es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 544 suscriptores, ocupando la posición 8 357 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 176 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 544 suscriptores.

Según los últimos datos del 01 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 22, y en las últimas 24 horas de 4, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.24%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.50% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 921 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 563 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 544
Suscriptores
+424 horas
-357 días
+2230 días
Archivo de publicaciones
በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች በስፋት ወደ ሥራ መግባታቸው ወጪን ለመቀነስ የጎላ ፋይዳ እንዳላቸው ተገለፀ ……...///……... የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በስፋት ወደ ሥራ መግባታቸው ለነዳጅ የሚወጣ ወጪን ከመቀነስ አኳያ ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያ ለመገንባት በተዘጋጀው የማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ሥራ አስፈፃሚው አቶ አንዱዓለም ሲኣ እንደገለፁት ህብረተሰቡ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ሲጠቀም እስከ 50 በመቶ የትራንስፖርት ወጪ ይቀንሳሉ። ህብረተሰቡ በኃይል መሙያ ጣቢያዎች መስፋፋት የተነሳ የኃይል መቆራረጥ እንዳያጋጥመው ለመሙያ ጣቢያዎቹ ራሱን የቻለ መስመር ለመዘርጋት የሚያስችል በቂ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመዋል። በኤሌክትሪክ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያዎች ለመገንባት የፖሊሲና የህግ ማዕቀፍ ክፍተቶች እንዳያጋጥሙ ከወዲሁ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል። ተቋሙ ሙሉ ለሙሉ የአረንጓዴ ኢኮኖሚን የሚደግፍ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የጠቀሱት ሥራ አስፈፃሚው የካርቦን ልቀትን ለሚቀንሱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግረዋል። እንደ አቶ አንዱዓለም ገለፃ በየጊዜው እያጋጠሙ ያሉ የኃይል መቆራረጦች በቂ ኃይል በግሪድ ቋት ውስጥ ባለመኖሩ ሳይሆን ለረጅም ዓመታት ማሻሻያ ሳይከናወንላቸው በቆዩ ያረጁ መስመሮችና ጣቢያዎች ምክንያት ነው። አሁን ላይ ለሀገር ውስጥ እና ለጎረቤት ሀገራት እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል መጠን ከተቋሙ የማምረት አቅም 86 ከመቶ ብቻ መሆኑን ጠቅሰዋል። ተቋሙ የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን በመገንባት መንግሥት የነዳጅ ፍጆታን ለመቀነስ የጀመረውን አበረታች ጅማሮ እንደሚያግዝም ነው ሥራ አስፈፃሚው የተናገሩት። ኢትዮጵያ ከውሃ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት በአፍሪካ ቀዳሚ ሀገር ስትሆን ግዙፍ የሆነ ግሪድ ከማስተዳደር አንፃር ከደቡብ አፍሪካ እና ግብፅ ቀጥላ በሦስተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ አቶ አንዱዓለም ጠቅሰዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 07 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

በዓመት 500 የኤሌክትሪክ ኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት ዕቅድ ተይዟል  ...///... በዓመት 500 የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት ዕቅድ መያዙን ካርዲናል ኢንደስትሪያል ኃላፊቱ የተወሰነ የግል ማህበር አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ካርዲናል ኢንደስትሪያል ኃላፊቱ የተወሰነ የግል ማህበር የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት የተስማሙበትን ሒደት አስመልክቶ በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫው ላይ የካርዲናል ኢንደስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሊሊያ ኃይሉ እንደገለፁት ድርጅቱ ከኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ኃይል መሙያ ጣቢያዎች ግንባታ ጎን ለጎን ዘመናዊ የፋይናንስ ሥርዓት ለመዘርጋት ታቅዷል። በአዲስ አበባና በአንዳንድ የክልል ከተሞች ለመገንባት የታቀዱት የኤሌክትሪክ ኃይል መሙያ ጣቢያዎች ብዛት በየዓመቱ እየጨመረ እንደሚሄድ ወ/ሮ ሊሊያ ተናግረዋል። በመጀመሪያው ዓመት ብቻ ለኤሌክትሪክ ኃይል መሙያ ጣቢያዎች ግንባታ እስከ 25 ሚሊዮን ዶላር ወጪ እንደሚደረግም ነው ሥራ አስፈፃሚዋ የጠቆሙት። በመግለጫው ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደተናገሩት ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚያስፈልገውን ኃይል እና ለኃይል መሙያ ጣቢያዎቹ የሚያስፈልጉ መሠረተ ልማቶችን ለማቅረብ መዘጋጀቱን ገልፀዋል። የኃይል መሙያ ጣቢያዎቹ ግንባታዎቹ በዋናነት በሀገሪቱ  ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል ፍላጎት ለማርካት ያለመ መሆኑንም ነው ያብራሩት። የኃይል መሙያ ግንባታዎች የሚከናወኑት የተቋሙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በሚገኙባቸው ቦታዎች መሆኑ ለተደራሽነቱ ትልቅ ማሳያ ነውም ብለዋል። የሚገነቡ የኃይል መሙያ ጣቢያዎች አሁን ባለው የኃይል አቅርቦት ላይ ተፅዕኖ ማሳረፍ እንዳይችሉ ራሳቸውን የቻሉ መስመሮች ከመገንባት ጀምሮ የተቋሙን የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች አቅም ሙሉ ለሙሉ ለመጠቀም የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን አቶ ሞገስ ተናግረዋል። አሁን ባለው ሁኔታ በዓመት እስከ 1ሺህ ጌጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ለኃይል መሙያ ጣቢያዎቹ ለማቅረብ የሚያስችል አቅም መኖሩን ተናግረዋል። ለተግባራዊ ለሚደረጉት የኃይል መሙያ ጣቢያዎ ኃይል በማቅረብ በዓመት እስከ አንድ ቢሊየን ብር ገቢ ይገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ሞገስ ጨምረው ጠቅሰዋል። የኃይል መሙያ ጣቢያዎቹ ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ የታሰበው አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙ የማመንጫ ጣቢያዎች ነው ያሉት ዳይሬክተሩ  ወደፊት በግንባታ ላይ ያሉት ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት ሲጀምሩ በዕቅዱ ታሳቢ እንደሚደረጉም አስረድተዋል። መንግሥት ከውጭ በሚገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ በሚመረቱ የኤሌክትሪክ የህዝብ ማመላለሻ፣ የቤት አውቶሞቢሎች እና የዕቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ላይ የጉምሩክ ቀረጥ፣ የኤክሳይዝ ታክስ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የሱር ታክስ ማሻሻያዎች ማድረጉ ለኃይል መሙያ ጣቢያዎች መገንባት ዋነኛ ምክንያት ነው ተብሏል። መንግሥት በዓመት ለነዳጅ ፍጆታ ብቻ ከ3 እስከ 3 ነጥብ 5 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ወጪ የሚያደርግ ሲሆን በዓመት በአማካይ እስከ 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ነዳጅ እንደሚቀርብም ነው መረጃዎች የሚያሳዩት። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 06 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+9

ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያ ለመገንባት የሚያስችል የማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ተካሔደ ....///...... ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያ ለመገንባት የሚያስችል የማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት በስካይ ላይት ሆቴል ተካሔደ። የግንባታ ማስጀመሪያ ሥነ- ሥርዓቱ የተካሄደው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ካርዲናል ኢንደስትሪያል ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በጋራ ለመስራት የተፈራረሙትን የመግባቢያ ስምምነት ተከትሎ ነው። በማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ከጊዜ ወደ ጊዜ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ እየጨመሩ መምጣታቸውን ጠቅሰዋል። በኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ተደራሽነት ለማሳደግ የሚቻለው የኃይል መሙያ ጣቢያ መሠረተ ልማቶችን በማስፋፋት መሆኑን ነው አቶ አሸብር የገለፁት። ተቋሙ መቶ በመቶ የአረንጓዴ ኢነርጂ ፖሊሲን በመተግበር ኤሌክትሪክ እያመነጨ እንደሚገኝ የጠቆሙት ሥራ አስፈፃሚው በሀገሪቱ ከ180 በላይ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ያሉት በመሆኑ ከዘርፉ ተዋናዮች ጋር በቅርበት በመስራት ኢንዱስትሪውን ማሳደግ እንደሚቻል ተናግረዋል። እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ተቋሙ በኤሌክትሪክ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት የሚያስችሉትን ቅድመ ዝግጅቶች አጠናቋል። በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ እንደተናገሩት ኢነርጂ ለአንድ ሀገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ወሳኝ ሚና ይጫወታል። በቅርቡ ሥራ ላይ የሚውለው የኢነርጂ ፖሊሲ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ተደራሽነት ከማሳደግ አኳያ የማይተካ ሚና እንደሚኖረው ጠቅሰዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤታቸው በዘርፉ መዋዕለ ንዋያቸውን ለሚያፈሱ ተቋማትና ባለሀብቶች አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል። የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ አሊ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በአስር ዓመት የልማት ዕቅዷ ልታከናውናቸው ካቀደቻቸው ተግባራት መካከል የኢኖቬሽን እና ኢንፎርሜሽን ሥራዎች ግንባር ቀደም እንደሆኑ ጠቅሰዋል። ዓለም የደረሰባቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ሒደት ውስጥ ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ እንደሚገኝ የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታዋ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የነዳጅ ፍጆታን ከመቀነስ አኳያ ሚናቸው የጎላ እንደሆነም ጨምረው ገልፀዋል። የትራስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርሆ ሁሴን በበኩላቸው ታዳሽ፣ ተደራሽ፣ የተቀናጀ እና የደንበኞቹን ፍላጎት የሚያረካ እንዲሁም ለአካባቢ ተስማሚና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የትራንስፖርት ሥርዓት መዘርጋት የሚኒስትር መስሪያ ቤቱ የአስር  ዓመት ዋነኛ የልማት ግብ መሆኑን ተናግረዋል። በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የነዳጅ ብክነትን ከመቀነስ ባሻገር የካርበን ልቀትን መቆጣጠር እንዲያመች የታክስ ቅነሳ እና ማበረታቻዎችን በማድረግ በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ የሚታይ ለውጥ ማስመዝገብ እንደተቻለ አቶ በርሆ ገልፀዋል። የካርዲናል ኢንደስትሪያል ኃላፊቱ የተወሰነ የግል ማህበር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሊሊያ ኃይሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን በሀገር ውስጥ ለመጀመር ስለተደረገው ቅድመ ዝግጅት እና ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ስለታቀደው ዓለም አቀፍ ቴክኖሎጂ ዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተዋል። በይፋዊ የሥራ ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው የተቋማት ተወካዮች እና የሚዲያ አካላት ተሳትፈዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 06 ቀን 2015 ዓ.ም

ሃራ፣ ድሬ ሮቃ፣ ሃሮ እና አካባቢው በዛሬው ዕለት ከሰዓት በኋላ ኤሌክትሪክ ያገኛሉ ……….////………. በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ወቅት ተዘርፎ የነበረውን የወልዲያ ዶሮ ግብር ተንቀሳቃሽ
ሃራ፣ ድሬ ሮቃ፣ ሃሮ እና አካባቢው በዛሬው ዕለት ከሰዓት በኋላ ኤሌክትሪክ ያገኛሉ ……….////………. በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት ወቅት ተዘርፎ የነበረውን የወልዲያ ዶሮ ግብር ተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በቋሚ ማከፋፈያ ጣቢያ ለመተካት ሲካሄድ የነበረው ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ዘርፍ የራስ ኃይል መምሪያ አስታውቋል፡፡ በመምሪያው የማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ሥራ አስኪያጅ አብርሃም እንደገለፁት በ15 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚያገኙ አካባቢዎች ከሳምንታት በፊት በፊት ኃይል አግኝተዋል፡፡ በ33 ኪሎ ቮልት ኃይል ለመስጠት ሲከናወኑ የቆዩ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ባለመጠናቀቃቸው እስከትናንት የካቲት 04 ቀን 2015 ዓ.ም.ድረስ ወደ ሃራ፣ ድሬ ሮቃ፣ ሃሮ እና አካባቢው የሚሄዱ መስመሮች ኃይል ሳያገኙ ቆይተዋል፡፡ ይሁንና ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችን ለመቆጣጠር የተገጠሙት የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎች ፍተሻ በተሳካ ሁኔታ ትናንት በመከናወኑ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ከዓመት ከስድስት ወር በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦባቸው ወደነበሩት ሃራ፣ ድሬ ሮቃ፣ ሃሮ እና አካባቢው የሚሄዱ መስመሮች ኃይል እንዲያገኙ ይደረጋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 05 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የኃይል ሥርጭትና አቅርቦት ለማሻሻል የሚያግዝ ስምምነት ተፈረመ ....///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ሥርጭትና አቅርቦት ለማሻሻል የሚያግዝ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ ስምምነቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሀሰን መሀመድ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በዋናነት በሀገሪቱ ያለውን የማምረቻ ኢንዱስትሪዎችን አቅም ለማዳበር የኤሌክትሪክ ኃይል ሥርጭትና አቅርቦትን ማሻሻል ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል እንደተናገሩት አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ለአምራች ኢንዱስትሪው የጀርባ አጥንት ነው። ስምምነቱ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ባለሀብቶች ወደ ማምረቻ ኢንዱስትሪው በስፋት ገብተው ዘርፉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የኤክስፖርት ምርት እና ገቢ የሚያሳድጉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል። ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ሂደት ውስጥ የሚገጥሙ ችግሮችን በጋራ ለመፍታት እና የኃይል አቅርቦት ከመቋረጡ አስቀድሞ ሊደርሱ የሚችሉ ጉዳቶችን ለመቀነስ ስምምነቱ የማይተካ ሚና እንደሚኖረው ገልፀዋል። ለአምራች ኢንዱስትሪዎች እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት በሒደት መሻሻሎችን እያሳየ በመምጣቱ ተቋሙ ሊመሰገን እንደሚገባውም ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በበኩላቸው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለይቶ ለሚያቀርባቸው የአምራች ኢንዱስትሪዎች ፣ ለቡሬ፣ ለቡልቡላ፣ ለይርጋለምና ለባዓከር የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንደሚሰራ ተናግረዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et የካቲት 01 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+9

ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የኃይል አቅርቦትና ስርጭት እንዲሻሻል ተጠየቀ .....///...... የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እና ስርጭት ለማሻሻል ያለመ ውይይት በስካይ ላይት ሆቴል ተካሔደ። የኢንዱስትሪ ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት የኃይል አቅራቢ ተቋማት በአምራች ዘርፉ ላይ የሚስተዋሉ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጦችን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሥራዎች ሊሰሩ ይገባል። በዋነኝነት ከኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጋር የተያያዙ ክፍተቶችን በመሙላት ዘርፉን ማበረታታት እንደሚገባም ነው ሚኒስትሩ የጠቆሙት። በአምራች ዘርፉ ላይ የሚታዩ የመሰረተ ልማት፣ የኃይል አቅርቦት፣ የሰው ኃይል፣ የገበያ ትስስር ማነቆዎችን ለመቅረፍ የሁሉም ባላ ድርሻ አካላት ሚና የጎላ እንዲሆን አቶ መላኩ ጠይቀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ በውይይት መድረኩ ላይ እንደገለፁት የአምራች ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝና ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንዲኖራቸው የሚያደርጉ የተለያዩ ሥራዎች እየተሰሩ ነው። ተቋሙ ከውጭ በሚያስገባቸው ግብዓቶች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታዎችን እያካሄደ ቢሆንም የውጭ ምንዛሪ እጥረት ጫና እንደፈጠረበት ጠቁመዋል። በውይይቱ ላይ በአምራች ኢንዱስትሪው በኩል ከኃይል አቅርቦት ጋር የተያያዙ ክፍተቶችን ለመፍታት እና ዘርፉን ለመደገፍ የሚያስችሉ፣ ከኃይል አቅርቦት ጋር ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎችን እንዲሁም ከኃይል አቅርቦት ማስተላለፊያና ግንባታ ሥራዎችን የተመለከቱ ሰነዶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 01 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+7

የኢትዮ ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን ለዋንጫ እየተፎካከረ ይገኛል …….///……. በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮ - ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን የዘንድሮውን ዋንጫ ለማንሳት ብርቱ ተፎካካሪ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ ክለቡ በመጀመሪያ ዙር ካደረጋቸው 12 ጨዋታዎች ዘጠኙን አሸንፎ፤ በአንዱ አቻ ወጥቶ በሁለት ጨዋታዎች ተሸንፎ በ28 ነጥብ ከሊጉ መሪ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአንድ ነጥብ ብቻ ተበልጦ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ በሶስተኛ እና በአራተኛው ሳምንት ጨዋታዎች በተከታታይ መሸነፉን ተከትሎ ራሱን በመገምገም እና ስህተቶችን በማረም ወደ ሜዳ የገባው የእንስት ኮረንቲዎቹ ስብስብ በቀጣይ ያከናወናቸውን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በማሸነፍ 18 ነጥቦችን መሰብሰብ ችሏል፡፡ በዚህ ውድድር የዋንጫ ብርቱ ተፎካካሪ የሆኑትን ሐዋሳ ከነማ፣ መቻል እና አርባምንጭ ከነማን በማሸነፍ ጭምር ግስጋሴያቸውን ያሳመሩት እንስት ኮረንቲዎቹ እስከአሁን ባደረጓቸው 12 ጨዋታዎች 30 ጎሎችን በተቃራኒ ቡድን መረብ ላይ በማሳረፍ፤ 5 ጎሎች ብቻ ተቆጥረውባቸው 25 ንፁህ ጎል መሰብሰብ ችለዋል፡፡ የፊት መስመር ተጫዋች የሆኑት ትንቢት ሳሙኤል 6 ጎል፤ ምንትዋብ ዮሐንስ እና ሰላማዊት ጎሳዬ 5 ጎል እንዲሁም አይናለም አሳምነውና 4 ጎል በማስቆጠር ለክለባቸው ማሸነፍ ጉልህ ሚና የተጫወቱ ሲሆን የግብ ዘቧ ማርታ በቀለም ከኋላ መስመር የቡድን አጋሮቿ ጋር በመናበብ አስደናቂ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡ በ2014 ዓ.ም በተካሔደው የኢትዮጵያ ፕሪሜርሊግ ሁለተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ኢትዮ - ኤሌክትሪክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በዚህ የውድድር ዘመን ዋንጫ ለማንሳት እየተፎካከረ ሲሆን በባህርዳር ለሚካሄደው ሁለተኛው ዙር ጨዋታ ለመዘጋጀት ጥር 24 ቀን 2015 ዓ.ም ልምምዱን እንደሚጀምር ታውቋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 24 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ለሚገነቡ ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ ከ2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ያስፈልጋል ........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ለማስገንባት ላቀዳቸው የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልገው የተቋሙ የስትራቴጂ እና ኢንቨስትመንት መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ተሾመ የተቋሙ የሦስት ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ ለውይይት ሲቀርብ እንደገለፁት አስር የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ከንፋስ እና ከፀሐይ ኃይል ለመገንባት ዕቅድ ተይዟል። በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ተቋሙ አሁን የሰረሰበትን 16 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት የማመንጨት አቅም ወደ 27 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ከፍ ለማድረግ ማቀዱን ነው አቶ ወንድወሰን የገለፁት። ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ አሰላ ንፋስ እና አሉቶ ጂኦተርማል ፕሮጀክቶች በዕቅዱ ታሳቢ በመደረጋቸው በቀጣይ ዓመታት ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ከፀሐይ ኃይል በዲቼቶ፣ ጋድ አንድ እና ሁለት፣ ወለንጪቲ እና ወራንሶ አካባቢዎች እንዲሁም ከንፋስ ኃይል በኢተያ፣ አይሻ አንድ እና ሦስት አካባቢዎች የአዳዲስ ፕሮጀክቶች ግንባታ በማከናወን የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመነጩ በመሪ ልማት ዕቅዱ መካተቱን ገልፀዋል። የኃይል ማመንጫዎቹን ለመገንባት የግል ባለሃብቶች ተሳትፎ እንደሚጠበቅ የጠቆሙት አቶ ወንድወሰን አጠቃላይ የፋይናንስ ግምታቸው ከ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ መሆኑን ጠቁመዋል። በግሉ ዘርፍ ሊለሙ ከታቀዱት የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች ላይ ኃይል ለመግዛት የታሪፍ ዋጋ ክለሳ ተሰርቶ መጠናቀቁንም ነው አቶ ወንድወሰን ያብራሩት። በቀጣይ ሦስት ዓመታት ከ3 ሺህ 8 መቶ ኪሎ ሜትር በላይ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለመገንባት መታቀዱን የገለፁት ዳይሬክተሩ 61 አዳዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለመገንባት መታቀዱን ጨምረው ተናግረዋል። በ52 ነባር የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም የማሳደግ እና የማሻሻያ ሥራዎች ለማከናወን መታሰቡንም ነው አቶ ወንድወሰን ያብራሩት። የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹን ለመገንባት ከ1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር በላይ የፋይናንስ ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን ከዚህ የፋይናንስ ወጪ ውስጥ 84 ነጥብ 1 ከመቶ የሚሆነውን ተቋሙ ከራሱ ገቢና ከአበዳሪ ባንኮች በሚያገኘው የብድርና ድጋፍ የሚሸፍን መሆኑን ገልፀዋል። ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች ቀሪ 12 በመቶ የሚሆነውን የፋይናንስ ወጪ ይሸፍናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ነው ያስረዱት። የሦስት ዓመት መሪ የልማት ዕቅዱን ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው የጠቀሱት አቶ ወንድወሰን ተቋሙ የሰው ኃይል አደረጃጀቱን ከማዘመን ጀምሮ የአስተሳሰብ ሪፎርሞችን በማከናወን ለዕቅዱ መሳካት የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 22 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

ተቋሙ የሦስት ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ገብቷል ......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሦስት ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ አዘጋጅቶ ወደ ትግበራ መግባቱን የተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ሁሉንም የተቋሙ ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች ባሳተፈ መልኩ መሪ ዕቅዱን ለማስተዋወቅና ተጨማሪ ግብዓቶችን ለመሰብሰብ በተዘጋጀው ውይይት ላይ የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲኣ እንደገለፁት ተቋሙ ለቀጣዮቹ 25 ዓመታት የሚመራበትን መሪ የልማት ዕቅድ አዘጋጅቶ ወደ ሥራ ገብቷል፡፡ በየጊዜው እየተለዋወጠና ፈጣን ለውጦችን እያሳየ ከመጣው የሀገሪቱ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ጋር የተጣጣመ እና ከ25 ዓመቱ መሪ ዕቅድ የተቀዳ የ10 ዓመት መዘጋጀቱንም ነው ሥራ አስፈፃሚው የተናገሩት። የሦስት ዓመቱ ዕቅድም የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ዕድገት ያለውን ድርሻ በሚያሳይ መልኩ መዘጋጀቱን እና በተቋሙ ከፍተኛ ሥራ አመራር እና የሥራ አመራር ቦርድ ተገምግሞ ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉንም አስረድተዋል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ከሠራተኞችና ከሥራ መሪዎች የሚገኙ ገንቢ ሃሳቦችን እንደ ግብዓት በመውሰድ ዕቅዱ ተግባራዊ ይደረጋል። የሦስት ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ የኤሌክትሪክ ማመንጨት ሥራው ከውሃ ጥገኝነት ተላቆ በሌሎች የኤሌክትሪክ ኃይል ምንጮች ላይ ትኩረት በማድረግ ከዚህ በፊት ሲያጋጥሙ ለነበሩ ችግሮች መፍትሔ ይዞ እንደመጣ አቶ አንዱዓለም ገልፀዋል። የተቋሙ የስትራቴጂና ኢንቨስትመንት መምሪያ የሦስት ዓመቱን መሪ የልማት ዕቅድ መነሻ በማድረግ በኃይል ማመንጨት እና ማስተላለፍ ሊሰሩ በታቀዱ ሥራዎችና ምን ያህል ወጪ እንደሚያስፈልግ ለውይይቱ ተሳታፊዎች ገለፃ አድርጓል። መሪ የልማት ዕቅዱ ከውሃ ኃይል ማመንጫ ባሻገር ሌሎች የታዳሽ ኃይል ማመንጫ አማራጮችን በስፋት መጠቀም የሚያስችል እንዲሁም የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮችን ተደራሽነት ለማስፋት የሚያግዝ እንደሆነም ነው አስታውቋል። ተቋሙ በውሃ ኃይል ማመንጨት ዘርፍ በአፍሪካ ቀዳሚ ሲሆን በኃይል ማስተላለፊያ የግሪድ ኦፕሬሽን ሽፋን ደግሞ ከደቡብ አፍሪካና ግብፅ ቀጥሎ በሦስተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል። በውይይቱ ላይ ከሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች የተለያዩ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች ቀርበው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 19 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

የወልዲያ ዶሮ ግብር ማከፋፋያ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቆ ፍተሻ ተጀመረ ……///…… የወልዲያ ዶሮ ግብር ባለ 230/33/15 የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኮንስትራክሽን የራስ ኃይል መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የግንባታ ሳይቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ አስኪያጅ አብርሃም አባተ እንዳስታወቁት የማከፋፈያ ጣቢያው በ230 ኪሎ ቮልት መስመር ኃይል እንዲያገኝ የተደረገ ሲሆን ትራንስፎርመሩን ኃይል በመስጠት መፈተሽ ተጀምሯል። ፍተሻው  ከ24 እስከ 48 ሰዓት ሊፈጅ የሚችል እንደሚችል  ይጠበቃል ብለዋል። የማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል ግንባታ ተጠናቆ ሥራ መጀመር ከነባሩ የወልዲያ ባለ 66 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ሲያገኙ የነበሩ አካባቢዎችን ጨምሮ ከዓመት በላይ ኃይል የተቋረጠባቸው  ሃራ ገበያ ፣ ጭፍራ እና በአካባቢው ያሉ ሌሎች ከተሞች ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል እንዲያገኙ ያስችላል። በተጨማሪም ደሴ እና አካባቢው ላይ የነበረው የኃይል መጨናነቅ ወልዲያ እና አካባቢው ከማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ ኃይል በማግኘቱ የኃይል መቆራረጡ እንደሚቀንስ ገልፀዋል፡፡ የማከፋፋያ ጣቢያው አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር ሲኖረው፤ አምስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ ጣቢያው አንድ ባለ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር የሆነ 230/33/15 ትራንስፎርመር አለው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በፍጥነት ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ርብርብ ሲያደርግ እንደነበር ይታወሳል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት ልባዊ ምኞታችንን እንገልፃለን!! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ በማለት ልባዊ ምኞታችንን እንገልፃለን!! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል