es
Feedback
ሕይወተ ወራዙት (የወጣቶች ሕይወት)

ሕይወተ ወራዙት (የወጣቶች ሕይወት)

Ir al canal en Telegram

✝️ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ወጣቶች ታስቦ ከተለያዩ መጻሕፍት እና ማሕበራዊ ድኅረ ገጾች የተገኙ ሕይወት ተኮር መንፈሳዊ ጽሑፎች የሚለቀቁበት ጦማር ነው። #ገጹን_በማጋራት_አገልግሎቱን_እንደግፍ።🙏

Mostrar más
457
Suscriptores
+124 horas
Sin datos7 días
-130 días
Archivo de publicaciones
#ፀሎት_የነፍስ_መብራት.......... ፀሎት የነፍስ መብራት ነው። እውነተኛ የሆነ እግዚአብሔርን ማወቅ ነው። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለም አስታራቂ ሽማግሌ ነው። ፀሎት በቃላት ሊገለጽ የማይ
#ፀሎት_የነፍስ_መብራት.......... ፀሎት የነፍስ መብራት ነው። እውነተኛ የሆነ እግዚአብሔርን ማወቅ ነው። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለም አስታራቂ ሽማግሌ ነው። ፀሎት በቃላት ሊገለጽ የማይቻለውን እግዚአብሔርን ለማቀፍ እጆችን የሚያዘረጋ፣ ነፍስንም ወደ ገነት መዐዛ የሚስብና የሚያነሳሳ ነው። ወተት ፍለጋ አምርሮ እንደሚያለቅስና የእናቱን ጡቶች እንደሚሻ ህፃን ልጅ እግዚአብሔርን መሻት ነው። ፀሎት ስዕለትን የሚሞላ፣ ከሁሉ የሚሻል ያልታየና ያልተሰማ ድንቅ ስጦታንም የሚያሰጥ ነው። #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ @kidyeeee @kidyeeee

ሰው ሆይ! የሚጎዳህ ሀብትህ አይደለም፣ ድኽነትህም አይደለም። ሰው የሚጎዳው ክፉ ልብ ነው። ክፉ ልብ ደግሞ በሀብትም ሀብት በማጣትም የሚመጣ አይደለም። ክፉ ልብ ሌሎች ክፉ ልቦች ይወልዳል። እሳት እሳትን እየወለደ ብዙ ዕንጨቶችን እንደሚበላ ኹሉ ክፉ ልብም እንደዚህ ነው። አንተ ሰው! ይህን ማወቅ ትወዳለህን? ክፉ ምግባር ወይም በጎ ምግባር በተፈጥሮ የሚገኙ አይደሉም። እነዚህ ኹለቱ ከክፉ ልብ ወይም ከመልካም ልብ የሚገኙ ናቸው። @kidyeeee @kidyeeee @kidyeeee (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - አምስቱ የንስሐ መንገዶች ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)

“ፆም የፀሎት ምክንያት ናት፤ የፀጋ ዕንብ መገኛ ናት አርምሞን የምታስተምር ናት፤ ለበጎ ስራ ሁሉ ታነቃቃለች፤ የፀዋሚ ስጋው ምንጣፉን አንጥፎ ሌሊቱን ሁሉ ተኝቶ ማደር አይቻለውም በምን ጎኑ ይተኛዋል? ሰው አብዝቶ በፆመ ያህል በዚህ መጠን በትህትና ሁኖ እያለቀሰ ይፀልያል፤ ፀሎታት ከልቡናው ይታሰባሉ አንድም ፀሎተ ልብ ይሰጠዋል፤ በፊቱ የትእግስት ምልክት ይታያል በሃጢአቱ ያዝናል ክፉ ህሊና ይርቅለታል የበጎ ነገር መገኛ መከማቻ በምትሆን በፆም ይኖራልና፤ ፆምን የናቀ ያቃለለ ሰው በጎውን ነገር ሁሉ ከራሱ አራቀ፡፡” @kidyeeee @kidyeeee @kidyeeee ማር ይስሃቅ ከቤተ ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ ቻናል የተወሰደ።

"ከባልንጀራህ ፍቅርን አትጠይቅ፤ ከጠየቅክ እሱ የማይመልስልህ ከሆነ ትጨነቃለህ፤ ይልቁንም ለባልንጀራህ ያለህን ፍቅር አሳይ ዕረፍት ትሆናለህ፣ ባልንጀራህንም መውደድ ታደርጋለህ።" @kidyeeee @k
"ከባልንጀራህ ፍቅርን አትጠይቅ፤ ከጠየቅክ እሱ የማይመልስልህ ከሆነ ትጨነቃለህ፤ ይልቁንም ለባልንጀራህ ያለህን ፍቅር አሳይ ዕረፍት ትሆናለህ፣ ባልንጀራህንም መውደድ ታደርጋለህ።" @kidyeeee @kidyeeee 🙏የጋዛ ቅዱስ ዶሮቴዎስ🙏

🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹✨✨✨ፍቅርን የያዘ ሰው ሙት ከሚያነሣ ይበልጣል (ዘሰ የዐቅባ ለፍቅር ውእቱ የዐቢ እምአለ ያነሥኡ ሙታነ) ማለትም ፍቅርን ገንዘብ ያደረገ ምውት ከሚያነሱ ድውይ ከሚ
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹✨✨✨ፍቅርን የያዘ ሰው ሙት ከሚያነሣ ይበልጣል (ዘሰ የዐቅባ ለፍቅር ውእቱ የዐቢ እምአለ ያነሥኡ ሙታነ) ማለትም ፍቅርን ገንዘብ ያደረገ ምውት ከሚያነሱ ድውይ ከሚፈውሱ ከጴጥሮስና ከጳውሎስ አያንስም።እንዳለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ። ✨✨ጌታም የእኔ ደቀመዛሙርት እንደኆናችሁ ፍቅርን ብትይዙ ሁሉ ያውቃቹኋል አለ እንጂ ሙት ብታስነሱ ድውይ ብትፈሱ አላለም። ✨ፍቅርም፦ ባዕድ፣ዘመድ፣ደሃ፣ባለጸጋ፣ጠላት፣ወዳጅ፣አዋቂ፣አለዋቂ ሳይሉ ሳይለያዩ ነው።(አፍቅር ኩሉ ከመ አኃዊከ) ሁሉንም  እንደ ወንድሞችህ ውደድ። እንዳለ ቅዱስ ወንጌል። ✨ፍቅርን የያዘ ሰው፦ጌታ አምላኩ የማይወደውን ሥራ አይሰራም፤፤ወንድሙን(እኅቱን) አያሳዝንም፤፤የሚወደውን የጌታው ትዕዛዝ በማይረባ ባልንጄራው ምክር ዳግመኛ አያፈርስም፤፤ ለክርስትና (ለተወለደባት ቤተ-ክርስቲያን እናቱ) ፊቱን እንጂ  ጀርባውን አይሰጥም፤በሚያልፈው ዓለም ምናምንቴ የማያልፈውን ዓለም አይቀይርም። ምክንያቱም ፍቅር ማለት ክርስቶስ ነው!! @kidyeeee @kidyeeee @kidyeeee ምንጭ፦ ቃለ-ምዐዳን በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገ/ኪዳን

ብልጡ_ዲያብሎስ "ከዲያብሎስ ዘዴዎች አንዱ በመከራችን ሰዓት እንድንፈዝ ማድረግ ነው፡፡በዚህ ጊዜ በእግዚአብሔር ላይ ያለን ተስፋ ይሟጠጣል፡፡ እግዚአብሔር በእርሱ ተስፋ የምታደርገውን ነፍስ እግዚአብሔ
ብልጡ_ዲያብሎስ "ከዲያብሎስ ዘዴዎች አንዱ በመከራችን ሰዓት እንድንፈዝ ማድረግ ነው፡፡በዚህ ጊዜ በእግዚአብሔር ላይ ያለን ተስፋ ይሟጠጣል፡፡ እግዚአብሔር በእርሱ ተስፋ የምታደርገውን ነፍስ እግዚአብሔር አይረዳኝም እስክትል ድረስ በመከራ እንድትንገላታ አይተዋትም፡፡" #አባ_መቃርዮስ " እግዚአብሔርን በተስፋ ለሚጠብቁት ለምትሻውም ነፍስ መልካም ነው።" (ሰቆቃው ኤርምያስ 3፥25) @kidyeeee @kidyeeee ከኤሊ ኤዜር ቻናል የተወሰደ።

-----------------------()------------------------- ያለርሱ፡ፈቃድ፡የበላ፡ደስ፡ብሎትም፡ተድላን፡የቀመሰ፡ማን፡ነው።ርሱም፡ደስ፡ለሚያሠኘው፡ሰው፡ጥበብንና፡ዕውቀትን፡ደስታንም፡ይሰጠዋል፤ለኀጢአተኛ፡ግን፡እግዚአብሔርን፡ደስ፡ለሚያሠኘው፡ሰው፡ይሰጥ፡ዘንድ፡እንዲሰበስብና፡እንዲያከማች፡ጥረትን፡ይሰጠዋል።ይህም፡ደግሞ፡ከንቱ፡ነፋስንም፡እንደ፡መከተል፡ነው። --------------------()-------------------- 💙 መክ. ም:2 ቁ:25-26 💙

~ እግዚአብሔር መንፈስ ነውና ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ባለበት #ነጻነት አለ።እኛስ ሁላችን ፊታችንን ገልጠን በመስተዋት እንደሚያይ የእግዚአብሔርን ክብር እናያለን ፤ #ከእግዚአብሔር_መንፈስ_እንደ_ተሰጠን_መጠን_የእርሱን_አርአያ_እንመስል_ዘንድ_ከክብር_ወደ_ክብር_እንገባለን። ~~~~ 💙2ኛ ቆሮ. ም፡፫ ቁ፡፲፯-፲፰💙

💙ቅዱስ ሚካኤል ሆይ በእውነት አንተ ያልረዳኸው ማን አለ??🥺✨✨✨ ወጣቱን ባሕራን የሞቱን ደብዳቤ ለውጠህ ለሕይወት እንዳደረግሕለት ፣ የቅድሰት ሀገር ኢትዮጵያን፤ የቅድሰት ቤተክርስቲያንን የሞት
💙ቅዱስ ሚካኤል ሆይ በእውነት አንተ ያልረዳኸው ማን አለ??🥺✨✨✨ ወጣቱን ባሕራን የሞቱን ደብዳቤ ለውጠህ ለሕይወት እንዳደረግሕለት ፣ የቅድሰት ሀገር ኢትዮጵያን፤ የቅድሰት ቤተክርስቲያንን የሞት ደብዳቤ ወደ ሕይወት ለውጥልን።🙏 ቅድስት አፎምያን በሃይማኖት እንዳጸናሃት ከክፉ ዲያብሎስ ወጥመድ እንዳወጣኻት እኛንም ከሀጢአት ወጥመድ አድነን።በቸርነት ለመንግሥቱ እንዲያበቃን በእግዚአብሔር ፊት የምትቆም ርኅህሩህ መልአክ ለምንልን።🙏 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 💙፲፪🙏🌹

#ዝም_ብለህ_አመስግን🙏 "ወዳጄ ሆይ! በጎ ነገር አግኝተህ እንደ ኾነ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያም በጎ ነገር ከአንተ ጋር ጸንቶ ይኖራል፡፡ በጎ ያልኾነ ነገር ደርሶብህ እንደ ኾነም እግዚአብሔርን
#ዝም_ብለህ_አመስግን🙏 "ወዳጄ ሆይ! በጎ ነገር አግኝተህ እንደ ኾነ እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያም በጎ ነገር ከአንተ ጋር ጸንቶ ይኖራል፡፡ በጎ ያልኾነ ነገር ደርሶብህ እንደ ኾነም እግዚአብሔርን አመስግን፤ ያም በጎ ያልኾነ ነገር ወደ በጎ ነገር ይቀየራል፡፡" 💙ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ💙

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ "ጥሩ ያለሆኑ ሐሳቦች መጀመሪያ ወደ አእምሮ ሲመጣ ደካማ ስለሚሆን ወዲያውኑ ማጥፋት ይገባል። ከተቀበሉትና በስሜታዊነት ከያዙት ግን እስከ ልቦና ድረስ ዘልቆ በመግባት ከስሜት ጋር ተ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ "ጥሩ ያለሆኑ ሐሳቦች መጀመሪያ ወደ አእምሮ ሲመጣ ደካማ ስለሚሆን ወዲያውኑ ማጥፋት ይገባል። ከተቀበሉትና በስሜታዊነት ከያዙት ግን እስከ ልቦና ድረስ ዘልቆ በመግባት ከስሜት ጋር ተቀላቅሎ ውስጣዊ ፈተና ያመጣል። ከዚያም በኋላ ከሕሊና ለማስወጣት ያስቸግራል። ቅዱስ ድቅስዮስ 'ትንሽ ችግኝን መንቀል ቀላል ነው፤ ነገር ግን ዋርካ (ዛፍ) እስኪሆን ድረስ ችላ ብትለው ለመንቀል ያስቸግራሃል' ያለው ለዚያ ነው" @kidyeeee @kidyeeee 🕯ከመንፈሳዊ ተጋድሎ መጽሐፍ🕯 @kidyeeee ከአፈ በረከት... ቻናል የተወሰደ።

ተአምራትን ማድረግ ትፈልጋለህን?    እንኪያስ በዘፈን የደነቆረን ጆሮ መዝሙር እንዲሰማ አድርገው። በስርቆት የሰለለውን እጅ በምጽዋት እንዲዘረጋ አድርገው።ወደ ኃጢአት ቤት በመኼድ ሽባ የኾነውን እግር ወደ እግዚአብሔር ቤት እንዲሮጥ አድርገው።ሐሜት በማውራት ዲዳ የኾነውን ከንፈር መልካም ንግግር እንዲናገር አድርገው።ከተአምራት ኹሉ የበለጠ ተአምር ይኼ ነውና።   #ቅዱስ_ዩሐንስ_አፈወርቅ አምስቱ የንስሐ መንገዶች ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።

✨ርሱ፡ስለ፡እናንተ፡ያስባልና፥የሚያስጨንቃችኹን፡ዅሉ፡በርሱ፡ላይ፡ጣሉት።በመጠን፡ኑሩ፡ንቁም፥ባላጋራችኹ፡ዲያብሎስ፡የሚውጠውን፡ፈልጎ፡እንደሚያገሣ፡አንበሳ፡ይዞራልና፤ በዓለም፡ያሉት፡ወንድሞቻችኹ፡ያን፡መከራ፡በሙሉ፡እንዲቀበሉ፡እያወቃችኹ፡በእምነት፡ጸንታችኹ፡ተቃወሙት።በክርስቶስ፡ኢየሱስ፡ወደዘለዓለም፡ክብሩ የጠራችኹ፥የጸጋ፡ዅሉ፡አምላክ፥ለጥቂት፡ጊዜ፡መከራን፡ከተቀበላችኹ፡በዃላ፥ራሱ፡ፍጹማንያደርጋችዃል፥ያጸናችኹማል፥ያበረታችኹማል።✨        💙 1ኛ ጴጥ 5፥7-10 💙

አቤቱ አምላኬ ሆይ ነፍሴ አንተን ተጠማች...በፊትህ ዝም ብዬ ያለ ሀሳብ እምቆምበትን ቀን ናፈቅሁ...ያለ ጥያቄ አንተን ብቻ ለማመስገን የምቆምበት ቀን ራቀኝ....ጌታ ሆይ አሁን የእኔ የምለው አቅም የለኝም አንተ በወደድከው ምራኝ... ~ነግድ ወፈላሲ~

~ጌታ ሆይ በድለናል ይቅር በለን።እስከመቼ ለአሕዛብ ትተወናለህ።አቤቱ ሕዝቦችህን አስበን የሚያስጨንቁን በእኛ ላይ ተነሳስተውብናልና።~
~ጌታ ሆይ በድለናል ይቅር በለን።እስከመቼ ለአሕዛብ ትተወናለህ።አቤቱ ሕዝቦችህን አስበን የሚያስጨንቁን በእኛ ላይ ተነሳስተውብናልና።~

ሕይወተ ወራዙት (የወጣቶች ሕይወት) - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @kidyeeee