የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Ir al canal en Telegram
4 770
Suscriptores
-23224 horas
-1 7917 días
-3 26430 días
Archivo de publicaciones
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
"ኢትዮጵያ ሀገራችን በተላላኪ ባንዳዎችና የውጭ ሴረኞች በሸረቡት ሴራ የምትፈርስ ሳይሆን በጀግኖች ልጆቿ መስዋዕትነት ፀንታ የምትኖር ሀገር ናት!!" ፦ ሜጀር ጄኔራል ታደሰ ሌምባቦ
የመከላከያ የውጊያ ምህንድስና ኮሌጅ ያሰለጠናቸውን የውጊያ ምህንድስና ባለሙያዎች ምረቃ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የኮማንዶና የአየር ወለድ ኃይል ም/ል አዛዥ ሜ/ጄ ታደሰ ሌምባቦ ፤ ተመራቂዎች ሀገረ አፍራሹ አሸባሪው የህወሓት ቡድን የከፈተብንን ጦርነት ለመመከት የጀግኖች አባቶቻችንን ታሪክ መድገም እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡
ጠላት በለኮሶው እሳት እየተለበለበ ነው ያሉት ጁኔራል መኮንኑ ፤ ተመራቂዎች ጠንካራ ወታደራዊ ዲሲፒሊን ፤ የሀገርና የህዝብ ፍቅርን በመያዝ ደማቅ ታሪክ ለመፃፍ መዘጋጀት እንደሚኖርባቸው ተናግረዋል፡፡
የውጊያ ምህንድስና ኮሌጅ ዋና አዛዣ ኮሎኔል ኪታባ እንሰርሙ ፤ ኮሌጁ የተቋሙን የሰው ሃይል ፍላጎት ለማሳካት በተሰጠው ተልዕኮ መሰረት ብቁ የውጊያ መሀንዲስ ባለሙያዎችን በማፍራት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
ተመራቂዎች ባላቸው የስራ ልምድና በማሰልጠኛው ያገኙትን ዕውቀት በመጠቀም የተጣለባቸውን ሙያዊ ኃላፊነት በቁርጠኝነት መወጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ያነጋገርናቸው ተመራቂ ወታደሮችም በወሰዱት ስልጠና በቂ እውቀት ማግኘታቸውንና ሀገርን ከጥፋት ለማዳን በግንባር እየተዋደቀ ከሚገኘው ጀግናው ሰራዊታችን ጎን በመሰለፍ ታሪካዊ ግዴታችንን ለመወጣት ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡
ሰበር ዜና‼️
በተለያየ አቅጣጫ ውጊያ የከፈተው ህውሀት በሱዳን ድምበር ሀምዳይት፣ በአበርግሌ፣ በአደርቃይ፣ በራያ፣ በወርቄ በሁሉም ግምባር የተሰለፈው መንጋው በኢትዮጵያ ጥምር ጦር ተደምስሷል!!
ምሽጎች ነጭድንጋይ፣ አዘዛ፣ ሸረሪማ.. በሱዳን ግምባር ተደርምሰው በኢትዮጵያ ጥምር ጦር ቁጥጥር ስር ውለዋል። የተረፈው መንጋ እየተሳደደ ይገኛል። ይህ በእንደህ እንዳለ የኢትዮጵያ ጥምር ጦር ሰራዊቶች ከመከላከል ወደ መልሶ ማጥቃት በመሸጋገር ተከዜን ተሻግሮ ወደ ደደቢትና በአበርግሌ ሳምሪ ተሸጋግረዋል።
በሌላ ዜና አሜሪካ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ፣ አየርላንድ፣ ኖርዌይና አልባኒያ የፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ እንዲወያይ ለሀሙስ ስብሰባ መጥራታቸው ተሰምቷል።
መረጃ‼️
በተለያየ አቅጣጫ ውጊያ የከፈተው ህውሀት በሱዳን ድምበር ሀምዳይት፣ በአበርግሌ፣ በአደርቃይ፣ በራያ፣ በወርቄ በሁሉም ግምባር የተሰለፈው መንጋው በኢትዮጵያ ጥምር ጦር ተደምስሷል!!
ምሽጎች ነጭድንጋይ፣ አዘዛ፣ ሸረሪማ.. በሱዳን ግምባር ተደርምሰው በኢትዮጵያ በቁጥጥር ስር ውለዋል። የተረፈው መንጋ እየተሳደደ ይገኛል። ይህ በእንደህ እንዳለ የኢትዮጵያ ጥምር ሰራዊቶች ከመከላከል ወደ መልሶ ማጥቃት በመሸጋገር ተከዜን ተሻግሮ ወደ ደደቢትና በአበርግሌ ሳምሪ ተሸጋግረዋል።
በሌላ ዜና አሜሪካ፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ፣ አየርላንድ፣ ኖርዌይና አልባኒያ የፀጥታው ምክር ቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ እንዲወያይ ለሀሙስ ስብሰባ መጥራታቸው ተሰምቷል።
👉 ልብ እንቅርት ይመኛል‼~ባሻዬ እንኳንስ "ቀይ ቦኔት"ን ልትማርክ ቀርቶ፤ ቀና ብለህ የማየትም ድፍረት የለህም‼
♦ አናውቅህም እንዴ⁉️-- ፈርጣጭ፣ ወዲ ፈርጣጭ‼
በማንኛውም ጦርነት ውስጥ በተፋላሚ ወገኖች መካከል መማረክ የነበረና ያለ ጉዳይ ነው። ጦርነት ካለ ምርኮ ይኖራል። ታዲያ ምርኮው የሚኖረው፤ በአብዛኛው በተመጣጣኝ ቁመና ላይ በሚገኙ ኃይሎች መካከል ነው። የኢትዮጵያ ባለ ቀይ ቦኔቶች ኮማንዶ፣ አየር ወለድና ልዩ ኃይል ናቸው። ዝርዝሩ ውስጥ መግባት አስፈላጊ ባይሆንም፤ ለዓመታት በከፍተኛ ስልጠናዎች ውስጥ ያለፉ ትንታጎች- ባለፉት ሁለት ዙሮች የወያኔ ወረራዎች ታላቅ ገድል የፈፀሙ በራሪ ነብሮች ናቸው። በሶስተኛውም ዙር የወያኔ ወረራ የአሸባሪውን ጀሌ ቅስም በመስበር ወደር የላቸውም። የትሕነግ ፈርጣጮች በተወርዋሪዎቹ አቦሸማኔዎች ፊት ደፍረው አይቆሙም። የወያኔ ግብስብስ ጀሌ እነርሱ መጡ ሲባል፤ ሮጦ እንኳን ማምለጥ እንደማይችል ስለሚያውቀው፤ እጅ ለመስጠት እሽቅድድሙ አይጣል ነው። ርግጥ በባህላዊ ጄኔራሎች በለብ ለብ ስልጠና መሳሪያ መፍታትና መግጠምና መፍታት ሰልጥኖ የወጣን ቅጥረኛ፤ "የሺህ ሰው ግምት" ከሚባሉት ከኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ጋር ማወዳደር የክፍለ-ዘመኑ ቀልድ ነው‼ማሰቡም ራሱ ይከብዳል‼
ታዲያ እነዚህን ከዓይን የፈጠኑ የጀግናው ሠራዊታችንን ፈርጦች "ማረኩኝ" ብሎ ለማውራት የቀረፃ ፕሮፖጋንዳ ለመስራት እየተዘጋጀ መሆኑን የሰማሁት ቅድ አፉ ትሕነግ፤ በእንዲህ ዓይነት ቀልዱ የዓለም መሳቂያና መሳለቂያ ከመሆን አያድነውም። ምክንያቱም ነገርዬው "ኤሊ ጥንቸልን ማረከቸው" የማለት ያህል ፉክክር ስለሚሆን ነው። ታዲያ እዚህ ላይ አንድ እውነት መታለፍ የለበትም። ወያኔ ውሸታምና ቀባጣሪ ነው‼ዓለም ጭምር ይህን ማንነቱን እየተገነዘበው መጥቷል። እናም የወያኔን ፕሮፖጋንዳ ገልብጠን ስናየው፣ አንድም ቀይ ቦኔት አለመማረኩን እየነገረን ነው። ደግሞም ሊማርክም አይችልም። ሊነግረን የፈለገው ከንቱ ምኞቱን ነው። "ልብ እንቅርት ይመኛል" ይሉት ምኞት እንዲህ ዓይነቱን የሕልም እንጀራ ነው። ከግብፅ ተሰርቶ በተላከለት ቀይ ኮፍያ የራሱን ጀሌዎች አልብሶ የአሻንጉሊት ድራማ ለመስራት መዘጋጀቱ፤ የሽብር ቡድኑ ሁሉም ሰው እንደ እርሱ ቆሞ ቀር ስለሚመስለው ስለሆነ ብዙም ሊደንቀን አይገባም። በነገራችን ላይ ለአሸባሪው ህወሓት አፈር-ድሜ መብላት ከፍተኛ ሚና ከተጫወቱት የጦር ክፍሎቻችን ውስጥ አንዱ ባለቀይ ቦኔቶቹ ናቸው። በብዙ ግንባሮችም የቅጥረኛውን ቡድን አከርካሪ ሰባብረውታል። እንዳይነሳ ድምጥማቱን አጥፍተውታል። ወያኔ በባህሪው ቂመኛ ስለሆነ፤ ውሸት በማውራት ቀይ ቦኔቶችን የሚበቀላቸው ይመስለዋል። እኛ ያለን፤ በመብረቃዊ ምቱ የጠላትን መሐል አገዳ የሚሰብር እጅግ ጠንካራ ሠራዊት እንጂ፣ በወያኔ ተራ የአሉባልታ ዘመቻ የሚሰበር ጀግና የለንም። በሙሉ ወታደራዊ፣ ስነ-ልቦናዊና ሞራላዊ ቁመና እና ዝግጁነት ላይ የሚገኙት ጀግኖቻችን፤ ወያኔን በሁሉም ግንባሮች እንደ ቆሻሻ እያፀዱት ነው። የጁንታው ጀሌ ባለ ቀይ ቦኔቶችን እንኳንስ ሊማርክ ቀርቶ፤ በመሉ ዓይኑ ቀና ብሎ ሊያያቸው የሚያስችለው ድፍረት የለውም--በራሪ ነብሮቹን አሳምሮ ያውቃቸዋልና‼~ፈርጣጭ፣ ወዲ ፈርጣጭ‼
ድል ለአይበገሬዎቹ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች‼
ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም
ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን አሸባሪው ህወሓት የከፈተብንን ጦርነት ለመመከት በሚወጣው ግዳጅ የደጀኑ ህዝባችን ድጋፍ እስከ ምሽግ ድረስ አልተለየውም።
ነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም
"ምሽግ መቆፈሩን አልረሡትም አሳምረው ሠርተውታል። የዘነጉት ግን ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን ምሽግ ደረማምሶ ማለፍ መቻሉን ነው።"
፦ በግዳጅ ቀጠናው የሚገኙ የክፍለ ጦር አዛዥ
ሸኔ‼️
ከወራሪው የህወሓት ኃይል ጋር የተሰለፉ በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች ተማረኩ‼️
የህወሓት ወራሪ ኃይል ሰሞኑን ጥቃት በከፈተባቸው የአማራና የአፋር ግንባሮች ከቡድኑ ጋር ተሰልፈው ሲዋጉ የነበሩ በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች መማረካቸው ታወቀ፡፡
የህወሓት ወራሪ ኃይል በአማራና በአፋር ግንባሮች ጥቃት ከመክፈት ጎን ለጎን በተለያዩ አካባቢዎች ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጋር በመነቀናጀት ሽብር ለመፍጠር እየሠራ እንደሚገኝ የጠቆሙት ምንጮች፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት ከተፈረጀው የሸኔ ቡድን ጋር በገባው ስምምነት መሠረትም በተለያዩ ግንባሮች የቡድኑን ታጣቂዎች አሰልፏል፡፡
በተለይ በቆቦ ከተማ ወረራ የፈጸመው ህወሓት የሸኔ ታጣቂዎችን ከፊት በማሰለፍ ወደ ፊት ለመግፋት ቢሞክርም በሀገር መከላከያ ሠራዊትና በጥምር ጦር በተሰነዘረበት መልሶ ማጥቃት ከፍተኛ ኪሳራ እንደደረሰበት የተገለጸ ሲሆን፤ በርካቶችም ተማርከዋል፡፡ ከምርኮኞችም መካከልም በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች መኖራቸው ታውቋል፡፡
ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶችና ከውስጥ ባንዳዎች ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ቀውስ ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ህወሓት በተለያዩ ግንባሮች ጥቃት ከመክፈት ጎን ለጎን በየክልሎች የሚገኙ ታጣቂዎች የሎጀስቲክስ፣ የፋይናንስና የመሣሪያ ድጋፍ እንዲደርሳቸው እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡
ነሐሴ 25 ቀን 2014 ዓ.ም
በፈተና ነጥራ የወጣች ሀገር ኢትዮጵያ!!
ሀገራችን ኢትዮጵያ ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ፈተናዎች ያጋጥሟታል። ኢትዮጵያን ፈተናዎች አላዳከሟትም ይልቁንም ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ሆና ወደፊት እንድትቀጥል አበርትቷታል።
ኢትዮጵያ ወርቅ ነች። ወርቅ በእሳት ነጥሮ አምሮና ደምቆ እንደሚወጣው ሁሉ ኢትዮጵያም በፈተናዎች አልፋ ለዘመናት ታፍራና ተከብራ ኖራለች ትኖራለችም።
ኢትዮጵያ ፈታኞቿ የውጭ ጠላቶቿ ናቸው። እነዚህ ኃይሎች ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ሀገራችንን ፊት ለፊት ገጥመው ማሸነፍ እንደማይችሉ ከታሪክ መዝገብ የተረዱ በመሆናቸው በባንዳና ተላላኪዎች አማካኝነት ፍላጎታቸውን ማሳካት ይፈልጋሉ።
በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የሚጋለበው አሸባሪው የህወሓት ቡድንም እነሱ ያልተሳካላቸውን ሀገር የማፍረስ ህልምቸውን ተቀብሎ መቃዠት ከጀመረ ሰምበትበት ብሏል ብቻ ሳይሆን ከርሟል።
ኢትዮጵያን ፊት ለፊት ገጥመው የሆኑትን እና የሚሆኑትን የሚያውቁት የውጭ ጠላቶቻችን የወስጥ አንድነታችን ተበጣጥሶ አሸባሪውን ለማንገስ ዳክረዋል።
ወርቅ በእሳት ነጥሮ ወርቅ እንደሚሆነው ሁሉ ኢትዮጵያም በፈተናዎቿ ነጥራ የምትወጣ እንጂ ጠላቶቻችን እንደሚያስቡት የምትፈረካከስ ሸክላ አይደለችም።
የጀግኖች አባቶቹ ልጆች የሆነው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን የተረከባትን ሉአላዊ ሀገር ከጠላት እና ከባንዳ ተከላክሎ ለቀጣዩ ትውልድ የማሸጋገር ታሪካዊ ኃላፊነት ያለበት ኃይል ነው።
ለዚህም ሠራዊታችን የገጠመንን ጠላት በማንኛውም ጊዜ እና ሠአት በመንግስት በሚሠጠው አቅጣጫ መሠረት ጠላትን በማደባየት ታሪካዊ ኃላፊነቱን ይወጣል።
#ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች!!
ኢትዮጵያ ወደ ሶስትዮሹ የህዳሴው ግድብ ድርድር ለመመለስ ዝግጁ መሆኗን ገለጸች
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት ስር ለሚካሄድ ድርድር ዝግጁ መሆኗን የገለፁት በሱዳን የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ናቸው።
አምባሳደር ይበልጣል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተለይም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ከተቀሰቀሰው ጦርነት ጋር በተያያዘ መቀመጫቸውን ካርቱም ለሚገኙ ብዙሃን መገናኛዎች መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫው ዓለም አቀፍ ማሕበረሰብ የተጀመሩ የሰላም ጥረቶችን በመተው ጦርነት በጀመረውና በሽብረተኝነት በተፈረጀው ህወሓት ላይ ጫና እንዲያሳድር ጥሪ አቅርበዋል።
ተቋርጦ ረጅም ወራትን ስላስቆጠረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ጉዳይ የተጠየቁት አምባሳደር ይበልጣል ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት ስር ወደሚካሄድ የሶስትዮሽ ድርድር ለመመለስ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።
ነሐሴ 24 ቀን 2014 ዓ.ም
"........
የማንጨበጥ ነበልባል-እሳት ነን ለጠላታችን
ፍሙ ከርቀት ይፋጃል- ብረት ያቀልጣል ክንዳች
ኢትዮጵያ በእኛ ደም ደምቃ-በአፅማችን ፍላጽ ተማግራ
እንደ ታፈረች እንድትኖር-ከዘመን ዘመን ተከብራ፤
.........."
ይህ ስንኝ ከጀግናው መከላከያ ሠራዊታች መሪ መዝሙር ላይ ተቀንጭቦ የቀረበ ነው!!
ሠራዊታችን የተሠጠውን ግዳጅ በአስደናቂ ብቃት ፈፅሞ የሚያሳይ፤ ከፍተኛ ወታደራዊ የማድረግ ብቃት ያለው፣ የዘመኑን የጦርነት አቅሞች በሚገባ ተጠቅሞ በድል ላይ የሚረማመድ፤ በስነ-ልቦናዊና ሞራላዊ ዝግጁነቱ ጠንካራ የአሸናፊነትን መንፈስ የታጠቀ ነው።
የውጭም ይሁን የውስጥ ጠላቶቻችን በከንቱ ይዳክራሉ እንጂ ከአይበገሬው ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን እና የጥምር ኃይሎቻችን ፊት የሚቆም አንዳችም ምድራዊ ኃይል የለም።
#አሸናፊነት መለያችን ነው!!
ጀግኖቻችን ባለቀይ ቦኔት የቁርጥ ቀን ልጆች
በሁሉም በጦር ግምባሮች ሽንታሟን ወያኔ አይቀጡቅጣት እየቀጡ ይገኛሉ። በጀግናው መከላከያ ሃይላችን ድል አድራጊነት የሚጠራጠር ካለህ እሱ/እሷ ያለጥርጥር ኢትዮጵያዊ አይደለም/ችም። 101% ድሉ የጀግናው መከላከያ ሃይላችን ነው።
ድል ለቀያይ ነብሮቻችን ኮማንዶዎች ይሁን🙏🇪🇹🙏
መከላከያ ሰራዊት አሸባሪውን ቡድን እንደ አመጣጡ አፀፋዊ ምላሽ እየሠጠውና እየደመሰሰው እንደሚገኝ አስታወቀ!!
የአገር መከላከያ ሠራዊት ካለፈው የኅልውና ዘመቻዎች የጠላትን አሠላለፍ በውል በመገንዘብ አሸባሪውን የህወሓት ቡድን እንደ አመጣጡ አፀፋዊ ምላሽ እየሠጠው እና እየደመሰሰው እንደሚገኝ አስታወቀ።
ሠራዊታችን የድል ሠራዊት ነው በሚል ባወጣው መግለጫ በየትኛውም ቦታና ጊዜ፣ አስቸጋሪ መልክአ ምድርንም ሆነ የአየር ፀባይ ተቋቁሞ ግዳጁን በድል አድራጊነት የሚወጣው ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ጠላትን በአስተማማኝ መመከት የሚችል ኃይል መሆኑን አረጋግጧል።
ሠራዊቱ ከራሱ ይልቅ ሕዝብን ያስቀደመ፣ ለሀገር እና ለሕዝብ ራሱን አሳልፎ የሠጠ ብሔራዊ ኩራታችን ነው ብሏል።
ጠላቶቻችን ሕዝባዊ ባህሪውን በውል ስለሚገነዘቡ ህፃናትንና ሴቶችን ከፊት አሰልፈው ክፍለ ዘመን ባለፈበት ጦርነት በሕዝብ መአበል መዋጋታቸው የሠራዊታችንን አይበገሬነትና ጀግንነት ጠንቅቀው ስለሚያውቁት እንደሆነ ገልጿል።ጠላት ለዜጎቹ ደንታ እንደሌለው ባሳየው በዚህ የኋላ ቀር ጦርነት ሠራዊታችን በከፍተኛ ጥንቃቄ እና የኃላፊነት መንፈስ ግዳጁን እየተወጣ እንደሆነ በማመልከት አሸባሪው ህወሓት በለኮሠው እሳት መልሶ እየለበለበው እንደሚገኝ መከላከያ ሰራዊት አስታዉቋል።
ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም
"አየር ኃይሉ መክፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ሁሉ ከፍሎ ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ እንድትኖር ለማድረግ በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል።"
፦ ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ
የኢፌዲሪ አየር ኃይል አካዳሚ በኤሌክትሮኒክስ፣ በአውሮፕላን አካል እና ሞተር ጥገና እንዲሁም በመሰረታዊ የአቪዬሽን ሙያ ያሰለጠናቸውን የሰራዊት አባላት አስመርቋል።
በምርቃ ስነ -ስርዓቱ ተገኝተው በትምህርታቸው ብልጫ ላመጡ ሰልጣኞች ሰርተፍኬትና የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ ሲሆኑ አየር ኃይሉ ከሀገራዊ ለውጡና ከተቋማዊ ሪፎርሙ በኋላ የዝግጁነት አቅሙን ለማሳዳግ በሰው ኃይል ግንባታ፣ በዘመናዊ ትጥቆች እና ቴክኖሎጂ ብሎም ሰፋፊ የውጊያ መሰረተ ልማቶችን በማሟላት በትኩረት መስራት መቻሉን ገልፀዋል።
ተመራቂዎች ያለንበትን ወቅት በመረዳትና የተማራችሁትን ሙያ ወደ ተግባር በመቀየር ሀገራዊ ግዴታችሁን መወጣት አለባችሁ ሲሉ አሳስበዋል።
አየር ኃይላችን መከፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ሁሉ በመክፈል ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ እንድትኖር ለማድረግ በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ሲሉም አረጋግጠዋል ።
ለታላቅ ሀገር ታላቅ ተቋም በመገንባት ብሎም ብቃትና ጥራት ያላቸውን ባለሙያዎችን በማፍራትና የኢትዮጵያን ጠላቶች ድባቅ በመምታት አየር ኃይሉ የጀግኖች መፍለቂያ መሆኑን በተግባር እያስመሰከረ እንደሚገኝም ዋና አዛዡ ተናግረዋል ።
የኢፌዲሪ አየር ኃይል አካዳሚ አዛዥ ኮ/ል ገዛኸኝ ነጋሽ በበኩላቸው በአስተሳሰብና ክህሎት ብቁ የሆነ የሰው ኃይል በመፍጠር ዘመኑ የሚጠይቀውን ዕውቀት መሸከም የሚችል ፓይለትና ቴክኒሽያን እንዲሁም ሌሎች ሙያተኞችን በማፍራት በአካዳሚው በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።
የአካዳሚ አዛዡ አክለውም በቀጣይ ኮሌጁን በቴክኖሎጂ ይበልጥ በማዘመን ከአፍሪካ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም ለማድረግ በትጋት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል ።
ከተመራቂ ሙያተኞች መካከል አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት ዘመኑ የሚጠይቀውን የአቪዬሽን እውቀት መቅሰማቸውን ጠቁመው በዚህም የሚጠበቅባቸውን ሁሉ በማድረግ ሀገራዊ ግዳጃቸውን በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም
ሠራዊታችን የድል ሠራዊት ነው !!
በየትኛውም ቦታና ጊዜ ፤ አስቸጋሪ መልክአ ምድርንም ሆነ የአየር ፀባይ ተቋቁሞ ግዳጁን በድል አድራጊነት የሚወጣው ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ጠላትን በአስተማማኝ መመከት የሚችል ኃይል ነው።
መከላከያ ሠራዊታችን ከራሱ ይልቅ ህዝብን ያስቀደመ፤ ለሀገር እና ለህዝብ እራሱን አሳልፎ የሠጠ ብሔራዊ ኩራታችን ነው። ጠላቶቻችን ህዝባዊ ባህሪውን በውል ስለሚገነዘቡ ህፃናትንና ሴቶችን ከፊት አሰልፈው ክፍለ ዘመን ባለፈበት ጦርነት በህዝብ መአበል መዋጋታቸው የሠራዊታችንን አይበገሬነትና ጀግንነት ጠንቅቀው ስለሚያውቁት ነው።
በመሆኑም ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን ካለፈው የህልውና ዘመቻዎች የጠላትን አሠላለፍ በውል በመገንዘብ አሸባሪውን የህወሓት ቡድን እንደ አመጣጡ አፀፋዊ ምላሽ እየሠጠው እና እየደመሰሰው ይገኛል።
ጠላት ለዜጎቹ ደንታ እንደሌለው ባሳየው በዚህ የኋላ ቀር ጦርነት ሠራዊታችን በከፍተኛ ጥንቃቄ እና የኃላፊነት መንፈስ ግዳጁን እየተወጣ ያለ ሲሆን አሸባሪው ህወሓት በለኮሠው እሳት መልሶ እየለበለበው ይገኛል።
ድል ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን!!
ወዳጄ ውጊያው ከህወሃት ጋር ብቻ ከመሰለህ ተሳስተሃል!
ህወሃት በመቶ ሺዎች የትግራይን ህዝብ ደመከልብ ካደረገች ጥቂት ወራት በኋላ ዳግም ወደ እልቂት የትግራይን ህዝብ የምትገፋው ማን የልብ ልብ እየሰጣት ይመስልሃል
የእጅ አዙር ጦርነት ያወጀችብን እኮ ግብጽ ናት!
ይህንን በማስረጃ ላስረዳህ ማስረጃ አንድ 👇
ግብጽ ታሪካዊ ጠላቴ ኢትዮጵያ ናት ያለችው ዛሬ አይደለም። የህልውናዋ መሰረት የሆነው አባይ በኢትዮጵያ እጅ መሆኑን ጠንቅቃ ስለምታውቅ ኢትዮጵያ ከጠነከረች ውሃውን ለራሷ ልትጠቀምበት ትችላለች የሚለው እንቅልፍ ይነሳታል። ስለዚህ የተከፈለው ተከፍሎ ኢትዮጵያን ለማመስ ቀን ከሌት ትሰራለች። ማስረጃ ሁለት👇
የግብጽ ከፍተኛ ባለስልጣናት ቀጥታ ከኢትዮጽያ ጋር ጦርነት አንገጥምም፤ ኢትዮጵያን ከውስጥ መበጥበጥ፣ ጠላቶቿን በገንዘብም በመሳሪያም በማገዝ ከውስጥ ገዝግዘን እንጥላታለን ሲሉ ሁላችንም ሰምተናል። በዚህ ደግሞ ህወሃት ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሰይጣንም ጋር ቢሆን እናብራለን፤ ካስፈለገ ሲኦልም ድረስ እንወርዳለን ብሏል። ይህንን የህወሃት የክህደት ጥግ ለማገዝ ከግብጽ በላይ ማን ይመጣል። ህወሃት ኢትዮጵያን አፈርሳለሁ በሚል ለተነሳበት አላማ ሲኦልም መውረድ ሳያስፈልገው አጠገቡ ግብፅን አግኝቷል፤ ክህደት! ክህደት! ክህደት! ማስረጃ ሶስት 👇
ሰሞኑን ጀግኖቹ የሰማይ አናብስት የአየር ሃይላችን ለህወሃት መሳሪያ ሲያደርስ ቀልቦ ዶግ አመድ ያደረገውን አውሮፕላን ጉዳይ መቼም ሰምተሃል! በል ስለሱ ልንገርህ ስማኝ!
አውሮፕላኑ የግብጽ አንቶኖቭ ነው! ህወሃትን እንደ ፈረስ የምትጋልበው ታሪካዊ ጠላታችን ግብጽ ለህወሃት የላከችው መሳሪያ ነው። የተነሳው ደግሞ ሌላኛዋ ግብጽ እየተጠቀመችባት ከምትገኘው ከሱዳን ሰሜናዊ አካባቢ፤ መሮዌ ከተማ ነው! ህወሃት አንደኛውን ሃቁን ነግሮናል! ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሰይጣንም ጋር አብራለሁ ሲኦልም ቢሆን እወርዳለሁ ብሎናል! እንደ ፈረስ በታሪካዊ ጠላታችን እየተጋለበ የአይናችንን ብሌን ኢትዮጵያን ሲያፈርስ ቁጭ ብለን የምናይ መስሎት ነው?
እንደውም መንግስት ይህንን ኢትዮጵያን ለዘመናት ተጣብቶ የጭካኔ ጥግ ክህደቱን በተግባር እያሳየን ያለውን ህወሃት ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ያስወግድ! ኢትዮጵያ እፎይ የምትለው ከውስጧ የሚነክሳትን ህዝቧን በጭካኔ የሚጨፈጭፈውን ያረጀ ያፈጀ ቡድን ስታስወግድ ነው! በህወሃት መነከስ በቃን!
