የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Ir al canal en Telegram
4 648
Suscriptores
-23224 horas
-1 7917 días
-3 26430 días
Archivo de publicaciones
የሕዳሴ ግድቡ ኢትዮጵያን የማምረቻው ዘርፍ ማማ ለማድረግ ወሳኝ ነው- በኢትዮጵያ የኢንዶኔዥያ አምባሳደር
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ የማምረቻው ዘርፍ ማማ ለመሆን ቁልፍ ሚና እንደሚኖረው በኢትዮጵያ የኢንዶኔዥያ አምባሳደር አል ቡስራ ባንሱር ገለጹ፡፡
ኢዜአ እንደዘገበው አምባሳደር ባንሱር፤ የህዳሴ ግድቡ ለኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው ወሳኝ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
“የህዳሴ ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገራት ጭምር ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው አምናለሁ” ሲሉ ጨምረው ገልጸዋል።
ህዳሴ ግድቡ በሚያመነጨው ኃይል ኢትዮጵያን በኃይል አቅርቦት የበለጸገች ታላቅ ሀገር ያደርጋታል ያሉት አምባሳደሩ " በዚህም የኃይል አቅርቦት ማማ ትሆናለች ሲሉ" አመልክተዋል።
“በሚመነጨው ኃይል በመታገዝ ኢትዮጵያውያንና የጎረቤት ሀገራት ህዘቦች የራሳቸውን ኢንዱስትሪ በመመስረትና በቀላሉ በመበልጸግ የገቢ አቅማቸውንና ኢኮኖሚያቸውን ያሳድጋሉ" ነው ያሉት።
በርካቶች ኢትዮጵያን ድሃና በረሃብ የተጠቃች ሀገር አድርገው ይስሏታል፣ ነገር ግን “ዘወትር ለኢንዶኔዥያውያን ጎደኞቼ በተለይም በንግድ ስራ ላይ ለተሰማሩት የምነግራቸው፣ ኢትዮጵያ በ1977 ከነበረችበት ጋር ስትነጻጸር ፍጹም የተለየች አገር መሆኗን ነው" ብለዋል አምባሰደሩ።
አሁን ላይ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የጎረቤት ሀገራት ህዝቦች ኢኮኖሚያቸውን፣ ብልጽግናቸውን እና ኑሮአቸውን ማሻሻል መቻላቸውን አስረድተዋል።
በተመሳሳይ በኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር ሮበርት ሴኪንቶንግ፤ የህንድ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ኢትዮጵያ የማምረቻው ዘርፍ መዳረሻ ለመሆን የያዘቸውን ጉጉት በሚገባ በመገንዘባቸው በተለያዩ የኢኮኖሚ ዘርፎች ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ መድበው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
“የህዳሴ ግድቡን በተመለከተ ህንድ ሶስቱ ሀገራት ማለትም ኢትዮጵያ ፣ግብጽና ሱዳን ተቀምጠው በመነጋጋር ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሄ ማምጣት አለባቸው የሚል ግልጽ አቋም አላት" ብለዋል
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ደመቀ መኮንን ”ማንኛውም አይነት ሰው ሰራሽ ግፊቶች ቢያይሉብንም የህዳሴ ግድቡ የውሃ ሙሌት እውን መሆኑ አይቀርም፣ ግድቡ የኢትዮጵያውያን የአንድነት መንፈስና ህብረት የተንጸባረቀበት ነው” ማለታቸው ይታወሳል፡፡
ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድቡ ሶስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት እና የሁለተኛው ተርባይን ኃይል የማመንጨት ሙከራ በስኬት መጠናቀቁን ባሳለፍነው ሳምንት አብስራላች፡፡
በመርሐግብሩ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ”በህዳሴ ግድቡ ዙሪያ የሚከናወኑ ድርድሮችና እውነተኛ ምክክሮች ከማንኛውም አማራጭ በተሻለ ፍሬያማ ውጤት ያስገኛሉ’ ማለታችው ይታወሳል።
ሩሲያ ወዳጆቿን ዘመናዊ ጦር መሳሪያ ለማስታጠቅ ዝግጁ መሆኗን ገለጸች
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ ሃገራቸው ለወዳጆቿ ዘመናዊ ጦር መሳሪያዎችን ለማስታጠቅ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።
በላቲን አሜሪካ፣ ኤሽያ እና አፍሪካ ከሚገኙ ሃገራት ጋር ላላቸው ግንኙነት ዋጋ እንደሚሰጡ የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ ሃገራቱን ዘመናዊ ጦር መሳሪያ ለማስታጠቅ ዝግጁ ነን ብለዋል በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት በተላለፈ ንግግራቸው። የሩሲያ ጦር ዓመታዊ ፎረም በሞስኮ አቅራቢያ ተጀምሯል።
እንደ ሮይተርስ ዘገባ በፎረሙ የመክፈቻ ስነ ስርዓት ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግርም ነው ፑቲን ይህን ያሉት።
በንግግራቸው "ከቀላል እስከ ከባድ፤ ብረት ለበስ እና ሰው አልባ እጅግ ዘመናዊ ጦር መሳሪያዎችን ለወዳጆቻችን ለመስጠት ዝግጁ ነን" ብለዋል። የሩሲያ መሣሪያዎች "በአስተማማኝነታቸው፣ በጥራታቸውና በሚሰጡት ጥቅም እንዲሁም ባላቸው ከፍተኛ ብቃት" በወታደራዊ ጠበብት ዘንድ ተመራጭ ስለመሆናቸውም ተናግረዋል።
"ሁሉም በሚባል ደረጃ ከአንድ ጊዜ በላይ በአውደ ውጊያዎች ጥቅም ላይ ውለዋል" ሲሉም ነው ፕሬዝዳንቱ የተናገሩት። ሃገራቸው በዩክሬን በማካሄድ ላይ ካለችው ዘመቻ ጋር በተያያዘ በተገለለችበት በዚህ ወቅት ከጎኗ የቆሙ 'ብዙ' ወዳጆቿንም አመስግነዋል እንደ ኤ.ኤፍ.ፒ ዘገባ
✍️ አቶ ደመቀ መኮንን የእንግሊዝ የአፍሪካ ቀንድ እና ቀይ ባህር ልዩ መልዕክተኛን በጽ/ቤታቸው አነጋገሩ
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን የእንግሊዝ የአፍሪካ ቀንድ እና ቀይ ባህር ልዩ መልዕክተኛ የሆኑትን ክብርት ሳራ ሞንትጎመርይን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡
በውይይቱም እንግሊዝ ከአገራችን ጋር ስላላት የረጅም ጊዜ ወዳጅነት አስታውሰው ፤ በእንግሊዝ መንግስት በኩል እየቀረበ ስላለው ዘርፈ ብዙ ድጋፎች በተመለከተ አቶ ደመቀ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
በአገራችን ሰሜኑ ክፍል የተፈጠረውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መንግስት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ችግሩንም ለመፍታት በመንግስት በኩል እየተወሰዱ ስላሉ ዝርዝር ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ልዩ መልዕክተኛዋም በበኩላቸው የመጀመሪያቸው በሆነ ጉዞ ብዙ ነገሮች ላይ ግንዛቤ እየፈጠሩ መሆኑን ጠቅሰው ፤ በሃላፊነታቸው ጊዜያት በሁለቱ አገሮች መካከል ያለው የረጅም ጊዜ ወዳጅነት ተጠንክሮ እንዲቀጥል የድርሻቸውን እንደሚወጡ ገልጸዋል፡፡
የሰላም ሂደቱንም ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸው ጠቁመዋል፡፡
#ማሊ_ውጭ_ጉዳይ_ሚኒስቴር
ማሊ፤ ፈረንሳይ የአየር ክልሌን በመጣስ ታጣቂዎችን እየደገፈች ነው ስትል ከሰሰች
የፈረንሳይ ጦር ከማሊ መውጣቱ ይታወሳል
ምዕራብ አፍሪካዊቷ ማሊ፤ ፈረንሳይ የአየር ክልሌን በመጣስ ለታጣቂዎች ጦር መሳሪያ እያቀረበች ነው ስትል ከሰሰች።
የማሊ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሁኔታውን በማስመልከት ለተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ደብዳቤ ጽፏል።
በደብዳቤው የሃገሪቱ የአየር ክልል በዚህ ዓመት ብቻ ከ50 ለሚበልጡ ጊዜያት በዋናነትም በፈረንሳይ ወታደራዊ ድሮኖች፣ የጦር ሄሊኮፕተሮች እና የጦር ጄቶች መጣሱን ገልጿል እንደ ሮይተርስ ዘገባ።
ይህ ታጥቀው ለሚንቀሳቀሱ ቡድኖች የደህንነት መረጃዎችንና ጦር መሳሪያዎችን በማቅረብ ማሊን ለማተራመስ የሚደረግ እንደሆነም ነው ደብዳቤው የሚያትተው።
ሆኖም ፈረንሳይ ክሱን አስተባብላለች።
ከአል ቃይዳ ጋር ግንኙነት አላቸው በሚል በሽብተኝነት ከፈረጁት ታጣቂዎች ጋር በቀጥታም ሆነ ሆነ በተዘዋዋሪ ያደረገችው ድጋፍ እንደሌለም ነው ባማኮ የሚገኘው ኤምባሲዋ የገለጸው።
ፈረንሳይ ታጣቂዎችን ለመዋጋት በሚል ወታደሮቿን በማሊ ላለፉት 9 ዓመታት አሰማርታ ነበር።
ሆኖም ከአዲሱ የኮሎኔል አሲሚ ጎይታ መንግስት ጋር ስምምነት ባለመኖሩ ምክንያት ከቀናት በፊት ሙሉ በሙሉ ማሊን ለቀው መውጣታቸው ይታወሳል።
ይሄንን ተከትሎም ፈረንሳይ በማሊ በሶስት ካምፖች ሰፍሮ የነበረው የፈረንሳይ ጦር በተለያዩ ዙሮች ስታስወጣ የቆየች ሲሆን በዛሬው ዕለት የመጨረሻው ዙር ወታደሮች ከዘጠኝ ዓመት ቆይታ በኋላ ሙሉ ለሙሉ ሀገሪቱን ለቆ ወጥቷል።
ቻይና፣ ሩሲያና ህንድን ጨምሮ ስድስት ሀገራት የጦርነት ልምምድ
የጦርነት ልምምዱ ላይ አዘጋጇ ሩሲያን ጨምሮ ቻይና፣ ቤላሩስ፣ ታጃኪስታን፣ ህንድ፣ ሞንጎሊያ እና ሌሎችን ሀገራት ይሳተፋሉ ተብሏል።
በዚህ የጦር ልምምድ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ቻይና የአሁኑ የጦር ልምምድ ከወቅቱ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ጋር እንደማይገናኝ ገልጻለች።
ይህ የጋራ የጦርነት ልምምድ በሩሲያ እና ቻይና ድንበር አቅራቢያ ካቦራቭስክ በሚባል ስፍራ እንደሚካሄድ የሩሲያ መከላከያ መረጃ ያወጣው መረጃ ያስረዳል።
ምዕራባውያን ህወሃትን በተመለከተ መንግስት ላይ የሚያሳዩት አቋም የዘንዶና የታዳኙን ይመስላል ኢትዮጵያን በብዙ አሳሪ ሁኔታ እንደ ዘንዶ ተብትበው ታዳኟ በተነፈሰች ቁጥር ዘንዶው እየጨመቀ ትንፋሽ እንደሚያሳጣት ሁሉ መንግስት ደርዘን የሚጠጉ አወንታዊ የሰላም እርምጃዎችን ወስዶ እያለ ከማበረታታትና ከማገዝ ይልቅ ማለቂያ የሌለው ቅድመ ሁኔታ በማስቀመጥ መንግስት ወደ ሰላም ትንሽ ፈቀቅ ሲል እንደ ዘንዶ እየጨመቁ በሌላ በኩል ግን ሌላኛውን ወገን ማገዝና የሰላም እድሉን ማሰናከል የሰርክ ተግባራቸው ሆኗል።
አንድ የሚያገናዝብና ምክንያታዊ የሆነ ሰው ሊያነሳቸው የሚገቡ ነገሮችን እስቲ እንመልከት ህወሃት ዛሬም ለጦርነት ዝግጁ ነኝ እያለ ሲደነፋ መቼም ዝግጅቱ መሰረታዊ የጦርነት አስፈላጊ ነገሮችን ያካተተ መሆን አለበት። ለምሳሌ፤
1* የሰው ሃይል፤ ህወሃት በራሱ አንደበት ምን ያህል ሰዎችን ምክንያት አልባ ለሆነው የእብሪት ጦርነት እንደሰዋ ተናግሯል፤ ስለዚህ ለዳግም ጦርነት ተዘጋጀሁ ሲል ትግራይ ጦርሜዳ ለማይዘምት ማንኛውም ሰው ቦታ እንደሌላት በግልጽ እየተናገረ አይደለምን?
2* የጦር መሳሪያ፤ አዛኝ ቂቤ አንጓቾቹና የኢትዮጵያን ሰላም የማይፈልጉቱ ለህወሃት ጦር መሳሪያ ለማስታጠቅ ምን ያህል ርቀት እንደሚሄዱ የማንገምት ይመስላቸዋልን? መቼ፣ ስንት አውሮፕላን እንዳረፈ፣ ለመሳሪያዎቹ ማን እንደከፈለ፣ ማን እንዳጓጓዘ እኮ ይታወቃል። ለአሁን ግን ስም መጥቀሱ ይቅር። ግን ሁለን ይታወቃል። ያለንበት ዘመንና የቴክኖሎጂ ምጥቀት ይህንን ለመደበቅ አያስችልም። ታዲያ ምነው ደርሶ የሰላም ቀንዲል ከኛ በላይ የለም ማለቱን ቢተዉት
3* ገንዘብ፤ ገንዘብ በተለይም በጦርነት ወቅት እጅግ አስፈላጊ ነገር መሆኑ ግልጽ ነው። ታዲያ በአንድ በኩል ህወሃት የጦርነት ነጋሪቱን ሲጎስም በጎን ደግሞ በእርዳታ አመላላሽ ስም ወደ ክልሉ የሚገቡ ሰዎች እጅ በሚሊየኖች የሚቆጠር ገንዘብ ሲያዝ እነዚሁ ለአፋቸው ሰላም ሰላም የሚሉት ምዕራባውያን ሃይ ማለት አቃታቸው?
4* ነዳጅ፤ መቼስ ማገናዘብ የሚችል ማንኛውም ሰው ለጦርነት ወታደርና መሳሪያ ለማጓጓዝ ነዳጅ ምን ያህል እንደሚያስፈልግ መገመት ይችላል። ከህወሃት አፈቀላጤዎች ሰርክ የሚሰማው ለሰብአዊ እርዳታ ማከፋፈያ የሚሆን ነዳጅ አጠረን ለቅሶንም ያልሰማ የለም። ታዲያ ለጦርነት የሚዘጋጁበትን ነጃጅ ከየት አመጡት ብሎ መጠየቅ አይገባም?
5* ምግብ፤ በየቀኑ እህል የጫኑ በመቶዎች የሚቆጠሩ የጭነት መኪኖች ወደ ትግራይ እየገቡ አሁንም ህወሃት የትግራይ ተራበች ክሱን አላቆመም፤ ታዲያ ለጦርነት ሙሉ በሙሉ ተዘጋጅተናል ሲል ለጦርነት ያሰለፈውን ታጣቂ ምን እያበላ ነው ተብሎ መጠየቅ የለበትም? ነገርን ከስሩ፤ ውሃን ከጥሩ እንደሚባለው መጠየቅና ጥቂት ደቂቃ ወስዶ ማሰላሰል ቢቻል የህወሃትን አላማና አካሄድ ጠንቅቆ ማወቅ ይቻላል። እነዚህ በሰብአዊነት ስም መነገድና ግጭትን በእጅ አዙር እያራገቡ ትንሽ ቀና ማለት የጀመረን ሃገር መኮርኮም ልማዳቸው የሆኑት ሃገራትንም ፍላጎት ከዚሁ አቋማቸው ተነስቶ መረዳት ቀላል ነው።
ቻይና እና ሩሲያን ጨምሮ ስድስት ሀገራት የጦር ልምምድ ሊያደርጉ መሆኑን አስታወቁ
ቻይና በዚህ የጦር ልምምድ ስትካፈል የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜዋ እንደሆነ ተገልጿል
ቻይና እና ሩሲያን ጨምሮ ስድስት ሀገራት የጦር ልምምድ ሊያደርጉ መሆኑን አስታወቁ፡፡
በሩሲያ ግዛት ይካሄዳል የተባለው የጦር ልምምድ በፈረንጆቹ የፊታችን ነሃሴ 30 እስከ መስከረም አምስት ባሉት ስድስት ቀናት እንደሚካሄድ ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
እንደ ዘገባው ከሆነ በዚህ የጦርነት ልምምድ ላይ አዘጋጇ ሩሲያን ጨምሮ ቻይና፣ ቤላሩስ፣ ታጃኪስታን፣ ህንድ፣ ሞንጎሊያ እና ሌሎችን ሀገራት ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡
በዚህ የጦር ልምምድ ከሚሳተፉ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ቻይና የአሁኑ የጦር ልምምድ ከወቅቱ የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ጋር እንደማይገናኝ ገልጻለች፡፡እነዚህ የምስራቅ ሀገራት የጋራ የጦር ልምምዳቸውን ከአራት ዓመት በፊት ያካሄዱ ሲሆን ቻይና ለሁለተኛ ጊዜ በልምምዱ እንደምትካፈል አስታውቃለች፡፡
ይህ የጋራ የጦርነት ልምምድ በሩሲያ እና ቻይና ድንበር አቅራቢያ ካቦራቭስክ በሚባል ስፍራ እንደሚካሄድ የሩሲያ መከላከያ መረጃ ያወጣው መረጃ ያስረዳል፡፡
እንደ ቻይና መከላከያ ሚኒስቴር መግለጫ ከሆነ የዘንድሮው የጋራ የጦር ልምምድ ዓለም አቀፋዊ ትብብሮችን ለማስፋት ያለመ እና እየተከሰቱ ያሉ የደህንነት ስጋቶችን ለማስቆም ያለመ ነው፡፡
ቻይና እና ሩሲያ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ የሚተባበሩባቸውን አጀንዳዎች በየጊዜው እያሰፉ የመጡ ሲሆን ሩሲያ ከዩክሬን ጋር ጦርነት ከመጀመሯ በፊት ሁለቱ ሀገራት የማይተባበሩባቸው አጀንዳዎች አለመኖራቸውን ማሳወቃቸው ይታወሳል፡፡
አሜሪካ ከሁለት ሳምንት በፊት 11 ሀገራትን ያሳተፈ የጋራ የጦር ልምምድ በኢንዶኔዥያ ያካሄደች ሲሆን ከሚቀጥለው ሳምንት በኋላ ደግሞ በእስያ ደቡብ ኮሪያ፣ ጃፓን እና ሌሎች የእስያ ሀገራትን ያሳተፈ ወታደራዊ ልምምድ እንደምታደርግ አስታውቃለች፡፡
🛍ጥያቄ ቁ.2
የአባይ ወንዝ ተፋሰስ ከሆኑት አገራት መካከል ቢያንስ ስድስቱን (6)ይጥቀሱ⁉️
🛍ጥያቄ ቁ.2
በ14ኛው ምዕተ ዓመት የአባይ ወንዝን አቅጣጫ ለማስቀየስ ጥረት ተደርጎ ነበር
አቅጣጫ ለማስቀየስ የሞከሩት ማናቸው እንዲሁም ወዴት ወንዝ⁉️
🛍ጥያቄ ቁ.1
የታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ የተጣለው በምን ወር በስንተኛ ቀንና በስንት አመተ ምህረት ነው እንዲሁም በማን ነው መሰረተ ድንጋዩ የተጣለው
ልብ ያርጉ ወሩን ቀኑና ዓመተ ምህረቱን ሲጠቅሱ በውጮች ይጥቀሱ⁉️
በሱዳን በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከ8 ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶች መውደማቸው ተገለፀ
በትናንትናው ዕለት በበኮርዶፋን፣ ናይል እና ደቡባዊ ዳርፉር ግዛቶች በጣለ ከባድ ዝናብ ምክንያት በትንሹ 52 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡
የሱዳን ብሄራዊ የዜጎች ደህንነት ተቋም ቃል አቀባይ የሆኑት አብደል ጃሊል አብደልርሂም እንዳሉት በሶስቱ ግዛቶች ከሞቱት ዜጎች በተጨማሪ ከስምንት ሺህ በላይ መኖሪያ ቤቶች በጎርፍ ወድመዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ጎርፉ ከግለሰቦች መኖሪያ ቤቶች ባለፈ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት መሰረተ ልማቶች የግለሰቦች ኢንቨስትመንት ስራዎች መውደማቸውንም ቃል አቀባዩ አክለዋል፡፡
"አጋሮቻችንን ለማስታጠቅ ዝግጁ ነን" - ፕሬዝደንት ፑቲን
የሩሲያ ጦር ዓመታዊ ፎረም በሞስኮ አቅራቢያ ተጀምሯል
ወዳጆቿን ዘመናዊ ጦር መሳሪያ ለማስታጠቅ ዝግጁ መሆኗን ሩሲያ ገለጸች።
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፤ ሃገራቸው ለወዳጆቿ ዘመናዊ ጦር መሳሪያዎችን ለማስታጠቅ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።
በላቲን አሜሪካ፣ ኤሽያ እና አፍሪካ ከሚገኙ ሃገራት ጋር ላላቸው ግንኙነት ዋጋ እንደሚሰጡ የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ ሃገራቱን ዘመናዊ ጦር መሳሪያ ለማስታጠቅ ዝግጁ ነን ብለዋል በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት በተላለፈ ንግግራቸው።
የሩሲያ ጦር ዓመታዊ ፎረም በሞስኮ አቅራቢያ ተጀምሯል።
የሩሲያ መሣሪያዎች "በአስተማማኝነታቸው፣ በጥራታቸውና በሚሰጡት ጥቅም እንዲሁም ባላቸው ከፍተኛ ብቃት" በወታደራዊ ጠበብት ዘንድ ተመራጭ ስለመሆናቸውም ተናግረዋል።
"ሁሉም በሚባል ደረጃ ከአንድ ጊዜ በላይ በአውደ ውጊያዎች ጥቅም ላይ ውለዋል" ሲሉም ነው ፕሬዝዳንቱ የተናገሩት።
ሃገራቸው በዩክሬን በማካሄድ ላይ ካለችው ዘመቻ ጋር በተያያዘ በተገለለችበት በዚህ ወቅት ከጎኗ የቆሙ 'ብዙ' ወዳጆቿንም አመስግነዋል እንደ ኤ.ኤፍ.ፒ ዘገባ።
ጦር መሳሪያ አምራቹ የሃገሪቱ መንግስት ተቋም (ሮስቴክ) ግን በዚህ አይስማማም።
የተቋሙ ዋና አስተዳዳሪ ሰርጊ ኬሞዞቭ በፎረሙ እንደተናገሩት ከሆነ በዩክሬን በመካሄድ ላይ ያለው ዘመቻ የሩሲያን የጦር መሳሪያ ንግድ አላቀዛቀዘውም። በዚህ ዓመት ብቻ የአንድ ትሪሊዮን ሩብል ( 16 ቢሊዮን ዶላር ) ዋጋ ያላቸው የግዥ ስምምነቶችን ተፈራርመናልም ብለዋል።
በኬኒያ ምርጫ ተመራጩ ፕሬዚደንት ዊሊያም ሩቶ ላለፉት 10 ዓመታት በተለያዩ መንገዶች አብረዋቸው ለሰሩት የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ምስጋና አቅርበዋል።
ፕሬዚደንቱ በንግግራቸው "ለአለቃዬ ፕሬዚደንት ኡሁሩ ኬንያታ እውቅና መስጠት እፈልጋለሁ" ያሉ ሲሆን ኡሁሩ ባሰባሰቡት መሰረት ላይ ይህችን ሀገር ወደ ላቀ ደረጃ እንዳሸጋገር ለኬንያ ህዝብ ቃል መግባት እፈልጋለሁም ብለዋል።
ዊሊያም ሳሞይ ሩቶ (ዶ/ር) ከደቂቃዎች በፊት ይፋ በተደረገው የምርጫ ውጤት 5ኛው የኬኒያ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸው ታውቋል።
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ የበርካታ የአፍሪካ እና ሌሎች አለም ሀገራት መሪዎች ለተመራጩ ፕሬዚደንት የእንኳን ደስ ያልዎት መልዕክት አስተላልፈዋል።
ነሐሴ 9 ቀን 2014 ዓ.ም
በ2015 በጀት ዓመት ለሰራዊታችን የተሟላ ሎጂስቲስቲክስ በማቅረብ አስተማማኝና ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል ለመገንባት እየሰራን ነው ሲሉ ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ።
የመከላከያ ሎጂስቲክስ ዋና መምሪያ ከሁሉም ዕዞች ከተውጣጡ የሎጂስቲክስ አመራሮች ጋር ዓመታዊ የሥራ አፈፃፀምን በመገምገም ለጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ገለፃ አቅርበዋል።
የሎጀስቲክስ አቅርቦት የሰራዊቱ የጀርባ አጥንት መሆኑን የጠቀሱት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፣ በሁሉም አቅጣጫ የውስጥ እና የውጭ ጠላቶቻችን ግምባር ፈጥረው ቢሰለፉም ለሰራዊታችን የተቀናጀ ሎጂስቲካዊ ፍላጎቶችን በማቅረብ ከሰራዊቱ ጀግንነት ጋር ተዳምሮ ጠላትን ማሳፈር ችለናል ብለዋል።
በ2015 በጀት ዓመት ሰራዊቱ ዘመኑ ያፈራቸውን ወታደራዊ ቴክኖሎጂዎችን እናስታጥቃለን ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የሎጂስቲክስ አሰራር እና ስርዓት በሚፈቅደው ልክ ሰራዊቱ በሚያስፈልገው ቦታ እና ሰዓት የሚያስፈልገውን ሁሉ በማቅረብ ሎጂስቲክስ የሰራዊቱ ደጀን መሆኑን ገልጿል።
የመከላከያ ሎጀስቲክስ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሌ/ጀኔራል አብዱራህማን እስማኤል በበኩላቸው የሎጂስቲክስ ዝግጁነት ከመቸውም ጊዜ በላይ ያደገ መሆኑን ገልፀዋል።
በረከት አዳነ
ፎቶግራፍ በሃይሉ ስለሺ
ሩስያ ከሰሜን ኮሪያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት አጠናክራ ትቀጥላለች ሲሉ ፑቲን ተናገሩ፡፡
የሩስያው ፕሬዝዳንት ቨላድሚር ፑቲን ከሰሜን ኮሪያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል፡፡ የሰሜን ኮሪያ የመገናኛ አውታሮች ባወጡት መረጃ መሰረት ፔዮንግያንግ እና ሞስኮ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ማጠናከር በሚችሉበት መንግድ ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል፡፡
የሩስያው ፕሬዝዳንት ለሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን፣ ሰሜን ኮሪያ ከጃፓን ነጻ የወጣችበትን 77ኛ የነጻነት ቀንን በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት መላካቸውን ተነግሯል፡፡
ፑቲን በመልዕክታቸው ሰሜን ኮሪያ በሩቅ ምስራቅ ያላትን ቀጠናዊ ተሰሚነት እና የበላይነት አጠናክራ ትቀጥላለች ያሉ ሲሆን፣ ቀጠናዊ ትስስርን ማጠናከር የቀጠናው ጸጥታ ማስጠበቅ እና በኢኮኖሚው ረገድ ተደጋግፎ መስራት ሁለቱ ሀገራት ትኩረት የሚያደርጉባቸው ጉዳዮች ናቸው ብለዋል፡፡
የሰሜን ኮሪያ እና የሩስያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ወዲህ እንደጀመረ ይነገራል፡፡ የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን ሩስያ የአለምን ሰላም ከመጠበቅ አንጻር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያረገች የምትገኝ ሀገር መሆኗን ገልጸዉ፣ ከሩስያ ጋር አብሮ መስራት እድለኝነት ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሁለቱ ሀገራት በወታደራዊ ዘርፎች ላይ በጋራ የሚሰሩ ሀገራት ሲሆኑ በተለያዩ ጊዜያትም ወታደራዊ ለምምዶች ሲያደርጉ ይስተዋላል፡፡
አልጀዚራ
የመጀመሪያዋ ዘመናዊ የኢትዮጵያ የጦር መርከብ ማን ትባላለች ?
🛳 🛳 ⚓️ 🟩🟨🟥
የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ ዘመናዊ የጦር መርከብ ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም ከመያዟ በፊት P.C. 1616 ትባል ነበር። ይህች ዘመናዊ መርከብ ከአሜሪካን መንግስት በእርዳታ የተገኘች ነበረች።
ይህቺ P.C. 1616 መርከብ ኢትዮጵያዊ የሆነ ስም እንዲወጣላት በማስፈለጉ በጊዜው የነበረውን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ እና ለኢትዮጵያ ታላቅ ዓስተዋጾ ባደረገው በጀግናው ዘርዓይ ደረስ ስም ተሰየመች።
➛ ከላይ የ 3ቱ ምስል መግለጫ ፦
P.C. 1616 መርከብን ወደ ምፅዋ ወደብ ይዞ የመጣው መርከበኛ ቡድን ፣ ግርማዊ ጃንሆይ (ቀ.ኃ.ሥ) P.C. 1616 መርከብን ሲጎበኙ እና ጥቅምት ፭ ቀን ፩፱፻፶ ዓ.ም ላይ በተዘጋጀው የጉብኝት ፕሮግራም ላይ የጀግናው የዘርዓይ ደረስ እናት በልጃቸው ስም የተሰየመችውን የጦር መርከብ ሲጎበኙ ይታያሉ።
#ታሪክን_ወደኋላ
©️ ኢትዮጵያ የባህር ጠረፏ እና ባህር ኃይሏ (ሰዋሰው ታሪክ)
የአሜሪካ ህግ አውጭዎች ታይዋን ገብተዋል፤ የአሜሪከ እና ቻይና ፍጥጫም ቀጥሏል
ከፔሎሲ ጉብኝት በኋላ ከፍተኛ የአሜሪካ የልኡካን ቡድን ታይዋን ገብቷል
የአሜሪካ ህግ አውጭዎች ለሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት በዛሬው እለት ታይዋን ገብተዋል፡፡
የህግ አውጭዎቹ ጉብኝት፤ የአሜሪካ አፈጉባኤ ናንሲ ፔሎሲ በታይዋን ካደረጉት ጉብኝት ቀጥሎ ታይዋንን የጎበኘ የከፍተኛ ባለስልጣናት የልኡክ ቡደን መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የፔሎሲ የታየዋን ጉብኝት ታይዋንን የግዛቷ አካል አድርጋ የምታያትን ቻይናን ክፉኛ ማስቆጣቱ ይታወሳል፤ ሁለቱ ኃያላን ሀገራትም ወታደራዊ ፍጥጫ ውስጥ ውስጥ ሊገቡ ችለዋል፡፡
የልኡክ ቡድኑ ከታይን ፕሬዝደንት ጻይ ኢንግ ዌን ጋር ይገናኛሉ፡፡
በታይፔ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ የልዑካን ቡድኑ በሴናተር ኢድ ማርኬይ እየተመራ የሚያካሂደው የኢንዶ-ፓሲፊክ ክልል ትልቅ ጉብኝት አካል እንደሆነ ገልጿል።
የታይዋን ፕሬዚዳንታዊ ጽህፈት ቤት ቡድኑ ሰኞ ማለዳ ላይ ከፕሬዝዳንት ጻይ ኢንግ ዌንግ ጋር እንደሚገናኝ ተናግሯል።
በፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት የተቆጣችው ቻይና፤ በታይዋን ዙሪያ ወደራዊ ልምምድ አድርጋለች፤ በፔሎሲም ላይ ማእቀብ ጥላለች፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ቻይና ከአሜሪካ ጋር የነበራትን ወታደራዊ ትብብር ማቋረጧን ማስታወቋ ይታወሳል፡፡
#Egypt_ኢትዮጵያ ከግድቡ ሙሌት ማግስት
በዛሬው ዕለት የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ የካቢኔ ሹም ሽር አድርገዋል።
በዚህ የካቢኔ ሹም ሽር ላይ የውሃና መስኖ ሚንስትሩ ሞሐመድ አብድል አቲን (የታላቁ ግዳሴ ግድብን ድርድር የሚመሩ) ከሥልጣን ተነስተው በሌላ ሰው ተተክተዋል።
ሞሐመድ አብድል አቲን የተከቱት ዶ/ር ሐኒ ስዌይላም የተባሉ ሰው ሲሆኑ ታዋቂ የውሃ ሃብት ተመራማሪ ናቸው ተብሏል። በካይሮ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲም እንደሚያስተምሩ ተነግሯል።
ፕሬዝዳንት ሲሲ ሌሎች የካቢኔ ሹም ሽሮችንም ያደረጉ ሲሆን አጠቃላይ የ13 ካቢኔ አባላት ሹም ሽር ነው ያደረጉት።
የጤና፣ የቱሪዝም፣ የንግድ እና ኢንዱስትሪ፣ የሲቪል አቪየሽን፣ የትምህርት እና ሌሎች ሚኒስትሮችንም በአዲስ ተተክተዋል ተብሏል።
አል ሲሲ የመከላከያ፣ የደህንነት፣ የፋይናነስ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችን እንዳልቀየሩም ተገልጿል።
ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባን ያደረገው የሃገሪቱ ፓርላማም በፕሬዝዳንቱ የቀረበውን ሹም ሽር በሙሉ ድምጽ ማፅደቁን አል ዓይን የሀገሪቱን ሚዲያዎች ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
አል ሲሲ የካቢኔ ሹም ሽር ያደረጉት የመንግሥታቸውን የሥራ አፈጻጸም ለማሻሻል እና የግብጻዊያንን ጥያቄ ለመመለስ እንደሆነ አስታውቀዋል።
የካይሮ አዲስ ፀረ-ኢዮጵያ ፕሮጀክት
ግብፅ፦ በአፍሪካዊ ወጣቶችና ጋዜጠኞች የኢትዮጵያን ጉዳይ የማራገብ አህጉር-አቀፍ ዘመቻ
የዓባይልጅ ✍️ እስሌማን ዓባይ
ግብፅ ለዲጂታል ፕሮፓጋንዳ አላማ በተፋሰሱ ሀገራት የተለያዩ ቋንቋዎች የሚሰራጩ የራዲዮ ጣቢያዎች የመክፈት ስራዎችን ባሳለፍነው አመት መጀመሯን የምናስታውሰው ነው። በዚህ አመት ከወሰደችው ርምጃ ውስጥ ዋነኛ የሚባለው የሀገሪቱን የሚዲያ ጥናትና ስልጠና ኢንስቲትዩት በግብፅ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር ማድረግ ነበር። ይህን Center for Training and Media Studies በአዲሱ ተጠሪ ተቋም ስር ይሆን ዘንድ የአልሲሲ ትእዛዝ ሲሆን አቅጣጫውን በይፋ የሰጡት ደግሞ የግብፁ ጠቅላይ ሚኒስትር ናቸው፤ ጊዜውም በ 16/2 2022 እኤአ። ይህን ተከትሎም ግብፅ በአፍሪካ ትልቁ ነው የተባለውን አህጉራዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና በነገው እለተ እሁድ ይፋ እንደምታደርግ ሰምተናል።
የግብፁ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ እና የግብፅ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሊቀመንበር ካራም ጃብር ይከፍቱታል ተብሏል። በሚዲያ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች የግብፅ አንገብጋቢ በተባሉ ጉዳዮች ዙሪያ አውደ ጥናቶች የሚካሄዱበት ነው። ሲደረጉ እንጂ በሽፍንፍን መግለጫቸው በውል ያልተጠቆሙ ድብቅ አጀንዳዎች እንደተጠበቁ ሆነው በሰማነው ደረጃ ራሱ በዋነኛነት "የግብፅ የናይል ጥቅምና አፍሪካዊ የዲፕሎማሲና የግጭት ትርክት" የሚሉ አጀንዳዎችን ጨምሮ ተከታዮቹ የተካተቱበት ይሆናል፦
▪️በካይሮ እና ካርቱም መካከል የጋራ የሚዲያና ፕሬስ ራዕይ መንደፍ
▪️ማህበራዊ ሚዲያ በመገናኛ ብዙሃን ላይ ስላለው ተፅእኖ
በማህበራዊ ሚዲያና መገናኛ ብዙሃን እንዴት መዋጋት እንደሚቻል
▪️ግብፅ በናይል ወንዝና በተፋሰስ ሀገራቱ ላይ የሚኖራትን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና ጥቅም እንዴት ማስረፅ እንደሚቻል።
▪️አመጽ እና ግጭት ባለባቸው ቦታዎች ትርክትን እንዴት ማስኬድ እንደሚቻል የሚደረግ የውይይት መድረክ፣
▪️በአፍሪካ የውሃ ሃብቶችና የጎርፍ ስጋቶች ዙሪያ
▪️የዲጂታል ኃይሎች በአለም አቀፍ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ እንዲሁም በብሔራዊ ደህንነት ላይ የሚኖራቸውን ሚና የተመለከተ ስልጠና
በዚህ የስልጠና መርሃግብር ሰልጣኞቹ ከበርካታ ግብፃዊና አለም አቀፍ ከሆኑ ባለሙያዎች፣ ምሁራንና የግብፅ ሚዲያ መሪዎች ጋር ይገናኛሉ። የጥንቷና የአሁኗ ግብፅ ሀውልቶች በርካታ ውይይቶችና ትምህርታዊ ብሎም የመዝናኛ ጉብኝቶችን የተካተቱበትም ነው። በአፍሪካ ደረጃ ትልቁ የተባለው ስልጠና መርሃ ግብር የሚከተለውን ይመስላል።
▪️የአፍሪካ ሚዲያ የሥልጠና The African media training program ከ 14/8/2022 እስከ 9/8/2022 ለሱዳን ለሚገኙ የሚዲያ ባለሙያዎች ስፔሻላይዝድ የተደረጉ 10 የሥልጠና ኮርሶች ለ 4 ሳምንታት
▪️ለወጣት አፍሪካዊያን ለ (3 ሳምንታት) የሚሰጠው ስልጠና ከ9 ወይም 10 ጀምሮ እስከ 29/9/2022 ታቅዷል።
▪️በመቀጠልም ለእንግሊዘኛ ተናጋሪ አፍሪካዊ ብሮድካስተሮች መሰረታዊ ኮርስ ሲሆን ለ 4 ሳምንታት የሚቆይ ነው።
▪️በመቀጠልም ስፔሻላይዝድ የእንግሊዘኛ ኮርስ ከኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ስልጠናዎች በተመረጡ ዘርፎች ይከተላል ይህም ከ6/11 እስከ 17/11/2022..።
▪️ለደቡብ ሱዳን ጋዜጠኞች በልዩ የተዘጋጀው ስልጠና ከ20/11 እስከ 15/12/2022 ለ4 ሳምንታት ይቀጥላል።
▪️ለፈረንሳይኛ ተናጋሪ አፍሪካውያን ጋዜጠኞች የመሠረታዊ የሥልጠና ኮርስ ተግባራት ከ12/25 እስከ 19/1/2023 የሚቆይ ሲሆን በመቀጠልም ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ ልዩ ኮርስ በተመረጠ ዘርፍ የመረጃና ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ይሰጣል።
▪️ለአረብኛ ተናጋሪ አፍሪካዊ ጋዜጠኞች ለአንድ ወር የሚቆይ ስልጠና ከ5/2/2023 እስከ 2/3/2023
▪️የአረብኛ ስፔሻላይዝድ ስልጠና ከ5/3 ጀምሮ ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ ይሆናል።
▪️የአፍሪካ የሚዲያ ስልጠና መርሃ ግብር ሲጠናቀቅ የወጣት አፍሪካውያን ጋዜጠኞች ስልጠና ለሳምንታት ከ6/5 እስከ 25/5/2023 የሚቆይ ይሆናል።
ይህ እንደ አፍሪካ የጀመረችው የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ መነሻውም ሆነ መድረሻው የዓባይ ጉዳይ ነው። የህዳሴ ግድቡን ምንም ማድረግ ባትችልም ኢትዮጵያዊያኑን በመረጃ ጦርነት ማናከስና ማመሰቃቀል ግን ቀሪ አማራጯ የሆነ ይመስላል። ለዚህ ደግሞ በኢትዮጵያ ስር እየሰደዱ የሚታዩት የጥላቻ ንግግሮችና ግጭቶች አመቺ ሆኖላታል።
ይህ የካይሮ የፕሮፓጋንዳ ጦርነት እንደ ሀገር ሁሉንም ባለድርሻ ያቀናጀ አፋጣኝ ዝግጅት የሚጠይቀን ነው።
#የዓባይልጅ
/
