es
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Ir al canal en Telegram

Addis abeba Ethiopia

Mostrar más
5 400
Suscriptores
-22624 horas
-2 2007 días
-2 65830 días
Archivo de publicaciones
#Update የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዘዘ። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 6 ግለሰቦች ያቀረቡት የዋስትና ጥ
#Update የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዘዘ። ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 6 ግለሰቦች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ። ግለሰቦቹ ፦ - ዮሃንስ ዳንኤል - አማኑኤል መውጫ፣ - ናትናኤል ወንድወሰን፣ - ኤልያስ ድሪባ፣ - ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው። ዐቃቤ ህግ በ6ቱ ግለሰቦች ላይ የወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል። የቀረበባቸው ክስ ለተከሳሾች ከደረሰ በኋላ በተከሳሾች ጠበቆች በኩል ደንበኞቻቸው " የተከሰሱበት ድንጋጌ በመርህ ደረጃ ዋስትና ሊያስከለክል አይችልም " በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድ ጠይቀዋል። ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ፤ የወ/መ/ስ/ህግ ቁጥር 67/ለ ጠቅሶ በልዩ ሁኔታ ዋስትና ሊያስከለክል ስለሚችል በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው ማለትም ፦ ➡️ ከወንጀሉ ከባድነትና ከክሱ ተደራራቢነት፣ ➡️ ከጉዳዩ ባህሪና ከከባቢያዊ ሁኔታዎች አንጻር ዋስትና ሊያስከለክሉ የሚችሉበትን ትርጉም የተሰጠባቸው የሰበር ሰሚ ችሎት መዝገብ ቁጥሮችን ጠቅሶ የዋስትና መብታቸው እንዲታለፍ ጠይቆ ነበር። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የግራ ቀኝ የዋስትና ክርክሩን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ በሰጠው ቀጠሮ መሰረት ብይን ሰጥቶበታል። በዚህም ተከሳሾቹ ከቀረበባቸው ተደራራቢ ክስ አንጻር ቢወጡ የዋስትና ግዴታቸውን አክብረው ሊቀርቡ አይችሉም በማለት የጠየቁት የዋስትና ጥያቄን ውድቅ ተደርጎ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዟል። ክሱን ለመመልከትም ለጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡ #ኤፍቢሲ

ሶማሊያ የኢትዮጵያ አማጺያንን ልታስታጥቅ እንደምትችል አስጠነቀቀች በታሪክ ሁለት ጊዜ ይፋዊ ጦርነት ያደረጉት ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ አማጺያንን የማስታጠቅ ልምድ አላቸው ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችውን የወደብ ስምምነት ከተገበረች ሶማሊያ በኢትዮጵያ ያሉ ታጣቂዎችን እደግፋለሁ ብላለች ተጨማሪ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://bit.ly/3MN12xm

ኢትዮጵያና ቻይና ወታደራዊ ትብብራቸውን ለማሳደግ ተስማሙ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መስከረም 05 ቀን 2017 ዓ.ም በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የተመራ ከፍተኛ ወ
ኢትዮጵያና ቻይና ወታደራዊ ትብብራቸውን ለማሳደግ ተስማሙ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መስከረም 05 ቀን 2017 ዓ.ም በጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የተመራ ከፍተኛ ወታደራዊ ልዑክ የ11ኛው የቤጂንግ ሻንሻን ፎረም እየተሳተፈ ነው። "ለጋራ ወደፊት ሰላምን ማስተዋወቅ" በሚል መሪ ሀሳብ በቻይና በተዘጋጀው የ11ኛው የቤጂንግ ሻንሻን ፎረም እየተካሄደ ነው። በፊልድ ማርሻል ብርሃኑ የተመራው የልዑካን ቡድን ከፎረሙ ጎን ለጎን ከቻይና ወታደራዊ ጥምር ኃይል አዛዥ  ጀኔራል ሉኤ ዠን ሊ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ሁለቱም ወገኖች በአምስተኛው ትውልድ ዋር ፌር፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ በወታደራዊ ቁሳቁስና በወታደራዊ  አቅም ግንባታ  ረገድ ተባብረው ለመስራትና ትብብራቸውን ወደላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ስምምነት ላይ ደርሰዋል፡፡ በውይይቱ ማጠቃለያ  ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ እና ጀኔራል ሉኤ ዠን ሊና መግባባት የደረሱባቸውን ጉዳዮች ወደ ተግባር ለማሸጋገር የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡ በፊልድ ማርሻሉ የተመራው ከፍተኛ ወታደራዊ ልዑክ በፎረሙ እና በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ያደረገው ተሳትፎ ውጤታማና የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትን የማድረግ አቅም ለማሳደግ የሚያስችል ድጋፍን ያስገኘ ሆኖ መጠናቀቁን በቻይና የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ተፈራ ደርበው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል። ተጨማሪ መረጃዎችን join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93 #WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36

አሜሪካ፥ አፍሪካ በጸጥታው ምክር ቤት 2 ቋሚ መቀመጫዎች እንድታገኝ ድጋፍ አደርጋለሁ አለች የ1.3 ቢሊየን ህዝብ ባለቤት የሆነችውን አህጉር ቋሚ መቀመጫ መስጠት ከተመድ ማሻሻያ ጋር የሚያያዝ ነው ተብሏል። ህንድ፣ ጃፓን እና ጀርመን በምክር ቤቱ ቋሚ መቀመጫ እንዲኖራቸው እየጠየቁ ከሚገኙት መካከል ይጠቀሳሉ። ዝርዝሩን ከተከታዩ ሊንክ ይመልቱ፤ https://bit.ly/4gpFPXy

#ሶማሊላንድ ሶማሊላንድ በዋና ከተማዋ ሀርጌሳ የሚገኘውን የግብጽ ባህላዊ ቤተ መጽሃፍት ሙሉ በሙሉ የዘጋች ሲሆን የቤተ መጽሃፍቱ ሰራተኞችም በ72 ሰዓታት ውስጥ ሀርጌሳን ለቀው እንዲወጡ አዛለች። ሶማ
#ሶማሊላንድ ሶማሊላንድ በዋና ከተማዋ ሀርጌሳ የሚገኘውን የግብጽ ባህላዊ ቤተ መጽሃፍት ሙሉ በሙሉ የዘጋች ሲሆን የቤተ መጽሃፍቱ ሰራተኞችም በ72 ሰዓታት ውስጥ ሀርጌሳን ለቀው እንዲወጡ አዛለች። ሶማሊላንድ ከወራቶች በፊት ነበር ለኢትዮጵያ ወደብ ለመስጠት የተስማማችው። #Ethiopia ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93 #WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36

ያለፈው አመት እንደ አየር ሃይል በርካታ ሥራዎች በስኬት ተከናውነዋል። የአየር ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ያሳለፍነው ዓመት እንደ ሀገር ታላላቅ ስኬቶችን ያስመዘገብንበት ከነዚህም የታ
ያለፈው አመት  እንደ አየር ሃይል በርካታ ሥራዎች በስኬት ተከናውነዋል። የአየር ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ  ያሳለፍነው ዓመት እንደ ሀገር ታላላቅ ስኬቶችን ያስመዘገብንበት ከነዚህም የታላቁ ህዳሴ ግድባችን ወደ ተሟላ የኃይል ማመንጨት ብስራት በአረንጓዴ አሻራ ልማት በምግብ ራስን የመቻል ስኬትን ጨምሮ በማክሮ ኢኮኖሚ ፓሊሲ ወደ አለም የፋይናንስ ስርዓት የገባንበት ልዩ ዓመት ነው ሲሉ ገልፀዋል። በሰው ኃይል ግንባታ በስልጠና አቅም በዘመናዊ የአቭዬሽን ትጥቆች እና ከሀገር ውስጥም አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃም አድናቆትን ያተረፈው የምስረታ በአላችን በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ አየር ኃይል የድል አመት መሆኑንም ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ተናግረዋል። በአዲሱም ዓመት የኢትዮጵያ አየር ኃይል በላቀ የወትሮ ዝግጁነት አቅም ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የጠቆሙት ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የሀገራችን ብሔራዊ ጥቅም ለመጉዳት የሚንቀሳቀሱ ታሪካዊ ጠላቶቻችንና ተባባሪ የውስጥ ባንዳዎች ፍላጎታቸው መቼም እንደማይሳካ ተረድተው ከድርጊታቸው እንዲታቀቡም አሳስበዋል። በዕለቱ ለሚዲያ ሙያተኞች እንዲሁም ለኤር ፖሊስ የጥበቃ አባላት ፈጣን የማዕረግ ዕድገት በሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ አማካኝነት ሽልማት የተሰጠ ሲሆን ምክትል አዛዥ ለአየር ኃይል አካዳሚም አነስተኛ ገቢ ለሚያገኙ አቅመ ደካሞች ልዩ የበዓል ስጦታ አበርክቷል። #Ethiopia ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93 #WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36

"ማድረግ እንችላለን ስንል በህብራዊ ክንዳችን ጠላትን ደጋግመን ያሳፈርንበት ህያው ታሪክ ስላለን ነው።" የኢፌዲሪ መከላከያ  ሠራዊች ጳጉሜ 04 ቀን 2016 ዓ.ም ጦርነት የሚወደስ ጉዳይ አይደለም።ነገር ግን ሳንጋብዘው ደጋግሞ ጎብኝቶናል። ታዲያ የጎበኙንን ሁሉንም የውጭ ወራሪዎች ጥቃት ድል እየነሳን ወራሪን አሳፍረን ሀገራችንን በህብራዊ ክንዳችን በነጻነት ዛሬ ላይ አድርሰናታል። በ1900 ዓ.ም ከድፍን አፍሪካ የቀደመ የዘመናዊ ሰራዊት ግንባታን የጦር ሚኒስቴር ማቋቋም መጀመራችን የታሪክ ዶሴያችንን ስናገላብጥ ይነግረናል። በ1942 ዓ.ም ደግሞ የሠራዊት ግንባታችን ተመንድጎ የሜካናይዝድ ሃይል "10ኛው ሜካናይዝድ" በሚል ስያሜ ስለመመስረቱ የሀገራችን ወታደራዊ ታሪክ ላይ ተሰንዶ እናገኘዋለን። የሜካናይዝድ ሃይላችን ምስረታ እውን የሆነው በ1942 ዓ.ም ይሁን እንጂ በዘመናዊነት ጠብሰቅ ብሎ የማድረግ አቅሙ ከፍ ያለው የዚያድባሬን ወረራ ተከትሎና ከዚያ ወዲህ በተሰሩ ስራዎች ነው። ዕድሜ ጠገቡና ታሪከ ብዙው የሜካናይዝድ ሃይላችን አሁን ላይ ከነ ነባር ልምዱና ተደጋጋሚ ጦርነቶች የተግባር ችሎታው ከድል ወደ ድል እየተሸጋገረ ዛሬ ላይ ደርሷል። ከዘመናዊ ሰራዊት አኳያ 1942 አልን እንጂ       "ገበየሁ ቢሞት ተተካ ባልቻ፣       መድፍ አገላባጭ ብቻ ለብቻ።" የሚል ስንኝ ያስቋጠረው የአድዋ ድል ትርክትንም ሆነ ከዚያ በቀደመ ዘመን የአጼ ቴዎድሮስን የሴቫስቶፖል እውን ማድረግ ታሪካችንን ዘንግተን አይደለም። ሀገራዊ ብሄራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ፣ሉዓላዊነታችንን ከነተሟላ ክብሩ ለማጽናት በተባበረ ህብራዊ ክንድ አሁን ላይ እጅጉን በዘመነና የወታደራዌ ቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን በተላበሰ አኳኃን ኢትዮጵያን የሚያኮራ የሜካናይዝድ ሃይላችን አሁን ላይ በአስተማማኝነቱ ስንዱ ሆኖ አለ። የጀግናው ሰራዊታችን ሁነኛ የማድረግ አቅም ማሳያ ሆኖ ያለው አሁናዊው የሜካናይዝድ ሃይላችን ሀገራዊ ስጋትን፣ ቀጠናዊ እውነታን ታሳቢ ባደረገ ሁኔታ ጥንቅቅ ባለ አደረጃጀት በየግዳጅ ቀጠናው ዝግጁነቱን አረጋግጦ ይገኛል። በነገራችን ላይ የአለማችን ተለዋዋጭና ኢ-ተገማች ሁኔታዎች ሲጤኑ፣የወታደራዊ ቴክኖሎጂ በየጊዜው መሻሻል፣የቀጠናዊ የስጋት መልኮች መለዋወጥ የወታደራዊ ሳይንስ ዕውቀትና አመራርነትን ጥልቅ አድርጎታል። እናም የጀግናው መከላከያችን ሜካናይዝድ ሃይላችን ተቋማዊ የማድረግ አቅምን አስተማማኝ አድርጎ ይገኛል ስንል ይህንን ሁሉ ግምት ውስጥ አስገብቶ ነው። አሁን አሁን የታሪካዊ ጠላቶቻችን በውስጥ የማባላት ሴራቸው መሻታቸው አልሰምር ሲል በደከሙ ጎረቤቶቻችን አማካይነት ማንዣበብ ቢጀምሩም በመካከሉም በማጥቃቱም ብቃታችን ቅንጣት ጥርጣሬ እንዳይኖረን የሚያደርግ መቺ፣ደምሳሽ የሜካናይዝድ ሃይል ገንብተን ነው። እናም ደግሞ ታሪካችን ደጋግሞ እንዳሳየን በህብራዊ ክንዳችን ጠላትን ደጋግመን ያሳፈርን "ድል ሰሪዎች" መሆናችንም ልብ ይባል። ዛሬ በዝማኔ ተውቦ፣በዳበረ ልምድ አጊጦ፣በብቃትና ችሎታ አንጸባርቆ የብሄራዊ ጥቅምና ክብራችን አስጠባቂ የሆነውና የተባበሩ የኢትዮጵያ ህብራዊ አዕምሮና እጆች በጥበብ ያበጁት የሜካናይዝድ ሃይላችን የሚለን ይኖረዋል። ከቆይታ በኃላ እንገናኛለን። በአስቻለው ሌንጫ #Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93 #WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36

#መስራት_ያሸልማል። የቻይና የሕዝብ ደኅንነት ሚኒስቴር ለክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የGreat Wall Commemorative Gold Medal Award አበረከተ የቻይና የሕዝብ ደኅን
+4
#መስራት_ያሸልማል። የቻይና የሕዝብ ደኅንነት ሚኒስቴር ለክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የGreat Wall Commemorative Gold Medal Award አበረከተ የቻይና የሕዝብ ደኅንነት ሚኒስቴር ለክቡር ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የ Great Wall Commemorative Gold Medal Award አበረከተ፡፡ የተበረከተላቸው የወርቅ ሜዳሊያ ክቡር ኮሚሽነር ጀነራል የሁለቱን ሀገራት ፖሊስ ለፖሊስ ግንኙነት በማጠናከር በተለይ በቤልት ኤንድ ሮድ ኢኒሼቲቭ የፀጥታ ትብብር ስራዎች፣ የምስራቅ አፍሪካ ፖሊስ አዛዦች ህብረት ድርጅትንና የቀጠናውን ትብብር  ከቻይና ፖሊስ ጋር በማስተሳሰር ላበረከቱት ሚና እንዲሁም አሁን ላይ የዓለም አቀፍ የሕዝብ ደኅንነት ትብብር ፎረም የቦርድ አባል ሆነው ለዜጎች ሰላምና ደኅንነት ለማረጋገጥ እየተጫወቱ ላሉት ክፍተኛ አስተዋዕፆ ሲሆን በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የወርቅ ሜዳሊያ Great Wall Commemorative Gold Medal Award ከቻይና የህዝብ ደኅንነት ሚኒስትር ክቡር ዋንግ ዣዎሆንግ እጅ ተበርክቶላቸዋል፡፡ በሥነ-ሥርዓቱም ላይ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ክቡር አቶ ተፈራ ደርበው፣ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ክቡር ቼን ሃይ፣ የቻይና የህዝብ ደኅንነት ሚኒስቴር  ምክትል ሚኒስትሮችና እና የፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡ #Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93 #WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36

ፋኖ ወሎ ምድር ላይ ተገቢውን ትምህርት ወስዷል። ከዚህ በሗላ ወሎን እንዳያስብ ተደርጎ አስተማሪ ቅጣት ተሰጥቶት ተመልሷል። ፋኖም ሆነ ፅንፈኛ የአማራ ብሔርተኛ ፖለቲከኞች አንድ መሰረታዊ ችግር አለባ
ፋኖ ወሎ ምድር ላይ ተገቢውን ትምህርት ወስዷል። ከዚህ በሗላ ወሎን እንዳያስብ ተደርጎ አስተማሪ ቅጣት ተሰጥቶት ተመልሷል። ፋኖም ሆነ ፅንፈኛ የአማራ ብሔርተኛ ፖለቲከኞች አንድ መሰረታዊ ችግር አለባቸው - የወሎን ህዝብ ዝቅ አድርጎ የማየት የመናቅና ሁለተኛ ደረጃ አማራ አድርጎ የማሰብ። ይህ ትምክህት እና ባዶ ትእቢትም ዋጋ እያስከፈላቸው ይገኛል። ራያ ወርቄን እቆጣጠራለሁ ብሎ ከጀግኖቹ ደጃፍ የረገጠው በምሬ ወዳጆ የሚመራው ፋኖም የገጠመው ይህ ነው ። የጁ እሳት ይዟል በእጁ የተባለለት አርበኛ የአርሶ አደርና አርብቶ አደር ሰራዊት አካባቢውን ሊወር የመጣውን ሀይል አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ ከአካባቢው ብቻ ሳይሆን ከበርካታ ቦታዎች አፅድቶ አባሮታል። ከቦታው ባገኘሁት መረጃ መሰረት ገበሬው የሰሜን ወሎ ታጣቂ ማህበረሰብ ከመከላከያ ሰራዊቱ ጋር ቅንጅት በመፍጠር ዞብልን ቆቦንና ቦረንን በማፅዳት ከራማ አካባቢ በማስወጣት አካባቢውን አስከብሯል። ጥምር ጦሩ ወደፊት እየተጓዘ እንደሆነም ተገልጿል። በዚህም ፋኖ ያለባቸው ቦታዎች በሙሉ በቀጣዩ ዘመቻ ይፀዳሉ የተባለ ሲሆን የፋኖ ተወጊዎችም ልብሳቸውን እየቀየሩ ከፊሉ እየተማረከ የገቡበትን ቦታ እየለቀቁ ይገኛሉ። ወሎ ላይ ደግሰውት የነበረው አደገኛ መጠፋፋትም በወሎ ህዝብ ልበሰፊነትና መከባበር ከሽፎ የሚሰማቸው አጥተው በሽንፈት ተመልሰዋል። በዚህ አደገኛ የብሔር አዙሪት ውስጥ ገብተው በርካታ ወጣቶች ህይወታቸውን ማጣታቸው አሳዛኝ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቻያና የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት #Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቻያና የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት #Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93 #WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36

#Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https:/
+7
#Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93 #WhatsApp https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36

የመሻገር ቀን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 01 ቀን 2016 ዓ.ም "እዚህ የደረስነው ብዙ ነገሮችን ተሻግረን ነው። ያልተመዘዘ ሰይፍ፣ ያልተሰበቀ ጦር፣ ያልተተከለ ወጥመድ፣ ያልተሤረ ሤራ፣ ያልተ
                    የመሻገር ቀን የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጷጉሜ 01 ቀን 2016 ዓ.ም "እዚህ የደረስነው ብዙ ነገሮችን ተሻግረን ነው። ያልተመዘዘ ሰይፍ፣ ያልተሰበቀ ጦር፣ ያልተተከለ ወጥመድ፣ ያልተሤረ ሤራ፣ ያልተቆፈረ ገደል አልነበረም። በፈጣሪ እርዳታ ሁሉንም እየተሻገርነው ነው። ጦርነትን፣የኮሮና ወረርሽኝን፣ ግጭትን፣ የአንበጣ መንጋን፣ የሕዳሴ ግድብ ውጣ ውረድን፤ ተሻግረናቸዋል። ሌሎችንም እየተሻገርን ነው። ተሻጋሪዎች ነን። አሻጋሪያችንም የማይሰበር ነው። ከማዶ አንቀርም። በመሐልም አንወድቅም። በድል እንደምንሻገር ቅንጣት ጥርጥር የለንም" -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶክተር)

በኢትዮጵያ ሲሰለጠኑ የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የሶማሊላንድ ብሔራዊ ጦር አባላት ስልጠናቸውን አጠናቀው መመረቃቸው ተገለጸ ስልጠና ሲሰጣቸው የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ #የሶማሊላንድ ብሔራዊ ጦር አዳዲስ
+2
በኢትዮጵያ ሲሰለጠኑ የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ የሶማሊላንድ ብሔራዊ ጦር አባላት ስልጠናቸውን አጠናቀው መመረቃቸው ተገለጸ ስልጠና ሲሰጣቸው የነበሩ በሺዎች የሚቆጠሩ #የሶማሊላንድ ብሔራዊ ጦር አዳዲስ ምልምል አባላት ከኢትዮጵያ መከላከያ ማሰልጠኛ ማዕከል ስልጠናቸውን ጨርሰው መመረቃቸው ተገለጸ። ነሃሴ 24 ቀን 2016 ዓ.ም የተመረቁት የሶማሊንድ ወታደሮች በኢትዮጵያ ከአንድ አመት በፊት ጀምሮ በተከታታይ ዙር የተጠናከረ ስልጠና ሲሰጣቸው ከነበሩ የሀገሪቱ ጦር አባላት መካከል መሆናቸውን እና 8ኛ ዙር ሰልጣኞች መሆናቸውን ሆርን ዲፕሎማት በድረገጹ አስነብቧል። በታላቅ ድምቀት በተካሄደው የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ የሁለቱም ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት መታደማቸውን የጠቆመው ዘገባው በሶማሌላንድ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ወታደራዊ ትብብር አጉልቶ ያሳየ ነው መባሉን አስታውቋል። በምረቃ ስነስርአቱ ላይ በክብር ከታደሙት እንግዶች መካከል የሶማሌላንድ ብሄራዊ ጦር አዛዥ ሜጀር ጄኔራል ኑህ እስማኤል ታኒ ይገኙበታል ያለው የድረገጹ ዘገባ የጦር አዛዡ በምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ መገኘት ሶማሌላንድ ብሔራዊ የመከላከያ አቅሟን ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን ያሳየ ነው ነው ሲል ገልጿል።ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በርካታ የሶማሊላንድ ወታደሮች በተከታታይ በኢትዮጵያ ስልጠና መውሰዳቸውንም አውስቷል።

#Update " በረራውን ለማቋረጥ የተገደድኩት ገንዘብ እንዳላንቀሳቅስ በመታገዴ ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኤርትራ ሲቪል አቬሽን ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የሚያደርገው በረራ ከመስከረም 20፣ 2016 ዓ.ም  ጀምሮ እንዲቆም የሚያሳውቅ ደብዳቤ ጽፎ እንደነበር ይታወሳል። ዛሬ አየር መንገዱ በሰጠው መግለጫ ውሳኔው ይሻሻላል በሚል ሲጠብቅ እንደነበር እና የኤርትራ የሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣንን ለማናገር በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ አለማሳካቱን አስታውቋል። የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በመግለጫው እንደጠቀሱት በአስመራ የሚገኘው ተወካያቸው ከሽያጭ የተሰበሰበ ገንዘብ ለማስገባት ሲል ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ መላክ እንደማይቻል ተነግሮታል። ይህ የሆነው ሐምሌ 18/2016 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ አማካኝነት ነው። " ' ከነሐሴ 25/ 2016 ዓ.ም  በኋላ ሂሳባችሁ ታግዷል ለሀገር ውስጥ ወጪም (oppration fee) መጠቀም አትችሉም ' መባሉን ተከትሎ ከዛሬ ጀምሮ በረራውን ለማቋረጥ ተገደናል።  የበረራ ወጪያችንን መሸፈን ባለመቻላችን ተገደን ወጥተናል " ሲሉ ነው የገለጹት። አየር መንገዱ እንዳያንቀሳቅስ የታገደበት ገንዘብ መጠን ስንት ነው ? ይህ ጥያቄ ከጋዜጠኞች የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው የገንዘቡን መጠን ከመግለጽ ተቆጥበው ማብራሪያ ሰጥተዋል። አየር መንገዱ በኤርትራ ሁለት አካውንት እንዳለው የገለጹት አቶ መስፍን፥ አንዱ የናቅፋ አካውንት ሲሆን የቆየ እንዲሁም ወደ ዶላር መቀየር ያልተቻለ የማይንቀሳቀስ የሂሳብ አካውንት መሆኑን ገልጸዋል። ሌላኛው የባንክ አካውንት ደግሞ የዶላር ሲሆን ባለፉት ጥቂት ዓመታት ትኬት ሲሸጥ የነበረው በውጭ ምንዛሬ መሆኑን ገልጸው ይህንን ገንዘብም እገዳው እስከተላለፈበት ቀን ድረስ በተለያዩ ጊዜዎች ገንዘቡን ሲያንቀሳቅስ እንደነበረ ገልጸዋል።  " የበረራ እገዳውን ካወጡብን በኋላ ነው Block ያደረጉብን " ሲሉ ነው የገለጹት። አቶ መስፍን አክለውም ፥ "ለእኛ ገንዘቡ ካልተለቀቀልን ከዚህ በኋላ የሁለቱ ሀገራት ጉዳይ ነው የሚሆነው " ሲሉ ጉዳዩን ለኢትዮጵያ ለሲቪል አቬሽን ባለሥልጣን እና ለውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቃቸውን ገልጸዋል። " አየር መንገዱ ከኤርትራ የወጣው ተገዶ ነው " ያሉት አቶ መስፍን ዋናው ችግሩ ለምን እንደታገድን አለማወቃችን ነው፤ በተጻፈው ደብዳቤም ላይ ምንም የተገለጸ ነገር የለም ብለዋል። " ከዚህም በተጨማሪ በደብዳቤም በስልክም ለማናገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም " ሲሉ ገልጸዋል። የአየር ቀጠናውን አስመልክቶ ጥያቄ የቀረበላቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚው አሁን ባለው ሁኔታ በኤርትራ የአየር ክልል መብረር እንዳልተከለከሉ ገልጸው የሚያስገድድ ጉዳይ ካለ ግን አማራጭ መጠቀም እንደሚችሉ አንስተዋል። #Ethiopia #GERD🇪🇹 ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇👇 https://t.me/Commando_And_Airborne_Command https://www.youtube.com/@%E1%88%B0%E1%89%A0%E1%88%AD_%E1%8B%9C%E1%8A%93