es
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Ir al canal en Telegram

Addis abeba Ethiopia

Mostrar más
4 889
Suscriptores
-25624 horas
-1 8217 días
-3 02830 días
Archivo de publicaciones
👉 "የአረብ ሊግ ታላቁ የሕዳሴ ግድብን አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ አንቀበልም‼" ♦ "ሊጉ የአንድ ሀገር ቃል አቀባይ ሆኗል‼"                                                          - ኢትዮጵያ  ኢትዮጵያ የአረብ ሊግ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታና ውሃ ሙሌት ላይ ያስተላለፈውን የ“ውሳኔ ሀሳብ” እንደማትቀበል አስታወቀች። ኢትዮጵያ የአረብ ሊግ ትናንት በሕዳሴ ግድብ ግንባታ እና ውሃ ሙሌት ላይ ያወጣውን መግለጫ የማትቀበለው መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የሕዳሴ ግድብ ግንባታ እና ውሃ ሙሌትን ጨምሮ የአባይ ወንዝ አስተዳደርና አጠቀቃም ጉዳይ በአፍሪካ የሚገኙ ባለድርሻ አካላትን ብቻ እንደሚመለከትም ገልጿል። “ለአረብ ሊግ የናይል ወንዝ እና ሁሉም የተፋፈሱ አገራት የሚገኙት በአፍሪካ እንደሆነ ማስታወስ አያስፈልገንም" ያለው መግለጫው፤ "ሊጉ የዓለም አቀፍ ሕግ መሰረታዊ መርሆዎችን ወደ ጎን በመተው የአንድ ሀገር ቃል አቀባይ ሆኗል” ሲል አስታውቋል። የአፍሪካ ሕብረት “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ” መርህ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ በግድቡ የሶስትዮሽ ድርድር በሚያነሷቸው መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ እንዲስማሙ እየተሰራ እንደሚገኝ ጠቅሷል። ይሁንና አረብ ሊግ “የሶስትዮሽ ድርድሩን ያስቀመጠበት መንገድ ስህተት ነው” ሲል ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤቱ ገልጿል። “ግብጽ በቅኝ ግዛት ዘመን በራሷ የወሰነችው የውሃ ሀብት ክፍፍል መቀጠል አለበት የሚለው ግትር አቋምና ጉዳዩን ዓለም አቀፋዊ ይዘት እንዲኖረው እያደረገች ያለችው ማብቂያ የሌለው ጥረት የድርድሩ ሂደት እንዲዘገይ አድርጎታል” ሲል አመልክቷል። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕብረት ለሚመራው የሶስትዮሽ ድርድር ቁርጠኛ መሆኗን አስገንዝቧል።  የአረብ ሊግ የ”ውሳኔ ሀሳብ” እና የግብጽ መግለጫዎች በአፍሪካ ሕብረት ስር በሚካሄደው ድርድር “በጎ በሆነ መልኩ” ተሳትፎ እያደረገች መሆኑን ጥያቄ ምልክት ውስጥ ይከታዋል ብሏል። ኢትዮጵያ እ.አ.አ 2015 በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብጽ መካከል በተፈረመው የመርዎች ስምምነት አማካኝነት የሕዳሴ ግድቡን ግንባታ እና ውሃ ሙሌት እንደምትቀጥል ነው ቃል አቀባይ ጸህፈት ቤቱ በመግለጫው ያስታወቀው። ኢትዮጵያ የድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብቶችን ፍትሐዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ የመጠቀም መርህ እንደምታከብር እና ተገዢ እንደሆነችም ገልጿል። # ለተጨማሪ መረጃዎች👇👇👇

👉 ወጣቶች ሆይ~የጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን አባል ሁኑ‼ ♦ ሀገርን ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ አኩሪ ታሪክ ነው‼ 📌 ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ምዝገባ የወጣ የቅጥር ማስታወቂያ👇👇 የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር  ከየካቲት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መጋቢት  20 ቀን 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ  መስፈርቱን የሚያሟሉ  ወጣቶችን መልምሎ በመደበኛ ሰራዊትና በልዩ ልዩ ሙያዎች በማሰልጠን የሠራዊት አባል ማድርግ ይፈልጋል። ለመመልመልና ለማሰልጠን የተፈለገባቸው መስኮች፦ *** 1. ለመደበኛ ሠራዊት 2. ለዕጩ መኮነን 3. ለኢንጂነሪግ 4. ለሪሶርስ ማኔጅመንት 5. ለጤና  ሙያተኛ 6. ለመሀንዲስ ባለሙያ 7. ለህግ ባለሙያ እና 8.ለሎጂስቲክስ ባለሙያነት አወዳድሮና አሰልጥኖ መቅጠር ይፈልጋል። የማወዳደሪያ መስፈርቶች፦ **** 1. ሕገ መንግሥቱን የተቀበለ/ች ለዚህ በፅናት ለማገልገል ፈቃደኛ የሆነ/ች 2. በብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት የሚያምን /የምታምን 3. ከአሁን በፊት የፖሊስ ወይም የመከላከያ አባል ያልነበረ/ች 4. ከወንጀል ነፃ የሆነ የፍርድ ቤት ቀጠሮና ክርክር የሌለበት/ባት 5. ከማንኛውም ሱስና አጉል ልማድ የፀዳ/ች እና ሙሉ ጤንነት ያለው/ያላት 6. በመከላከያ መደበኛ ሰራዊትነት ለ7 ዓመት እና ለሌሎቹ ሙያዎች ከሰለጠነ በኋላ ለ10 አመት ለማገልገል ፈቃደኛ የሆነ/ች በማንኛውም ቦታ ተመድቦ መሥራት የሚችል/የምትችል 7. ፆታ፡- አይለይም 8. ኢትዮጵያዊ የሆነ/ች በሚኖርበት ቀበሌ 2 ዓመት የኖረ/ች 9. ዕድሜ፡- ከ18-25 ዓመት ፤ ቁመት ለወንድ 1.60 እና ከዚያ በላይ ፣ ለሴት ደግሞ 1.55 እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች 10. ክብደት፡- ለወንድ ከ50-75 ኪ.ግ የሆነ፤ ለሴት ደግሞ 45-66 ኪሎግራም የሆነች፣ 11. የትምህርት ደረጃ ለመደበኛ ሰራዊት ለወንድ 8ኛ ክፍል የሆነ እና ለሴት እውቅና ካለው የትምህርት ተቋም ዲፕሎማ ወይም በሌቭል ያጠናቀቁ እና ከዚያ በላይ የሆኑ የ8ኛ ክፍል የሚኒስትሪ ካርድ ማቅርብ የሚችሉ ፣ለቀሪ የሙያ መስኮች ከሌቭል 3+4+5 እና ድግሪ ያለው/ያላት 12. ያላገባ/ችና ያልወለደ/ች 13. ደመወዝ በመከላከያ ስኬል መሰረት ሆኖ፤ ጥቅማጥቅም የመኖሪያ ቤትና ህክምና አገልግሎት በነፃ የሚያገኙ ሲሆን፤ በመከላከያ ዕቅድና ፍላጎት መሰረት በትምህርት ተቋም ገብተው የመማር ዕድል አላቸው፣ 14. የምዝገባ ቦታ፦  በአቅራቢያው በሚገኙ የፀጥታ ተቋማት በሚሊሻ ፣ በፖሊስ ፣ በሰላምና ደህንነት እና በቀበሌ አስተዳደር  ጽሕፈት ቤቶች 15. የምዝገባ ቀን፡-  ከየካቲት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ  እስከ መጋቢት  20 ቀን 2015 ዓ.ም የጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን አባል በመሆን ኢትዮጵያን ጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ የዛሬው ትውልድ ታላቅ ኃላፊነት ነው‼ ለተጨማሪ መረጃዎች👇👇👇

👉 እንኳን ለ45ኛው የካራማራ የድል ቀን አደረሳችሁ፤ አደረሰን‼️ በገበሬው በኢትዮጵያ ሰራዊት የተማረኩ የሶማሊያ ምርኮኞችና በር መሳሪያዎች 🙏🇪🇹🙏 ♦️"ይህ ነው ምኞቴ      እኔ በሕይወቴ      ከራሴ በፊት ለኢትዮጵያ እናቴ።" - የካቲት 26 1970 ዓ.ም ካራማራ የመላው ኢትዮጵያዊያን ድል ነው‼️ ክብር ለካራማራ ጀግኖች‼️ ለተጨማሪ መረጃዎች👇👇👇 https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter

👉 እንኳን ለ45ኛው የካራማራ የድል ቀን አደረሳችሁ፤ አደረሰን‼️ ♦️"ይህ ነው ምኞቴ እኔ በሕይወቴ ከራሴ በፊት ለኢትዮጵያ እናቴ።" - የካቲት 26 1970 ዓ.ም ካራማራ የመላው ኢትዮጵያዊያን ድ
👉 እንኳን ለ45ኛው የካራማራ የድል ቀን አደረሳችሁ፤ አደረሰን‼️ ♦️"ይህ ነው ምኞቴ      እኔ በሕይወቴ      ከራሴ በፊት ለኢትዮጵያ እናቴ።" - የካቲት 26 1970 ዓ.ም ካራማራ የመላው ኢትዮጵያዊያን ድል ነው‼️ ክብር ለካራማራ ጀግኖች‼️ ለተጨማሪ መረጃዎች👇👇👇

👉 ዘንድሮ ለ127ኛ ጊዜ "አድዋ- አንድነት፣ ጀግንነትና ፅናት" በሚል መሪ ቃል የምናከብረው የድል በዓል በጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን አዘጋጅነት እንዲከበር የተደረገበት ምክንያት፤ መከላከያ ሠራዊ
👉 ዘንድሮ ለ127ኛ ጊዜ "አድዋ- አንድነት፣ ጀግንነትና ፅናት" በሚል መሪ ቃል የምናከብረው የድል በዓል በጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን አዘጋጅነት እንዲከበር የተደረገበት ምክንያት፤ መከላከያ ሠራዊታችን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የሚገኙበት ስለሆነ እንዲሁም በብሔር፣ በሃይማኖት ወይም በሌላ ልዩነት ሳይፈጥርና ሳይከፋፈል ለመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ሠላም እና እድገት ስለቆመ ብሎም በዓሉ ይበልጥ አንድነትንና መግባባትን ሊፈጥር እንደሚችል በማሰብ ነው‼ከዚህ ውጭ፤ የሚከፋፍልና የሚለያይ አጀንዳ አንግበው ሌት ከቀን ከሠላም ይልቅ ጥላቻን የሚሰብኩ፣ ከአንድነት ይልቅ ልዩነትን የሚያራምዱ ቡድኖች የሚያናፍሱት የሴራ ፖለቲካ የአይበገሬውን ሠራዊታችንን አንድነት ከቶም ሊሸረሽረው አይችልም‼ ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን ዛሬም ይሁን ነገ፤ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ሕይወቱን እየሰጠና የሚበጀውን ሁሉ እያደረገ በፅናት ይቀጥላል‼ ክብር ለኢትዮጵያ የሁልጊዜ ጋሻችን‼

https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces ይህ የፌስቡክ ገፃችን ነውና አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ 🙏🇪🇹🙏

ፒኤስጂ ድል ቀንቶታል ! በፈረንሳይ ሊግ የሀያ አምስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር የሊጉ መሪ ፒኤስጂ ከተከታዩ ማርሴይ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 3ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል። የፒኤስጂን የማሸነፊያ ግቦች ኪሊያን ምባፔ 2x እና ሊዮኔል ሜሲ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል። አርጀንቲናዊው ተጨዋች ሊዮኔል ሜሲ ያስቆጠራት ግብ በእግር ኳስ ታሪኩ ሰባት መቶኛ የክለብ ግቡ ሆና ተመዝግባለች። የፒኤስጂ የፊት መስመር ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ለፒኤስጂ ሁለት መቶኛ ግቡን በማስቆጠር ከክለቡ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ኤድሰን ካቫኒ ጋር መስተካከል ችሏል። ኪልያን ምባፔ በውድድር አመቱ ያስቆጠረቸውን የሊግ ግቦች አስራ ሰባት በማድረስ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ መሆን ችሏል። ፒኤስጂ ማሸነፉን ተከትሎ ነጥቡን ስልሳ በማድረስ #አንደኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ማርሴይ በበኩላቸው በሀምሳ ሁለት ነጥብ #ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ። በቀጣይ የሊጉ መርሐ ግብር ፒኤስጂ ከ ናንትስ እንዲሁም ማርሴይ ከሬንስ የሚገናኙ ይሆናል።

የአድዋ ዘመቻ ከመካሄዱ በፊት በጀግኖቹ ዓፋሮች የመከነው ወረራ ነገሩ እንዲህ ነው። ጆስፍ ሙዚንገር የተባለ ሰው ነበር። ይህንንም ሰው ግብጾች ሙዚንገር ፓሻ ይሉታል። የስዊስ ፌደራል ምክር ቤት አባል ልጅ ሲሆን ኦልተን በሚባል ስፍራ ተወልዶ ሳይንስና ታሪክን በበርን ዩኒቨርሲቲ አጠና። ከዚያም ወደ ግብጽ በ1852 በመምጣት ካይሮ ውስጥ ለአንድ ዓመት ያህል በመቀመጥ የዓረብኛ ቋንቋ ችሎታውን አዳበረ። በአንድ የፈረንሳይ የንግድ ድርጅት ውስጥ በመግባትም በተለያዩ የቀይ ባህር ዳርቻ ወደቦች በመዟዟር የንግድ ሥራውን ማከናወን ጀመረ። በ1855 ላይም ተቀማጭነቱን በምጽዋ በማድረግ የፈረንሳይ ምክር ቤት አገልጋይ ሆነ። ከዚያም ወደ ከረን በመዛወር ለስድስት ዓመታት ተቀምጦ የቦጎስን አካባቢ ሁሉ እየተዘዋወረ አጠና። በ1861 ላይ ማዕከላዊ አፍሪካን ለመጎብኘት ፍላጎት የነበረውን ቴዎዶር ቮን ሄግሊን ከተባለ ሰው ጋር ለመሥራት ፈቃደኛ ሆኖ ጉዞ ጀመረ። ዳሩ ግን በጋሽና አትባራ (ተከዜ) በኩል አድርጎ ወደ ካርቱም ከሚወስደው ስፍራ ተለየው። እዚያም  ቮን ሄግሊንን በመተካት የጉዞው መሪ በመሆን በ1862 ኮርዶፋ ደረሰ። ዳሩ ግን ዳርፉርና ዋዳይ ከተባለው ስፍራ ለመድረስ አልቻለም። ከዚያም በ1863 ወደ አውሮፓ ተመልሶ ጥቂት ቆይቶ በመመለስ በሰሜንና ሰሜን ምሥራቅ ኢትዮጵያ ዳርቻዎች መኖር ጀመረ። ወርነር ሙዚንገር 1865 በኢትዮጵያ ድንበር ላይ የነበረውን የእንግሊዝ ቆንስላ አባል በመሆን ቢያገለግልም ከምጽዋ አልወጣም ነበር። እንግሊዝ ኢትዮጵያን በ1868 ስትወር ግን የፈረንሳይ ቆንስላ ሆነ። እዚያም የሐማሴን የጦር መሪ የሆነው የደጃዝማች ወልደ ሚካኤልን ሴት ልጅ አገባ። ደጃዝማች ወልደ ሚካኤልንም ሐማሴንን ለፈረንሳይ እንዲሰጥ ይወተውት ጀመር። ዓላማው ሲሳካለትም ወደ ፈረንሳይ ተመለሰ። የፍራንኮ ፕራሺያ ጦርነት ሲጀመርም በ1870 ወደ ምጽዋ ለመመለስ ዝግጁ ሆነ።  ዳሩ ግን የፈረንሳይ የትኩረት አቅጣጫ ወደዚሁ ትልቅ ጦርነት በመቀየሩ ምክንያት ወርነር ሙዚንገር ከፈረንሳይ ቆንስላነት ወደ ምጽዋ መምጣቱ ቀርቶ ፊቱን ወደ ግብጽ አዞረ። በዚያን ጊዜም የግብጽ መሪ ከዲቭ ኢስማኤል ነበር። ከዲቭ ኢስማኤልም የከረንና የምጽዋ ገዥ አደረገው። በሥልጣን ላይ ሲቀመጥም ከደጃዝማች ወልደ ሚካኤል ጋር በመነጋገር በፈረንሳይ ሥር እንድትሆን አድርጓት የነበረችውን በጎስን በግብጽ ሥር እንድትሆን አደረጋት። በ1875 ዋርነር ሙዚንገር ግብጽ በሦስት አቅጣጫ ኢትዮጵያን ለመውረር ካሰማራችው ጦር የአንደኛው ክንፍ መሪ በመሆን በታጁራ ክንፍ ተሰለፈ። በዚህም ግንባር ተሰልፎ ሲዋጋ ታጁራ ላይ በተለይም ገመሪ ተብሎ በሚጠራው ሐይቅ ዳርቻ በአውሳው ሱልጧን በመሐመድ ኢብን ሐንፈሬ (ዒሊልታ) የሚመራ ጦር ገጠመው። በተካሄደው ጦርነትም ድል ሆኖ እራሱ ወርነር ሙዚንገር ደጃዝማች ወልደ ሚካኤል፣ ሚስቱና ልጁ ተገደሉ።

በአድዋ ድል የነገሱ ጀግኖች አባቶቻችን የድል ሚስጢር ምንድን ነው? የሚለው በቀዳሚነት መታየት ያለበት ጉዳይ ይመስለኛል። የአሁኑ ትውልድ ከጀግኖች አባቶች ምን ትምህርት መውሰድ አለበት? አሁን ሀገር እየገጠሟት ያሉ ችግሮችን በፅናት በማለፍ እንዴት ኢትዮጵያን ማሳደግና ማጽናት ይቻላል? የሚለው ላይ ትውልድ መግባባት ያስፈልገዋል። ጀግኖች አባቶቻችን የአድዋን ጦርነት በድል ያጠናቀቁበት አንዱ ስልት የፋሺስት ጣሊያንን የመከፋፈል ሴራ በመበጣጠስ ነው። ከምስራቅ እስከ ምዕራብ፤ ከደቡብ እስከ ሰሜን ኢትዮጵያዊያን የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክን የሀገር ጥሪ ተቀብለው በአንድነትና በህብረት ወደ አውደ ግንባር መትመማቸውም ዋነኛ የድሉ ምስጢር ነው። ከንጉሱ ጋር የሃሳብ ልዩነት ያላቸው መኳንንቶች፣ የጎበዝ አለቆች እና ዱር ቤቴ ብለው የሸፈቱ አርበኞች ሳይቀሩ በአድዋ ጦርነት ልዩነታቸውን ወደ ጎን ብለው አብሮነታቸውን አሳይተዋል። የንጉሱን “ሃገርና ሃይማኖት የሚያጠፋ ጠላት ባህር ተሻግሮ…ያገሬ ሰው ጉልበት ያለህ ተከተለኝ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎት እርዳኝ” የሚለውን አዋጅ ኢትዮጵያዊያን ሲሰሙ በአንድነት ወደ አድዋ በመትመም በሀገራቸው ጉዳይ ልዩነት እንደሌላቸው አሳይተዋል። በጦር ግንባርም በጋራ በመዋጋት በአንድነት ሞተውና ቆስለው ሕብረታቸውን አስመስክረዋል። የአድዋ ድል ኢትዮጵያዊያን በጽናትና በአንድነት ያመጡት ድል መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። አንዱ ጠላትን በግንባር ሲፋለም ሌላው ስንቅ አዘጋጅቶ አቅብሏል፣ በኋላ ደጀን የወገንን ጦር በማበርታትና ምርኮኛን በማንሳት ጭምር የበኩሉን ተወጥቷል። የአሁኑ ትውልድ ከጀግኖች አባቶቻችን መውረስ ያለበት ይሄን የአገርና የህዝብ ፍቅር፣ የዓላማ ጽናት እንዲሁም ቁርጠኝነትና አንድነትን ነው። ከምንም በላይ አሁን እየገጠሙን ላሉ የጣሊያን ፋሽስት የመከፋፈል ቅሪት ሳንካዎችን መፍቻ ቁልፉ አብሮነት መሆኑን መረዳት ይገባል። ከመረዳት ባለፈም ጉልበት ያለው ለፍቅር፣ ለአንድነት፣ ለአብሮነትና ለአገር ግንባታ የሚሰራውን ይከተል። አቅመ ደካማው ደግሞ በጸሎቱ ይርዳ። በአንድነት ለመጽናት “የእናቴ ቀሚስ አደናቀፈኝ” የሚባለውን አይነት ሰበብ ወደ ጎን ማለት ያስፈልጋል። ከወንዜና ከመንደር አስተሳሰብና አመለካከት ወጥቶ ታላቋን ኢትዮጵያ ከፍ ለማድረግ በዓላማ ጽናትና በቁርጠኝነት መስራትም ያስፈልጋል። እርግጥ ነው ይህ ትውልድ ዘመኑ የሚጠይቀውን ጀግንነት በልማት፣ በአገር እድገትና ሉዓላዊነት በማስከበር እየደገመው ነው። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ የዛሬው ትውልድ አንዱ የጀግንነት አርማ ሆኖ በታሪክ ሲታወስ ይኖራል። ሠራተኛው ከደመወዙ፣ ገበሬው ከምርቱ፣ ነጋዴው ከትርፉ፣ ጉሊት ቸርቻሪዋ ከመቀነቷ አውጥተው የገነቡት ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለግድቡ የበኩሉን አድርጎ አሻራውን አሳርፏል፤ እያሳረፈም ይገኛል። መላው ኢትዮጵያዊያን በሀሳብ፣ በጉልበት፣ በገንዘብ አስተዋጽኦ በማድረግ ግድቡ አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ ደርሷል። በቀጣይም የዛሬው ትውልድ በመንግስት የሚቀረጹ የልማት ፕሮጀክቶችን አውን በማድረግ የራሱን ደማቅ ታሪክ እንደሚጽፍ ማረጋገጫ ነው። የዛሬው ትውልድ የጥንት አባቶቹን ፈለግ ተከትሎ ኢትዮጵያ ጸንታ እንድትቆይና ሁሌም ሉዓላዊነቷ እንዲጠበቅ ከሁሉም በላይ አንድነቱን ማጠንከር ይኖረበታል። ድር ቢያብር አንበሳ ያስር እንደሚባለው ከእኔነት አስተሳሰብ ወጥቶ በአብሮነት ላይ ከእዚህ ከፍ ሲልም እንደሀገር አስቦ መንቀሳቀስ ይኖርበታል።   ጀግኖች አባቶቻችን በዚያን ወቅት በታጠቀው ዘመናዊ መሳሪያ ለመድፈር ይቅርና ሊታሰብ የማይችል የሚመስለውን ወራሪው የጣሊያን ጦርን ድል የነሱት የውስጥ ልዩነትን ትተው አንድ በመሆናቸው ነው። ዛሬም ጠፍሮ የያዘንን ድህነት ድል በመንሳት ሀገርን ወደ ብልፅግና ማማ ማምጣትና ዜጎችን ተጠቃሚና የተሻለች ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ እርስ በርስ መከፋፈልን መተው ያስፈልጋል። የእኛ የምንለውን ጎጥና መንደር ሳይሆን ትልቁን የኢትዮጵዊነትን ምስል ማሰብ ነው የሚበጀው። ያኔ ለእኔ የሚለው ቀርቶ ለእኛ ማለት እንጀምራለን። እንዲህ አብሮነቱ ሲጸናና ሲጠናክር ደግሞ ጥንታዊ፤ ታሪካዊቷና የነፃነት ቀንዲልና ተምሳሌት የሆነችው ኢትዮጵያችን ታፍራና ተከብራ ትኖራለች።

የነፃነት ቀንዲል ነጸብራቅ የአንድነት ተምሳሌት-አድዋ! አድዋን ስናስብ ከኢትዮጵያ አራቱም ማዕዘናት የተሰባሰበው ጦር ወደ ሰሜን የሀገሪቱ ክፍል ተሞ ለወረራ የመጣውን ፋሺስት ጣሊያንን ድል የነሳባት ቦታ ብቻ አድርገን የምናያት አይደለችም። ወራሪው ኃይል በጀግኖች አባቶቻችን አከርካሪው ተመቶ ሽንፈት የተከናነበባት ምደር ናት ብቻ ማለትም በቂ አይሆንም፤ በእብሪት ተወጥረው የነበሩ ነጭ ቅኝ ገዥዎች ድንገት የተነፈሱበት ቦታ ብቻ አድርገን ከደምደምንም ድሉን ማሳነስ ይሆናል። ታዲያ ምን እንበላት አድዋን? የሚል ጥያቄ ሊመጣባችሁ ይችላል። በመላው የጥቁር ህዝብና በቅኝ ግዛት ባርነት ውስጥ ወድቀው በነበሩ የተገፉ ህዝቦች ልብ የታተመች፣ ለእነዚህ ህዝቦችም የነፃነት ቀንዲልን ያጎናጸፈች የዓርነት ምልክት ጭምር ናት-አድዋ!።  የአድዋ ድል በአፍሪካ ብቻ ሳይሆን በቅኝ ግዛት አስተዳደር ስር ወድቀው በነበሩ የላቲንና የእስያ አገራት የነፃነት ተጋድሎ እንዲቀጣጠል ምክንያት ሆኗል። የተገፉ ህዝቦች የነፃነት መለያ ምልክት ሆኖ ሲዘከር ኖሯል፣ ዛሬም ወደፊትም መዘከሩ ይቀጥላል። እኤአ በ1885 ጀርመን አገር በተካሄደው የበርሊን ኮንፈረንስ አውሮፓውያን መላ አፍሪካን በካርታ ላይ የተከፋፈሉትን በተግባር መሬት ላይ ለመቀራመት ጦራቸውን ሰብቀው፣ ስንቃቸውን ጭነውና ትጥቃቸውን አጥብቀው ያካሄዱት ዘመቻና የወረራ ጉዞ የተገታባት አድዋ እና እለቷ ዛሬ ድረስ በተገፉ ህዝቦች ልብ ታትማ በአዕምሮ ውስጥ ተቀርጻ ትኖራለች። ጣሊያን የኢትዮጵያን መሬት፣ የአየር ንብረትና መልክዓ ምድር ተቆጣጥሮ ሀብቷን ለሮምና ለመላው አውሮፓ ለማቅረብ የቋመጠበት የዘመናት ህልሙ የተኮላሸበት ቦታ ጭምር ናት – አድዋ። ይህ ወራሪ ኃይል ሊቢያን በእጁ ካስገባ በኋላ ጉዞውን በቀይ ባሕር አስመራ አድርጎ መላ ኢትዮጵያን የመቆጣጠር ግብ ነበረው። ጄነራል ባራቴሪ የመደባቸው ጄነራል አልበርቶኒ፣ ጄኔራል አሪሞንዲ እና ጄነራል ቦርሜዳ በግንባር የተሰለፈውን ጦር ሲመሩ የኋላ ደጀንም እንደነበራቸው የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። ከ17 ሺህ በላይ የጣሊያን ሠራዊት 66 የሚሆኑ መድፎች፣ በርካታ መትረየሶች እና አውቶማቲክ መሳሪያዎችን ታጥቆ የግንባር ሜዳው ላይ ስለመድረሱ “የኢትዮጵያ ታሪክ ከመጀመሪያው እስካሁኑ ዘመን” በሚል በአንድርዜይ ባርይትኒስኪ እና ዮዓና ማንቴል-ኒየችኮ ተጽፎ በዓለማየሁ አበበ የተተረጎመው መጽሐፍ ያስረዳል። በአንጻሩ ዓጼ ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ከሚመሩት ጦር በተጨማሪ በፊታውራሪ ገበየሁ፣ ንጉስ ተክለ ሃይማኖት፣ ራስ ወሌ፣ ራስ ሚካኤል፣ ራስ መኮንን፣ ዋግሹም ጓንጉል እንዲሁም ከትግራይ ገዢዎች በራስ መንገሻ፣ ራስ አሉላና ሐጎስ የሚመራ በአጠቃላይ ከ73 ሺህ እስከ 100 ሺህ የሚገመት ጦር በግንባር መሰለፉን መጽሐፉ አትቷል። መጽሐፉ እንደሚያስረዳው የራስ መኮንን ጦር ቀድሞ አምባለጌ ደርሶ በአካባቢው መሽጎ የነበረውን የጣሊያን ጦር ደምስሶ መቐለን ማስለቀቁ የኢትዮጵያ ጦር የሞራል የበላይነት ይዞ ወደ አድዋ እንዲዘምት አድርጎታል። በአምባላጌ የተሸነፈው የጣሊያን ጦር በበኩሉ የደረሰበትን የሞራል ልሽቀት ለመመለስ ፊቱን ወደ አድዋ አዙሯል። የዛሬ የ127 ዓመት፤ ዕለቱም የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በአድዋ ጦርነት ዓለም የተደመመበትና ዛሬ ድረስ እንቆቅልሽ የሆነበት ደማቅ ታሪክ በጀግኖች አባቶች ተሰራ። ከንጋቱ 11:00 ሰዓት አካባቢ የዓጼ ምኒልክ ጦር በስንቅ እጥረትና በሌሎች ምክንያቶች ተበትኗል በሚል የመጣው የጣሊያን ጦር በቀላሉ አድዋን ተቆጣጠሮ ወደ ፊት ለመግፋት ጦርነቱን ስለመጀመሩ በታሪክ ድርሳናት ተቀምጧል። በወቅቱ ለጣሊያን የተሳሳተ መረጃ በመስጠት የጣሊያን ጦር መሃል እንዲገባ ያደረጉ እንደ በሻህ አውአሎም ያሉ ጀግኖች የተወጡት ሚና በቀላሉ የሚታይ አይደለም። በሶሎዳ፣ ማርያም ሸዊቶ፣ አዲ ተቡን፣ ረቢ አርእየኒ በሚባሉና ሌሎች የአድዋ ተራሮች ላይ የመሸገው የኢትዮጵያ ጦርም መሃል የገባውን ጠላት እንደ በጋ ስንዴ እያጨደ መሬት ላይ እንዳሰጣው ታሪክ መስክር ነው። የጣሊያን መንግስት ለብዙ ጊዜ የተዘጋጀበት ጦርነት በአምስት ሰዓታት ጊዜ ውስጥ ተደመደመ። ጀግኖች አባቶች ዓለምን ያስደመመ ደማቅ ድል በደምና አጥንታቸው ጻፉ። ድሉም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና ነፃነት ከማስከበር አልፎ ለመላው ጥቁር ህዝብና በቅኝ ግዛት ባርነት ውስጥ የነበሩ የእስያና ላቲን አገራት ለነፃነታቸው እንዲታገሉ ትልቅ የሞራል ስንቅ ሆነ።  በጦርነቱ የጣሊያን መንግስት የጎመጀውን የኢትዮጵያን መሬት ሊያገኝ ይቅርና ከ11 ሺህ በላይ ሠራዊቱ ሙትና ቁስለኛ ሆኑ። 4ሺህ የሚሆኑት ደግሞ ለጀግኖች አባቶቻችን እጃቸውን ሰጥተው ተማረኩ። እንዲሁም 56 መድፎች፣ በርካታ መትረየሶች እና ሌሎች አውቶማቲክ መሳሪያዎቹን ለወገን ጦር አስረከበ። በአድዋ ድል ከሮም እስከ አስመራ እንደ ፊኛ የተወጠረው እብሪቱ ፈንድቶ መላ አውሮፓ በሃፍረት ራደ። የቀረው የፋሽስት ሠራዊትም ተንጠባጥቦ እግሬ አውጪኝ ብሎ ፈረጠጠ። ጀግኖች ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ክብር፣ ነፃነትና ሉዓላዊነት በአውደ ግንባሩ በፈጸሙት የጀግንነት ተጋድሎ ዓለምን ያስደመመና መላውን ጥቁር ሕዝብ ያኮራ ድል ተጎናጽፈዋል። በወቅቱ ነጭን ታግሎ ማሸነፍ አይቻልም የሚለውን አስተሳሰብ በይቻላል ተክቶ ሌሎችም ለነፃነታቸው እንዲታገሉ ያነሳሳ ደማቅ የታሪክ አሻራ አኑረዋል። የአድዋን ጦርነት የተለየ ከሚያደርጉት ጉዳዮች አንዱ ጦርነቱ ከመጀመሩ አስቀድሞ ሁለቱም ወገኖች አሸናፊ ለመሆን የተለያዩ ስልቶችን መጠቀማቸው ነው። ጀኔራል ባራቴሪ ባይሳካለትም ቅሉ የትግራዩን ገዥ ራስ መንገሻን ጨምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የየአካባቢውን ገዥዎች ዳግማዊ አፄ ምኒልክን ክደው ጣሊያንን እንዲተባበሩ ለማድረግ መሳሪያ በመስጠት፣ የተለያዩ ስጦታዎችን በማቅረብና “ስልጣን እንሰጣችኋለን” በማለት የመከፋፈል ሥራ በስፋት ለመስራት ሞክሯል። በተጨማሪም ዓፄ ምኒልክን አታሎ ስምምነት እንዲፈርምና ዓለም አቀፉን ማህበረሰብ ከጎኑ ለማሰለፍ ያደረገው ጥረት በቀላሉ የሚታይ አይደለም። ለእዚህም ለጦርነቱ ምክንያት የሆነውን የውጫሌ ውል አንቀጽ 17 በማሳያነት መጥቀስ ይቻላል። በዓፄ ምኒልክ በኩልም ከጣሊያን ጋር በድብቅ ስምምነት የሚፈጽሙ የአካባቢ ገዥዎችን በምህረት በመመለስ ከጎናቸው አሰልፈዋል። እምቢ ያሉትን በመቅጣት፣ ከውጭ ሀገራት ጋርም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት በመፍጠርና በማግባባት ጭምር የነፍስ ወከፍ ጦር መሳሪያ ከፈረንሳይና ከሌሎች አገራት አስገብተዋል። ከአልበርቶኒ ጋር የሚስማሙ መስለው ጊዜ በመግዛት ለማይቀረው ጦርነት ያደረጉት ዝግጅት እንደዋዛ አይታይም። ኋላም በጦርነቱ የተገኘው ድል ሲታይም ፃጼ ምኒልክ ከጄኔራሉ የበለጠ ስልታዊ መሪ አስብሏቸዋል። በጦርነቱ በቴክኖሎጂ፣ በዘመነ ሠራዊት፣ በስንቅና ትጥቅ አቅርቦት እንዲሁም ከአሰላለፍ አንጻር በጣሊያንና በኢትዮጵያ መካከል የነበረው ልዩነት የምድርና የሰማይ ያህል የሚራራቅ ነው። በአድዋ ጦርነት የኢትዮጵያ ጦር ይዞ የተሰለፈው መሳሪያ፣ ጦርና ጋሻ ከዘመኑ ስልጣኔ አንጻር ሲታይ እጅግ ኋላ ቀር ቢሆንም ጀግኖች አባቶቻችን በአድዋ ተራሮች ላይ በከፈሉት የጀግንነት ተጓድሎ የጣሊያንን ወራሪ ጦር ድል በማድረግ ዓለምን በእጅጉ ያስደመመ ለመላው ጥቁር ህዝቦች የነፃነት ብስራትን በየካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም በአድዋ ተራሮች አብስረዋል።

👉 የጀግና አቀባበል~ለአይበገሬዎቹ የምድር ድሮኖች‼💪💪💪 ♦ ባለቀያይ መለዮ ለባሾች ከመላው ሠራዊታችን ጋር ተናበው የፈፀሙት መተኪያ የሌለው አንፀባራቂ ሀገራዊ የጀግንነት ታሪክ በሚገባ ተፅፎ
+2
👉 የጀግና አቀባበል~ለአይበገሬዎቹ የምድር ድሮኖች‼💪💪💪 ♦ ባለቀያይ መለዮ ለባሾች ከመላው ሠራዊታችን ጋር ተናበው የፈፀሙት መተኪያ የሌለው አንፀባራቂ ሀገራዊ የጀግንነት ታሪክ በሚገባ ተፅፎ ለትውልድ መተላለፍ አለበት‼--ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ኢትዮጵያን ከብተና ለመታደግ አገራዊ ተልዕኳቸውን በታላቅ ጀግንነት ሲወጡ ለቆዩ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የሰራዊት አባላት እና አመራሮች የጀግና አቀባበል ተደርጎላቸዋል‼ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ አመራሮች እና አባላት ባለፉት ሁለት ዓመታት ሀገርን ከብተና ለማዳን ያበረከቱት የማይተካ አስተዋፆ እና የከፈሉት መስዋዕትነት ሀገርን ያዳነ ወገንን ያኮራ ስለሆነ ለፈፀሙት ታላቅ የጀግንነት ተጋድሎ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ ባለቀያይ መለዮ ለባሾች ከመላው ሠራዊታችን ጋር ተናበው የፈፀሙት መተኪያ የሌለው አንፀባራቂ ሀገራዊ የጀግንነት ታሪክ በሚገባ ተፅፎ ለትውልድ መተላለፍ እንዳለበትም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናግረዋል፡፡ የኮማንዶ እና የአየርወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በበኩላቸው፤ የምድር ድሮኖች ፊት ለፊትም ሆነ ከጠላት ጀርባ ሠብሮ በመግባት በፈፀሙት አኩሪ ጀግንነት ሀገርን መታደግ እና መላው ህዝባችንን ማኩራት መቻላቸውን ገልፀዋል፡፡ ያለፈውን በታሪክ የሚከተብ የጀግንነት አሻራ ፅፎ ለማለፍም ሆነ ለማስቀጠል እንዲሁም የሀገራችንን እና የመከላከያን የሠላም ፍላጎት ለማሳካት ብሎም የዕዙን የሠራዊት አባላት ወታደራዊ ብቃት ይበልጥ ለማሣደግ በተደራጀ እና በተቀናጀ አግባብ መሠልጠን እና መብቃት እንደሚያስፈልግም ሌተናል ጄኔራል ሹማ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያን ከብተና ለመታደግ አገራዊ ተልዕኳቸውን በታላቅ ጀግንነት ሲወጡ ለቆዩ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የሰራዊት አባላት እና አመራሮች የጀግና አቀባበል ተደረገላቸው፡፡ ኢትዮጵያን ከብተና ለመታደግ በተለያዩ ግንባሮች በጀግንነት ሀገራዊ ተልዕኳቸውን ሲወጡ ለቆዩ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ የሠራዊት አባላት እና አመራሮች በቡልቡላ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ማዕከል ነው የጀግና አቀባበል ስነ ስርዓት የተደረገላቸው። በስነ ስርዓቱ ላይ የመከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰን ጨምሮ ከፍተኛ ጄኔራል መኮንኖች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የሠራዊት አባላት  ተገኝተዋል። የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ አመራሮች እና አባላት ባለፉት ሁለት ዓመታት ሀገርን ከብተና ለማዳን ያበረከቱት የማይተካ አስተዋፆ እና የከፈሉት መስዋዕትነት ሀገርን ያዳነ ወገንን ያኮራ ነውና ለፈፀሙት ታላቅ የጀግንነት ተጋድሎ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል፡፡ የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ አባላት ከመላው ሰራዊታችን ጋር ተናበው የፈፀሙት መተኪያ የሌለው አንፀባራቂ ሀገራዊ የጀግንነት ታሪክ በሚገባ ተፅፎ ለትውልድ ሊተላለፍ እንዳለበትም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናግረዋል፡፡ የኮማንዶ እና አየርወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በበኩላቸው የምድር ድሮኖች ፊት ለፊትም ሆነ ከጠላት ጀርባ ሠብሮ በመግባት በፈፀሙት አኩሪ ጀግንነት ሀገርን መታደግ እና መላው ህዝባችንን ማኩራት መቻላቸውን ገልፀዋል፡፡ ያለፈውን በታሪክ የሚከተብ የጀግንነት አሻራ ፅፎ ለማለፍም ሆነ ለማሥቀጠል እንዲሁም የሀገራችንን እና የመከላከያን የሠላም ፍላጎት ለማሳካት ብሎም የዕዙን የሠራዊት አባላት ወታደራዊ ብቃት ይበልጥ ለማሣደግ በተደራጀ እና በተቀናጀ አግባብ መሠልጠን  እና መብቃት እንደሚያሥፈልግም ሌተናል ጄኔራል ሹማ ተናግረዋል፡፡ በዚሁ የአቀባበል ሥነ ሥርዓት ላይ  የዓውደ ውጊያ ውሎዎችን የሚያስቃኝ የፎቶ ዐውደ ርዕይና ገላጭ የሆነ ዘጋቢ ፊልም ታይቷል። ውብሸት ቸኮል ፎቶግራፍ ምስጋና ከበደ

ኢትዮጵያና አቡዳቢ በመከላከያ ኢንዱስትሪ ልማት እና ኢንቨስትመንት መስኮች በጋራ ለመስራት ተስማሙ በመከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ እና በመከላከያ ሠራዊት ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄ
ኢትዮጵያና አቡዳቢ በመከላከያ ኢንዱስትሪ ልማት እና ኢንቨስትመንት መስኮች በጋራ ለመስራት ተስማሙ በመከላከያ ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ እና በመከላከያ ሠራዊት ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሠ የተመራ ልዑክ የመከላከያ አለምአቀፍ  ኤግዚቪሽንና ኮንፈረንስ ላይ ለመሳተፍ አቡዳቢ ገብቷል:: በቆይታቸው ከተባበሩት አረብ ኢምሬት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ከመከላከያ ሚኒስትሩ እና ከቺፍ ኦፍ ስታፉ ጋር በመገናኘት በሁለቱ ሀገራት መካከል እስካሁን የነበሩ አጠቃላይ ትብብሮችን ይበልጥ ማጠናከር እና ማስፋፋት በሚቻልበት ሁኔታ መክረዋል፡፡ የኢትዮጵያ እና የአቡዳቢ ወዳጅነት እና ትብብር የቆየ ቢሆንም ይህንኑ በጎ ገፅታ ለማሥቀጠል በቀጣይ አብሮ ለመስራት በሚቻልባቸው ዘርፎችም ተወያይተዋል፡፡ የመከላከያ ኢንደስትሪ የልማት እና ኢንቨስትመንት ስራዎች በተቋሙም ሆነ በሀገራችን ላይ ያለውን ዘላቂ ጠቀሜታ በመገንዘብ በእነኝህ ዘርፎች የመልካም ተሞክሮ ልውውጥ ከማድረግ ባለፈ ይበልጥ ማስፋት በሚቻልባቸው መንገዶች በዝርዝር ተወያይተዋል:: የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከዘመኑ ጋር የዘመነ ቴክኖሎጂን መታጠቅ እንዲችል በተለይ በኢንዱስትሪው ዘርፍ ከሀገራት ጋር የተሞክሮ ልውውጦችን እያደረገ ይገኛል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ የካቲት 12 ቀን 2015 ዓ.ም የካቲት 12 በታሪካችን ውስጥ ከ86 ዓመታት በፊት፤ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም  ቀኑ ረፋድ ላይ የኢጣሊያዊቷን ልዕልት ልደት ምክንያት በማድረግ፤ የአዲስ አበባና የአካባቢው የፋሺስት ኢጣሊያ ገዢ ጄኔራል ግራዚያኒ፡- መኖሪያና መብል የሌላቸውን ኢትዮጵያውያን ምንዱባን በቤተ መንግሥት ሠብሥቦ እየመገበ ሣለ ነው ድንገት በተከታታይ ሠባት ቦንቦች ወደ ጄኔራል ግራዚያኒ የተወረወሩት፡፡ ግራዚያኒ ጠረጴዛ ሥር ገባ፡፡ በአካባቢው ከባድ ድንጋጤ ሠፈነ፡፡ ለተወሰኑ ቅፅበቶች አካባቢው በጭሥ ታፈነ፡፡ ቦንቦቹን የወረወሩት፡- ይሄንን ግዳጅ ለመወጣት ለበርካታ ቀናት ምሥጢራዊ ወታደራዊ ልምምድ ሲያደርጉ የቆዩት፤ በትውልድ ኤርትራዊ መሠረት ያላቸው በነፍሥና በመንፈሣቸው ልባቸው በኢትዮጵያዊነት የአገር ፍቅር የተሞላና የነደደ ጀግኖቹ ኢትዮጵያውያን አብርሃም ደቦጭ እና ሞገሥ አሥገዶም ናቸው። በእብሪት ያበጠውና በቦንብ ፍንጣሪ የቆሠለው ጄኔራል ግራዚያኒ፤ በቁጣ ነድዶ ለወታደሮቹ ኢትዮጵያዊ የሆነውን ሁሉ በጥይት ቁሉት አላቸው፡፡ “ፍጁት!...ያገኘኸውን ሁሉ ግደል!” የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈ። የፋሺስት ኢጣሊያ ወታደሮች፡- የጠመንጃ ቃታ የሣቡበት ጣታቸው እስኪዝል ድረስ በመላው አዲስ አበባ ዳር እስከ ዳር ተኩስ በመክፈት ያልታጠቀውን የከተማዋን ነዋሪ ህፃን ሽማግሌ፤ ነፍሰ ጡር አሮጊት ሣይሉ ኢትዮጵያዊ የሆነውን የአገሬውን ሰው ሁሉ በጅምላ በጥይት የቆሉት ከዚህ በኋላ ነው፡፡ ጠመንጃ ያልታጠቁት የፋሺስት ወታደሮች በቆንጨራ፣ በገጀራ፣ በአካፋ፣ በመጥረቢያ ከፊታቸው ያዩትን ኢትዮጵያዊ ሁሉ በጭካኔ ጨፈጨፉት፡፡ በወቅቱ ብዙዎቹ የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች የሣርና የገለባ (የምርቅ) ክፍክፋት ደረባ ጣሪያ ያላቸው ጐጆ ቤቶች በመሆናቸው ጣሊያኖች ከእልቂት ከፍጅቱ ሸሽቶ ወደቤቱ በሚገባው ኢትዮጵያዊ ላይ ሁሉ እሣት ለቀቁበት፡፡ በውስጣቸው የተሸሸጉ ኢትዮጵያውያን የሞሉባቸውን ጐጆ ቤቶች ሁሉ በእሣት አነደዷቸው፡፡ ከሚነድደው ጐጆ ውስጥ ወጥቶ ለማምለጥ የሚሞክረውን በጥይት ለቀሙት፡፡ ሲል ጰውሎስ ኞኞ የኢትዮጵያ ና የጣሊያን ጦርነት በሚለው መፅሐፉ ላይ አስፍሯል። ለወትሮ በአዲስ አበባ ጎዳዎች በዚያ ልክ ሲፈስ የሚታየው ዘንቦ ሲያበራ የሚከተለው ጎርፍ ነበር። በዚያን ዕለት ግን የሰው ልጅ ደም መንገዶቿን አጠባ።ሠፈሮቿን አጨቀየ። በወንዞቿ እንደ ውሃ ሞልቶ ፈሰሰ። በእሩሞታ ተኩሶች የአዛውንት ጎልማሶች ወጣትና ህፃናት ጭንቅላት ተፈካከሰ። ቤቶች በእሳት ተቀጣጠሉ። ከእሳቱ ለማምለጥ የሞከሩ ህፃናት ሳይቀሩ መልሰው ወደ እሳቱ ተጨመሩ ።አሊያም የጥይት እራት ሆኑ። የጥይት የሚደበደቡት በአካፋና ዶማ ብሎም በተገኘው የስለት መሣሪያ የሚጨወጨፉት መሣሪያ አንግበው ለፍልሚያ በአውደ ውጊያ የተገኙ ወታደሮች አልነበሩም። የተለየ ይሄንን ሁሉ ቁጣ የሚያስከትል ሐጥአትም አልሠሩም። ወንጀላቸው አንድ ብቻ ነበር። እሱም ኢትዮጵያዊ መሆናቸው ነው። ይሄ የግፎች ሁሉ ግፍ የበደሎች ሁሉ በደል ከተፈፀመ መቶ ዓመት እንኳን አልሞለም። በኛ አቆጣጠር የካቲት 1929 ዓም በአዲስ አበባ ከተማ በጣሊያን ወታደሮች የተካሄደ የዘር ፍጭት ሲሆን ዛሬ 86 ዓመት ሆኖታል። የከተማዋ ነዋሪ አስክሬን ከቤት እንሰሳት ጋር ቢደበላለቅም፣ የምድር አውሬዎችና የሠማይ አሞራዎች የሰው ሥጋ በልተውት የማይጨርሱት ቢሆንባቸውም  ፋሺስቶች ያሰቡትን ውጤት አላገኙም። የሞሶሎኒ ወታደሮች ዓላማ የኢትዮጵያውያን ቅስም መስበር፣ የነፃነት ተስፋ መግደል ፣እኔን ያየ ይቀጣ ብለው ዜጎች አርፈው እንዲገዙ ባሪነትን አሜን ብለው ተቀብለው ለቅኝ ገዥዎቻቸው እንዲታዘዙ ነበር። በተቃራኒው በመላ ሀገሪቱ ከፍተኛ የመጠቃት ስሜት ተፈጠረ። ስሜቱ ወደ ከፍተኛ ቁጣ ተሸጋገረ። በሁሉም አቅጣጫ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወኔ ፋመ ጋለ። አርበኝነቱ ይበልጥ ተጠናከረ። በፅናትና በጀግንነት ትግሉ በየዱር ገደሉ ተፋፍሞ የጣሊያንን የግዛት ዕድሜ አሳጠረ። ከአድዋው ዘመን የማይተናነስ ሽንፈትና ውርደት አስከተለ። በየካቲት ወር 1929 ዓም በንፁሐን ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመው ግፍ ለዓለም አንድ ነገር አስተምሮ አለፈ። እሱም  በተገፋን ቀጥር የምንወድቅ ሳይሆን ወደ ከፍታን የምንደረደር በተመታን ልክ የምንሰበር ሳይሆን የምንጠነክር ህዝቦች መሆናችንን ነው። እኛ የኢፌዲሪ መከላከያ ሠራዊት አባለት ለሀገር ሉዓላዊነት ለህዝባችን ክብር እና ነፃነት የተከፈለውን የህይወትና የአካል መስዋዕትነት እንገነዘባለን።  በአያት ቅድመ አያቶቻችን ደምና አጥንት ፀንታ የኖረችውን ሀገራችንን ከልኳ ሳትጎድል ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ ታሪካዊ ሐላፍነት እንደተጣለብንም በሚገባ እንረዳለን። የካቲት ወር 1929 ዓም የተፈፀመው ግፍና በደል እንዳይደገም ከዘመኑ ጋር ዘምነን ጠላትን በሩቅ ለማስቀረት አልፎ ከመጣም ተገቢው ምላሽ ለመስጠት ሁሌም ዝግጁዎች ነን። ክብርና ነፃነታችንን ትላንት አላስደፈርንም። ነገም አናስደፍርም። የደም አደራ አለብንና። ፈይሳ ናኔቻ

#_ሰውን_ያላካተተ_ስብሰባ_ተጠራ👍 ✅አንድ ጊዜ ፈጣሪ ሰውን ያላካተተ ስብሰባን ጠራና ፍጥረትን ሁሉ ሰብስቦ አንድን ጥያቄ ጠየቃቸው ፣ ይላል አንድ ምንጩ ያልታወቀ አፈ-ታሪክ ፡፡ #_ጥያቄው_እንዲህ_የሚል_ነበር ✅✅ “ለነገሩ ዝግጁ እስኪሆኑ ድረስ አንድን ነገር ከሰው ልጆች ልሰውርባቸው እፈልጋለሁ፡፡ ስለሆነም ያንን ከሰዎች ለመሰወር የምፈልገውን ነገር የት ባስቀምጠው ሰዎች ላያገኙት የሚችሉ ይመስላችኋል ?” አላቸው፡፡ ለዚህ ጥያቄ መልስ ለመስጠት ብዙም የደፈረ እንስሳ ማግኘት ከባድ የነበረ ቢሆንም አራት እንስሶች የየግል ሃሳባቸውን ሰነዘሩ፡፡ #_ንስር_እንዲህ_አለ ✅✅ “ከሰዎች ለመሰወር የፈለከውን ነገር ለእኔ ስጠኝና ከፍ ብዬ መብረር ስለምችል ጨረቃ ድረስ ይዤው እወጣና እዚያ አስቀምጠዋለሁ”፡፡ ፈጣሪም መልሶ ፣ “አንድ ቀን የሰው ዘር ጨረቃ ላይ የመውጣት ብቃት ስለሚኖረው ማግኘታቸው አይቀርም” አለው፡፡ #_አሳ_እንዲህ_አለ ✅✅ “እንደ ውቂያኖስ ጥልቅ ነገር እንደሌለለና ሰዎች እዚያ ጥልቀት ድረስ እንደማይሄዱ አውቃለሁና እኔ በዋና እዚያ ድረስ መጥለቅ ስለምችል ይዤው ልግባና እዚያ አስቀምጠዋለሁ” ፡፡ ፈጣሪም መልሶ ፣ የሰው ልጅ ወደጠለቀው ባህር የመግባት አቅም ለማዳበር ብዙ ጊዜ ስለማይፈጅበት ማግኘቱ አይቀርም” ብሎ መለሰ፡፡ #_አንበሳ_በተራው_እንዲህ_አለ ✅✅ “እንኳን ሰው አብዛኛዎቹ የዱር እንስሶች እንኳ የሚፈሩት ጥቅጥቅ ያለውን ጫካ የምደፍር እኔ ነኝ ፡፡ እዚያ ወስጄ ባስቀምጠው ስለማያገኙት ለእኔ ስጠኝ” ፡፡ ፈጣሪም ፣ “ሰዎች ጫካን መመንጠር ብዙም ስለማይከብዳቸው ቀስ በቀስ ይደርሱበታል” አለ፡፡ #_ጦጣ_በመጨረሻ_እንዲህ_አለች ✅✅ “ፈጣሪ ሆይ ፣ ከእነዚህ ሁሉ ሃሳብ ሰጪዎች በበለጠ ሁኔታ ከሰው ጋር ቀረብ ብዬ የምኖረው እኔ ስለሆንኩኝ ባህሪያቸው በደንብ አውቀዋለሁ፡፡ ሰዎች አብዛኛውን ነገር ፍለጋ ውጪ ውጪውን ነው የሚሉት፡፡ ውስጣቸው ያለው ነገር ትዝም አይላቸው፡፡ ስለዚህ ውስጣቸው ብታስቀምጠው በቀላሉ አያገኙትም” አለችው ፡፡ ✅✅ የጦጣ መልስ ተቀባይነት ስላገኘ ፈጣሪ ለመደበቅ ያሰበውን ነገር በሰው ውስጥ አስቀመጠው ይባላል ፡፡ ይህ የተደበቀው ነገር የራሳቸው የሰዎቹ እምቅ ብቃት ነው ፡፡ ብዙ ሰዎች በውስጣቸው ፈጣሪ ያስቀመጠው አስገራሚና የታመቀ ብቃት እያላቸው ምንም እንደሌላቸው በከንቱ ጊዜያቸውን ያባክናሉ ፡፡ ✅✅ በውስጣችሁ ተዝቆ የማያልቅ እምቅ ብቃት እንዳለ ታውቃላችሁ ? ፈልጋችሁ አግኙት! አውጡት! አዳብሩት! ተጠቀሙበት!