es
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Ir al canal en Telegram

Addis abeba Ethiopia

Mostrar más
5 082
Suscriptores
-11024 horas
-1 9137 días
-2 77030 días
Archivo de publicaciones
#ጀነራል_ሙሁዚ_ኬኒሩጋባ ፑቲንን መከላከል ካስፈለገ ኡጋንዳ ወታደሮቿን ወደ ሞስኮ ትልካለች -የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ልጅ ኡጋንዳ በዩክሬን ግጭት ላይ በተባበሩት መንግስታት ምክረ-ሀሳብ ድምጽ ከመስጠት ተቆጥባለች በሳለፍነው አርብ ምሽት የሩሲያው የቅጥረኛ ወታደር ቡድን ዋግነር ከዩክሬን ወደ ሩሲያ ገብቶ ሮስቶቭ የተሰኘችውን ከተማ አብዛኛው ክፍል መያዙን ተከትሎ በትናትናው እለት በሩሲያ ውጥረት ነግሶ ውሏል። ዋግነር በመሪው ይቪግኒ ፕሪጎዥን በኩል የአመጽ ጥሪ ማስተላለፉን ተከትሎም በትናትናው እለት በሩሲያ ጦርና በዋግነር ቡድን መካከል ግጭቶች ተከትሰተው ነበር። ይህንን ተከትሎም የኡጋንዳ መሪ ዩዌሪ ሙሴቬኒ ልጅ ሙሁዚ ካይኔሩጋባ የ"ኢምፔሪያሊስት" ስጋት ሲያጋጥም የኡጋንዳ ወታደሮች ሞስኮን እንደሚከላከሉ ተናግረዋል። "ከፈለግክ የፑቲን አፍቃሪ ብለህ ጥራኝ፤ እኛ ኡጋንዳዊያን ሞስኮ በኢምፔሪያሊስቶች ስጋት ውስጥ ከወደቀች ወታደሮችን መላክ አለብን" በማለት በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል። በትዊተር ላይ አወዛጋቢ መግለጫዎችን መስጠት የሚታወቁት የ48 ዓመቱ ካይኔሩጋባ በዚህ ወር ለ2026 ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እንደሚወዳደሩ አስታውቀዋል። ኡጋንዳ በዩክሬን ግጭት ላይ በተባበሩት መንግስታት ድምጽ ከመስጠት ተቆጥባለች። ሩሲያ ዩክሬንን የወረረችበትን አንደኛ ዓመት አስመልክቶ ሞስኮ ወታደሮቿን ከሀገሪቱ እንድታስወጣ የሚጠይቀውን ድምጽም እንዲሁ።  በአህጉሪቱ ከቅኝ ገዢዎች ጋር ይታገሉ የነበሩትን የነጻነት እንቅስቃሴዎችን በመደገፍ ሩሲያ ከአፍሪካ ጋር ጠንካራ ግንኙነት ነበራት።  ተንታኞች ሙሁዚ ካይኔሩጋባ የ78 አመቱ የአባታቸው ዩዌሪ ሙሴቬኒ ተተኪ እንደሆኑ አድርገው ይቆጥሯቸዋል።

#ሰበር_ዜና የህብረተሠቡን ሠላም ለማናጋት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጥፋት ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ። በሰሜን ሸዋ ዞን ከነፍስ ወከፍ እስከ ቡድን መሣሪያ ዲሽቃ በመታጠቅ የህብረተሰቡን ሠላም ለማናጋት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የጥፋት ቡድኑ አባላት በዞኑ ፀጥታ ኃይልና በመከላከያ ሠራዊቱ የተቀናጀ ዘመቻ እኩይ ዓላማቸውን ለመፈፀም እየተማከሩ ባሉበት ድንገት በቁጥጥር ስር ውለዋል። በቁጥጥር ሥር የዋሉት የቡድኑ አባላት ቁጥር 25 ሲሆን  ከዚህ ቀደም የመከላከያ ሠራዊትና የልዩ ኃይል አባል የነበሩ በኅቡዕ ሴራቸውን ለማስፈፀም በሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ተታለው ጫካ የገቡ ወጣቶች ናቸው። የሰሜን ሸዋ ዞን የፀጥታ ኃይል ክትትል እያደረገ ባለበት ወቅት የጥፋት ቡድኑ አባላት ተኩስ በመክፈታቸውና የከፋ ጉዳት ሊያደርሱ  በመሆኑ በቀጠናው ለሚገኘው መከላከያ ሠራዊት አስቸኳይ ሪፖርት በማድረግ በፍጥነት በቦታው ላይ በመድረስ መቆጣጠር ተችሏል። የሠላም ፀር የሆኑ እነኝህ የቡድኑ አባላት የግለሰብ ቤት በመከራየት በሚሰጣቸው ተልዕኮ መሠረት የጥፋት ተግባራቸውን  ለመፈፀም 1ዲሽቃ፣ 2 ብሬን ፣4 ስናይፐር ፣5 ክላሽ፣ 2 ሽጉጥና ከ2,300 በላይ ተተኳሽ ጥይቶችን እንዲሁም ጥሬ ገንዘብና በባንክ አካውንት ላይ እስከ ግማሽ ሚሊዮን  ብር ድረስ ይዘው ሲንቀሳቀሱ ተይዘዋል። የጥፋት ቡድኑን አባላት  በፈጣን ክትትል መቆጣጠር ባይቻል ኖሮ  በሕብረተሰቡ  ላይ ጥፋት ያደርሱ እንደነበር የገለፁት  የፀጥታ ኃይል አባላት የሕዝቡን ሠላም ለማስጠበቅ አበክረው እየሰሩ መሆኑንም ተናግረዋል። በሕግ ጥላ ሥር የዋሉት ግለሰቦችም አብዛኞቹ ተታለው እንደገቡና ሕገ ወጥ አደረጃጀት ፈጥረው መንቀሳቀሳቸውን በማመን ወጣቶች ከእንደዚህ ዓይነቱ ዓለማ ከሌለው  ተግባር መቆጠብ እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

👉 "የሠራዊቱን አኗኗር ለማሻሻል የሚደረጉ የካምፕና የመኖሪያ ቤት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ‼️"   -ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ የተገነባው የኮማንዶና የአየር ወለድ ዕዝ የመኖሪያና የስራ ካምፕ ምረቃ ተካሄዷል። በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የጦር ሀይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ  የሰራዊቱን ካምፕና የመኖሪያ ቤቶችን በብዛትና በጥራት የመገንባት ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በዋና መምሪያው የሚገነቡ ካምፖችና ቤቶች  ወጪና ቦታ ቆጣቢ እንዲሆኑ ለማስቻል የኮንስትራክሽን ስራውን የሚያሳልጡ አደረጃጀቶችና ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም ላይ  በትኩረት መስራት እንደሚኖርባቸውም  ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ገልፀዋል። የመከላከያ መሐንዲስ ዋና መምሪያ ሀላፊ ሌተናል ጄኔራል ደስታ አብቼ ፤ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ለሰራዊቱ ዘመናዊ ካምፖች ፤ የትምህርት ተቋማት እና የመሰረተ ልማት ግንባታዎችን በሰራዊቱ ሙያተኞች አቅም በታቀደላቸው ጊዜና በጀት እየተገነቡ እንደሚገኙ ተናግረዋል። የግንባታ ዕቃዎች ዋጋ መጨመርና የተቋራጮች የአቅም ውስንነትን እንደ ተግዳሮት ቢያጋጥሙም በበጀት ዓመቱ ለሀገርና ለተቋም መሰረታዊ ጥቅም የሚሰጡ ግንባታዎችን ማከናወኑን ገልፀዋል። የወንዶ ጢቃ ፕሮጀክት ሀላፊ ሻለቃ እሸቱ ተስፋዬ ግንባታው እስከ ሰባት ሺህ ሰራዊት የሚይዝ መሆኑን ገልፀው ከዘመናዊ የመኖሪያና የስራ ቢሮዎች በተጨማሪ  ከ7.5 ኪሎ ሜትር በላይ የአጥር ስራ ፤ የጎርፍ መከላከያ ፤  ሁለት የጥልቅ ጉድጓዶች ፤ የህክምና የመመገቢያ ዘመናዊና የመሰብሰቢያ አዳራሾች የዳቦ  ቤትና ቄራ የተገነባ መሆኑን አብራርተዋል። በዝግጅቱ ማጠናቀቂያ ላይ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ  ከመሀንዲስ ዋና መምሪያ ካምፑን ተረክቧል። በምረቃው መርሃ ግብር ላይ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ጨምሮ በኬንያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ባጫ ደበሌ፣ የሻሸመኔ ከተማ ከንቲባ፣ የሠራዊቱ ከፍተኛ አመራሮችና የአካባቢው ማህበረሰብ ተገኝተዋል። ሙሉውን ከወደዱት ሼር ያድርጉት ✌ https://t.me/CommandoAndAirborneCommand ሰብስክራይብ ያድርጉን 👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034

በሚሊየን ከፍለው ህይወታቸውን ያጡት ባለሀብቶች ሰሞኑን መነጋገሪያ ሆና ባለሀብቶቹን ይዛ የጠፋችው ሰርጓጅ መርከብ ትናንት ፈንድታ ሰዎቹንም እስከወዲያኛው አሰናብታ ተገኝታለች። ከ100 አመታት በፊት
በሚሊየን ከፍለው ህይወታቸውን ያጡት ባለሀብቶች ሰሞኑን መነጋገሪያ ሆና ባለሀብቶቹን ይዛ የጠፋችው ሰርጓጅ መርከብ  ትናንት ፈንድታ ሰዎቹንም እስከወዲያኛው አሰናብታ ተገኝታለች። ከ100 አመታት በፊት የሰጠመችውን የታይታኒክ መርከብ ለማየት ተንቀሳቅሰው የነበሩ አምስት ሰዎች የተሳፈሩባት ቲታን የተሰኘችው ባህር ሰርጓጅ ጀልባ አደጋኛ በሆነ ሁኔታ ፈንድታ ህይወታቸው ማለፉን የአሜሪካ የድንበር ጠባቂ አስታውቋል። ሰዎቹን በህይወት ለማዳን ሲደረግ የነበረው የአምስት ቀናት ፍለጋም አብቅቷል። ቲታኗን የመፈለግ ስራው ይዛው የነበረው ለ96 ሰአታት እንደሚበቃ የተገመተው የኦክስጅን መጠን በትናንትናው እለት ማለቁ ተስፋ አስቆራጭ ደረጃ ደርሶ ነበር። ከካናዳ መርከብ የተላከ በሮቦት አማካኝነት ጠልቆ በገባ መሳሪያ ከባህር ገጽ 488 ሜትር ርቀት ላይ ቲታን የፈነዳችበትን ቦታ በሰሜን አትላንቲክ ጫፍ  ማግኘቱን የአሜሪካ ድንበር ጥበቃ አዛዥ አድሚራል ጆን ማጉዋር ተናግረዋል። የድንበር ጥበቃ ባለስልጣናት እንደገለጹት 6.7 ሜትር ርዝመት ካላት ቲታን አምስት ትላልቅ ስብባሪዎች ተገኝተዋል። ባለስለጣናቱ በቦታው የሰው አካል ስለመገኘቱ ያሉት ነገር የለም። "ይህ ሰብርባሪው ያለበት ቦታ ሰርጓጇ ጀልባ በአደገኛ ሁኔታ ከፈነዳችበት ጋር ተመሳሳይ ነው" ብለዋል ማጉዋር። ቲታን የሚያመርተው ድርጅት ኦሽንጌት፣ የድንበር ጥበቃ ባለስልጣናት ከመናገራቸው ቀደም ብሎ ቲታንን ሲያበር የነበረውን ሰው ጨምሮ በህይወት የተረፈ አለመኖሩን ገልጾ ነበር።

ሀብታሞች ሊደባደቡ ነው 🥊🥊 ፊስቡክ ና ትዊተር ሊደባደቡ ነው 🥺 የዓለም ሀብት ማማ ላይ የተቀመጡት እነዚህ ሁለት የአለማችን ቢሊየነሮች ቦክስ ሊገጥሙ ሁለቱም challenge ተቀብለዋል የትዊተሩ
ሀብታሞች ሊደባደቡ ነው 🥊🥊 ፊስቡክ ና ትዊተር ሊደባደቡ ነው 🥺 የዓለም ሀብት ማማ ላይ የተቀመጡት እነዚህ ሁለት የአለማችን ቢሊየነሮች ቦክስ ሊገጥሙ ሁለቱም challenge ተቀብለዋል የትዊተሩ እንዲሁም :- * የተስላ መኪና ድርጅት ባለቤት ኤሎን ማስክ * 232 ቢሊዮን ዶላር ሀብት ሲኖረው * የዋትሳብ * የኢንስትግራም ና * የፊስቡኩ ባለቤቱ ማርክ ደሞ * 100 ቢሊዮን ዶላር ሀብት አለው ኤሎን እኔ ማርክ እንደ ቆሎ እበትነዋለ እያለ እየፎከር ሲሆን ማርክ ደሞ አረ እኔ እልል ብዬ አሳምሬ እዘርረዋለው እያለ ነው ማን ያሸንፋል የሚሉት ጥያቄዎች በማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ዘንድ እንደገዱ ወሬው እየሞቀ ሲሆን ድብዱብ በአሜሪካኗ በላስ ፌጋስ ከተማ ሊካሄድ እንደሚችል እየተነገረ ነው ድብድቡ የዓለማችን ውድ ድብድብ ሊሆን እንደሚችልም እየተነገረ ይገኛል:: ማን ያሸንፍ ይሆን ? * ማርክ የፌስቡኩ ወይንስ * ኤሎን የትዊተሩ እንዲሁም ሀብታም ሲጣላ ለማየት ብዙ ሚሊዮን ሰዎች ይገባሉም ተብሏል:: 🥊🥊🥊 🌴🌴🌴

01💓ጠንካራ ሰው ሁን ማለት አትውደቅ ማለት አይደለም           ወድቀህ መነሳትን ልመድ ማለት እንጂ! 02💕ዝም በል ማለት አትናገር ማለት አይደለም           ሌሎችን ለመስማትም ጆሮ ስጥ ማለት እንጂ! 03💔 ሆዳም አትሁን ማለት አትብላ ማለት አይደለም           በሰዎች ሃቅ ላይ አትለፍ ማለት እንጂ! 04√💓አትቆጣ ማለት ስሜት አይኑርህ ማለት አይደለም           ከቁጣ ቶሎ ተመለስ ማለት እንጂ! 05√√ ይቅርታ አድርግ ማለት አልተጎዳህም ማለት አይደለም           በሆድ ቂም መያዝ ሌላ ጉዳት ስለሆነ እንጂ! 06√√ ጠላትህን ውደድ ማለት ጠላት ጥሩ ነው ማለት አይደለም           ከጥላቻ ይልቅ ፍቅር ስለሚያሸንፍ እንጂ! 07√√ ደስተኛ ሁን ማለት ሁሉ ይኑርህ ማለት አይደለም           ባለህ ነገር ደስ ይበልህ ማለት እንጂ 08√√ ስራህን ወደድ ማለት የምትሰራው ስራ ጥሩ ነው ማለት           አይደለም ነገ ጥሩ ስራ እንዲኖርህ ዛሬ የምትሰራውን ወደድ           ማለት እንጂ! 09√√ ወረኛ አትሁን ማለት አታውራ ማለት አይደለም           ምንም ስለማታውቀው ነገር አታውራ ማለት እንጂ! 10√√ ትሞታለህ ማለት አትስራ ማለት አይደለም           ምንም ቁም ነገር ሰትሳራ አትሙት ማለት እንጂ! 11💕ብቸኛ አትሁን ማለት ሮጠህ ትዳር ያዝ ማለት አይደለም           ልብህን ጊዜህን ያለህን ሁሉ አሳልፈህ ለመስጠት ዝግጁ           ሁን ማለት እንጂ! 1💚 እውነተኛ ሁን ማለት ሰዎች ባሉበት ብቻ እውነት ተናገር ማለት           አይደለም ለራስህም የእውነት ኑሮ ኑር ማለት እንጂ! 13💗አትጣላ ማለት ከሰው ጋር አትጋጭም ማለት አይደለም           ቂም ይዘህ አትቆይ ማለት እንጂ! 14💜ኩራተኛ አትሁን ማለት አትዘንጥ ማለት አይደለም           ሌሎችን አትናቅ ማለት እንጂ! 15💝 ቆንጆ ነህ ማለት ከሌሎች የተሸልክ ነህ ማለት አይደለም           አምሮብሃል ማለት እንጂ! 16💟 አዋቂ ሁን ማለት እንደገና ት/ቤት ሂድ ማለት አይደለም           ብልህ ሁን ማለት እንጂ ❤ ስንተኛው ተራ ቁጥር ላይ ያለውን ወደዱት ? ሙሉውን ከወደዱት ሼር ያድርጉት ✌

የገነት መግቢያ ትኬት በ 500$ እየሸጠ የነበረ የዝንባብዌ ፓስተር ታሰረ። እየሱስ ክርስቶስ በአካል መጥቶ አግኝቶኝ ነው ትኬቶቹን የሰጠኝ ብሏል። ዘንድሮ የማንሰማው ጉድ የለም 😳 ወሳኝ መረጃዎችን
የገነት መግቢያ ትኬት በ 500$ እየሸጠ የነበረ የዝንባብዌ ፓስተር ታሰረ። እየሱስ ክርስቶስ በአካል መጥቶ አግኝቶኝ ነው ትኬቶቹን የሰጠኝ ብሏል። ዘንድሮ የማንሰማው ጉድ የለም 😳 ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇 https://t.me/reporter_ethiopian https://t.me/reporter_ethiopian

ሩሲያ በቤላሩስ የኒውክሌር ጦር መሳሪያን አስቀመጠች ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ምዕራባውያን በዩክሬን ጦርነት በሞስኮ ላይ ስልታዊ ሽንፈት ለማድረስ ሁሉንም ነገር እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል ።ለዙህም
ሩሲያ በቤላሩስ የኒውክሌር ጦር መሳሪያን አስቀመጠች ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ምዕራባውያን በዩክሬን ጦርነት በሞስኮ ላይ ስልታዊ ሽንፈት ለማድረስ ሁሉንም ነገር እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል ።ለዙህም ሩሲያ በቤላሩስ የመጀመሪያውን ታክቲካል የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ማስቀመጧን ገልፀዋል። ፑቲን በኢኮኖሚ ፎረም ላይ እንደተናገሩት ታክቲካል የኒውክሌር መሳሪያው ጥቅም ላይ የሚውለው የሩሲያ ግዛት ላይ አደጋ ከደረሰ ብቻ መሆኑን አክለዋል። የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት ሩሲያ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ለመጠቀም ማቀዱን የሚጠቁም ምንም ነገር የለም ብሏል። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ዋና ፀሀፊ አንቶኒ ብሊንከን ከፑቲን አስተያየት በኋላ "ሩሲያ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ለመጠቀም እየተዘጋጀች ስለመሆኗ ምንም አይነት ምልክት አላየንም" ብለዋል። ቤላሩስ ቁልፍ የሩሲያ አጋር ናት እናም ባለፈው አመት የካቲት ወር ላይ ፑቲን በዩክሬን ላይ ላደረጉት ሙሉ ወረራ እንደ ማስጀመሪያ ቤላሩስ አገልግላለች ሲሉ ተደምጠዋል። ፑቲን ታክቲካል የኑክሌር ጦር መሳሪያዎችን ወደ ቤላሩስ ማስቀመጥ እስከ ወሩ መጨረሻ ይጠናቀቃል ሲሉም አክለዋል ። ሩሲያ በቤላሩስ የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ማሰማራቷን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ በኒውክሌር አቀማመጥዋ ላይ ምንም ዓይነት ማስተካከያ እንዳላደረገች ተሰምቷል። ፑቲን ሞስኮ በግዛቷ ወይም በህልውናዋ ላይ ስጋት ካለ "በንድፈ ሀሳብ" የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ልትጠቀም ትችላለች ሲሉ አስተያየት መስጠታቸውን ዋሽንግተን አውግዛለች። ከሶቪየት ኅብረት ውድቀት በኋላ ከሩሲያ ውጭ የመጀመሪያው የኒውክሌር ጦር መሳሪያን በሌላ ሀገር ሩሲያ ያስቀመጠች ሲሆን ዩክሬንን ለሚያስታጥቁ እና ለሚደግፉ የምዕራቡ ዓለም ሀገራት ማስጠንቀቂያ ነው ተብሏል ።

"ወጣት የሕዋ መሪ" በሚል የተመረጠው ኢትዮጵያዊው ትንሳኤ አለማየሁ ኢትዮጵያዊው ወጣት ትንሳኤ አለማየሁ የ 2023 IAF young space leaders (ወጣት የሕዋ መሪዎች) መካከል አንዱ ሁኖ ተ
"ወጣት የሕዋ መሪ" በሚል የተመረጠው ኢትዮጵያዊው ትንሳኤ አለማየሁ ኢትዮጵያዊው ወጣት ትንሳኤ አለማየሁ  የ 2023 IAF young space leaders (ወጣት የሕዋ  መሪዎች) መካከል አንዱ ሁኖ ተመርጧል። ከወጣት ትንሳኤ ጋር በስራ ዘመናቸው ለጠፈር ምርምሮች አስተዋፅዖ ያደርጉ የተባሉ ሌሎች 4 ወጣቶችም ተመርጠዋል። ወጣቱ በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ በሜካኒካል ኢንጂነሪንግ በላቀ ውጤት የተመረቀ ሲሆን በአፍሪካ ስፔስ ሳይንስ እና ኢንጂነሪንግ አሻራውን እያሳረፈ የሚገኝ ወጣት ነው። በአሁኑ ጊዜ በበጎ ፈቃደኝነት ለስፔስ ጀነሬሽን አማካሪ ምክር ቤት (SGAC) የአፍሪካ አስተባባሪ በመሆን እያገለገለ የሚገኝ ሲሆን ትንሣኤ ቀጣዩን የጠፈር ባለሙያዎችን በማብቃት ወሳኝ ሚና ይጫወታል ተብሎ ተስፋ የተጣለበት ወጣት ሆኗል። ወጣቱ በዘርፉ ላበረከታቸው ልዩ አስተዋፅዖዎች፦ - እ.ኤ.አ. በ2022 ከዓለም አቀፉ የጠፈር ተመራማሪዎች ፌደሬሽን (አይኤኤፍ) የተበረከተውን ተስፋ የተጣለባቸው ስፔስ መሪዎች ሽልማትን፤ - ከ30 አመት በታች የአፍሪካ ስፔስ ኢንዱስትሪ ሽልማት፤ - በ2021 ከስፔስ ኢን አፍሪካ እና ከSGAC የግሎባል ግራንት ፕሮግራም ሽልማትን፤ - በ2019 ደግሞ ከኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ ሶሳይቲ የወጣት ሕዋ አምባሳደርን ጨምሮ ሌሎች ብዙ ሽልማቶችን እና እውቅናዎችን አግኝቷል። ወጣት ትንሣኤ፥ በSGAC ካለው የሥራ ድርሻ በተጨማሪ በቅርቡ CubeSpace የተባለ በዓለም መሪ የሳተላይት ADCS ማምረቻ ድርጅትን በመቀላቀል የሽያጭ መሐንዲስነት እየሰራ ይገኛል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሰኔ 10 ቀን 2015 ዓ.ም ወታደራዊ መደብርና መዝናኛ ክበቦች የሠራዊቱን ማህበራዊ ህይወት እየደገፉ ነው፡፡ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ወታደራዊ መደብርና መዝናኛ ክበብ የሠራዊቱንና የሠራዊቱን ቤተሰብ ኑሮ የሚደግፉ ተግባራትን እያከናወነ መሆኑ ተገልጿል። የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ወታደራዊ መደብር እና መዝናኛ ክበቦች የስራ አመራር ቦርድ ሰበብሳቢ ተወካይ ኮሎኔል አንበሱ ማርያም እንደተናገሩት አሁን በሀገራችን ካለው የኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ የሠራዊቱንና የቤተሰቡን ኑሮ ከመደገፍና የኑሮውን ጫና ከማቃለል አኳያ ወታደራዊ መደብሩና መዝናኛ ክበቡ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እየደረገ ይገኛል ፡፡ የክፍሉ ወታደራዊ መደብርና መዝናኛ ክበቦች ሃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ታደለ ደራጎ እንዳሉት የክፍሉ ወታደራዊ መደብርና መዝናኛ ክበብ በሰዓት ሶስት መቶ ስልሳ ደቦ ማምረት የሚችለውን ማሽን ገዝቶ በመትከል አሥመርቋል። መዝናኛ ክበቡ የዳቦ ማሽኑንም ያስተከለበት ዋናው አላማ የሠራዊቱን ኑሮ ከመደገፍ አኳያ ዳቦ በተመጣጣኝ ዋጋ ለሠራዊቱና ለሠራዊቱ ቤተሰብ  ለማቅረብ መሆኑን ሃላፊው ገልፀዋል።  ሌተናል ኮሎኔል ታደለ ደራጎ እንዳሉት የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ  ወታደራዊ መደብርና መዝናኛ ክበቦች ከላይ አስከታች በለው መዋቅር መሠረት በተመጣጣኝ ዋጋ ለሰራዊቱ የመዝናኛ አገልግሎት እየሰጠ ከመሆኑም በላይ ለሠራዊቱ እና ለሠራዊቱ ቤተሰብ የፍጆታ ቁሳቁሶችን በጥራትና በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ አጠቃላይ የሠራዊቱን ኑሮ የመደገፍ ስራዎችን በትጋት እየሰራ ይገኛል።     ከተጠቃሚዎች መካከልም መቶ አለቃ ንጉሴ ኪዳኔ እና መቶ አለቃ አማኑኤል ቶማ በሰጡት አስተያየት የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ወታደራዊ መደብር እና መዝናኛ ክበብ የሰራዊቱንና የሰራዊቱን ቤተሰብ ኑሮ እየደገፈ እንደሚገኝ ገልፀው በተለይ አሁኑ ካለው የኑሮ ሁኔታ አኳያ እየተደረገ ያለውን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡

የሞባይል ባንኪንግ የደህንነት ስጋቶች እና መከላከያ መንገዶች ከጥቂት ዓመታት በፊት  የሞባይል  ባንኪንግ አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር  አነስተኛ የነበረ ሲሆን አብዛኛው ህብረተሰብ የባንክ አገልግሎቶችን በአካል በመገኘት ነበር የሚፈጽመው፡፡ ከቴክሎጂዎች መዘመን እና የዲጂታል ክፍያ ስርአቶች መስፋፋት ጋር ተያይዞ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎቶች በብዙ ሰዎች ዘንድ ተመራጭ ሆኗል፡፡ በሳይበር ምህዳር ማንኛውም ቴክኖሎጂ ተቀባይነቱ እየጨመረ ሲመጣ ከሚሰጠው ግልጋሎት በተቃራኒ የሳይበር  ደህንነት ስጋቶችም ይደቀኑበታል፡፡ በተለይም ከቅርብ አመታት ወዲህ የሞባይል መተግበሪያዎችን ኢላማ ያደረጉ የሳይበር ጥቃቶች በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ይስተዋላል፡፡  በዚህም በባንክ ደንበኞች ላይ በሚደርስ የሞባይል ባንኪንግ ጥቃት  ግለሰቦች እና ተቋማት ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፓለቲካዊ ጉዳቶችን አስተናግደዋል፡፡ የተለመዱ የሞባይል ባንኪንግ የሳይበር ጥቃት አይነቶች • የትሮጃን ጥቃቶች /trojan attack/ • ጥልቅ ጥቃቶች/deep attack/ • ኪሎገር እና ስክሪን ሎገሮች (ተጠቃሚዎች በስክሪኖቻቸው ላይ የሚጽፉትን በመቅዳት የሚፈጸም ጥቃት ) • የተደራሽነት ማእቀፍ ጥቃቶች  ( accessibility frame attacks ) • ተደራራቢ ጥቃቶች (overlay attacks )    የሞባይል ባንኪንግ የሳይበር ጥቃቶችን እንዴት መከላከል ይቻላል • ጠንካራ ምርመራ ማድረግ (intensive testing)፦ ባንኮች ጥቅም ላይ የሚውሉ መተግበሪያዎችን ጥልቅ ምርመራ በማድረግ፤ ተጋላጭነቶችን እንዲለዩ ፤ • ኮድ መደበቅ (code obfuscation)፦  የመተግበሪያውን ምንጭ ኮድ መደበቅ የሳይበር ሰርጎ ገቦችን ገደብ ለማረጋጋት ያስችላል፤ • ባለ ብዙ ደረጃ ማረጋገጫ መጠቀም (implementation of  multi  factor authentication )፤ • ካልታወቁ ምንጮች  መተግበሪያዎችን ከመጫን መቆጠብ ፤ ምንጭ:- ኢንሳ Insa ከጋዜጠኛ ዳኛቸው

ዩክሬንን እና ሩሲያ ለማሸማገል የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ኪየቭ ሲገቡ ከባድ ፍንዳታ ተሰማ!! የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ እና የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር እና የኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አዛ
ዩክሬንን እና ሩሲያ ለማሸማገል የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ኪየቭ ሲገቡ ከባድ ፍንዳታ ተሰማ!! የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ እና የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር እና የኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አዛሊ አሱማኒ የአፍሪካ የሰላም ተልእኮ አካል ለመተግበር ዩክሬን ሲደርሱ ዋና ከተማዋ ኪዬቭ በፍንዳታ ተናውጣለች። በዛሬው እለት ከዩክሬኑን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪን ጋር የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እየመከሩ ሲሆን በነገው እለት ቅዳሜ ወደ ሩሲያ በማቅናት ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በሴንት ፒተርስበርግ እንደሚነጋገሩ ይጠበቃል።የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ዲሚትሮ ኩሌባ በትዊተር ገፃቸው ላይ "ፑቲን በሳምንታት ውስጥ በኪዬቭ ላይ ትልቁን የሚሳኤል ጥቃት ከፍተዋል" ብለዋል። “የሩሲያ ሚሳኤሎች ለአፍሪካ መልእክት ናቸው፤ ሩሲያ የበለጠ ጦርነት እንጂ ሰላም አትፈልግም።" ሲሉ አክለዋል። አስቀድመው  የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ራማፎሳ ፖላንድ ያቀኑ ሲሆን ከፖላንድ በባቡር ወደ ዩክሬን ሲደርሱ የሚያሳይ ምስል ተጋርቷል። ራማፎሳ የልዑካን ቡድኑን እየመሩ ያቀኑ ሲሆን ከእርሳቸው በተጨማሪ የኮሞሮስ ፕሬዝዳንት አሱማኒ ፣ የዛምቢያ ፣ሴኔጋል እና የግብፅ ጠቅላይ ሚኒስትር በልዑካን ውስጥ ይገኛሉ። የኡጋንዳው ፕሬዝዳንቶች ዮዌሪ ሙሴቬኒ፣ የኮንጎ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ዴኒስ ንጌሶ እና የግብፁ አብደል ፋታህ ኤል ሲሲም አብረው በጉዞው ላይ እንዲሄዱ ታስቦ የነበረ ቢሆንም ከልዑኩ በመውጣት ተወካዮቻቸውን ልከዋል። በሮይተርስ የዜና ወኪል መሰረት የሰላም ረቂቅ ማዕቀፍ ሰነዱ በሽምግልና የመጀመሪያ ጥረቶች ላይ ተከታታይ “የመተማመን ግንባታ እርምጃዎችን” ሊያቀርብ ይችላል ተብሎ ታምኖበታል።  

“ኦክሲጅን መጣጩ” ከአየር ላይ ኦክሲጅን አጥፍቶ ጠላትን የሚገድለው አደገኛው የሩሲያ የጦር መሳሪያ በT-72 ታንክ ላይ የሚገጠመው መሳሪያው በ90 ሰከንድ ውስጥ ኢላማውን ይመታል። መሳሪያው በአየር ላይ ጥቁር ደመናን በማሰራጨትና ከሳንባ ውስጥ ኦክሲጅን በመምጠጥ  ጠላትን በማፈን ይገድላል። ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤ https://am.al-ain.com/article/russian-oxygen-sucker-tos1

በጃፓን ላይ ከተጣለዉ የአቶሚክ ቦምብ በሶስት እጥፍ የበለጠ የኒዉክሌር ጦር በቤላሩስ ሩሲያ ልታከማች ነዉ የቤላሩስ ፕሬዝዳንት "መሳሪያዉን ለመጠቀም ዉሳኔ እንዳልሰጥ እግዚያብሄር ይጠብቀኝ " ብለዋል
በጃፓን ላይ ከተጣለዉ የአቶሚክ ቦምብ በሶስት እጥፍ የበለጠ የኒዉክሌር ጦር በቤላሩስ ሩሲያ ልታከማች ነዉ   የቤላሩስ ፕሬዝዳንት "መሳሪያዉን ለመጠቀም ዉሳኔ እንዳልሰጥ እግዚያብሄር ይጠብቀኝ " ብለዋል የቤላሩስ ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ በሰጡት መግለጫ ሀገራቸው በሂሮሺማ እና ናጋሳኪ ከተጣሉ የአቶሚክ ቦምቦች "በሶስት እጥፍ የሚበልጡ" የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን ከሩሲያ እየተቀበለች እንደሆነ ጠቁመዋል። ቤላሩስ ሊደርስባት  የሚችለውን ጥቃት ለመከላከል ወደ የጦር መሳሪያዉ አስፈላጊ እንደሆነ አስታዉቃለች። ከቀናት በፊት ሩሲያ እንዳስታወቀችው ከሆነ ከሀምሌ ወር አንስቶ  ታክቲካል የኒውክሌር ጦር መሳሪያን በቤላሩስ ምድር እንደምታሰማራ ገልፃለች። ይህን ለምዕራቡ ዓለም እንደ ማስጠንቀቂያ ተደርጎ ተወስዷል። ሉካሼንኮ እንዳስታወቁት ሚንስክ የጦር መሳሪያዎቹን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ገልፀዋል። "ሁሉም ነገር ዝግጁ ነው። የጠየቅነውን በጥቂት ቀናት ውስጥ ትንሽም ቢሆን የምናገኝ ይመስለኛል” ሲሉ ተናግረዋል። ሉካሼንኮ በምዕራባውያኑ ሀገራት አነሳሽነት ጥቃት የሚሰነዘርብን ከሆነ ምላሽ ለመስጠት መሳሪያውን ከመጠቀም ወደኋላ እንደማይሉ አስጠንቅቋል። "ለምን የኒውክሌር የጦር መሳሪያእን እንደምንፈልግ ልንገራችሁ አንድም የውጪ ወታደር በቤላሩስ ምድር ላይ እግሩን ካሰረፈ እንጠቀምበታለን" ሲሉ ተናግረዋል። “እግዚያብሄር እነዚህን መሳሪያዎች ለመጠቀም ውሳኔ እንዳልሰጥ ይጠብቀኝ። ነገር ግን በኛ ላይ ጥቃት ሲሰነዘር ማመንታት እንደማይኖር እወቁት ሲሉም አክለዋል። ከሶቪየት ኅብረት መፍረራረስ በኋላ ሩሲያ የጦር መሳሪያዎችን ስታንቀሳቅ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

" ጥንቃቄ አድርጉ " የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፤ የተቋሙ አርማ የታተመባቸውን የኪስ ቦርሳዎች በማዘጋጀትና መታወቂያ በማስመሰል ለሕገወጥ ተግባራት ጥቅም ላይ ለማዋል ሙከራ ሲያደርጉ የነ
+1
" ጥንቃቄ አድርጉ " የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፤ የተቋሙ አርማ የታተመባቸውን የኪስ ቦርሳዎች በማዘጋጀትና መታወቂያ በማስመሰል ለሕገወጥ ተግባራት ጥቅም ላይ ለማዋል ሙከራ ሲያደርጉ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገለፀ። አገልግሎቱ በላከው መግለጫ ÷ የተቋሙ አርማ የታተመባቸው የኪስ ቦርሳዎችን ወይም ዋሌቶችን በማዘጋጀትና መታወቂያ በማስመሰል ለሕገወጥ ተግባራት ጥቅም ላይ ለማዋል ሙከራ ሲያደረጉ የነበሩ ተጠርጣሪ ግለሰቦች #እጅ_ከፍንጅ መያዛቸውን ገልጿል። ኅብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግም ጥሪ ቀርቧል። አገልግሎቱ ፤ በዚህ ሕገወጥ ድርጊት የተሰማሩ ተጠርጣሪ ግለሰቦች የተቋሙ አርማ የታተመባቸውን የኪስ ቦርሳዎችን ወይም ዋሌቶችን መታወቂያ አስመስለው በማዘጋጀት በተለያዩ አካባቢዎች ለማሰራጨት ሙከራ ሲያደርጉ እንደነበርና ካዘጋጇቸው የኪስ ቦርሳዎች ውስጥ #የተወሰኑት በአንዳንድ ግለሰቦች እጅ እንደገቡ መታወቁን አመልክቷል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች የተቋሙ አርማ የታተመባቸውን የኪስ ቦርሳዎች እንደ መታወቂያ በማሳየት በሕገወጥ ተግባር መሰማራታቸውንና በተቋሙ ስም ያለአግባብ አገልግሎት ለማግኘት ሙከራ እያደረጉ መሆኑ እንደተደረሰበት አስታውቋል፡፡ የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ፤ የተቋሙ አርማ የታተመበትን የኪስ ቦርሳ ወይም ዋሌት ይዞ መገኘት ብሎም ሕገወጥ ለሆነ ተግባር ማዋል ሕጋዊ ተጠያቂነትን ያስከትላል ብሏል። ይህ የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ አርማ የታተመበት የኪስ ቦርሳ በእጁ የገባ ግለሰብ በአካባቢው ለሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ እንዲያስረክብ ወይም በስልክ ቁጥሮች 0115543681 እና 0115543804 በመወደል እንዲያሳውቅ በጥብቅ አሳስቧል። ይህን ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውም ግለሰብም በሕግ ተጠያቂ እንደሚሆን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስጠንቅቋል።