 días
+2230 días
Archivo de publicaciones
እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ መልካም
እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡  በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ ከልብ እመኛለሁ፡፡   አሸብር ባልቻ፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ

photo content

በበዓሉ ወቅት የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም ዝግጅት ተደርጓል ..........///............ ለትንሳኤ በዓል የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም ዝግጅት መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ የማነ ኢሳይያስ እንዳስታወቁት በዋዜማውና በበዓሉ ዕለት የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም ለማድረግ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ሁሉም ዩኒቶች ላይ የፍተሻ ሥራ በማከናወን ዩኒቶች ዝግጁ ተደርገዋል፡፡ የኃይል መቆራረጥ እንዳያጋጥም በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይም የቅድመ መከላከልና የፍተሻ ሥራዎች መከናወናቸውንም ጠቁመዋል፡፡ በበዓሉ ዕለት በመላ ሀገሪቱ የሚኖረው የኃይል ፍላጎት 2 ሺህ 850 ሜጋ ዋት ሊደርስ እንደሚችል በመተንበይ ይህን ታሳቢ ያደረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መከናወናቸውን ነው ያነሱት፡፡ በበዓሉ ወቅት ይኖራል ተብሎ ከታሰበው የኃይል ፍላጎት በላይ ከመጣ ፍላጎቱን ማስተናገድ የሚያስችል ተጨማሪ 350 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመጠባበቂያነት ዝግጁ መደረጉንም አስታውቀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ በበዓሉ ወቅት የኃይል መቆራረጥ እንዳይከሰት ለማድረግ ወደ ጎረቤት ሀገራት ኤክስፖርት ከሚደረገው እና ከተቋሙ በቀጥታ ኃይል ከሚያገኙ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ከዚህ በፊት ከሚያገኙት ኃይል የመቀነስ ሁኔታ ሊኖር ይችላል፡፡ በበዓሉ ወቅት የኃይል አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም እና በተገቢው ሁኔታ ለተጠቃሚው እንዲደርስ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና ከአገልግሎቱ የክልል ሥራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከሁሉም ሪጅኖች ጋር ውይይት ተካሂዷል ብለዋል፡፡ የኃይል መቆራረጥ እንዳይኖር ከአገልግሎቱ በቀጥታ ኃይል የሚያገኙ የመካከለኛ ቮልቴጅ ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች ከዚህ በፊት ከሚጠቀሙት መቀነስ እንዲችሉ ከአገልግሎቱ ጋር ከመግባባት ላይ መደረሱንም አቶ የማነ ተናግረዋል፡፡ በትንሳዔ በዓልና በረመዳን ፆም የተነሳ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን ለመፍታት እና በሚሰራው ሥራ ላይ ውሳኔ የሚያስፈልጋቸው ችግሮችን መፍትሔ ለመስጠት በየደረጃው የሚገኙ የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል የሥራ ኃላፊዎች በኦፕሬሽን ሥራው ላይ እንደሚገኙ ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 06 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

ተቋሙ ከ78 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለሠራተኞች ሰርቪስ የሚያገለግሉ የአምስት አውቶብሶች ግዥ ፈፀመ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከቢሾፍቱ የአውቶሞቲቭ ማምረቻ ፋብሪካ ከ78 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የገዛቸውንና በዋናው መስሪያ ቤት ለሚገኙ ሠራተኞች የሰርቪስ አገልግሎት የሚሰጡ አምስት አውቶብሶችን ተረከበ። አውቶብሶቹን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቴክኒሽያንና ዋና ጉዳይ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ከማል አሊ እና በፋብሪካው የሻንሲ ወርክ ሾፕ ኃላፊ የሆኑት አቶ ተስፋሁን ተረፈ ተረካክበዋል። አቶ ከማል አውቶብሶችን በተረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት አውቶብሶቹ በስምምነቱ ላይ በተቀመጡ መስፈርቶች መሠረት መገጣጠማቸውን የማረጋገጥ ሥራ ተከናውኗል። ለአውቶብሶቹ ግዥ 78 ነጥብ 16 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደተደረገ የጠቆሙት አቶ ከማል አውቶብሶችን ውስጣዊ ሁኔታቸውን እና ሌሎች አክሰሰሪዎች መሟላታቸውን በማረጋገጥ መረከባቸውን ተናግረዋል። በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ኃይላይ ተስፋዬ በበኩላቸው ለሠራተኞች ምቹ የሆኑ ለመፍጠር ተቋሙ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ተሽከርካሪዎችን ለማቅረብ በትኩረት እየሰራ ይገኛል። ተቋሙ በአሁኑ ወቅት ከተለያዩ መንግስታዊ ተቋማትና የግል ባለንብረቶች የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን በመከራየት በሥራ መግቢያና መውጫ ሰዓት ለሠራተኞች የሠርቪስ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ያነሱት ዳይሬክተሩ በዚህም ከጥራት እና ከሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ በርካታ ጥያቄዎች በሠራተኞች በኩል ሲነሱ እንደነበር አስታውሰዋል። ተቋሙ በአሁኑ ወቅት ለሰርቪስ ኪራይ በወር እስከ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን የሚጠጋ ብር ወጪ እንደሚያደርግም አቶ ኃይላይ አመላክተዋል። የአውቶብሶቹ ግዥ የሁለቱን ተቋማት ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ የተፈጸመ መሆኑን እና አውቶብሶች በሠራተኞች የሚነሡ ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ ለተቋሙ ወጭ ቅነሳ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖራቸው እና ሠራተኛው ተረጋግቶ ሥራውን እንዲያከናውን እንደሚያግዘው ተናግረዋል። ተቋሙ በሀገር ውስጥ የተገጣጠሙ አውቶብሶችን ግዥ መፈጸሙ ከግዥ በኋላ የሚካሄዱ የጥገና ሥራዎችን በአቅራቢው በኩል እንዲከናወኑ በማድረግ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በወቅቱ ለመፍታት ያግዛል ብለዋል። አውቶብሶቹ የታርጋ እና የኢንሹራንስ ሂደታቸው እንደተጠናቀቀ ረጅም ርቀት ባላቸው መስመሮች ላይ በመግባት በቅርቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ ጠቁመዋል። አውቶብሶቹ እያንዳንዳቸው በወንበር 43 ሰው የመጫን አቅም እንዳላቸውም ተመላክቷል። በቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ማምረቻ ፋብሪካ የኦፕሬሽን መምሪያ ኃላፊ ተወካይ አቶ ዮሐንስ ገብሬ በበኩላቸው ተቋማቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማትና ድርጅቶች የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን እያቀረበ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ ከዚህ በፊት የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን ለተቋሙ ማቅረቡንም በማስታወስ ተቋማቸው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የረጅም ጊዜ የሥራ ግንኙነትእንዳለው ተናግረዋል። ተቋማቸው ተሽከርካሪዎችን ገጣጥሞ መሸጥ ብቻ ሳይሆን ደንበኞቹን በተለያዩ መሳሪያዎችና በሰው ኃይል የማጎልበት ሥራ ስለሚያከናውን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣይ የቴክኒክና የሹፍርና ስልጠናዎችን እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል። በአሁኑ ወቅት ርክክብ የተካሄደባቸው አውቶብሶች ከዚህ በፊት ፋብሪካው ሲያቀርባቸው ከነበሩት አውቶብሶች ከመሬት ባላቸው ከፍታ፣ በነዳጅ ፍጆታቸው፣ በወንበር ብዛት እና በተገጠሙላቸው የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች የተሻሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በ14 መስመሮች ለሠራተኞች የሰርቪስ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 12ቱ በኪራይ ተሽከርካሪዎች የሚሰጡ ናቸው። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 04 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ተቋማችን በፕሮኪዩርመንት 1ኛ የስራ መደብ ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የቅጥር ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም ለፈተናው ብቁ የሆናችሁ ተፈታኞች ሚያዚያ 17 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ንግድ ስራ ት/ቤት ( ኮሜርስ) በመገኘት ፈተናውን እንድትወስዱ ጥሪ እናቀርባለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

photo content
+4

የጥናት፣ ምርምርና ሥልጠና ማዕከሉ ሥራ መጀመር የጣቢያውን አሠራርን እያቀላጠፈ ነው ……....///…….... በጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተቋቋመው የጥናት፣ ምርምርና ሥልጠና ማዕከል የኃይል ማመንጨት ኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን እያገዘ መሆኑ የጣቢያው ኃላፊ ገለፁ፡፡ ኃላፊው አቶ ሀብታሙ ሰሙ እንደገለፁት ጊቤ 3 በሀገሪቱ ትልቁ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በመሆኑ ሥራውን ያለምንም ችግር ማከናወን እንዲችል፣ ለሰው ኃይል ልማት፣ ለጣቢያው ግዙፍ ንብረት አጠባበቅና በዕውቀት ላይ የተመሠረተ አሠራርን ለመተግበር ማዕከሉ እንዲቋቋም ተደርጓል፡፡ በማዕከሉ የሚቀረጹት ዘመናዊ አሰራሮች ሲተገበሩ በልማዳዊ አሠራርና በግለሰቦች ዕውቀት ላይ የተንጠለጠሉ አሠራሮችን አስቀርቶ ችግር ፈቺ የሆነና ዘላቂ የአሠራር ሥርዓት ለማስፈን ያስችላል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በጣቢያው ዘመናዊ የአሠራር ሥርዓት ለመዘርጋት ጊቤ ፕላስ (+) የተባለ ሶፍትዌር በልጽጎ በጣቢያው ብቻ በሚያገለግለው ሎካል ኤርያ ኔትወርክ የማመንጫ ጣቢያው የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ እየተመራ ነው፡፡ በጊቤ ፕላስ ሶፍትዌር የእያንዳንዱን የማሽን ታሪክ፣ የንብረት አያያዝ ሥርዓቱን፣ የሰው ኃይሉንና የሚጠቀምባቸውን መሣሪያዎች (tools ) በቀላሉ ለማወቅ እንደሚቻል ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ የጊቤ 3 የጥናት፣ ምርምርና ሥልጠና ማዕከል በጣቢያው የሰለጠነ የሰው ኃይል እንዲኖርና ባሉት የጥገና መሳሪያዎች በአግባቡ የሚጠቀም ሠራተኛ በማብቃት ከሥልጠና በፊት ለአንድ ሥራ ክንውን ይወስድ የነበረውን ሰዓት በግማሽ ቀንሶ በጥራት መፈፀም እንዳስቻለ አቶ ሀብታሙ ገልፀዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሚያዚያ 02 ቀን 2015 ዓ.ም

የኘሮግራም ግብዣ በተቋማችን የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማስተዋወቅና በየጊዜው በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየደረሱ ያሉ የስርቆትና ውድመት ወንጀሎችን ለመከላከል በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
የኘሮግራም ግብዣ በተቋማችን የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማስተዋወቅና በየጊዜው በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየደረሱ ያሉ የስርቆትና ውድመት ወንጀሎችን ለመከላከል በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን መደበኛ የሬዲዮና ቴሌቭዥን ፕሮግራም እንዲሁም በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሳምታዊ የጋዜጣ ህትመት እንደጀመርን መግለፃችን ይታወሳል። ስለሆነም ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 3:30 እስከ 4:00 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዜና ቻናል፣ ዘወትር እሁድ  ከምሽቱ 12:10 እስከ 12:40 በኦሮምኛ ቋንቋ  በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የኦሮምኛ ቋንቋ ቻናል እና  ዘወትር  ዓርብ ከምሽቱ 3:00 እስከ 3:30 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ሬድዮ ብሄራዊ አገልግሎት የሚተላለፉ ፕሮግራሞቻችንን እንዲሁም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ዘወትር ሰኞ የሚወጣውን ህትመት እንድትከታተሉ በአክብሮት ግብዣችንን እናቀርባለን። ስለምትከታተሉን አስቀድመን እናመሰግናለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ሚያዚያ 01 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

ፕሮጀክቱ ለከተማዋ የዘመናት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ ነው ……...///…….... በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን ደብረታቦር ከተማ አዲስ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ የተመራው የተቋሙ የልዑካን ቡድን ከደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር አዲስ በሚገነባው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ዙሪያ ውይይት አካሂዷል። ሥራ አስፈፃሚው በውይይቱ ላይ እንደገለፁት በከተማዋ አንድ ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያ የሚገኝ ቢሆንም ጣቢያው የነዋሪውን የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ጥያቄ በዘላቂነት መፍታት የሚያስችል አይደለም፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ፕሮጀክቱ ከካሳ ክፍያ፣ ከፀጥታ እና ከሲሚንቶ አቅርቦት ጋር የተያያዙ መሰል ችግሮች እንዳያጋጥሙት የከተማው አስተዳደር ከተቋሙ ጋር በቅርበት መስራት እንደሚጠበቅበት ነው ያሳሰቡት። የደብረታቦር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ ደሳለኝ በላቸው በበኩላቸው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት የከተማዋን የዘመናት የኤሌክትሪክ ኃይል ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ ነው። የፕሮጀክቱ መገንባት ለደብረ ታቦር ከተማ ብቻ ሳይሆን በአካባቢው ለሚገኙ አራት ወረዳዎች ጭምር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ነው ተቀዳሚ ከንቲባው የጠቆሙት። የፕሮጀክቱ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ እንዲሆን ለማድረግ ከተማ አስተዳደሩ ቁርጠኛ መሆኑን የገለፁት አቶ ደሳለኝ ግንባታው የሲሚንቶና የሌሎች ግብዓቶች እጥረት እንዳያጋጥመው የቅርብ ክትትል እንደሚያደርጉም አረጋግጠዋል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር በከተማዋ ለሚገኙ ነባር እና አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች የኃይል ፍላጎት ጥያቄ አስተማማኝ ምላሽ ለመስጠት ስለሚያስችል የከተማዋን ኢንቨስትመንት የመሳብ አቅም አሁን ካለው በእጥፍ ያሳድጋል ብለዋል። ከተማዋን አቋርጦ የሚያልፈው የባህርዳር- ወልዲያ- ኮምቦልቻ ባለ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ የስርቆት እና የፀጥታ ስጋቶችን ለመቅረፍም የከተማ አስተዳደሩ ህግ የማስከበር ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለደብረታቦር ከተማ የኢንቨስትመንት ፍሰት መጨመር እና ለቱሪዝም ዕድገት እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ በማድነቅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የልዑካን ቡድኑ ደብረታቦር የሚገኘውን የባህርዳር- ወልዲያ- ኮምቦልቻ ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዕቃ ግምጃ ቤት ጎብኝቷል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

በተቋሙ መተግር የጀመረው የሳፕ ሲስተም 95 በመቶ የወረቀት ሥራዎችን ያስቀራል ………///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚሰጡ አገልግሎቶችንና አሰራሮችን ለማዘመን ሳፕ ከተባለው የጀርመን ሶፍትዌር አምራች ኩባንያ ተገዝቶ ተግባራዊ የተደረገው የሳፕ ሲስተም ወደ ሁለተኛው ምዕራፍ የትግበራ ምዕራፍ ተሸጋገረ፡፡ የትግበራው የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ዛሬ በስካይላይት ሆቴል ሲካሄድ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት በሁለተኛው ምዕራፍ የሚተገበሩት የሳፕ ቴክኖሎጂዎች የተቋሙን አሰራር ወደ ዲጂታል አሰራር የሚያሸጋግሩ ናቸው፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ ወቅት የታዩ ክፍተቶችን በመሙላት ሁለተኛውን ምዕራፍ በተያዘለት ዕቅድ መሰረት ማሳካት እንደሚቻል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡ ሠራተኛውን ከቴክኖሎጂው ጋር በማስተዋወቅ በመጀመሪያው ምዕራፍ ያጋጠሙ የዕውቀት ክፍተቶችን በሥልጠና ለመሙላት ትኩረት እንዲደረግ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሳስበዋል፡፡ እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለፃ የሳፕ ሲስተምን በተቋሙ ለማስተግበር እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትብብር ትልቅ ውጤት በማስገኘቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በሁለተኛው የሳፕ ሲስተም የትግበራ ምዕራፍ የሚተገበሩ ሞጁሎችን አስመልክተው ማብራሪያ የሰጡት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ቺፍ ኢንፎርሜሽን ኦፊሰር አቶ ጌትነት ታደሰ በበኩላቸው ፕሮጀክቱን ሰርቶ ለማጠናቀቅ የ9 ወራት ጊዜ መቀመጡን ገልፀዋል፡፡ ለፕሮጀክቱ መሳካት የሁለቱ ተቋማት የጋራ ትብብር አስፈላጊ በመሆኑ ተቋማቱ በሥራው የሚሳተፉ ቡድኖችን በማዋቀር እና መረጃዎችን በሚገባ በማደራጀት ወደ ሥራ መግባት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ የታዩ ችግሮችን በመቅረፍና መታረም ያለባቸውን ሞጁሎች በማስተካከል ሁለተኛውን ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ በጥራትና በስኬት ለማጠናቀቅ የጋራ ግምገማ ለማድረግ መታሰቡን ጠቁመዋል፡፡ ሁለተኛው ምዕራፍ የሳፕ ትግበራ እንደ ትሬዠሪ፣ የፈንድ አስተዳደር እና የንብረት ኪራይ እንዲሁም ከመጀመሪያው ምዕራፍ የቀጠሉ የፋይናንስ መተግበሪያ ሞጁሎችን ጨምሮ ከሎጅስቲክስ፣ ከቅጥር፣ ከቢ ኤስ ሲ፣ ሰው ሀብት አስተዳደር እና ሌሎች የአገልግሎት ትግበራዎች ጋር የተያያዙ ሞጅሎች ይኖሩታል፡፡ ሞጁሎቹ ሙሉ በሙሉ ሲተገበሩ ጠንካራ የሀብት ቁጥጥር ስርዓት ለመዘርጋት፣ የተቋሙን ወጭ ለመቀነስና ሥራን ለማቀላጠፍ እና መረጃዎችን ለማጥራት እንዲሁም በተቋሙ ያለውን የወረቀት ሥራ 95 በመቶ እንደሚያስቀሩ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገልጿል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

የማመንጫ ጣቢያዎቹ ሠራተኞች በከተማ ግብርና ላይ ውጤታማ ሥራ እያከናወኑ ነው ……..///……. የአዋሽ 2 እና 3 ማመንጫ ጣቢያዎች ሠራተኞች ከተሰጣቸው ኃይል የማመንጨት ተልዕኮ በተጨማሪ በከተማ ግብርና ውጤታማ ሥራ እያከናወኑ መሆኑን የጣቢያዎቹ ተወካይ ኃላፊና የጥገና ክፍል ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሮቤል አበበ እንዳስታወቁት በጣቢያዎቹ እየተከናወነ የሚገኘው የጓሮ እርሻ ልማት በጣቢያዎቹ የሠራተኞች የመረዳጃ ዕድር በባለቤትነት የሚመራ ነው፡፡ የጣቢያዎቹ ሠራተኞች በቅርብ የሚደርሱ የተለያዩ የጓሮ አትክልቶችንና ፍራፍሬዎችን እያለሙ ከራሳቸው አልፎ ለአካካቢው ማህበረሰብ እና ነጋዴዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ ከልማቱ በፍትሐዊነት ተጠቃሚ እየሆኑ እንደሚገኙ አቶ ሮቤል ተናግረዋል፡፡ ሥራው ሠራተኛው ሰዓቱን በአግባቡ እንዲጠቀም ለማድረግ እና በተቋሙ ላይ የባለቤትነት ስሜት ተሰምቶት ሥራውን በአግባቡ እንዲያከናዉን ለማድረግ እንዳገዘም ነው ኃላፊው የገለፁት፡፡ በጣቢያው እየተከናወነ ያለው የልማት ሥራ ከዚህ በፊት በነበሩ የተቋሙ አመራሮች እውቅና ተሰጥቶት ሲሰራ የነበረው ሲሆን የአሁኑ ትውልድ ሠራተኞችም የተጀመረውን በማስቀጠል ለቀድሞ አመራሮች እውቅና መስጠት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡ የጓሮ እርሻ ልማቱን ሠራተኞች በትርፍ ጊዜያቸው በራሳቸው አቅም እና የተወሰኑ ሠራተኞችን በመቅጠር እያከናወኑት እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ ይህም በአካባቢው ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ሮቤል የማመንጫ ጣቢያዎቹ የሚገኙበት አካባቢ በደን የተሸፈነ መሆኑ የግብርና ሥራው አካባቢውን ጽዱ ለማድረግና ምቹ የሥራ ቦታ ለመፍጠር አግዟል ብለዋል፡፡ የጓሮ እርሻ ልማቱ ጣቢያው ባለው ውስን ቦታ ላይ በመስራት ከሠራተኞቹ አልፎ ወገንንም መጥቀም እንደሚችል ያሳየበትና "አዋሽ የአትክልት ቦታ ማዕከል ናት” የሚለውን ያረጋገጠ መሆኑን አቶ ሮቤል አንስተዋል፡፡ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቹ ምቹ ያልነበረ መሬትን በማልማት አካባቢዉን መቀየር በመቻላቸው የከተማ አስተዳደሩ ለጣቢያዎቹ ምስጋና ማቅረቡን አቶ ሮቤል አስታውቀዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 28 ቀን 2015 ዓ.ም

የኘሮግራም ግብዣ በተቋማችን የሚከናወኑ ሥራዎችን ለማስተዋወቅና በየጊዜው በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ እየደረሱ ያሉ የስርቆትና ውድመት ወንጀሎችን ለመከላከል በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 3:30 እስከ 4:00 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዜና ቻናል፣ ዘወትር እሁድ ከምሽቱ 12:10 እስከ 12:40 በኦሮምኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የኦሮምኛ ቋንቋ ቻናል እንዲሁም ዘወትር አርብ ከምሽቱ 3:00 እስከ 3:30 በአማርኛ ቋንቋ በኢትዮጵያ ሬድዮ ብሄራዊ አገልግሎት እንድትከታተሉ ግብዣ ማቅረባችን ይታወሳል፡፡ ፕሮግራሙን የተከታተላችሁትን እያመሰገንን በተለያዩ ምክንያቶች ፕሮግራሙን መከታተል ላልቻላችሁት ደግሞ ሊንኩን አስቀምጠናል፡፡ እንድትመለከቱት እንጋብዛለን። https://youtu.be/qOOXO56RXJc https://youtu.be/Pg_NDJ7tEEk የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ መጋቢት 27 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

በክልሉ የሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን መጠበቅ የሁሉም ዜጋ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል ……...///……... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚገነባቸው ከፍተኛ የኃይል መሠረተ ልማቶች በፍጥነት እንዲጠናቀቁ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አስታወቀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኃይል ማከፋፈያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ የተመራ የልዑካን ቡድን ከክልሉ ዕሰ መስተዳድር የመሠረተ ልማት አማካሪ እና የባህርዳር ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ ጋር በግንባታ ላይ በሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች አፈፃፀም ዙሪያ ተወያይቷል፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ክብሮም ካህሳይ በውይይቱ ላይ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ክልሉ የሚያስፈልጉትን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ለማሟላት በቁርጠኝነት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በመገንባት ላይ ካሉት ፕሮጀክቶች መካከል በባህርዳር-ወልዲያ- ኮምቦልቻ እና በአዘዞ-ጭልጋ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ላይ ከካሳ ክፍያ፣ ከስርቆት እና ከፀጥታ ጋር ተያይዘው የሚስተዋሉ ችግሮችን ለኃላፊዎቹ አስረድተዋል። በግንባታ ላይ የሚገኙት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ተጠናቀው ለአገልግሎት ዝግጁ እንዲሆኑ የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን እገዛ እንዲያደርግም ጠይቀዋል። ተቋሙ በሀገር ደረጃ ከመቶ በላይ የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታዎችን ለማከናወን ዕቅድ መያዙን የጠቆሙት ሥራ አስፈፃሚው ፕሮጀክቶቹ የፋይናንስ አቅርቦታቸው ሲመቻች ግንባታቸው እንደሚጀመር ገልፀዋል። በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የርዕሰ መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት አማካሪ አቶ ደሴ አሰሜ እንደገለፁት ክልሉ በመሠረተ ልማት ወደኃላ ከቀሩ አካባቢዎች አንዱ በመሆኑ የህዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ዝርጋታዎች በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ። የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና ፍላጎት ያለመጣጣም ችግሮች በክልሉ በስፋት እንደሚስተዋሉ የጠቆሙት አቶ ደሴ ችግሩን ለመቅረፍም ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር በቅርበት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል። በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀመውን ስርቆት ለመከላከል ክልሉም ሆነ ተቋሙ እስከ ቀበሌ ድረስ ባለው የመንግሥት መዋቅር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። ይሁንና በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች አመራሩ እየተገነቡ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን በባለቤትነት ተቀብሎ የማስፈፀም አቅም አናሳ መሆኑ ለችግሩ መባባስ አንዱ ምክንያት ነው ብለዋል። የፀጥታ እና የፍትህ አካላት በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ የስርቆት ወንጀል በሚፈፅሙ ህገ- ወጦች ላይ አስተማሪ እርምጃ እንዲወስዱ እና ህብረተሰቡም በአካባቢው የሚገኙ የኤሌክትሪክ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን እና ሽቦዎችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል። የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አስራቴ ሙጬ በበኩላቸው ከተማ አስተዳደሩ ከባህርዳር- ወልዲያ- ኮምቦልቻ የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ጋር ተያይዘው ለሚነሱ የካሳ እና መሬት ግምት ችግሮች አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ፕሮጀክቱ የሚያልፍባቸውን እና የሚነካቸውን ሁሉንም የከተማዋ ቦታዎች ተቋሙ በጥናት ለይቶ እንዲያቀርብ የጠየቁት ኃላፊዋ ይህም የመሬት ግምት ለማከናወን እና ለልማት ተነሺዎች የካሳ ክፍያ ለማስፈፀም ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መጋቢት 27 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4