es
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Ir al canal en Telegram

Addis abeba Ethiopia

Mostrar más
5 066
Suscriptores
-25624 horas
-1 8217 días
-3 02830 días
Archivo de publicaciones
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ2023 ፈጣን ብራንድ ዋጋ ዕድገት ማሳየቱ ተገለጸ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2023 ከዓለም አየር መንገድ ብራንዶች ሁሉ ፈጣን የተባለ እድገት ማሳየቱ ተገለጸ፡፡ ብራንድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ2023 ፈጣን ብራንድ ዋጋ ዕድገት ማሳየቱ ተገለጸ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2023 ከዓለም አየር መንገድ ብራንዶች ሁሉ ፈጣን የተባለ እድገት ማሳየቱ ተገለጸ፡፡ ብራንድ ፋይናንስ የተባለ የአየር መንገዶችን ብራንድ ደረጃ የሚያወጣ ድርጅት የ2023 አየር መንገዶችን ብራንድ ደረጃ ባወጣበት ሪፖርቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብራንድ በዓመቱ 79 በመቶ በማደግ እጅግ ፈጣን የሆነ የብራንድ ዕድገት ማስመዝገቡን አስታውቋል፡፡ በዚህም የአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ የብራንድ ዋጋው 498 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድረሱን ጠቁሟል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአሜሪካው ዴልታ አየር መንገድ በ8.9 ቢሊዮን ዶላር የብራንድ ዋጋ የዓለም ቁጥር አንድ አየር መንገድ ብራንድ መሆኑን ሪፖርቱ አመላክቷል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደ ኤምሬትስ እና ኳታር ኤርወይስ ከመሳሰሉ የመካከለኛው ምስራቅ አየር መንገዶች ከፍተኛ ውድድር እንደምጠብቀውም መረጃው ያሳያል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ ከስሮ የተዘጋውን የናይጀሪያን አየር መንገድ በሽርክና ወደ በረራ ሊመልስ መሆኑን የገለጸው መረጃው ስምምነቱ ለአየር መንገዱ በአህጉሩና በናይጀሪያ ትልቅ የገበያ ዕድልን ይፈጥርለታልም ብሏል፡፡ አየር መንገዱ በሚቀጥሉት 12 ዓመታት ውስጥ የአውሮፕላኖቹን ቁጥር ከ140 ወደ 270 በእጥፍ እንደሚያሳድግ በመረጃው ተመላክቷል፡፡ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ በመቀጠል በየዓመቱ ከፍተኛ የብራንድ ዋጋ እድገት ካሳዩት ውስጥ የስፔኑ ቩውሊንግ የ44 በመቶ ሲያድግ የአሜሪካው ዩናይትድ አየርላይንስ 42 በመቶ እንዲሁም ቻይና ሳውዘርን 39 በመቶ የብራንዳቸው ዋጋ መጨመሩን መረጃው ያመለክታል፡፡

ቻይና በራሷ የሰራችው አውሮፕላን መንገደኞችን አሳፍሮ የመጀመሪያ በረራ አድረገ አውሮፕላኑ 130 መንገደኞችን አሳፍሮ ከሻንጋይ ወደ ቤጂንግ የ3 ሰዓት በረ አድርጓል። የC919 አውሮፕላን አምራች ኮማክ ኩባያ የ1 ሺሀ 200 የአውሮፕላን ምርት ትእዛዝ መቀበሉን አስታውቋል። ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤ https://am.al-ain.com/article/china-produced-passenger-jet-flight

ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችንን ማክበር፣ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ክብር መስጠት ነው! ዳግም የማትገኝ ሕይወቱን ገብሮ፣ ደሙን አፍስሶና አጥንቱን ከስክሶ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ሠላምና አንድነት ቀን ከሌሊት
+9
ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችንን ማክበር፣ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ክብር መስጠት ነው! ዳግም የማትገኝ ሕይወቱን ገብሮ፣ ደሙን አፍስሶና አጥንቱን ከስክሶ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ሠላምና አንድነት ቀን ከሌሊት የሚተጋው አይበገሬው መከላከያ ሠራዊታችን፤ የመላው ኢትዮጵያዊያን አንጡራ ሐብት ነው። ሠራዊታችን ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በእኩልነት የሚመለከትና ሕዝቡንም የግዳጁ አካል በማድረግ ተቀናጅቶ የሚሰራ፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ወገንተኝነት የፀዳ፤ ወገንተኝነቱም ለሕዝቡ፣ ለሀገሩና ለሕገ-መንግሥቱ ብቻ የሆነ ፕሮፌሽናል ኃይል ነው። ከዚህ ውጭ፣ የራሳቸው የፖለቲካ እሳቤ ያላቸው አንዳንድ ፅንፈኛ ቡድኖች የሚያስወሩት አሉቧልታ የኢትዮጵያና የሕዝቧ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነውን ሕዝባዊ ሠራዊት ፈፅሞ የሚመለከተው አይደለም። እነዚህ ፅንፈኛ ቡድኖች በፖለቲካው ውስጥ ሕግና ሥርዓትን አክብረው ስልጣን መያዝ ሲያቅታቸው፤ ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን በአንዳንድ የሀገሪቱ ክፍሎች የሕግ የበላይነትን ለማስከበር የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ለማስተጓጎል ሲሯሯጡ ይታያል። ይህን የፅንፈኞች የሴራ ፖለቲካ የሚሰማ ሕዝብ የለም። ምክንያቱም ሕዝቡ የጀግናው መከላከያ ሠራዊታችንን ሕዝባዊ ወገንተኝነትና ሀገራዊ ተልዕኮን ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ነው። በአሁኑ ወቅትም በየአካባቢው ከሠራዊታችን ጋር እጅና ጓንት ሆኖ በመስራት ላይ ይገኛል። የሀገር ሕልውና፣ የሕዝብ መከታና አለኝታ የሆነውን መከላከያ ሠራዊታችን ማክበር፤ ለኢትዮጵያና ለሕዝቧ ክብር መስጠት ነው እናም በፅንፈኞች "የበሬ ወለደ" ጥላቻ ትርክት፣ የሚሳሳት ሕዝብም ይሁን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ከመታደግ ተልዕኮው ለአፍታም ቢሆን የሚዛነፍ ሠራዊት እንደሌለ መገንዘብ ብልህነት ነው ክብር ለጀግናው የታላቋ ኢትዮጵያ መከላከያ 👉

ልዩ መረጃ በከሚሴ አካባቢ የሸኔ አመራር እና በቅርቡ የብርጌድ አመራር ሊሆን የነበረዉ እና ቄሬንሶ ወይም ኢብሳ ተብሎ የሚጠራዉ የአሸባሪዉ ቡድን መሪ ዛሬ ፖሊስና ሚሊሻ ባደረጉት እልህ አስጨራሽ ተጋ
ልዩ መረጃ በከሚሴ አካባቢ የሸኔ አመራር እና በቅርቡ የብርጌድ አመራር  ሊሆን የነበረዉ እና  ቄሬንሶ ወይም ኢብሳ ተብሎ የሚጠራዉ  የአሸባሪዉ ቡድን መሪ ዛሬ ፖሊስና ሚሊሻ ባደረጉት  እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ ደዌ ሀረዋ ኡረኔ ሰላማ ሂጅራ ጎጥ ላይ እርምጃ ተወስዶበታል። ምስል 1 ጃል ሴና የኦነግ ወታደራዊ አሰልጣኝ:: ምስል 2 ጃል ቄሬንሶ በወሎ የኦነግ አዛዥ

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከህወሓት ታጣቂዎች የቡድን መሳሪያ ተረከበ። በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከህወሓት ታጣቂ ሃይሎች የቡድን መሳሪያ ተረከበ፡፡ ርክክቡ
+2
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከህወሓት ታጣቂዎች የቡድን መሳሪያ ተረከበ። በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ከህወሓት ታጣቂ ሃይሎች የቡድን መሳሪያ ተረከበ፡፡ ርክክቡ በመቀሌ ከተማ አቅራቢያ በሚገኝ ልዩ ቦታው ላጪ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተካሄደ ሲሆን፥ በርክክብ መርሐ ግብሩ የአፍሪካ ህብረት ታዛቢዎች ተገኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ተወካይ ብርጋዲየር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ እንደገለጹት የመሳሪያ ርክክቡ የሰላም ስምምነቱ አንድ አካል ነው። በርክክቡም የቡድን መካከለኛ መሳሪያ የሚባሉ የጦር መሳሪያዎችን መረከባቸውን ገልጸዋል። የህወሓት ታጣቂ ኃይሎች ተወካይ ብርጋዲየር ጄኔራል ምግበይ ኃይለ በበኩላቸው የቡድን መሣሪያ ርክክቡ በሰላም ስምምነቱ መሰረት መፈጸሙን ገልጸው፥ ለሰላም ስምምነቱ ተፈጻሚነት የበኩላቸውን እያደረጉ መሆኑን ተናግረዋል። ርክክቡን የታዘቡት የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ እና አረካካቢ ኮሚቴ አባል ብርጋዲየር ጄኔራል ቴፎ ሶኮሌ ርክክቡ የሰላም ስምምነቱ በጥሩ ሁኔታ እየተፈጸመ ለመሆኑ ማሳያ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

ዓርብ ጠዋት! ግንቦት 18/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች 1፤ የአፍሪካ ኅብረት ገምጋሚ ኮሚቴ የሰሜን ኢትዮጵያ የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ተቆጣጣሪ ቡድን የቆይታ ጊዜ እስከ ቀጣዩ ዓመት ታኅሳስ እንዲራዘም መጠየቁን ኅብረቱ አስታውቋል። ገምጋሚ ኮሚቴው፣ የትግራይ ተዋጊዎችን ትጥቅ የማስፈታት፣ ወደ ሰላማዊ ኑሮ የመመለስ ሥራ እና ተፈናቃዮችንና ስደተኞችን ወደ ቦታቸው የመመለስ ሥራ ባስቸኳይ እንዲከናወን አሳስቧል። የኢትዮጵያ መንግሥት የተመድ የፈንጂ አምካኝ ቡድን በፈንጅ ማምከን ሥራ እንዲሠማራ ፍቃድ መስጠቱንም የኅብረቱ ገምጋሚ ኮሚቴ አድንቋል። የኅብረቱ ገምጋሚ ኮሚቴ ይህን ያለው፣ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና ሕወሃት ሰላም ስምምነት አተገባበርን ለሁለተኛ ጊዜ ከገመገመ በኋላ ባወጣው መግለጫ ነው። 2፤ ከቃሊቲ ወህኒ ቤት ረቡዕ ሌሊት ለማምለጥ የሞከሩ 10 ታራሚዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የመንግሥት ዜና ምንጮች ዘግበዋል። መሬት በመቆፈር ከወህኒ ቤቱ ሊያመልጡ ሲሉ የተያዙት ታራሚዎች፣ የከባድ ውንብድና ወንጀሎች ፍርደኞች እንደኾኑ ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል። ከወህኒ ቤቱ በማምለጥ ሙከራው ከተሳተፉት መካከል፣ ቀደም ሲል ከወህኒ ቤት አምልጦ ጣሊያን ውስጥ በቁጥጥር ስር የዋለና ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፎ የተሰጠ አንድ ፍርደኛ ይገኝበታል ተብሏል። ኢትዮጵያ ኢንሳይደር የዜና ምንጭ በበኩሉ፣ በሙከራው ወቅት አንድ እስረኛ በጸጥታ ኃይሎች እንደተገደለና አምስት ደሞ እንደቆሰሉ  ከዓይን ምስክሮች መስማቱን ጠቅሶ ዘግቧል። 3፤ አሜሪካ ለአልሸባብ የገንዘብና ሌሎች ድጋፎችን ያደርጋሉ ያለቻቸውን 26 ግለሰቦችንና ድርጅቶችን በአሸባሪነት ፈርጃለች። በአሸባሪነት ከተፈረጁት መካከል፣ ከአካባቢው ማኅበረሰብ ገንዘብ ለቡድኑ መዋጮ የሚሰበስቡ፣ የአልሸባብን የበቀል ርምጃዎችን የሚያስተባብሩ፣ ለቡድኑ ተቀጣጣይ ፈንጂዎችን የሚያመርቱና የቡድኑን ሕገወጥ የክሰል ንግድ የሚያቀላጥፉ ግለሰቦችና ድርጅቶች ጭምር ይገኙበታል። የፍረጃው ዒላማ የኾኑት አካላት፣ በሱማሊያ በታችኛው ሸበሌ፣ በታችኛው ጁባ እና በመካከለኛው ጁባ ግዛቶች የሚገኙ እንደኾኑ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። በአሸባሪነት ፍረጃው መሠረት፣ ግለሰቦቹና ድርጅቶቹ በአሜሪካ ያላቸውን ንብረትና ገንዘብ ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ መታገዳቸው ተገልጧል። 4፤ ኬንያ የቻይና የመረጃ ጠላፊዎች በመንግሥታዊ ተቋሞቿ ላይ የበይነ መረብ ጥቃት ፈጽመዋል ተብሎ የየሠራጨውን መረጃ አጣጥለዋለች። ሮይተርስ የሠራው ዘገባ፣ "በሉዓላዊነቷ ላይ የተቃጣ የተቀነባበረ ፕሮፓጋንዳ" መኾኑን መግለጧን ደይሊ ኔሽን ዘግቧል። የመንግሥታዊ ተቋማቷን የኢንፎርሜሽን መረብ የዘረጋችላት ቻይና መኾኗን የገለጠችው ኬንያ፣ ቻይና ራሷ የዘረጋችውን መረብ ለመጥለፍ ሦስተኛ አካላትን ለመረጃ ጠላፊነት መጠቀም አያስፈልጋትም ማለቷን ዘገባው ጠቅሷል። ቻይናም የሮይተርስን ዘገባ "መሠረተ ቢስ" በማለት ማጣጣሏ ይታወሳል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን🙏

ሰኞ ጠዋት! ግንቦት 14/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች 1፤ የኢትዮጵያ ኮምንኬሽን ባለሥልጣን ሦስተኛውን የቴሌኮም ፍቃድ በሰኔ ወር እሰጣለሁ ማለቱን ኢዜአ ዘግቧል። የኬንያው ሳፋሪኮም ኩባንያ በ2013 ዓ፣ም የመጀመሪያውን የቴሌኮም ፍቃድ ወስዶ አገልግሎት በመጀመር የመጀመሪያው የውጭ ኩባንያ መኾኑ ይታወሳል። ባለሥልጣኑ በወቅቱ ጨረታ ያወጣው ለሁለት የውጭ ኩባንያዎች ፍቃድ ለመስጠት ነበር። ኾኖም ሌላኛው ተጫራች ኤምቲኤን ኩባንያ ያቀረበው ገንዘብ ከሳፋሪኮም ጋር ሰፊ ልዩነት በማሳየቱ፣ ባለሥልጣኑ ሁለተኛውን ጨረታ ለመሰረዝ እንደተገደደ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። 2፤ የሰሜኑ ጦርነት በአገሪቱ ላይ ከ1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር በላይ ውድመት እንዳስከተለ ሪፖርተር የገንዘብ ሚንስትር አሕመድ ሽዴ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡት ሪፖርት ላይ መናገራቸውን ጠቅሶ ዘግቧል። አሕመድ፣ ጦርነቱ ያደረሰው ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ ብቻውን ስድስት ቢሊዮን ዶላር እንደተገመተ በሪፖርታቸው መጠቀሳቸውን ዘገባው አመልክቷል። ጦርነቱ ሦስት ሚሊዮን ዜጎችን ወደ ከፋ ድህነት ውስጥ ማስገባቱም በሪፖርቱ ተገልጧል ተብሏል። ሚንስትሩ፣ መስሪያ ቤታቸው ጦርነቱ ባስከተለው ውድመትና በመልሶ ግንባታ ፍላጎቶች ላይ ያካሄደውን የዳሰሳ ጥናት ለመንግሥት ማቅረቡን እንደገለጡ ዘገባው ጨምሮ ጠቅሷል። 3፤ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያን "በጊዜያዊነት" ማገዱን አስታውቋል። ባለሥልጣኑ ጣቢያውን ያገደው፣ ጣቢያው ትናንት ያሰራጨው ዘገባ የቤተክርስቲያኗ ቅዱስ ሲኖዶስ እያካሄደው ያለውን ስብሰባ "የሚያውክና ሕዝብን ለግጭት የሚያነሳሳ መልዕክት መኾኑን አረጋግጫለኹ በማለት ነው። ባለሥልጣኑ ጣቢያው የመገናኛ ብዙኀን አዋጅን በመተላለፍ፣ "በአገር ሁለንተናዊ ሰላም ላይ ጉዳት ሊያስከትል የሚችል" ዘገባ አስተላልፏል በማለትም ከሷል። 4፤ ሁለቱ የሱዳን ተፋላሚ ወገኖች የ7 ቀናት ተኩስ አቁም ለማድረግ ከተስማሙ በኋላም ግጭቱ መቀጠሉን የፈረንሳይ ዜና ወኪል ዘግቧል። ቅዳሜ'ለት የተፈረመው የተኩስ አቁም ስምምነት፣ ከዛሬ ምሽት ሦስት ሰዓት ከ45 ደቂቃ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚኾን ይጠበቃል። ተኩስ አቁሙ በሁለቱ ወገኖች ስምምነት በድጋሚ ሊራዘም እንደሚችል የተገለጠ ሲኾን፣ የስምምነቱን አፈጻጸም ገለልተኛ አካላት ማለትም አሜሪካና ሳዑዲ ዓረቢያ እንደሚቆጣጠሩትም ተገልጧል። #ሼር በማድረግ ተባበሩን🙏

ሩሲያ የዩክሬንን ጠንካራውን የባኽሙት ምሽግ ሰበረች ቅዳሜ እለት ከሩሲያው የግል ወታደራዊ ኮንትራክተር የዋግነር ግሩፕ ቅጥረኞች ለስምንት ወራት ከዘለቀው አሰቃቂ ጦርነት በኋላ በምስራቅ ዩክሬን የምትገኘውን ባኽሙት ከተማ በቁጥጥር ስር አውለዋል። የሞስኮ ደጋፊዎች እጅግ ግትርና አስቸጋሪ የተባለውን የዩክሬን ምሽግ በመስበራቸውን በደስታ ውስጥ ይገኛሉ። የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በትላንትናው እለት የባክሙት ምሽግ ተሰብሯል የሚለውን ቢያስተባብሉም፣ ሩሲያዊው ነጋዴ እና የዋግነር አለቃ ዬቭጄኒ ፕሪጎዚን 420 ሺህ ተከታዮች ባሉት የቴሌግራም ገፃቸው ባስተላለፉት የድምጽ መልዕክት የተገኘው ድል የዩክሬን ፕሬዝዳንት ከተናገሩት የተለየ ነው ሲሉ ገልፀዋል። እስረኞችን መያዝ ስላቆምን በባክሙት መንደር አንድም የዩክሬን ወታደር የለም" ሲሉ አክለዋል። የዩክሬን ወታደሮች አስከሬን እጅግ በጣም ብዙ ነው ሲሉ የሩሲያ ቅጥረኛ ወታደሮች ዋግነር ግሩፕ መሪ ዬቭጄኒ ፕሪጎዚን ተናግረዋል። የባክሙት ሁሉም ህጋዊ ድንበሮች እስከ መጨረሻው ሴንቲሜትር ድረስ ሙሉ በሙሉ በእጃችን ስር ይገኛል ብለዋል። አክለውም ቭላድሚር አሌክሳንድሮቪች ዘለንስኪ ሐቀኛ ነው፣ ወይም እሱ ልክ እንደ ወታደራዊ መሪዎቻችን፣ በመሬት ላይ ስለሚሆነው ነገር አያውቅም ሲሉ በነገር ወጋ አድርገዋል። ከክሬምሊን ቤተ መንግስት በተሰጠው መግለጫ ፣ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከተማዋ በሶቪየት ዘመን እና እስከ 2016 ድረስ ትታወቅ ስለነበር የሩሲያ ጦር እና የዋግነር ቅጥረኛ ቡድን አርቴሞቭስክን በመያዟ እንኳን ደስ አለዎት ። በሩሲያ ቴሌቪዥን እና በቴሌግራም ቻናሎች ላይ የተቀረጹ ምስሎች የሩሲያን ሰንደቅ በባክሙት ፍርስራሽ ላይ ወታደሮች ይዘው ታይተዋል።

የመንግስት ሰራተኞች ደመወዝ በ " ቴሌ ብር " መክፈል ሊጀመር ነው ? ገንዘብ ሚኒስቴር ፤ በባንኮች በኩል ተከፋይ የሚሆነውን የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ ወደ " ቴሌ ብር " የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ለማሸጋገር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል። የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕ/ተ/ም/ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡበት ወቅት ነው ይህ ይፋ የሆነው። አቶ አህመድ ሽዴ ምንድነው ያሉት ? " አሁን በባንኮች የክፍያ ሥርዓት በጥቅል (በበልክ) እየተከፈለ ያለውን ሒደት በቀጣይ ወደ ቴሌ ብር ለማሸጋገር ሥራዎች እየተሠሩ ነው። " ይህ በተመለከተ ' ኢትዮ ቴሌኮም  ' ምን አለ ? ቺፍ ኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ መሳይ ውብሸት ፦ " በመንግሥት የተያዙት ጉዳዮች ወቅቱን ጠብቀው ቢገለጹ ይሻላል። ነገር ግን ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን ለማቅረብ የሚያስችል በቂ ዝግጅትና አቅም አለው። ተቋሙ በሞባይል ገንዘብ ዝውውር አገልግሎቱ እስካሁን ከ32 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን አገልግሎት እየሰጠ እንደገሚገኘው መጠን የተዘረጋው ሲስተም አገልግሎቱን በቀላሉ ለመስጠት ያስችለዋል። የትኛውም ውሳኔ ከሚመለከተው አካል ከመጣ መሥራት ይቻል። ደመወዝ በቴሌ ብር መከፈሉ የተቋማትን ቅልጥፍና ለመጨመር አስተዋጽኦ ያድረጋል። በዕረፍትና በበዓላት ወቅት የሚውል የደመወዝ ክፍያ ቀንና ተዛማጅ ጉዳዮች ለደመወዝ ከፋዩም ሆነ ተከፋዩ በሚያመች ለመክፈል ያስችላል። እስካሁን ባለው አገልግሎቱ እንደ ደመወዝ ዓይነት የጅምላ (በበልክ) ክፍያ በሚከፈልበት ወቅት ሠራተኞች የደመወዛቸውን እስከ 35 በመቶ ያለምንም ዋስትና መበደር ይችላሉ። በቀጣይ ሌሎች ተጨማሪ አማራጮችም ይቀርባሉ። እስካሁን ድረስ ግን ከሚመለከተው አካል የመጣ አቅጣጫ የለም። " ብለዋል። አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈጉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሥራ ኃላፊ ደመወዥ በ " ቴሌ ብር " ለማድረግ ስለታሰበው እቅድ በተመለከተ " እንዲህ መባሉን መረጃ የለኝም " ብለዋል። በባንኩ በኩል የመንግሥት ሠራተኞችን ደመወዝ የሚከፍል መሆኑን የገለፁት እኚሁ ኃላፊ ለዚህ አገልግሎቱ ምንም ዓይነት ክፍያ የማይጠይቅበት እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ በቴሌ ብር በኩል ደመወዝ ይከፈል ከተባለ ግን አሁንም ኢትዮ ቴሌኮም የሚጠቀመው ከባንኮች ጋር በመተሳሰር መሆኑ አይቀርም ብለዋል፡፡ አጫጭር መረጃ ፦ እንደ ገንዘብ ሚኒስቴር መረጃ ፦ - የመንግሥት ኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ድርሻን ለማሳደግና እስካሁን የ159 ባለ በጀት መ/ቤቶች የኤሌክትሮኒክስ ክፍያ ዘዴ እንዲተገብሩ ተደርገዋል። - በተያዘው ዓመት የዘጠኝ ወራት 79.2 ቢሊዮን ብር ክፍያ በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ተከፍሏል። - ኢትዮ ቴሌኮም የመንግሥት የኤክትሮኒክስ ክፍያ ድርሻ ለመወጣት እንዲያስችለው የሪፎርም ሥራዎችን እየሠራ ነው የታክስ ክፍያ አሰባሰብም ሥርዓቱ በቴሌ ብር እንዲከፈል የሚያስችል ሥርዓት ተዘርግቷል። እንደ ኢትዮ ቴሌኮም መረጃ ፦ - የቴሌ ብር የሞባይል ገንዘብ ዝውውርን ይፋ ከተደረገበት ጊዜ አንስቶ እስከ የግንቦት ወር 2015 ዓ.ም. ድረስ 32.2 ሚሊዮን ደንበኞች አፍርቷል። - እስካሁን ከ375.2 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ግብይቶች (ትራንዛክሽንስ) ተፈፅሟል። - የነዳጅ ክፍያ በአስገዳጅነት በዲጂታል እንዲፈጸም ከተደረገበት ከሚያዝያ 16 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ 2.7 ቢሊዮን ብር ግብይት ተፈፅሟል። Via ሪፖርተር ጋዜጣ

"መለዮዬን ሳጠልቅ ቃሌን ሰጥቻት ነው!!!" ጉሮሮዬ በጥም ከስሎ ጠብታ ውሃ ብርቅ ሆኖብኝ የነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢን የስቃይ ቃተታ ደጋግሜ አይቼዋለሁ። አንጀቴ በረሃብ ታጥፎ ትጥቄ ከወገቤ እስኪላላ መፈተንንም በደንብ አውቀዋለሁ። ላቤ ተንጠፍጥፎ አልቆ በድካም ዝለት መናገር እስኪያቅተኝ መቃተትም ደጋግሞ ጎብኝቶኛል። በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮች አሳር በሚያበሉ በመሰናክል የተሞሉ ገጸ-ምድሮችን እግሬ እስኪዝል ኳትኜ አካልያቸዋለሁ። ሰውነቴ በጥይት አረር ተነድሎ ደሜ ተንዠቅዥቆ ያለቀ እስኪመስለኝ ከሞት ጋር ያፋጠጠኝ አጋጣሚም ብዙ ነው። እነዚህን ሁሉ ፈተናና መከራ በፅናት ያለፍኳቸው የተለየሁ ፍጡር ሆኜ አይደለም። አንድም የውትድርና ሞያዬ ያስገኘልኝ ጠንካራና ፈተናን ቀድሞ የቃኘ ስልጠና ስብዕናዬን በፅናት ገንብቶት ችግር የመጋፈጥ ብርታትን በትሩፋትነት ስለቸረኝ ሲሆን ሌላኛውና ወሳኙ የጽናት ምንጬ ደግሞ ገና ውትድርናን "ሀ" ብዬ ስጀምር መለዮዬን ሳጠልቅ እኔነቴን ሙሉ ለሙሉ ለኢትዮጵያ አሳልፌ የመስጠቴ ቃል - ኪዳን እያጀገነኝ ነው። ፈተናዎችን በማለፍ ድልን ደጋግሞ የማብሰር በግዳጅ የተሞላ ህይወቴን አብዝቼ እወደዋለሁ። ስለ ሀገሬና ህዝቤ ያለ አንዳች አድሎ ለመላው ኢትዮጵያዊ ዜጋ ሁሉ እኔነቴን አሳልፌ ሰጥቼ በሙሉ ጊዜዬ እውቀቴና ጉልበቴ ማገልገሌን ሳስብ ሙሉዕነት ይሰማኛል። እውነቴን ሳይረዳ አሊያም መረዳት ሳይፈልግ አለፍ ብሎም ኢትዮጵያንና ሠላምን የጠላ የሆነ ሰው በሞቀ ቤቱ ቁጭ ብሎ ስሜን ለማጠልሸት ቢዳዳ በጭራሽ ሆድ የሚብሰኝ አይደለሁም። ምክንያቱም እኔ የማደርገውን ጠንቅቄ የማውቅ የኢትዮጵያዬ ወታደር ነኝና። ወደፊትም ፈተናዎችን በጽናትና በጀግንነት ብሎም በጥበብና በዕውቀት ሰንጥቄ እያለፍኩ ሰላምን የማብዛት ተልዕኮዬን የመፈጸም ሂደቴ እስከወዲያኛው ይቀጥላል። ምክንያቱም ምንም ነገር ሳይበግረኝ ስለ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን ሰላም መጽናት እስከ ህልፈቴ በጽናት ለማገልገል ገና ከጅምሬ መለዮዬን ሳጠልቅ ቃሌን ለሀገሬ ሰጥቻለሁና ነው።      "ክብር ለሀገሬ መለዮ ለባሽ ይሁን"

የወሎ ልጅ አፍቅሬ የገጠምኳት ግጥም የሙሐባ ችግኝ የፍቅር አዝመራ፣ ደሴ ላይ ተዘርቶ ሐይቅ ላይ አፈራ። ውጫሌና እሮቢት ሊብሶን ይዞ ሐብሩ፣ ውብ ይወጣበታል ጋራው ሸንተረሩ። ጊራና ወርጌሳ ሐራና ወል
የወሎ ልጅ አፍቅሬ የገጠምኳት ግጥም የሙሐባ ችግኝ የፍቅር አዝመራ፣ ደሴ ላይ ተዘርቶ ሐይቅ ላይ አፈራ። ውጫሌና እሮቢት ሊብሶን ይዞ ሐብሩ፣ ውብ ይወጣበታል ጋራው ሸንተረሩ። ጊራና ወርጌሳ ሐራና ወልዴያ፣ የማይጠገበው የቆንጆ መብቀያ። መርሳ ራያ ቆቦ የጀግኖቹ መንደር በክፉ ለመጡ የማይደራደር። ኧረ ወሎ ወሎ ምድሩ ገደላማ፣ ያበቅላል ከስሩ አንገተ መለሎ አይነ ኮለምላማ። ኮምቦልቻና ባቲ ደጋንና ገታ፣ ደግነት ልምዳቸው ሳቅና ፈገግታ። ሐርቡና ከሚሴ ሚጢቆሎ አንቻሮ፣ ፍቅር በጅምላ ነው የለም በችርቻሮ። ተንታና መቅደላ ከላላ ወግዴ፤ ልቤ ናፍቆብኛል አልቀረም መሄዴ። አቃስታ ገነቴ ለሚና ቀይመብራት፣ ትዝታው ከመጣ አያስበላም እራት። ወረኢሉ ካቤ ጃማና ልጓማ፣ ያፈራል ሸበላ ቆንጆ ውብ አይናማ። መካነሰላምን የሸሆቹን አገር፤ አይቼው በመጣሁ ሂጄ በወፍ በረር። አጅባርና ማሻ ተንታና ደጎሎ፣ ልጆቹ ሸንቃጦች አንገተ መለሎ። ጉጉፍቱና ጊንባ አየረ ቀዝቃዛ፣ የሚታፈስበት ፍቅር እንደዋዛ። ዋድላና ደላንታ መገን ወገልጤና ሐገሩ እህል አብቃይ ሰው መልከቀና። ወረባቦን ብየ ልዝለቅ በቢስቲማ: ገደራ ነው ምንጩ ፍቅር ለተጠማ።

You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
You Tube ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉን🙏🇪🇹🙏 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://www.youtube.com/@theredtigers_4034

♥እናት ለዘላለም ትኑር!♥ ♥እናት የአለም መድሃኒት ነች‼️ ስለእሷ ለመግለፅ ለሁሉም በየትኛውም ቋንቋ ይከብዳል።ለዚህም ይመስላል "እናት ለዘላለም ትኑር" የሚለው ሃሳብ አብዝሃኞቻችንን የሚያግባባን።
እናት ለዘላለም ትኑር!♥ ♥እናት የአለም መድሃኒት ነች‼️ ስለእሷ ለመግለፅ ለሁሉም በየትኛውም ቋንቋ ይከብዳል።ለዚህም ይመስላል "እናት ለዘላለም ትኑር" የሚለው ሃሳብ አብዝሃኞቻችንን የሚያግባባን።የፍቅር ተምሳሌቷ፣ዝቅ ብላ ሠርታ ለልጇ ከፍታ የምትደክመዋ፣ቤትና ትዳሯን አክባሪዋ፣የአለም ጌጧ እናት ለዘላለም ትኑር‼ ♥የእናቶች ቀን እናቶችን፣ እናትነትን እና እናቶች በህብረተሰቡ ላይ ያላቸውን ተጽዕኖ የምናስብበት ቀን ነው።ዘመናዊው የእናቶች ቀን የተከበረው በ1908 እ.ኤ.አ. አና ጃርቪስ የተባለች ሴት እናቷን ለመዘከር ባዘጋጀቸው ዝግጅት ሲሆን ጃርቪስ ከዚያን ጊዜ አንስቶ የእናቶች ቀን በአሜሪካ እንዲታወቅ እና እንዲከበር የተለያዩ ቅስቀሳዎችን ማድረግ ጀመረች። ከ6 አመት በኋላ ውጤቱ ሰምሮላት በ1914 በዓሉ መከበር ጀመረ:: ♥በተለያዩ የአለም ክፍሎች በተለያየ ቀን ታስቦ የሚውለው ይህ በአል በሰኔ ወር ከሚከበረው የአባቶች ቀን ጋር ወላጅነትን የምናወድስበት ቀን ነው። በአሉ በዘመናዊነት በ አሜሪካ መከበር ከመጀመሩ በፊት በግሪክእና በሮም በተመሳሳይ ፌስቲቫሎች ይካሄዱ እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ። ክብር ለእናቶቻችን♥ ❤❤❤እ❤❤❤ና❤❤❤ት❤❤❤

ኢትዮጵያ ከብሪታንያ ጋር ሽብርተኝነትን ለመከላከል የ12 ሚሊዮን ዶላር ሰምምነት ተፈራረመች ብሪታንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሶስት የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ጋር ሽብርተኝነትን መከላከል ያለመ ስምምነትን ተ
ኢትዮጵያ ከብሪታንያ ጋር ሽብርተኝነትን ለመከላከል የ12 ሚሊዮን ዶላር ሰምምነት ተፈራረመች ብሪታንያ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከሶስት የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ጋር ሽብርተኝነትን መከላከል ያለመ ስምምነትን ተፈራርማለች። እንደ ቢቢሲ ዘገባ ይህ ስምምነት 12 ነጥብ 5 ሚሊዮን ዶላር በጀት የተመደበለት ሲሆን፤ ሀገራቱ በጋራ ሽብርተኝትን እንዲከላከሉ ያግዛል። በአፍሪካ ቀንድ ሽብርተኝነትን ለመከላከል ያግዛል የተባለው ይህ ስምምነት በተለይም ሀገራቱ በድንበሮች አካባቢ ጥብቅ ክትትል እና ቁጥጥር እንዲያደርጉ ያግዛል ተብሏል። የብሪታንያ ደህንነት ሚኒስትር ቶም ቱገንዳት ለቢቢሲ እንዳሉት ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ በሚደረግላቸው ድጋፍ የሽብርተኝነት መከላከያ ፖሊሲዎችን እና አሰራሮችን እንዲቀርጹ ይረዳቸዋል ብለዋል። ብሪታንያ በሽብርተኝነት ጉዳይ ከሶስቱ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ጋር እንዲህ አይነት የበጀት ድጋፍ ስታደርግ የመጀመሪያዋ ነው የተባለ ሲሆን በበጀት ድጋፉ በድንበሮቻቸው አካባቢ ያለውን የደህንነት ስጋት እንዲቆጣጠሩ ያደርጋል ተብሏል። የሶስቱ ሀገራት የድንበር አካባቢዎች ጥብቅ ቁጥጥር አይደረግባቸውም የተባለ ሲሆን ቴክኖሎጂ እና የሰለጠነ የሰው ሀይል ደግሞ ድንበሮቹን መቆጣጠር እንዳይችሉ ያደረጉ ምክንያቶች እንደነበሩ በዘገባው ላይ ተጠቅሷል። ለቁጥጥር አስቸጋሪ ናቸው የተባሉ የኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ የድንበር አካባቢዎች ላይ ውጤታማ የአስተዳድር ስርዓት አለመዘርጋታቸው ለደህንነት ስጋቱ ሌላኛው ምክንያት ነውም ተብሏል። በነዚህ ምክንያቶችም አልሻባብ እና ሌሎች የሽብር ቡድኖች ጥቃቶችን እንዲያደርሱ አድርጓል ያሉት የብሪታንያ ደህንነት ሚኒስትር ብሪታንያ በምታደርገው ድጋፍ መሰረት በድንበሮች አካባቢ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የጸጥታ ስራዎችን መስራት እንደሚያስችልም ተናግረዋል።