es
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Ir al canal en Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Mostrar más
637
Suscriptores
-124 horas
-47 días
-1230 días
Archivo de publicaciones
❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ #የባረከ_የየካቲት_ወር_መዓልቱ_ዐሥራ_አንድ ሰዓት ነው ከእግዲህም ይጨምራል።           ❤ #የካቲት ፩ (1) ቀን። ❤ እንኳን #በታላቁ_ቴዎዶስዮስ_ዘመነ_መግሥት በቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት ስለሆነው የክብር ባለቤትን የሆነ መንፈስ ቅዱስን በከፋች ኀሳቡ ፍጡር ነው ስለ ብሎ ስለ ካደው ስለ መቅዶንዮስ፣ አንድ ገጽ ስለሚሉ ስለ ሰባልዮሳውያንና ወልድ ከብቻው ሥጋ በቀር ነባቢት ለባዊት ነፍስን አልነሣም መለኮቱ በነፍስና በልቡና ፈንታ ሆነው ስለሚሉ ስለ አቡሊናርዮሳውያን #መቶ_ኃምሳ_ኤጲስቆጶሳት_በቊስጥንጥንያ_ከተማ_381ዓ.ም_ተሰብስበው_ሦስቱንም መናፍቃን_ላወገዙበት_ቅድስት_ተዋሕዶ_ሃይማኖትን_ላጸኑበትና በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ መንግሥት በሰማዕትነት ለሞተ ከሀዲ አርዮስም ላወገዘ ለሰማዕታትም ፍጻሜ ለሆነ ለሊቀ ጳጳስ #ለቅዱስ_ጴጥሮስ ቤተ ክርስቲያን ለከበረችበት በዓል በሰላም አደረሰን። ከእነዚህ ቅዱሳን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                         ✝ ✝ ✝ ❤ #የከበሩ_የመቶ_ሃምሳ_ኤጲስቆጶሳት_ስብሰባ #በቊስጥንጥንያ_ከተማ_በታላቁ_ቴዎዶስዮስ_ዘመነ_መንግሥት_መደረግ፦ ስብባቸውም የሆነው በቊስጥንጥን አገር ላይ ሊቀ ጳጳሳት ስለ ሆነው የክብር ባለቤት የሆነ መንፈስ ቅዱስን በከፋች ኀሳቡ ፍጡር ነው ብሎ ስለ ካደው ስለ መቅዶንዮስ ሁለተኛም አንድ ገጽ ስለሚሉ ስለ ሰባልዮሳውያን ሦስተኛም ወልድ ከብቻው ሥጋ በቀር ነባቢት ለባዊት ነፍስን አልነሣም መለኮቱ በነፍስና በልቡና ፈንታ ሆነው ስለሚሉ ስለ አቡሊናርዮሳውያ ነው ❤ የእሊህ ከሀድያንም ስሕተት ግልጽ በሆነ ጊዜ አሰባስቦ የአንድነት ጉባኤ ያደርግላቸው ዘንድ ንጉሥ ቴዎዶስዮስን ለመኑት እርሱም ቃላቸውን ተቀብሎ ወደ ሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ኢየሩሳሌምም ሊቀ ጳጳሳትም መልክትን ላከ ምሁራን  የሆኑ ኤጲስቆጶሶቻቸውንም ይዘው እንዲመጡ አዘዛቸው እሊህም አባቶች በቊስጥንጥንያ ከተማ ተሰብሰቡ የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ግን አልመጣም ምሁራን የሆኑ ሰዎችን ላከ እንጂ ከእርቸውም ጋር በእጁ የጻፋትን ደብዳቤ ላከ። ❤ የጉባኤውም ሊቀ መንበር የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ጢሞቴዎስ ነው መቅዶንዮስንም ጠርቶ የረከሰች ሃይማኖቱን ይናገር ዘንድ አዘዘው ያ ከሀዲም "እንደ ፍጥረቶች ሁሉ መንፈስ ቅዱስ የተፈጠረ ነው" አለ። ጢሞቴዎስም መልሶ "መንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ሕይወቱ እንደሆነ አታውቅምን የእግዚአብሔርን ሕይወት እንዴት ፍጡር ታደርገዋለህ አሁንም ከዚች ከረከሰች ሃይማኖትህ ተመለስ ወደ ዘላለማዊ እሳት ገሃገም ከመግባትህ በፊት ንስሓ ግባ" አለው። እርሱ ግን ሰምቶ አልተመለሰም እነርሱም አወገዙት ከሹመቱም ሻሩት ከቤተ ክርስቲያንም አሳደዱት። ❤ ከዚህም በኋላ ሰባልዮሳውያን ጠርቶ "እናንተስ ስለ ሃይማኖታችሁ ምን ትላላችሁ ተናገሩ" አላቸው። እነርሱም "አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ገጽ አንድ ህላዌ ነው በምንም በምን ሦስት አይሆንም" አሉ። አባ ጢሞቴዎስም መልሶ እንዲህ አላቸው "በዮርዳዮስ ውስጥ ወልድ ቁሞ ሳለ በፀዓዳ ርግብ አምሳል መንፈስ ቅዱስ ወርዶ በራሱ ላይ የተቀመጠ አብም ከደመና ውስጥ ሁኖ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ብሎ አሰምቶ ተናገረ ያለው የወንጌል ቃል ተሻረን? እናንተ እንደምትሉት ከሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የተጠመቃችሁት የክርስትናችሁ ጥምቀት ተሽሮአል አሁንም ክህደታችሁን ተዉ ብትመለሱም ይሻላችኋል። አርዮስም አስቀድሞ ወልድን ካደው ይህ መቅዶንዮስም መንፈስ ቅዱስን ካደው እናንተም የእነርሱ ተሳታፊዎች ሆናችሁ"። እነርሱም ሰምተው አልተመለሱም የአንድነት ጉባኤም አውግዞ ከምእመናን አድንነት ለያቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ ወልድ ነባቢት ለባዊት የሆነች ነፍስን አልነሳም ሥጋን ብቻ እንጂ የሚለውን አቡሊናርዮስን ትምህርት አወገዙ። እሊህ መቶ ኃምሳ የሆኑ ኤጲስ ቆጶሳት አባቶቻችንም በጸሎተ ሃይማኖት ላይ "ጌታ አዳኝ በሚሆን ከአብ በሠረፀ በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እንሰግድለት እናመሰግነውም ዘንድ ከአብና ከወልድ ጋራ በነቢያት አድሮ የተናገረ" የሚለውን ጨመሩ። ❤ ከሁሉ በላይ በምትሆን ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እናምናለን። ኃጢአትን ለማስተስረይ በአንዲት ጥምቀት እናምናለን። የሙታንም መነሣት የሚመጣውንም ሕይወት ለዘላለሙ ተስፋ እናደርጋለን። ሃይማኖታቸው የቀና ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት አባቶቻችን የተናገሩት ለመንግሥቱ ፍጻሜ የለውም እስከሚል ነው። እሊህ መቶ ኃምሳው አባቶች የሰበሰቡት ስለ መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ስለርሱ የእርሱን ነገር አብራሩ። ለእርሱም ምስጋና ይሁን የአባቶቻችንም በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                                                     ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ሣህሉ ለእግዚአብሔር መልአ ምድረ። ወበቃለ እግዚአብሔር ፀንዐ ሰማያት። ወእምእስትንፋሰ አፋሁ ኵሉ ኃይሎሙ"። መዝ 32፥5-6 ወይም መዝ 72፥7-8። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 15፥17-26 ወይም ማቴ 12፥31-38።                  

"ከአባቶችህ ጋር ትኖር ዘንድ ወደ ገዳምህ ተመለስ" የሚል ቃል መጣ፡፡ በተመለሰም ጊዜ አቡነ አክርስጥሮስ በሰላም ዐረፈ፡፡                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ሰማዕቷ_ቅድስት_ጤቅላ፡- ጤቅላ ማለት "ልጅ፣ ለግላጋ" ማለት ነው፡፡ ቅድስት ጤቅላና ከእርሷ ጋር የነበሩ አራት ደናግል ጥር 30 ቀን ፎላ በሚባል ኃጥእ ቄስ እጅ ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ፡፡ ይህም ፎላ የተባለ ቄስ በአመጽ የሰበሰበው ብዙ ገንዘብ እንዳለው በከሃዲው መኰንን ዘንድ ነገሩበት፡፡ ስለዚህም መኮንኑ ገንዘቡን ሁሉ እንዲወርሱ አዘዘ፡፡ ፎላም ወደ መኰንኑ ዘንድ በመሄድ ገንዘቡን ይመልስለት ዘንድ ቢለምነው እምቢ አለው፡፡ ከሃዲው መኰንንም ስለ እነቅድስት ጤቅላ የምግባር የሃይማኖታቸውን ዜናቸውን በሰማ ጊዜ ወደ እርሱ እንዲያመጧቸው አዘዘና አስመጣቸው፡፡ ጌታችንን አስክዶ እምነታቸው አውጥቶ ለጣዖት እንዲገዙ ግድ አላቸው፡፡ እነርሱ ግን በእምነታቸው በጸኑ ጊዜ መኰንኑ ፎላንን ጠርቶ "እነዚህ ደናግል ለፀሐይ ይሰግዱ ዘንድ እነርሱን ብትሸግልልኝ ገንዘብህን መልሼ እሰጥሃለሁ" አለው፡፡ ፎላንም እነ ቅድስት ጤቅላን ይሸነግላቸው ጀመረ፡፡ ደናግሉም "አንተ የሰይጣን ልጅ የክብር ባለቤት ክርስቶስን እንክው ዘንድ እንዴት ትፈትነናለህ? አንተ ቀድሞ መምህራችን የነበርክ ስትሆን" ብለው ዘለፉት፡፡ መኰንኑም ይህን ቃላቸውን ከአንደበታቸው በሰማ ጊዜ በጅራፍ ጽኑ ግርፋትን አስገረፋቸው፡፡ እነዚህ ቅዱሳት ደናግል ግን ስለ ጌታችን ይመሰክሩ ነበር እንጂ ምንም አልፈሩም ነበር፡፡ መኰንኑም ፎላንን "የበከተ ብትበላ ደምንም ብትጠጣ ገንዘብህን እመልስልሃለሁ" ባለው ጊዜ እንዳለው አደረገ፡፡ ዳግመኛም "እነዚህን ደናግል ብትገድላቸው ገንዘብህን እመልስልሃለሁ" አለው፡፡ ፎላም ይህን በሰማ ጊዜ እንደ አስቆሮቱ ይሁዳ ልቡ በገንዘብ ፍቅር ተነድፏልና ልቡናውን አጽንቶ ቅዱሳት ደናግሉን ሊገድላቸው ሄደ፡፡ እነርሱም እንዲህ አሉት፡- "ከሃዲ ሆይ የመድኃኒታችንን የክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን በእጅህ ታቀበን አልነበረምን? ስለ ገንዘብ ፍቅር ብለህ እኛን የክርስቶስን በጎች ልታርድ መጣህን?" እያሉ በገሠጹት ጊዜ ሰልፍ እንደተማረ አርበኛ ሰው ሆኖ በሰይፍ ራስ ራሶቻቸውን ቆረጣቸው፡፡ መኰንኑም የፎላንን ብላሽነትና ድንቁርናውን አይቶ ወዲያው በሰይፍ ገደለው፡፡ ፎላም ገንዘቡን፣ ሃይማኖቱንና ነፍሱን አጣ፡፡ የእነዚህም ቅዱሳት ደናግል ስማቸው መሪ የሆነቻቸው ጤቅላ፣ ማርያ፣ ማርታ፣ አመታ፣ አበያ ሲሆን ጥር 30 ቀን ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመው የክብር አክሊልን ተቀዳጅተዋል፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን በአባ ጎርጎርዮስና አቡነ አክርስጥሮስ በቅድስት ጤቅላ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር30 ስንክሳር።                                                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወይወስዱ ለንጉሥ ደናግል ድኅሬሃ። ወቢጻሂ ይወስዱ ለከ። ወይወስድዎን በትፍሥሕት ወበኃሤት"። መዝ 44፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 5፥1-7፣ 1ኛ ጴጥ 5፥2-5 እና የሐዋ ሥራ 9፥37-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 23፥26-32። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታች የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የማኅበረ ጻድቃን (ዴጔ) በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                   

                          ✝ ✝ ✝ ❤ #ታላቋ_ሰማዕት_ቅድስት_ኦርኒ፡- ይኽችም ቅድስት ስሙ መርቅያኖስ የሚባል ለጣዖት የሚሰግድ የሮሙ ንጉሥ ልጅ ናት፡፡ እናቷ ግን ክርስቲያናዊት ናት፡፡ ንጉሡ አባቷም እልፍኝ አሠርቶላት በወርቅና በብር አስጊጦ ከ12 ደናግል ጠባቂዎች ጋር ወደዚያ አስገባት፡፡ ከዚያም ልጁ ኦርኒና ደናግሉ ይሰግዱላቸው ዘንድ 17 ጣዖታትን አመጣላቸው፡፡ ቅድስት ኦርኒም ሰባት ዓመት በዚያ ስትቆይ ወደ እግዚአብሔር ከመጸለይ አላቋረጠችም ነበር፡፡ ❤ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ዐይኖቿን አቅንታ ስትጸልይ በአፏ የዘይት ቅጠል የያዘች ርግብን አየች፡፡ ርብቧም ቅጠሉን ከማዕዷ ላይ ጥላው ወጣች፡፡ ዳግመኛም ወደ ቅድስት ኦርኒ ወደ ምዕራብ ስትመለከት በአፉ ከይሲ የያዘ ቁራ መጥቶ በመዕዷ ላይ ጥሎት ሄደ፡፡ መምህሯም በመጣ ጊዜ ያየችውን ራእይ ነገረችው፡፡ እርሱም ሲተረጉምላት "ርግብ የጥበብ ነገር ነው፣ የዘይቱም ቅርንጫፍ በጥምቀት የሚገኝ ክብር ነው፣ ቁራውም ንጉሥ ነው፣ ከይሲውም መከራ ነው፣ አንቺም በርቺ ጠንክሪ በክርስቶስ ስም መከራ ትቀበይ ዘንድ አለሽና የሕይወትንም አክሊል ትቀበያለሽ" አላት፡፡ ❤ ቅድስት ኦርኒ ዕድሜዋ ከፍ ሲል ወላጆቿ ከታላላቅ ወገን ለሆነ ለከበረ ሰው ሊድሯት አሰቡ እርሷ ግን "ሰባት ቀን ታገሱኝ" አለችና ወደ ፈቀደው መንገድ እንዲመራት እግዚአብሔርን በጸሎት ጠየቀች፡፡ በዚህም ጊዜ የታዘዘ መልአክ መጥቶ "ኦርኒ ሆይ በርቺ፣ ኃይልንም ልበሺ፣ ሐዋርያው ጢሞቴዎስ ወዳንቺ መጥቶ የወንጌልን ትእዛዝ ያስተምርሻል፣ ያጠምቅሻል" አላት፡፡ ወዲያውም ሐዋርያው ቅዱስ ጢሞቴዎስ መጥቶ የቤቷን ግድግዳ ሰንጥቆ ገብቶ ሁሉንም ነገር አስተማራት፡፡ ከቆመበትም መሬት ውኃ አፍልቆ በውኃው ላይ ጸልዮ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃትና ከእርሷ ዘንድ ሄደ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ቅድስት ኦርኒ ተነሥታ የአባቷን ጣዖቶች ሰባበረቻቸው፡፡ አባቷም መጥቶ ይህን ባየ ጊዜ በንዴት ወዲያው ሊድራት ሞከረ፡፡ እርሷ ግን "እኔስ ለሰማያዊው ሙሽራ ለክርስቶስ ተጠርቻለሁ፣ በስሙም ተጠምቄያለሁ" አለችው፡፡ ንጉሡ አበቷም የቅድስት ኦርኒ ንግግር በሰማ ጊዜ ታላቅ ቁጣን ተሞልቶ ከእልፍኟ እየጎተተ አወረዳት፡፡ ክርስቲያናዊት እናቷም ይህንን ስታይ እያለቀሰች በራሷ ላይ አመድ ነሰነሰች፡፡ አባቷም ታስረው ይቀለቡ የነበሩ 4 ኃያላን ፈረሶችን አምጥቶ የቅድስት ኦርኒን ፀጉር ከጅራታቸው ጋር አሥሮ እንዲጎትቷትና ሰውነቷ ተቆራርጦ እንዲያልቅ ፈረሶቹን አስሮጣቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አንዱ ፈረስ ሲሮጥ ሰንሰለቱን በጥሶ ሲያመልጥ የንጉሡን ቀኝ እጅ ቆረጠውና አባቷ ወዲያው ሞተ፡፡ የከበረች ቅድስት ኦርኒ ግን ተነሥታ ጸሎት በማድረግ ንጉሥ አባቷን ከሞት አስነሣችው፡፡ የተቆረጠ እጁንም እንደቀድሞው አድርጋ መለሰችለት፡፡ ሕዝቡም ይህንን ድንቅ ተአምር አይተው ከንጉሡ አባቷ ጋር በጌታችን አምነው ተጠመቁ፡፡ በዚህም የቅድስት ኦርኒ ተአምር ምክንያት የተጠመቁት ሰዎች ቁጥር ከሰላሳ ሺህ በላይ ነው፡፡ ❤ ንጉሥ ዳኬዎስም ይህን ተአምርና የቅድስት ኦርኒ ዜና ስለሰማ ወደዚያች አገር ገባ፡፡ የከበረች ቅድስት ኦርኒንም ይዞ በራሷ ፀጉር ሰቀላትና አሠቃያት፡፡ ዳግመኛም መርዛማ እባቦችና ጊንጦች ወደተሞሉበት ጉድጓድ ውስጥ ጨመራት፣ ነገር ግን መርዛማ እባቦቹና ጊንጦቹ በእግዚአብሔር ኃይል ሁሉም ወዲያው ሞቱ፡፡ ዳግመኛም ንጉሥ ዳኬዎስ በመጋዝ ይሰነጥቋት ዘንድ አዘዘ፤ እንዳዘዘውም ሊያደርጉባት ሲሉ መጋዙ ተሰበረ፡፡ ንጉሡም ወዲያው በሞት ተቀሰፈ፡፡ የዳኬዎስ ልጅም ይህን ሰምቶ በታላቅ ሆኖ መጣና አገሪቱን ከበባት፡፡ ቅድስት ኦርኒንም ይዞ የተሳሉ ወስፌዎችን በእጆቿና በእግሮቿ እንዲሰገሰጉ አደረገ፡፡ በጀርባዋም ላይ አሸዋ የተመላ ዳውላ አድርገው ከአራት ፈረሶች ላይ አስረው ሥጋዋ ተበጣጥሶ እስኪጠፋ ድረስ ፈረሶቹን አስሮጧቸው፡፡ በዚህም አልቻሏትም፤ የታዘዘ መልአክ መጥቶ እርሷ ከፈወሳት በኋላ የዳኬዎስን ልጅ በጦር ወግቶ ገደለው፡፡ ❤ የከበረች ቅድስት ኦርኒም ሃይማኖትን እያስተማረች፣ ድውያንን እየፈወሰች፣ ሙታንን እያስነሣች በታላቅ አገልግሎት ተቀመጠች፡፡ ከዚህም በኋላ 4ኛ ንጉሠሥ መጣና የእርሷን ዜና ሰምቶ ወደ እርሱ አስመጣት፡፡ ለጣዖትም እንድትሰግድ ባስገደዳት ጊዜ ጣዖቱቹንና እርሱን ረገመቻው፡፡ ንጉሡም በዚህ ተናዶ ከእሳት ውስጥ ጨመራት፡፡ እርሷም ከእሳቱ ውስጥ ሆና ስትጸልይ የታዘዘ መልአክ መጥቶ እሳቱን አቀዝቅዞ በሰላም አወጣት፡፡ ከእሳቱም ከወጣች በኋላ የንጉሡን ጣዖታት ዳግመኛ ዘለፈች፡፡ ንጉሡም በእርሷ ላይ የተፈጸመውን ታላቅ ተአምር አይቶ ቤታችን አመነ፡፡ አምስተኛውም የፋርስ ንጉሥ በመጣ ጊዜ ቅድስት ኦርኒን ይዞ በእጁ በያዘው ጦር ወጋትና ሞተች፡፡ የታዘዘ መልአክም መጥቶ ከሞት አስነሣትና ዳግመኛ በጌታችን ስም ማስተማር ጀመረች፡፡ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ተነጥቃ ወጣች፡፡ ማኅበርተኞቿ የሆኑ 13 ሺህ ሰዎች በዚሁ ዕለት በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ኦርኒ በጸሎቷ ይማረን በከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የመለኮትን_ነገር_የሚናገር_አቡነ_ጎርጎርዮስ፡- በሌላም በኩል "ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ" እየተባለም ይጠራል፡፡ ሀገሩ ቂሳርያ ነው፡፡ በመጀመሪያ የሕግ ባለሙያ የነበረ ሲሆን በኋላ ግን የቍስጥንጥንያ ሊቀጳጳስ ሆኖ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በሐዋርያነት አገልግሏል፡፡ በደራሲነቱ ምድራውያን መላእክት ከተሰኙት ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ነው፡፡ የአምላክን ሰው መሆንና ምሥጢረ ሥላሴን እጅግ አስፍቶና አራቆ ያስተማረ ከመሆኑም በላይ ‹‹ዳግማዊ ዮሐንስ ነባቤ መነኮት›› ተብሎ እስኪጠራ ድረስ በነገረ መለኮት የተራቀቀ ታላቅ ሊቅ መምህር ነው፡፡ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙን የማይጠቅስ መጽሐፍና መምህር የለም፡፡ ሃይማኖተ አበው አጥብቆ የሚጠራው የቤተ ክርስቲያናችን መመኪያ ነው፡፡ የአርመንን ኦርቶዶክስ ያቀና ሲሆን መንበሩን የኖኅ መርከብ ባረፈችበት አራራት ተራራ ላይ ነው የሠራው፡፡                          ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_አክርስጥሮስ፡- ይኽም ቅዱስ አባት በዮርዳኖስ በረሃ የሚኖር ታላቅ ተጋዳይ ነው፡፡ ከመነኮሳቱም አንዱ በፊቱ እየሰገደ ሥራውን ይገልጥለት ዘንድ በእግዚአብሔር ስም አማለው፡፡ ሽማግሌው አክርስጥሮስም እንዲህ ብሎ መለሰለት፡- "ልጄ ሆይ! ጎልማሳ ሆኜ ሳለ በመነኰስኩ ጊዜ በዚያ እጸልይ ዘንድ በሌሊት ወደ ቅዱስ ቴዎድሮስ መቅደስ እሄድ ነበር፡፡ 12 ደረጃዎችም አሏት፣ በእንዳንዱ ደረጃ መቶ መቶ ስግደቶቸን እሰግዳለሁ፡፡ ደወልንም በሚደውሉ ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን በመግባት ከወንደሞች ጋር የማኅበሩን የጸሎት ሥርዓት እፈጽማለሁ፣ እንዲህም በማድረግ 10 ዓመት ኖርኩ፡፡ ከሌሊቶቹም በአንዲቱ የተለመደ ጸሎቴን ከፈጸምኩ በኋላ ልቡናዬ በተመስጦ ተማረከ፡፡ ነጫጭ ልብሶችን የለበሱ ሁለት ሰዎች መቅረዞችን ሲያበሩ እኩሌቶቹ ሲበሩ እኩሌቶቹ ሲጠፉ አየሁ፡፡ እኔም "ይህ ሥራ ምንድነው?" አልኳቸው፡፡ እነዚያም አባቶች "ባልጀራውን የሚወድ መቅረዙ ይበራለታል" አሉኝ፡፡ እኔም ደግሙ "መቅረዜ የትኛው ነው?" አልኳቸው፡፡ እነርሱም "ሂድ ከወንድሞችህ ጋር ተፋቀር፣ እኛ እናበራልሃለን" አሉኝ፡፡ በነቃሁም ጊዜ ማንንም አላገኘሁም" ብሎ ለጠየቀው መነኮስ ነገረው፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ አክርስጥሮስ ብቻውን ወደ ደብረ ሲና ሄዶ በዚያ እየተጋደለ 50 ዓመት ኖረ፡፡ ወደ እርሱም

❤ ጌታችን "እግድያስ እኔ የጠጣሁበት ዋንጫ ትቅረብና ትመስክርብኝ" አለው። በዚህ ተስማምተው ሙሴው ሄዶ አንድ ሽራፊ ዋንጫ አምጥቶ "በዚህ ነበር የሚሰጠውና የሚጠጣው" ብሎ አቀረበ። ዋንጫዋም ከተቀመጠችበት አንድ ክንድ ከስንዝር ተነስታ "ዓለማትን የፈጠረ አምላክ ምስክሬ ነው እኔ የያዝኩትን የወይን ጠጅ ዕቃ ሙሴም በእጆቹ አልያዘኝም በከንፈሩ አልካኝም በሌሎች ሰዎች እጅ ግን ተይዤ ያየን ነበር" አለች። ያን ጊዜ ሰውም እንስሳትም እፀዋትም ሁሉ ፆራ (ተሸክማ) የምትሔድ ሙሴን ልትጾር (ልትሸከመው) አልቻለችም። እንደ ዳታ አቤሮን ምድር ተከፍታ ከነልጁ ጋር ዋጠቻቸው። ማኅበረ ጻድቃንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን ተረድተው እንደገና ከእግሩ ወድቀው ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ለመኑት ቀኑም ጥር29 ነበር። ጌታችን ኢየሱስ ክስቶስ ይቅርታ ካደረገላቸው በኋላ "ስማችሁን የጠራ በስማችሁ ተዝካር ያወጣ በስማችሁ ድሆችን የረዳ፣ ያለበሰ፣ ያጎረሰ፣ የሰጠ፣ የመፀወተ፣ ቤተ ክርስትያኖች ሆነ የሠራ ያሠራ፣ እስከ14 ትውልድ ድረስ ምሬላችኋለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣቸው። ይህችን ቦታችሁ መጥቶ የሳመ ኢየሩሳሌም እንደሳመ አድርጌላችኋለሁ" አላቸው። ❤ በኦሪት ኄኖክና፣ ዕዝራና ኤልያስ በሐዲስ ኪዳን እነ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድና በየጊዜው የሚሰወሩ ቅዱሳን ግልጽ ነውና እንዚሁም ጌታችን እነዚህ የማኅበረ ደጔ ጻድቃንም ከሞት ተሰወሩ ብሎ በበነገታው ጥር30 ቀን ሠውሮአቸዋል። በዚህም መሠረት ይህ ታላቅ በዓል ሆኖ ዛሬም በየዓመቱ ጥር30 ሲከበር ይኖራል። በገዳሙ ውስጥ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው የተፈጸመውን ነገር በውል የሚያስረዱ በዐይን የሚታዩ በእጅ የሚዳሰሱ በጌታችን ተአምራት የተደረገባቸው ቅርሶች በክብር ተጠብቀው ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ፡- 1.ክንድ ከስንዝር ወደላይ ተነሥታ በሰው አንደበት በመመስከር ጌታችን በእርሷ እንዳልጠጣባት የመሰከረችው ዋንጫ (ጽዋ) 2.ጌታችን የተቀመጠባትና ያስተማረባት ድንጋይ ከነምልክቷ። 3.ምስዋሮም የሚባል ጻድድቃኑ የተሰወሩበትን ሥፍራ። 4.ጌታችን ከድንጋይዋ ላይ ሁኖ ወርቅ ዘንጉን ወርውሮ ያፈለቀውና "ማየ ዮርዳኖስ" ይሁን ብሎ የሰየመው ጠበል። 4.ቅዱሳኑ ሲወቅጡበት የነበረው የድንጋይ ሙቀጫ። 5.በማህበራቸው ጊዜ ሲደግሱባቸው የነበሩ የድንጋይ ገበታዎች። 7.ቅዱሳኑ ከሀገራቸው ከሮም ያመጡት ባለመስታወት ቋሚ ዕፀ መስቀል። 8.ርዕሰ ዮሐንስ የሚባል ነገሥታት ከነዘውዳቸው ጳጳሳት ከነአክሊላቸውና ከነመስቀላቸው በዚያን ጊዜ የተሳሉበት ሥዕል። 9.ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ በማኅበረ ጻድቃን ዴጔ ሆኖ ያስተማረበትና የጠመቀበትን በሥዕል የሚያሳይ። 10.ይህ ገዳሙ በዐፄ ካሌብ ዘመነ መንግሥት እንደተገደመና የገደሙትም ራሳቸው መሆኑን በአክሱም መጽሐፍ ክብረ ነገሥት ላይ ተጽፎ እንደሚገኝ በታሪኩ ተረጋግጦ ተላልፎልናል፡፡ ምንጭ፦ የማኅበረ ጻድቃን ዴጔ ጥንታዊ ገዳም ታሪክ ባጭሉ ከሚለው መጽሐፍ።                                                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የከበሩ_ቅዱሳን_ደናግል_ጲስጢስ_አላጲስና_አጋጲስ_እናቸው_ቅድስት_ሶፍያ፦ እናታቸው ከአንጾኪያ ከከበሩ ወገኖች ውስጥ ናት። እነዚህንም ሦስት ልጆች በወለደቻቸው ጊዜ በእሊህ ስሞች ጠራቻቸው ትርጓሜያቸውም ሃይማኖት ተስፋ ፍቅር ነው የራሷም ስም ትርጓሜ ጥበብ ማለት ነው። ጥቂትም በአደጉ ጊዜ ወደ ሮሜ ከተማ ወስዳ በጎ አምልኮን እግዚአብሔርን መፍራትን የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት አስተማራቻቸው በከሀዲውም የሮሜ ንጉሥ በአርያኖስ ዘንድ ወሬያቸው ተሰማ ወደ ርሱም ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘና አመጡአቸው እናታቸውም በማስተማር ትመክራቸውና ታጸናቸው ነበር። እንዲህም ትላቸዋለች "ልጆቼ ተጠበቁ የዚህን የኃላፊውን ዓለም ክብር በማየት ልባችሁ እንዳይደክምና ከዘላለማዊ ክብር እንዳትርቁ ከሙሽራው ከክርስቶስ ጋር ሁናችሁ ወደ ሰማያዊ ሠርግ እንድትገቡ ጠንክሩ"። ዕድሜያቸውም የታላቂቱ ዐሥራ ሁለት የሁለተኛዪቱ ዐሥር የሦስተኛዪቱ ዘጠኝ ነው። ❤ እናታቸው ወደ ንጉሥ በአቀረበቻቸው ጊዜ ታላቂቱን ጲስጢስን "እኔን ስሚ ከቤተ መንግሥቴ ታላላቆች ለአንዱ አጋባሻለሁ ብዙ ስጦታም እሰጥሻለሁ ለአጵሎን ስገጂ" አላት። እርሷም እርሱንና የረከሱ አማልክቶቹን ሰደበች እርሱም ተቆጥቶ በብረት ዘንጎች እንዲደበደቧት ጡቶቿንም እንዲቆርጡ እሳትንም ከብረት ምጣድ በታች በማንደድ ባሩድ፣ ሙጫ፣ ሰሊጥን በውስጡ አድርገው እጅግ አፍልተው ወደዚያ ይጨምሩዋት ዘንድ አዘዘ። በጨመሩዋትም ጊዜ እየፀለየች በብረት ምጣዱ ውስጥ ቆመች ከቶ እሳት አልነካትም። የምጣዱም ግለት ጸጥ ብሎ እንደ ጥዋት ጊዜ ጤዛ ቀዝቅዛ ሆነ ከዚያ ያሉ ሰዎችም አድንቀው እግዚአብሔርን አመሰገኑት ብዙዎችም በክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቈርጡዋቸውና በሰማዕትነት ሞቱ። ❤ ከዚህም በኋላ የቅድስት ጲስጢስን ራስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ምስክርነቷንም ፈጽማ የምስክርነት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ሥጋዋን አንሥታ ወሰደች። ዳግመኛም ሁለተኛዋን አላጲስን አቀረቧትና ደበደቧት ጽኑዕ ግርፋትንም ገረፏት ከጋለ ብረት ምጣድ ውስጥ ጨመርዋት በዚያንም ጊዜ ቀዝቅዞ እንደ ጥዋት ጤዛ ሆነ ንጉሡም ከዚያም እንዲአወጧትና ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ምስክርነቷንም አድርሳ በመንግሥተ ሰማያት የሕይወት አክሊልን ተቀበለች እናቷም ሥጋዋን ወሰደች። ❤ ቅድስት ሶፍያም ከሥቃይ የተነሣ እንዳትደነግጥ ስለ ልጅዋ ስለ አጋጲስ ትፈራ ነበር ታጽናናትና እንድትታገሥ ታደርጋት ነበር በዚያንም ጊዜ ወስደው ከመንኰራኩር ውስጥ ጨመርዋት እግዚአብሔርም መልአኩን ልኮ ያንን መንኰራኲር ሰበረው እርሷም በደኅና ወጣች ዳግመኛም እሳትን አድደው ከውስጡ እንዲጥሏት አዘዘ እርሷም ፊቷን በመስቀል ምልክት አማትባ ወደሚነደው እሳቱ ተወርውራ ገባች በዚያንም ጊዜ እሳቱ እንደ ጥዋት ውርጭ የቀዘቀዘ ሆነ ከዚያ ያሉትም ሰዎች ብርሃን የለበሱ ሁለት ሰዎች ከነጫጭ ልብሶች ጋር ሲጋርዷዋት አይተው እጅግ አደነቁ ብዙዎችም በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ራሶቻቸውንም ቆርጠዋቸው በሰማዕትነት ሞቱ ያቺንም የዘጠኝ ዓመት ልጅ የከበረች አጋጲስን ራሷን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። ምስክርነቷንም ፈጸመች ሁሉም የማያልፍ የማይጠፋ ሰማያዊ መንግሥትን ወረሱ። ❤ የከበረች ሶፍያም የሦስት ልጆቿን ሥጋቸውን ወስዳ ገነዘቻቸው ወደ ከተማውም ውጭ አድርሳ በዚያ ቀበረቻቸው በሦስተኛውም ቀን ወደ መቃብራቸው ሔዳ አለቀሰች ነፍሷንም ይወስድ ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነች ልመናዋንም ተቀብሎ ነፍሷን ወሰደ ምእመናን ሰዎችም መጥተው ገንዘው ከልጆቿ ጋር ቀበሩዋት። በከሀዲው ንጉሥ ላይ ግን እግዚአብሔር ጭንቅ የሆነ ደዌ ላከ ዐይኖቹም ፈረጡ ዐጥንቶቹም እስከማሚታዩ ሥጋው ሁሉ ተሠነጣጠቀ እጆቹም ተቆራረጡ ከእርሱም ደምና መግል ፈሰሰ ትልም ይወድቅ ነበር ሁለመናውም ተበላሽቶ በክፉ ሞት ሞተ። ስለ እነዚያ ደናግል ጌታ ተቀበቅሎታልና። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ደናግላን ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ጥር ፴ (30) ቀን። ❤ እንኳን #ለማኅበረ_ዴጔ_ለሦስት_ሺህ_ጻድቃን እንደ ቅዱሳን ኄኖክና ዕዝራ ከዚህ ዓለም ከሞት ለተሰወሩበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው፣ ለከበሩ ደናግል #ለቅድስት_ሶፍያ_ልጆች ለቅድሳት #ለጲስጢስ_ለአላጲስና_ለአጋጲስ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ ስሙ መርቅያኖስ ለሚባል ለጣዖት ለሚሰግድ ለሮሜ ንጉሥ ልጅ ለከበረች #ለቅድስት_ኦርኒ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ለዕረፍቷ በዓል፣ ለከበረች #ቅድስት_ጤቅላ ከእርሷ ጋር ከሚኖሩ አራት ደናግል ጋር ፎላ በሚባል ኃጥእ ቄስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና ተጋዳይ ለሆነ ለመነኰስ ለከበረ #አባ_አክርስጥሮስ ለዕረፍት በዓልና ለመለኮትን ነገር ለሚናገር ለቅዱስ ጎርጎርዮስ ለመታሰቢያ በዓሉ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክድርያ አገር አርባ ሰባተኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_ሚናስ ዕረፍትና #ከቅድስት_ኦርኒ_ማኅበር ከሆኑ #ከዐሥራ_ሦስት_ሺህ_ሰዎች በሰማዕትነት  ከዐረፉ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                        ✝ ✝ ✝ ❤ #ማኅበረ_ዴጔ፦ ማለት የደጋጎች አገር ማለት ነው። የደጋጎች አገር የተባለበት ምክንያት ብዙ ሺህ ቅዱሳን ተሰብስበው ስለሚኖሩበት ነው፡፡ ገዳሙ የሚገኘው በትግራይ ክልል በአክሱም አውራጃ ከአክሱም ከተማ ወደ ደቡብ ምዕራብ በሚወስደው መንገድ ዐሥራ ሁለት ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ ነው፡፡ ከገዳሙ ተያይዞ የተላከልን ዘገባ እንደሚያስረዳው ቤተ ክርስትያኑ በ39ዓ.ም እንተተተከለ በግልፅ ያስረዳል። ይኸውም መጽሐፈ ሱባኤ በተባለው በመሪ ኤ.ኤም የተዘጋጀው መጽሐፍ ከምዕራፍ 11 በገጽ 132 ላይ አቴዥን ሕንደቼ ንግሥት ነገሥታት ዘኢትዮጵያ ሆና በነገሠች በ39ዓ.ም በአንደኛው ዓመተ መንግሥትዋ ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ በ40ዓ.ም ማኅበረ ጻድቃን ዴጔ ገብቶ ሲያስተምርና ሲያጠምቅ ሰምታ መኳንንትና መሳፍንትን አሰከትላ መርዌ ወረደች ይላል። ❤ በዚህም ንግሥቲቱ ቅዱስ ማቴዎስ አግኝታ "ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር አብ የባሕሪ ልጅ መሆኑ አውቃለሁ ይሁን እንጂ ዳግመኛ ከእግዚአብሔር ከድንግል ማርያም መወለዱን አላውቅም ነበር አሁን ግን በትምህርትህ መንፈስ ቅዱስ ስለ ገለጸልኝ አጥምቀኝ" አለችው። ቅዱስ ማቴዎስም ንግሥቲቱን ካጠመቀ በኋላ ቀጥሎ መኳንንቱን፣ መሳፍንቱን የጦር ሠራዊቱን ሁሉ አጥምቋቸዋል ይላል፡፡ አያይዞም ንግሥቲቱ ቅዱስ ማቴዎስን ይዛው ወደ አክሱም ተመለሰች፣ ልጆችዋንና ቤተሰቦችዋንም አስጠመቀች እንዲሁም አክሎስ የሚባል ባልዋም አምኖ ተጠመቀ። ቅዱስ ማቴዎስ ከዚህ በፊት የነባቡና የናግራንን ህዞቦች አጥምቆ ከዚህም በኋላ የጻድቃንን ዴጔ ማህበር አቋቁሞ በጌታችን ስም በየወሩ በ29ቀን እየተሰበሰቡ ጽዋ እንዲጠጡ አድርጓቸው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዷል፡፡ ❤ በ365ዓ.ም በአስፍሕ ወልደ አብርሃም ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ዘመነ መንግሥት "ሮምያ" ከምትባል መንደር ቅዱሳን "ስለ ጽድቅ ብለው የሚሰደዱ ብፁአን ናቸው መንግሥተ ሰማያት የነርሱ ናትና" ያለውን ዳግመኛም "አባቱንና እናቱን ሚስቱንና ልጆቹን ያልተወ ሊያገለግለኝ አይችልም" ብሎ ጌታችን የተናገረውን አስበው ቅዱሳን የዚህም ዓለም ጣዕም ጥቅም ንቀው አገራቸውን ትተው መንነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ነበሩ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን በአክሱም ከተማ በስተሰሜን በሐውልቱ ጀርባ ቤተ ቀጠንት በሚባል ስፍራ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህል እንደ ተቀመጡ በዚያም ምቾትና ድሎት ስለተሰማባቸው "ለዚህ ለዚህማ አገራችንን ለምን ትተን መጣን? ስለዚህ ሱባዔ ገብተን በጾም በጸሎት ተወስነን የምንሄድበትን ቦታ በረከተ ነፍስ የምናገኝበትን ስፍራ እግዚአብሔር እንዲያሳየን እናመልክት" ብለው ሱባዔ ገቡ ጾም ያዙ፡፡ ከሱባዔውም በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጻላቸው ግማሾቹን እያንዳንዳቸው የሚኖሩበትን በዓት አመልክታቸው፣ በዚያም በጾምና በጸሎት ጸንተው እንዲኖሩ ነገረቻቸው፡፡ ሦስት ሺህ ያህሉን ደግሞ ከላይ ወደጠቀስነው ሥፍ ሄዱ፡፡ ከእነርሱ የተቀሩት ደግሞ ወደ ቆየፃ ሓባር፣ ተድባ፣ አኮርየን፣ ተንስሓ፣ ደብረ አንሳ ወደ ተባሉ ቦታዎች ሄደዋል፡፡ ተጨማሪ ሦስት ሺህ የሚሆኑት ደግሞ እዚያ ከነበሩት ጋር ተደመሩ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ እነዚህ ቅዱሳን "ከሁሉ ፍቅር ይበልጣል" የሚለውን ጠብቀው በእምነት በፍቅር በአንድነት ጸንተው በየሣምንቱ እሁድ እሁድ ተዝካረ ሰንበትን ጠብቀው ማኅበር ሲጠጡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅራቸው አይቶ በአምሳለ ነዳይ ደሀ መስሎ በመካከላቸው ተገኘ። ከነርሱ ጋርም አንድ ማኅበርተኛ ሁኖ እንዲታወቅ ጠየቃቸው፤ እነርሱም ፈቀዱለት አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህልም ከነርሱ ጋር ሳይለይ ቆየ በዚሁ ጊዜ "ለእኔም ተራ ስጡኝ እንደ አቅሜ ዝክር ላውጣ"አላቸው። እነርሱም ግን "አይሆንም አንተ ደሀ ነህ ከኛ ጋር ሁነህ በዓሉን አክብር እንጂ ምን አለህ እና ነውን" አሉት፣ እርሱም "አይሆንም ስጡኝ እንጅ አላቸው" እርሱም ካልክማ ብለው ቀን ወስነው ሰጡት ቀኑም ጥር29 ነበር። ከማኅበርተኞቹ መካከል "ሣይዳን" የሚባል ሰው ነበር፡፡ ይህም አሳላፊ ወይም ሙሴ ማለት ነው። ይህም ሰው እንግዳና ድሀ ሰው ፈጽሞ አይወድም ነበር፣ ጌታችንም ከማኅበርተኞቹ መካከል ሲገኝ ደሀ መስሎ ስለ ነበር በጣም ይጠላው ነበር። ❤ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ከነርሱ ጋር ሲቀመጥም አንድ ቀን ስኳን አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ ሰጥቶት አያውቅም ነበር፣ ሆኖም የጌታችን ማኅበር ደረሰ፣ እንደ ማኅበሩ ሥርዓት አሳላፊው ጠርቶ "ጋኖችን እጠብልኝ አለው" አሳላፊው "ቤትህ የማይታወቅ ከየት አምጥተህ ማኅበር ልታደርግ ነው" ብሎ አናንቆ ተመለከተው ጌታም አንድ እረኛ ጠርቶ "አንተ ልጅ ከብቶችህን እኔ እጠብቅልሃለሁና ውኃ አምጣልኝ" አለው፣ ልጁም ገምቦውን ይዞ ትንሽ ወጣ እንዳለ ጌታ ዘወትር ከሚቀመጥበት ድንጋይ ላይ ሆኖ ዘንጉን ወደ ልጁ አቅጣጫ ወረወረው፣ ዘንጉንም ከልጁ ፊት ሂዶ ተተከለ ልጁንም ጠርቶ ዘንጉንም ንቀለው አለው ልጁም ዘንጉን ቢነቅለው ውኃ ፈለቀ "ከርሱ ቀድተህ አምጣልኝ" አለው። ልጁም ከዚህ ውሃ ቀድቶ አመጣለት ጌታም ልጁ ባመጣው ውኃ ጋኖቹ ቀድቶ አጠባቸው፣ በበዓሉ ቀን ማኅበርተኞቹ ምን ሊያበላን ነው ምን ሊያጠጣን ነው ሳይሉ ሁሉም ተሰበሰቡ ጌታችንም በፊታቸው ጋኖቹን ቢባርካቸው የወይን ጠጅ ሞልተው ተገኙ። ቀድቶ ቢሰጣቸውና ቢቀምሱትም በጣም ግሩም ጣፍጭ ስለነበር እጅግ አደነቁ፣ እነርሱም ጌታችን ከጻድቃን አንዱ ስለመሰላቸው ከእግሩ ላይ ወድቀው "እስካሁን ድረስ ሳንበድልህ አልቀረንምና ይቅር በለን" ብለው ለመኑት ተነሡ ብሎ ካስነሳቸው በኋላ "እናንተ አልበደላችሁም፡ በደለኝ አሳላፊያችሁ ነው አንድ ቀን ስንኳ አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ አልሰጠኝምና አፋራርዱኝ" አላቸው። ነገር ግን ሙሴው የማያፍር ደፋርና ርጉም ስለነበር ሲጠይቁት "ይህ ሰው ጌታችንን በልቶ አልበላውም ጠጥቶ አልጠጣሁም የሚል ስለሆነና ስለማይጠግብ ነው እንጂ እንዲያውም ለናንተ አንድ አንድ ዋንጫ ሲሰጣችሁ ለእርሱ ሁለት ሁለት ነበር የሚሰጠው" ብሎ የሐሰት ቃል መለሰ።

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ  አሜን"። ❤             ❤ #ጥር ፳፱ 29 ቀን ❤ እንኳን #ጌታችን_አምላካች_መድኀኒታችን_ኢየሱስ ክርስቶስ በአካል ተገልጦ በደሃ ሰው ተመስሎ ከማኅበረ ዴጔ ጋር በመካከላቸውም ተገኝቶ የጽዋ ማኅበር እየጠጣ ተራው ደርሶ ተዓምር አድርጎ አምላክነቱ ለገለጠበት ቀን ለመታሰቢያ በዓል፣  የስሟ ትርጓሜ መጻተኛ ለሆነ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ በራእይ ለተገለጠላትና ከከበሩ ነገሥታት ወገን ለሆነችው ዓለምን ንቃ በመመንኰስ በምትተኛ ጊዜ ያለ ምንጣፍ በምድር ላይ እየተኛችና ጥሬ ባቄላን ብቻ እየተመገበች በታላቅ ተጋድሎ ለኖረችው ለከበረች #ቅድስት_አክሳኒ ለዕረፍቷ በዓል መታሰቢያ፣ ተጋዳይ ለሆነ በበረሃ ውስጥ የሞተ ሰው ራስ ቅል አግኝተው የራስ ቅሉን ላነጋገሩና ሥራውን መርምረው ለተረዱ በኋላም አማልደውት ምሕረትን ላሰጡት #አባ_እስጢፍኖስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከድንግል እመቤታችን ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከተወለደበት #ከልደቱ_በዓለ_ወልድ_ወራዊ መታሰቢያ፣ ከመስተጋድል ከከበረ #ሰማዕት_ከሰርያኮስ ከመታሰቢያው፣ ከሮሜ ሰዎች ውስጥ #ከንጹሐት_ሴቶች ከመታሰቢያቸው፣ #ከፊልንማ_ከኢያልኒ_ከሰረባሞኒና_ከቃውት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                                                       ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_አክሳኒ፦ ይችም ቅድስት የስሟ ትርጓሜ መጻተኛ ለማለት ነው። እርሷም ከሮሜ አገር ለከበሩ ሰዎች ልጅ ናት ወላጆቿም ከርሷ በቀር ልጅ የላቸውም እርሷም የምትጋደል ሆነች በቀንና በሌሊትም ትጾማለች ትጸልያለች በሮሜ አገር ወዳለ የደናግል ገዳም በመሔድ ከእርሳቸው ጋር ታገለግላለች ትጸልያለች በሮሜ አገር ወዳለ የደናግል ገዳም በመሔድ ከእሳቸው ጋር ትጋደላለች ከአባቷ ቤት የሚያመጡላትን ምግብ ለድኆችና ለምስኪኖች ሰጥታ እርሷ ከደናግል ምግብ ትመገባለች የደናግል መነኵሳይትንም ገድል አዘውትራ ታነባለች ከእርሳቸውም ጋር አንድ ያደርጋት ዘንድ እግዚአብሔርን አብዝታ ትለምን ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ወላጆቿ ሊአገቧት አስበው ከሮሜ አገር ታላላቆች ለአንዱ አጭዋት የወርቅ ልብሶችን ከወርቅና ከብር የተሠሩ የከበሩ ሽልማቶችንና ጌጦችንም አዘጋጁላት። የጋብቻውም ቀን ሲደርስ እናቷን "እናቴ ሆይ በምታጋቡኝ ጊዜ ወደ ደናግል መሔድ አይቻለኝም እኔ ዛሬ ሔጄ በረከታቸውን ተቀብዬ ሰላምታ ሰጥቻቸው ፈጥኜ መመለስ እሻለሁ" አለቻት። እናቷም የነገሥታት የሆነ የወርቅ ልብሶችን አልብሳ ሴቶች አገልጋዮችን ከእርሷ ጋር አድርጋ አሰናበተቻት። ❤ እርሷም ግን ወደ ባሕር ወደብ ተጉዟ መርከብንም አግኝታ ተሳፈረችና ወደ ቆጵሮስ ደሴት ሔደች። ወደ ከበረ ኤጲፋንዮስም ደርሳ ኀሳቧን ሁሉ አስረዳችው የከበረ ኤጲፋንዮስም ወደ እስክንድርያ አገር ሰደዳት ወደዚያም በደረሰች ጊዜ በሕልሟ የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ተገልጾ ስሙን ነገራትና የምትሠራውን ሁሉ አስተማራት። በማግሥቱም ወደ ሊቀ ጳጳስት ቴዎፍሎስ ገባች የራሷንም ጠጉር ተላጭታ የምንኵሴና ልብስን ለበሰች ከርሷ ጋር ያሉ ሽልማቶችንና ጌጦችን የወርቅ ልብሶችንም ሸጠችና በሰማዕታት መጀመሪያ በከበረ እስጢፋኖስ ስም ቤተ ክርስቲያን ሠራች አባ ቴዎፍሎስም ብዙዎች ደናግል መነኰሳይትን ሰበሰበላትና በዚያ ገዳም ከርሷ ጋር የሚኖሩ ሆኑ። ❤ ይቺም ቅድስት አክሳኒ ታላቅ ተጋድሎን ጀመረች እርሷ ከጥሬ ባቄላ በቀር በእሳት ያበሰሉትን አትቀምስና በምትተኛም ጊዜ ያለ ምንጣፍ በምድር ላይ ትተኛ ነበር እንዲህም እየተጋደለች ሃያ ዓመት ያህል ከዚያም የሚበዛ ኖረች ከዚህም በኋላ ጥቂት ታመመችና ዐረፈች። ልዑል እግዚአብሔር የሰጣትን ልዕልና ሊገልጥ ወደደ። በአረፈችበትም ዕለት ሰዎች በቀትር ጊዜ የብርሃን መስቀል በሰማይ ውስጥ አዩ ብርሃኑም የፀሐይን ብርሃን ሸፍኖ ነበር የሚያበሩ ከዋክብትም አክሊላትም በዙሪያው ሁነው ሥጋዋን ከደናግል ሥጋ ጋር አስከ አኖሩ ድረስ የሚያበሩ ሆኑ ከዚያም በኋላ ተሠወረ ይህም ስርሷ እንደተገለጠ ሕዝቡ አወቁ። ❤ በዚያንም ጊዜ እነዚህ ሁለት አገልጋዮቿ የዚችን ቅድስት አክሳኒ ከመጀመሪያው እስከ ዕረፍቷ ያለ ገድሏን ለሊቀ ጳጳሳቱና ለሕዝቡ ሁሉ ስማቸውን ለውጣ እኅቶቿ እንዳለቻቸው እርሷንም እመቤታችን ማለት ሳይሆን እኅታችን እንዲሏት ምሥጢሯንም ሁሉ እንዲሠውሩ እንዳማለቻቸው ተናገሩ። ሊቀ ጳጳሳቱና ሕዝቡም ሁሉ አደነቁ ገድሏንም እስከመጨረሻው ጻፉ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት አክሳኒ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_እስጢፋኖስ፦ ይህም ቅዱስ ቅዱሳን ገዳማውያንን በመፈለግ በበረሀ ውስጥ ሲዞር የወደቀች የሰው ራስ አገኘ እርሷም ሥጋ የልላት ዐጥንት ብቻ ናት። ሥራዋንም ያስረዳው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ በዚያንም ጊዜ ከዚያች ራስ ውስጥ እንዲህ የሚል ቃል ወጣ "እኔ በብዝበዛ ጭምር የማተርፍ ነጋዴ ነበርኩ መመጽወትንም አላውቅም በእኔ ዘንድ ሩቅ ወደ ሆነ አገር ስጓዝ ውኃ ወደ ሌለበት በረሀ ደረስኩ የቀን ሐሩርም በጸና ጊዜ ግመሎቼ ሞቱ ባሮቼም ሸሹ ብቻዬንም ቀረሁ። በሦስተኛውም ቀን ዐይኖቼ ከበዱኝ እንደፋጨትም ያለ ሰማሁ ያንጊዜ ነፍሴ ወጣች እንደሥራዬም ቅጣቴን ልቀበል ወደ ሥቃይ ቦታ ወሰዱኝ አንተም በለመንክ ጊዜ ሥራዬን እነግርህ ዘንድ ወዳንተ አመጡኝ አሁንም ወደ ሥቃይ ቦታ እንዳይመልሱኝ እግዚአብሔርን ስለ እኔ ምሕረትን ትለምነው ዘንድ እማልድሃለሁ" አለው። ❤ ቅዱስም ወደ እግዚአብሔር ስርሱ ለመነለት በዚያንም ጊዜ ስለ አንተ ምሬዋለሁ የሚል ቃልን ሰማ ይህንንም ሰምቶ ወደ በዓቱ ሔደ እስከ ዐረፈ ድረስም እያለቀሰና ደረቱን እየደቃ ኖረ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ እስጢፋኖስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 29 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለ ኃይል። ወብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ"። መዝ 109፥3 ወይም መዝ 38፥12-13።የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 12፥16-40 ወይም ዮሐ1፥7-15።                              ✝ ✝ ✝ ❤ የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ ፈላሲ አነ ውስተ ምድር። ወነግድ ከመ ኵሉ አበውየ። ስሐተኒ ከመ አፅርፍ"። መዝ 38፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ  3፥14-1ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 1፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥12-17። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥7-15። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው።  መልካም የጌታችንን በማኅበረ ዶጌ ያደረገ የተአምር በዐል፣ የአቡነ ታዴዎስ፣ የአቡነ ማትያስና የአቡነ ገብረ ናዝራዊ  የዕረፍታቸው በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                 

አዋጅ ይደረግ" ብለው ነገሯቸው፡፡ ንጉሡም ጻድቁ እንዳሏቸው ቢያደርጉ በሦስተኛው ቀን ሽፍቶቹን በቀላሉ ማረኳቸውና አገሪቱ ሰላም ሆነች፣ ንጉሡም እጅግ ደስ አላቸው፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊንም በማስጠራት "ያልከው ተፈጸመ፣ ድል አድርጌያለሁና ደስ ብለኛል፡፡ የትኛውን አካባቢ ርስት ጉልት አድርጌ ልስጥህ?" አሏቸው፡፡ ጻድቁም ለመነኰሳት ልጆቻቸው የእርሻ ቦታ የሚሆን ርስትን ተቀበሉ፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊ ገዳማቸው ደብረ ኀረይክዋ በቁና በነጹ መነኮሳት እንዲገለገል ካላቸው ፍላጎት አኳያ መነኮሳቱንም ከዓለማዊ ፈተና ለመታደግ ሲሉ ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይወጡ ከልክለዋል፡፡ አንዲት ሴት የጻድቁን ቃል በመተላለፍና በመደፋፈር ወደ ተራራው በመውጠቷ አፋፉ ላይ እንደደረሰች ከያዘችው ድፎ ዳቦ ጋር ድንጋይ ሆና ቀርታለች፡፡ ይህ ምስሏ አሁንም ድረስ ከነሙሉ የሰውነቷ ቅርጽ በግልጽ ይታያል፡፡ ❤ ሴቶች አንዳንድ ገዳማት ላይ እንዳይገቡ ገዳሙን የገደሙት ቅዱሳን የከለከሉበትን በቂ የሆነ መንፈሳዊ ምክንያት ስላላቸው ነው እንጂ እንዲሁ ያወጡት ሕግ አይደለም፡፡ ለዚህም ተጨማሪ ማሳያ ይሆን ዘንድ የእመ ምዑዟ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የወንዶችና የሴቶች ገዳም የተለያየ እንዲሆን ያደረገችበት ምክንያት ከገድሏ ላይ እንይ፡- "እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ቤተ መቅደሷን በአንዲት ቀን ብቻ ሠርታ እንደጨረሰች ጌታችን ከመንበሩ ሆኖ ተገለጠላትና በቦታው ላይ ትልቅ ቃልኪዳን ሰጣት፡፡ ተአምራቶቿንና የትሩፋቷን ዜና የሰሙ ሁሉ ወደ እርሷ እየመጡ ተሰብስበው በተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ ቅድስት እናታችንም ትመክራቸውና ታስተምራቸው ነበር፡፡ በመንፈስ ቅዱስም ኃይል ተገልጾላት የበጎ ሥራ ጠላት የሆነው ሰይጣን በማኅበሩ ልቡና እርሻ ላይ እንክርዳድ ሽንገላን እንደዘራ ባየች ጊዜ ከዚህ በኋላ የወንዶቹንና የሴቶቹን ቦታ ለየች፡፡ ለወንዶቹ ለብቻ፣ ለሴቶቹም ለብቻ ገዳም መሥርታ ዘወትር እንዳይተያዩ አደረገች፡፡ ልጆቿንም ሁሉ የእግዚአብሔር መልአክ ይጠብቃቸው ነበር፡፡ እርሷም የአርባውን ጾም ስትጾም ምንም ሳትቀምስ በምድር ላይም ሳትቀመጥ ቆማ ትጨርሳለች፡፡ እንደዚሁም በሌሎች አጽዋማት እንዲሁ ታደርግ ነበር፡፡ በስግደትና በግርፋትም ብዛት ሰውነቷን እጅግ ትጎዳና ታደክም ነበር፡፡ መላእክትም ምግቧን ከሰማይ ኅብስትና ወይን ያመጡላት ነበር፡፡ ውዳሴ አምላክንና አርጋኖንን በጸለየች ጊዜ ጌታችንና እመቤታንም በየጊዜው እየመጡ እየባረኳት ይሄዳሉ፡፡ የዕረፍት ጊዜዋም ከመድረሱ በፊት መላእክትም በብርሃን ሠረገላ ወደ ብሔረ ሕያዋን ወስደው ሥጋ ወደሙን እንትድቀበል አድርገዋታል"፡፡ ❤ አንዳንድ አላዋቂ ሰዎች በተለይም ከእኛ እምነት ውጭ ያሉ ሰዎች የሴቶችን ወደ አንዳንድ ገዳማት መግባት አለመቻል በዘመኑ የእኩልነት ስሌት ያሰሉታል፡፡ ይህን ሀሳብ የሚጋሩ አንዳንድ ኦርቶዶክሳውያን እኅቶችና እናቶችም አይጠፉም፡፡ እውነታው ግን ይህ ነው፡- ቅዱሳን አባቶቻችንና ቅዱሳት እናቶቻችን ይህን ሕግ የሠሩበት ምክንያት ግን ከላይ እንዳየነው በውል የታወቀና የተረዳ እውነት ነው፡፡ "ገዳማቸው በቁና በነጹ መነኮሳት እንዲገለገል ካላቸው ፍላጎት አኳያ መነኰሳቱንም ከዓለማዊ ፈተና ለመታደግ ሲሉ ሴቶች ወደ ገዳሙ እንዳይወጡ ከልክለዋል"፡፡ ፤ "ለቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስም ኃይል ተገልጾላት የበጎ ሥራ ጠላት የሆነው ሰይጣን በማኅበሩ ልቡና እርሻ ላይ እንክርዳድ ሽንገላን እንደዘራ ባየች ጊዜ ከዚህ በኋላ የወንዶቹንና የሴቶቹን ቦታ ለየች፡፡ ለወንዶቹ ለብቻ፣ ለሴቶቹም ለብቻ ገዳም መሥርታ ዘወትር እንዳይተያዩ አደረገች"፡፡ ❤ ሌላው የአቡነ ገብረ ናዝራዊ ደብረ ኀረይክዋ ገዳማቸውን ልዩ ከሚያደርጉት ነገሮች ውስጥ ጻድቁ በዘንዶ አማካኝነት ወደ ተራራው ሲወጡ መጀመሪያ የረገጡት ዓለት የእግር ጣታቸው ምልክት ያለበት መሆኑ ነው፡፡ እናቶች ምጥ ሲይዛቸው ወይም ሰዎች ሲታመሙ ድርቅና ቸነፈር ሲከሰት የሚፈውስና ምሕረት የሚያወርድ እንዲሁም የተጣሉ ሰዎች የሚታረቁበት ነባኢ መስቀል (የሚያነባ መስቀል) በገዳሙ ይገኛል፡፡ በየዓመቱ ጥር 29 ቀን የዕረፍታቸው በዓል በድምቀት ይከበራል፡፡ ከአባታች ከአቡነ ገብረ ናዝራዊ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።                   

❤ "ከዚኸ ረጅምና ታላቅ ገደል ስለ እኔ የእውነት ምስክሮች ኾነው በመወርወር በድናቸው በወደቀበት በዚኸ ሥፍራ ቆመው የሚጸልዩትን ሰዎች እኔ ስለ ወዳጆቼ ስለ ታዴዎስና ስለ ማትያስ ጸሎታቸውን እሰማለሁ። የለመኑኝንም ኹሉ መሻታቸውንም እሰጣቸዋለሁ። ከወደቁበት ከገደሉ በታች በአለው ስለ እኔ ደማቸው በነጠበበት በዚኸ ውኃ የታጠበውን (የተጠመቀው) ሰው እኔ በደሉን እደመስስለታለሁ። በሕይወት ውኃም አጠራዋለሁ። ድኾችንና ታማሚዎችን አጋንንት የያዟቸውን፤ ለምፅና ቋቁቻ እብጠትና እከክ ያለባቸውን ሰዎች እፈውሳቸዋለሁ። በዚኸ ፈሳሽ ውኃ በመነከርም አድናቸዋለሁ"። ❤ ጌታችንም ይኸንን ተናግሮ የታዴዎስን ነፍስ ወሰዳት። በአፉም ሳማት። ክብርት እናቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንም "እንኪ የወዳጄን የታዴዎስን ነፍስ ወደ ግብጽ በተሰደድን ጊዜ እንዳዘልሽኝ እዘያት፤ የወንድሙ ለመታደግ የተክለ ሃይማኖት ነፍስ በአለችበት በዚያ ትኖር ዘንድ ወደ ብርሃን ገነት እናስገባታለን" አላት። የመላእክት ለቅዱስ ሚካኤልንም “አንተ ደግሞ የማትያስን ነፍስ ተቀብለህ ሐዋርያት ጴጥሮስና ጳውሎስ ወዳጄ ወንጌላዊ ለዮሐንስም ወደአሉበት ሥፍራ እናስገባት ዘንድ እስከ ገነት ድረስ በክንፎችህ ተሸከማት" አለው። ❤ ገብረ እግዚአብሔርና ውቢት የተባለች ሚስቱ አመተ ማርያምን ደቀ መዛሙርቱ ኣባ ዘሚካኤልንና አባ ፊንሐስንም እንዲኸ ኣላቸው፡- "በድኖቻቸውን አንሥታችሁ ቅበሯቸው። እኔ ዳግመኛ ለሕይወት እስካስነሣቸው ድረስ መቃብራቸውን ጠብቁ። በገድላቸው የተፈጸመውንም ተኣምር ለሚመጣው ትውልድ ንገሩ። ስለ እነርሱም ከሸመገላችሁ በኋላ አርባ ስምንት ዓመት ዕድሜ እሰጣችኋለሁ። ከእነርሱም ጋር ሰማያዊ ርስትን አወርሳችኋለሁ"። ይኽንንም ብሎ ወደ መለኮታዊ መንበሩ ወደ ሰማይ ዐረገ። ❤ ከዚኸም በኋላ ሌሊቱ ነግቶ ጥር ፳፱ ቀን ሲኾን በይኩኖ አምላክ ልጅ በዐምደ ጽዮን ዘመነ መንግሥት በድኖቻቸውን አንሥተው በዝም ባለው ዋሻ ውስጥ ቀበሯቸው። እኒኽ ስማቸውን አስቀድመን የጠራናቸው ቅዱሳንም ዳግማዊ ዳዊት እስከነገሠበት ጊዜ ድረስ መቃብሮቻቸውን እየጠበቁ በሰላም ኖሩ። ❤ ዳዊት በነገሠም ጊዜ ነገሩት። መቃብሮቻቸውንም አሳዩት። እርሱም በታላቅ ክብር ወደሌላ ሥፍራ አዘዋወራቸው። በዚያን ጊዜም በውስጧ ለተሰበሰብን የቤተ ክርስቲያን ልጆች ከመቃብሮቻቸው ትቢያ በድዉያንና ማን ላይ ብዙ ተኣምርና ድንቅ ተፈጸመ። ጌታችን ወድኀኒታችን እንደተናገረ መስተጋድላን የኾኑ የእነዚኽን ቅዱሳን አባቶቻችን የታዴዎስንና የማትያስን ተኣምርና ተጋድሎ ለመስማት እናስተውል። ከሰይጣን ውጊያ ከሥጋና ክነፍስ ደዌ ያድነን፤ በጸሎታቸው ሕሙማንን እንደ አዳናቸው በአማላጅነታቸውም ይጠብቀን፤ ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን አሜን ይኹን ይኹን። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ታዴዎስ።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ገብረ_ናዝራዊ_ዘደብረ_ኀረይክዋ፡- ሐውዜን እንዳጋ ሥሉስ ውስጥ የሚገኘው ገዳማቸው 44 የተለያዩ ጸበሎች የሚገኙበትና 28 ሜትር ርዝመት ያለው ነው፡፡ ይህ ድንቅ ገዳም እንደ ደብረ ዳሞ በገመድ ብቻ ነው የሚወጣው፡፡ ከአዲግራት በስተ ደቡብ ምዕራብ አቅጣጫ በ27 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘው ገዳሙ ኀረይክዋ የሚለውን ስያሜ ያገኘው ከራሳቸው ከአቡነ ገብረ ናዝራዊ ነው፡፡ ይኸውም ጻድቁ ብዙ ቦታዎቸን ሲያስሱ ከኖሩ በኋላ በመጨረሻ ይህን ስፍራ ተመልከተው እግዚአብሔርም የፈቀደላቸው በዓታቸው መሆኑን ዐውቀው "ዛቲ ይእቲ ምዕራፍየ እስመ ኀረይክዋ-ይህቺ ማረፊያዬ እንድትሆን መርጫታለሁ" በማለት ጻድቁ የሰየሙት ስያሜ መሆኑ በቅዱስ ገድላቸው ላይ ተጽፏል፡፡ ጻድቁ ወደ ዓምባው ላይ የወጡት እንደ አቡነ አረጋዊ በዘንዶ ታዝለው፡፡ ❤ ጻድቁ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በሰሜን ሸዋ ይፋትና ጥሙጋ ደብረ ሲና ውስጥ ቀወት በምትባለው ቦታ በ13ኛው መ/ክ/ዘ ተወለዱ፡፡ አባታቸው ስቡሐ አምላክ እናታቸው ክርስቶስ ክብራ የሚባሉ የነገሥታት ወገን ናቸው፡፡ የአባታችን የስማቸው ትርጉም "በስዕለት ለእግዚአብሔር የተሰጠ ልዩና የተቀደሰ" ማለት ነው፤ ይህም የበኩር ልጅ ስለሆኑና በስዕለት የተሰጡ ስለሆነ ነው፡፡ ወላጆቻቸውም ፈሪሃ እግዚአብሔርንና የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በሚገባ እያስተማሩ በምግር በሃይማኖት ኮትኩተው አሳደጓቸው፡፡ ዲቁናን ከተወበሉ በኋላ በሸዋ አካባቢ እየተዘዋወሩ ወንጌልን መስበክ ጀመሩ፡፡ ነገር ግን በዚህ በሐዋርያዊ አገልግሎታቸው ጊዜ ብዙ ፈተና ገጠማቸው ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ከላይ በአቡነ ታዴዎስ ገድል ላይ እንዳየነው ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ሚስት በማግባቱ ምክንያት አቡነ ገብረ ናዝራዊም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ በዚህም ምክንያት ንጉሡ በማሠር ብዙ አሠቃያቸው፡፡ ጳጳሱ አባ ያዕቆብን ጨምሮ ብዙ ቅዱሳንም ለስደት ተዳረጉ፡፡ ❤ አቡነ ገብረ ናዝራዊም አካባቢውን ለቀው እንዲሄዱ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ከእሥር እንደተፈቱ ወደ ላሊበላ በመሄድ 12 ዓመታት በተጋድሎ ኖሩ፡፡ ወደ ሐይቅ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ገዳምም በመሄድ ካገለገሉ በኋላ ወደ ትግራይ ሄዱ፡፡ ከዚያም ግብፅን አቋርጠው ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ከጳጳሱ አባ ያዕቆብ ጋር ሲነሡ አባ ያዕቆብ "በዓትህ ኢትዮጵያ ብቻ ናት" ብለው ስለነገሯቸው ሀሳባቸውን ትተው የጳጳሱን ምክራቸውን ተቀበሉና ከጉዞአቸው ቀሩ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ወደ አዲግራት በመሻገር ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ፈጽሙ፡፡ መጀመሪያ እንደመጡ ያረፉባት አጋዝና በተባለቸው ተራራማ ቦታ ነበር፡፡ የአባታችን ሁለተኛ ቤተ ክርስቲያናቸው በዚህ ቦታ ላይ ታንጾ ይገኛል፡፡ በቦታውም ላይ 8 ዓመት ኖረውበታል፡፡ ወደሸለቆመም ዘቅዝቀው ወርደው ወደ ማየ ኢየሱስ በመሄድ ሓባ በምትባለው ተራራ ላይ የቁፋሮ ሥራ ጀምረው ባለ ሁለት ዓምድ የሆነ አንድ በር ያለው ቤተ ክርስቲያን አንጸው ሲያበቁ አሁን ወዳለው ገዳማቸው ደብረ ኀረይክዋ መጡ፡፡ ❤ አቡነ ገብረ ናዝራዊ ደብረ ኀረይክዋ ዓምባ ላይ ከወጡ በኋላ በመጀመሪያ የተለያየ መጠንና መጠሪያ ስም ያላቸውን ከዓለት ላይ የተፈለፈሉ አስደናቂ የሆኑ ከ44 በላይ የውኃ ጉድጓዶችን አንጸዋል፡፡ ከጉድጓዶቹም በተአምራት ጸበሎች ፈልቀውላቸዋል፡፡ እነዚህንም ጸበሎች እስከዛሬ ድረስ መጠናቸው ምንም ሳይጎድል ገዳማውያኑ ይጠቀሙባቸዋል፡፡ ጻድቁ በዚሁ ቦታ ከዓለት ላይ ፈልፍለው ያነጹት አስደናቂ ቤተ መቅደስ ይኛል፡፡ መካነ መቃብራቸውም በዚሁ ገዳማቸው ውስጥ በክብር ተቀምጦ ይገኛል፡፡ ❤ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በጾምና በጸሎት ተወስነው ሕዝቡን በማስተማር ብዙ አስገራሚ ተአምራትን በመፈጸም ላይ እንዳሉ የቀድሞ ጓደኛቸው የነበሩትና በኋላም የነገሡት ዐፄ ዓምደ ጽዮን በትግራይ ከፍለ ሀገር አጋሜ አውራጃ ዓምባ ጽዮን በተባለው ተራራ ላይ ሽፍቶች ተነሥተው መሽገው ነበር፡፡ ንጉሡም እነዚህን የተነሡባቸውን ሽፍቶች ለመያዝ ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት ብለው 10 ሺህ ሠራዊት ይዘው ወደ አካባቢው ዘመቱ፡፡ ንጉሡም በአካባቢው እንደደረሱ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በዚያ እንዳሉ ስለሰሙ መልእክተኞችን ልከው አስመጧቸውና የመሸጉትን ሽፍቶች በምን ዓይነት ዘዴ ድል ማድረግ እንደሚችሉ የጠቋቸው፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊም "ለሦስት ቀናት ያህል በቤተ ክርስቲያን ጸሎትና ምህላ ይደረግ፣ ሕፃናት የእናቶቻቸውን ጡት እንዳይጠቡ ይከልከሉ፣ የሚጠቡ የቀንድ ከብቶችም ከጥጃዎቻቸው ጋር እንዳይገናኙ የአስቸኳይ ጊዜ

❤ "በስመ አብ  ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #ጥር ፳፱ 29 ቀን ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያኑ_ጻድቃን እንደ ሐዋርያው #ቅዱስ_ታዴዎስ ግመልን በመርፌ ቀዳዳ ላሾለኩ ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ታዴዎስ_ዘጽላልሽና #ለአቡነ_ማትያስ_ዘጽላልሽ ገደል ውስጥ በመጣል ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል፣ በገዳማቸው ደብረ ኀረይክዋ ከዓለት ላይ የተፈለፈሉ 44 የተለያዩ ጸበሎች ለሚገኙበትና እንደ ደብረ ዳሞ በገመድ ብቻ ለሚወጣው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ገብረ_ናዝራዊ_ዘደብረ_ኀረይክ ለዕረፍታቸው በዓልና ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ገብረ_መርዓዊ ለልደታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                                                      ✝️ ✝️ ✝️ ❤ #ስለ_አባቶቻችን_አቡነ_ታዴዎስና_አቡነ_ማትያስ ሰማዕትነት ቃል ኪዳን፦ በዚኸን ጊዜ ከእርሷ ጋር ወደ ቤቱ ገባ። "ከዚኸ በኋላ ከአጋንንት ሕመም ስላዳናቸው ይወዱታልና በሰራዊትህ ፊት ከእርሱ ጋር አትጣላ፤ ዛሬም እንኳ ኣጋንንትን ሲያወጣ አይተውታል። ስለዚኸም ሰራዊትህና ወዳጆችህ ሊከዱህ በአንተም ላይ ከጠላቶችህ ጋር ሊያምጹ ሊያሸንፉህም ይችላሉ። የምመክርህን ነገር ስማኝ፤ አሁን አባቴ ሆይ! ከአወገዝኸኝ ዘንድ ወደ ማንኛዪቱም ሴት አልደርስም" በለው። በሰላም ወደ ሀገርህ ተመለስ በአመንዝራዪቱ ሴት ምክንያት በዚኽን ጊዜ ከአንተ ዘንድ ተነሥቶ ይሔዳል። እኔም ወደ ሀገሩ ሲሔድ በዝም ሀገር ባለው ገደል በሚወስደው መንገድ ላይ እጠብቀዋለሁ። ባለሟሎቼንም ወደ ገደሉ ወርውረው እንዲገድሉት አዝዛቸዋለሁ" አለችው። ❤ እርሱም ይኸን ነገር ሰምቶ ምክሯ ደስ አሰኘው። አቡነ ታዴዎስንም ከአለበት ሥፍራ አስጠርቶ "አባቴ ሆይ! ከእንግዲኸ ከአዘዝኸኝ ወደ አመንዝራዪቱ ሴት አልደርስም፤ በሰላም ወደ ቤትህ ተመለስ፤ በጸሎትህም አስበኝ። ቅድም ስለ ተቈጣሁህ ይቅርታ አድርግልኝ፤ ይቅርታ ማድረግ ልማድህ ነውና። ስለ ይቅር ባዩ ጌታችንና አምላካችን ኀጢአቴን ይቅር በለኝ" አለው። አቡነ ታዴዎስም "ይኸ ንግግር እውነት ከኾነ ስለ አምላኬ ቅዱስ ስም ይቅር ብያለሁ፤ ነገርህ በሽንገላ ከኾነ ግን ስለ እኔ ፈንታ እግዚአብሔር ይበቀልሃል" አለው። ይኸንንም ተናግሮ ከንጉሥ ዘንድ ተነሥቶ ወደ ሀገሩ ተጓዘ። ❤ ወደ ዝም ሲወርድ ሳለ ሴቲቱ በንጉሥ ፈረስ ተቀምጣ ከባለሟሎቿ ጋር ከኋላው ተከተለችው። ወደ ዝም አፋፍ በደረሰም ጊዜ ብርቱዎች የኾኑት ባለሟሎቿ ጓደኛውና የአቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽ በሥጋም ዘመዱ ከኾነ ከአባ ማትያስ ጋር ይዘው ቃጭ ነጭሎ ከተባለ ሐረግ በተሠራ ጠንካራ ገመድ አሰሯቸው። ከአፋፉም ላይ ወደ ዝም ገደል ወረወሯቸው። የእግሮቻቸውና የጎኖቻቸውም አጥንቶች ደቀቁ። ስለ ጌታችንም ስም በሰማዕትነት ዐረፉ። ❤ ከዚኸ በኋላ ያች አመንዝራ ሴት ተመልሳ የሞታቸውን ዜና ለንጉሥ ነገረችው። እርሱም ልቡ በኀዘን ታወከ። የሚወዳቸው ሰራዊቱንም "በሉ እንግዲኸ ከሰማይ ኵነኔ እንደማላመልጥ አሁን ዐውቄአለሁ። አባ ፊልጶስንም ከክብሩና ከሹመት ወንበሩ አሳድዱት። አኖሬዎስንም በቆዳ ጅራፍ ግረፉት፤ ያለ ኀጢአት በድፍረት አውግዘውኛልና። ዐዋጅ ነጋሪም ታዴዎስና ማትያስ ወደ ዝም በሚወስደው ገድል ሲወርዱ ሞተዋል፤ እነርሱ እኔን ቢያወግዙኝ አምላኬ በግዛቴ ገደል ከተታቸው። ከእነርሱ ጋር የተባበረ ሰው ኹሉ ከሀገሬ ይሰደዳል፤ እንደ እነርሱም በሰይፌ ይሞታል" ብሎ ትእዛዜን ያውጅ" አላቸው። ❤ ከዚኸ በኋላ ገብረ እግዚአብሔርና ውቢት የተባሉት የተመረጠች የማርያም ሴት አገልጋይ ከኀጢአት የነጹ በኖቻቸውን ወስደው በዝም ቀበሌ በገርማሜ ወንዝ አጠገብ ትልቅ ነጭ ዋሻ ውስጥ ቀበሯቸው። ወደ ገደሉ በወረወሯቸው ጊዜ በጥር ፳፱ ቀን ከምሽቱ 6  የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ ወረደ። በዚያች ቀን የአቡነ ታዴዎስ የዕረፍት ሰዓት የወንድሙ የብፁዕ ትያስም ልደቱ በጌታችንና አምላካችን የመገለጥ ወር በጥር 29 በአንድነት ኾነ። እንደዚኹ ለሕይወትና ለደስታ የኾነ ዕረፍታቸውም ቀን በአንድ ላይ ኾነ። ❤ ስለዚኽህ ነገር ገብረ እግዚአብሔርና ውቢት የተባለችዪቱን ሴት የአቡነ ታዴዎስ ደቀ መዛሙርት ዘሚካኤልን የብፁዕ ማትያስንም ደቀ መዝሙር አባ ፊንሐስን ለብፁዓዊ አቡነ ታዴዎስ ለተገባለት ቃል ኪዳን ምስክሮች ሊኾኑ ዘንድ ይጠራቸው  ጌታችን ሳይወርድ በፊት ብርሃናዊ የአምላክ መልአክ ጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ወረደ። ❤ በመጀመሪያው ዕለት በጥር ፳፱ ቀን ከሌሊቱ በ፮ ሰዓት፤ ዳግመኛ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን መላእክቱን ሚካኤልና ገብርኤልን ሱራፌልና ኪሩቤልን ከየነገዶቻቸው  ፺፱ኙን ነገደ መላእክት ኹሉ አስከትሎ በአንዲት ቃል "ለአምላካችን ምስጋና ይገባል፤ ስለ ስሙ የሞቱ እኒኸን ቅዱሳን ለሠወራቸው ለፈጣሪያችን ምስጋና ይኹን" እያሉ እያመሰገኑት በድናቸው ወደወደቀበት ታላቅ ገደል ወረደ። እልፍ አእላፋት መላእክት ክንፎቻቸውን በአባቶቻችን ታዴዎስና በማትያስ ላይ ረበቡ። እመቤታችን ድንግል ርያም በልጇ ቀኝ ነበረች። ቅዱስ ዳዊትም ከመዝሙሩ "የጻድቅ ሰው ሞት የከበረ ነው፤ ክብሩም ከፍ ይላል፤ ጻድቃን ሞታቸው በአምላካቸው በእግዚአብሔር ፊት ሕይወታቸው ነው" ብሎ እየዘመረ በቅዱሳኑ ፊት ቆመ። ❤ በዚኸን ጊዜም በዚያችው ሌሊት ጌታ እግዚአብሔር አየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያቱ በአካል ተገልጦ ከአምላክነት ገንዘቡ ሥልጣንን፤ ከትምህርታቸው የተነሣ ለሚያምኑበት ሰዎች የሕይወት ቃል ኪዳን እንደሰጣቸው እነርሱም ተገለጠላቸው። ደግ ብርሃናዊ መልአኩ ለወዳጆቹ ለአባ ታዴዎስና ለአባ ማትያስ ለሚሰጣቸው ቃል ኪዳን ምስክሮች ይኾኑ ዘንድ ለጠራቸውም ሰዎች ተገለጠላቸው። እንዲኸም አላቸው፡- "የተመረጣችሁ ባለሟሎቼ (ምነግራችሁ ቃሌን ስሙኝ፤ እኔ ከአባቴና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የፈጠርሁት መታሰቢያቸውን የአደረገ፤ ስማቸውን የጠራ፤ ብዙዓን የወዳጆቼ የታዴዎስንና የማትያስን የጽድቃቸውን ምስክርነት ሰምቶ በእኔ አምኖ የተጋድሏቸውን መጽሐፍ ። የጻፈውንና ያጻፈውን እኔ ከክፉ ነገር ኹሉ ከጥፋትም አጠብቀዋለሁ። የእኔን ትእዛዝ ለመፈጸም እንደ ሐዋርያቴ ነፍሳቸውን ለሞት አሳልፈው ሰጥተዋልና"። ❤ "ከዚኸ ከዕረፍታቸው ቀን አስቀድሞ በሌሊት ጸሎት የማድረስና የሃይማኖትን ትምህርት ለማስተማር በቀን በብርድም፤ በፀሐይ ንዳድም፤ የአካላቸውን ልምላሜ እያደረቀው በየወረዳው የእናቴ ርስት ወደኾነች ወደ ኢትዮጵያ አድባራትም ኹሉ ፍጥረትን ኹሉ ለሞት ከመገዛት ከመታደግ ከንጽሕት ማርያም መወለዴን ያስተምሩ ዘንድወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገሠግሡ ብዙ ደክመዋል፤ በእጅግም ተንገላተዋል። "በስማቸው ድኾችንና ጦም አዳሪዎችን እንጀራ ማብላት፤ ብርዝ በማጠጣት፤ ጥቂትም ቢሆን ያገኘውን የአቅሙን መታሰቢያቸውን የሚያደርግ ሰው በደልም ኀጢአት ቢሠራ የልደቴና የመገለጫዬ መታሰቢያ በኾነ የወዳጆቼ የታዴዎስና የማትያስ ዕረፍት ቀን በጥር ፳፱ ቀን እኔ የኀጢአቱን ጽሕፈት እደመስሳለሁ"።

❤ ዮሴፍም ከዋሻ ገብቶ በሰባት ቀን እየጾመና እየጸለየ በገድል ተጠምዶ ሃያ ስምንት ዓመት ያህል ኖረ ከዚህም በኋላ ዕረፍቱ እንደቀረበ በአወቀ ጊዜ የቅዱስ ጊዮርጊስ ወደሆነች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ በቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ፊት ቁሞ ወደ ተወዳጅ ልጅዋ ትማልድለት ዘንድ ለመናት ከሥዕሉ ውስጥም እንዲህ አለችው "ዮሴፍ ሆይ በሦስተኛው ቀን በሦስት ሰዓት ወደኔ ትመጣለህና ደስ ይበልህ" በዚያችም ዕለት ጥር 28 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ዮሴፍ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለቀሌምንጦስ_ዘተበፅዐ_ትግሥቱ። በዐውደ ምኵናን ኃምስቱ። በብዙኅ ኵነኔ እምድኅረ ኰነንዎ ሎቱ። #እግዚአብሔር አስተቀጸሎ ህየንተ ፍሉሕ ሩጸቱ። #ከመ_ጊዮርጊስ_በአክሊል_ሰብዓቱ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር_28።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወይኤምሮ ፍኖተ ለልቡባን። ኵሉ ፍኖቱ ለእግዚአብሔር ሣህል ወጽድቅ። ለእለ የኀሡ ሕጎ ወስምዖ። መዝ 24፥9። የሚነበበው ወንጌል ማር 10፥1-13።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወአዝነመ ሎሙ መና ይብልዑ። ወወሀቦሙ ኅብስተ ሰማይ። ወኅብስተ መላእክቲሁ በልዑ እጓለ እመሕያው"። መዝ 77፥24-25 ወይም መዝ መዝ 64፥4-5። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 11፥8-17፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም፣ የሐዋ ሥራ 2፥32-40። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 15፥32-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የአምላካችን የቅዱስ አማኑኤል በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።                

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤              ❤ #ጥር ፳፰ (28) ቀን። ❤ እንኳን #ለአምላካች_ለቅዱስ_አማኑኤል ተአምራት አድርጎ አምስት እንጀራንና ሁለት ዓሣን አበርክቶ ሕፃናትና ሴቶች ሳይቆጠሩ አምስት ሺህ (አምስት የገብያ ሕዝብ ለመገበበት (ላጠገበበት) ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል፣ ኪራኮስ ከሚባል አገር ስሟ አክሮስያ የምትባል ለመበለት ልጅ ሰባት ጊዜ ታላላቅ አሠቃቂ መከራዎችን በመቀበል ሰማዕትነቱን ለፈጸመው ለከበረ #ለቅዱስ_ቀሌምንጦስ ለዕረፍቱ በዓል፣ ፍዩም ከሚባል ሀገር ለሆነ ሰይጣን ይዞ በራሱ ጠጉር አሥሮ ለቀጣው ለከበረ መነኰስ #ለአባ_አካውህ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና፣ ለከበረ ለአይሁዳዊ ለማኅው ልጅ እመቤታችን ከእሳት ውስጥ አውጥታ ላዳነችው በዕረፍቱም ጊዜ "በሦስተኛው ቀን በሦስት ሰዓት ወደኔ ትመጣለህና ደስ ይበልህ" ላለችው #ለቅዱስ_ዮሴፍ ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ ሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_አባ_አካውህ_ማኅበር ከስምንት መቶ ሰማዕታት፣ ከአባቶቻችን #ከቅዱሳን_አብርሃም_ከይስሐቅና_ከያዕቆብ፣ #ከሠልስቱ_ደቂቅና_ከታቤላ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ቀሌምንጦስ፦ ይህም ቅዱስ ኪራስ ከሚባል አገር ስሟ አክሮስያ የምትባል የመበለት ልጅ ነው። ሰማዕት የሆነው በገላትያ ነገሥታት በአርያኖስና በሉቅዮስ ዘመን ነው ከታናሽነቱም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሥርዓቷንና ሕጓንም እናቱ አስተማረችው ዕድሜውም ዐሥራ ሁለት ዓመት ሲሆነው በጾምና በጸሎት መጋደል ጀመረ አገልግሎትንም አበዛ በእሳት የበሰለ ሥጋም ቢሆን አይበላም ነበር። እንደ ሠለስቱ ደቂቅ ጥሬ ባቄላ የሚመገብ ሆነ እንጂ ዲቁናም ተሾመ ጥበብና እውቀትም ተጨመረለት። ❤ ወሬውም በንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ በተሰማ ጊዜ ወደርሱ አስቀርቦ ብዙ ሸነገለው ለርሱም ልጁ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ትእዛዙንም ባልሰማ ጊዜ ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው እግዚአብሔርም አጸናው ያለ ጉዳትም በጤንነት አስነሣው ከሀድያንን አሳፈራቸው። በዚያንም ጊዜ የምስክርነቱ ተጋድሎ በዲዮቅልጥያኖስ እጅ ሰባት እስቲደርስ አንድ ተብሎ ተቈጠረለት። ❤ ማሠቃየቱንም በደከመ ጊዜ ዲዮቅልጥያኖስ ወደ ሮሜ ንጉሥ ላከው እንዲህም ብሎ ጻፈ "ይህ መሠርይ ከቶ እንደርሱ ያለ መሠርይ አላየሁም ለአማልክትም ይሠዋ ዘንድ ምናልባት ልቡን መመለስ። ብትችል እነሆ ወዳንተ ላክሁት"። ወደ ሮሜው ንጉሥም በደረሰ ጊዜ የወርቅ ልብሶችን አመጡለት እነርሱም ወደ ልብሶች አልተመለከተም ንጉሡም በእርሱ ላይ ተቆጣ ቊጣውንም አልፈራም በዚያንም ጊዜ በመንኰራኵር ታላቅ ሥቃይን አሠቃየው ገረፈውም ሕዋሳቱን አስቆራረጠ እግዚአብሔርም እንደ ቀድሞው ያለ ጥፋት በጤንነት አስነሣው ይህም ሁለተኛ ምስክርነት ነው። ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ወደ መክስምያኖስ ላከው በዚያም ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃዩት ጌታችንም እንደቀድሞው በጤንነት አስነሥቶት ጠላቶቹን አሳፈራቸው ይህም ሦስተኛ ምስክርነት ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ አደገባት ወደ ኪራስ ከተማ መለሱት በዚያም አሠቃዩት ጌታችንም በጤንነት ያለሥቃይ አስነሣው ይህም አራተኛ ምስክነት ነው። ዳግመኛም ወደ መክስምኖስ መለሱት በዚያም ቅዱስ ከልከላዎስንና ብዙ ሰማዕታትን አግኝቶ እርስ በርሳቸው ተጽናኑ የከበረ ቀሌምንጦስንም ጽኑ ሥቃይን አሠቃዩት ጌታችንም እንደቀድሞው አዳነው ይህም አምስተኛ ምስክርነቱ ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ መኰንን ሉቅዮስ ወሰዱትና በዚያ አሠቃዩት ጌታችንም አዳነው ይህም ስድስተኛው ምስክርነት ነው። ሰባተኛውም ምስክርነት ብዙ ከአሠቃዩ በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጡ ሶፍያ የምትባል አማኒት ሴት መጥታ የቅዱሱን ሥጋ ወስዳ ገንዛ ቀበረች። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ቀሌምንጦስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_አካውህ፦ ይህም ቅዱስ ፍዩም ከሚባል አገር ነው በምንኵስናም ታላቅ ተጋድሎን ሲጋደል የኖረ ነው ሰይጣንም ተገልጦ መጣበት ቅዱስ አካውህም ሰይጣንን ይዞ በራሱ ጠጉር አሠረውና ሊቀጣው ጀመረ። ሰይጣንም "ትለቀኝ ዘንድ በክርስቶስ መከራዎች አምልሃለሁ" ብሎ ጮኸ በዚያንም ጊዜ ሰደደው እንደ ጢስም ተበተነ። ❤ ከዚህም በኋላ በስደት ወራት ወደ ከሀድያን አደባባይ ሔደና "እኔ ክርስቲያን ነኝ" ብሎ ጮኸ ከሀድያንም ጽኑ ሥቃይን አሠቃይተው ጥር28 ቀን ራሱን በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አካውህ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ #የከበረ_አይሁዳዊ°የማኅው_ልጅ_ቅዱስ_ዮሴፍ፦ ይህም ቅዱስ እስራኤላዊ ነው የአይሁድንም ሃይማኖት እየተማረ አደገ መጻሕፍቶቻቸውንም ተማረ። በአንዲትም ዕለት እየተማሩ ሳለ የክርስቲያንን ልጆች አያቸው ከእርሳቸውም ጋር ትደምረው ዘንድ እናቱን ለመናት። በደመረችውም ጊዜ የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ሁሉ ተማረ የክርስቶስ ሃይማኖት ፍቅርም በልቡ አደረ ከዚህም በኋላ የቤተ ክርስቲያንን ሕግ ከሚወድና ከሚጠብቅ ከአንድ ክርስቲያናዊ ወጣት ጋር ተገናኘ እርሱም በቊርባን ጊዜ ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰደው ዮሴፍም ሥጋውንና ደሙን ተቀበለ። በማግሥቱም አናጒንስጢሶችና መዘምራን ከዮሴፍ ጋር ተሰበሰቡ ልብሶቻቸውንም እንደ ድንኳንና እንደ መጋረጃ አምሳል በመሥራት ከቤታቸው ዳቦ አመጡ በጨዋታ መልክ ከውስጣቸው ሊቀ ጳጳሳትን ኤጲስቆጶሳትን ሾሙና የቊርባን ሥርዓት ሠሩ ወደሚያስተምራቸውም መምህር ቤት ሔደው ይበሉ ይጠጡ ነበር እንዲህም እያደረጉ ኖሩ። ❤ የዮሴፍ አባት በሰማ ጊዜ ቊጣን ተመልቶ ልጁን የግንግሪት አሠረው በውጡ እሳትን የተመላ ጒድጓድ ወዳለበት ወህኒ ወስዶ ጨመረውና በላዩ የእቶኑን በር ዘጋበት የእግዚአብሔርም መልአክ እሳቱን አቀዘቀዘው እናቱ ግን ልጅዋን በአጣችው ጊዜ በመጮህ አለቀሰች የምታደርገውንም አጣች። ከሰባት ቀኖችም በኋላ የዮሴፍን ወሬ ወደ እሳት እንደተጨመረ ባልጀሮቹ ሰምተው በመጮህ እያለቀሱ ስሙንም እየጠሩ መጡ ዮሴፍም ከውስጥ እንዲህ ሲል መለሰላቸው "በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት በእመቤቴ ማርያም ርዳታ እኔ በሕይወት አለሁና ወንድሞቼ አታልቅሱ እርሷም ከእሳቱ በልብሷ ሸፍና አድናኛለችና" ይህንን በሰሙ ጊዜ ለሊቀ ጳጳሳቱ ነገሩት። እርሱም ወዲያውኑ ተነሣ ከካህናቱ ጋር ወንጌልን መስቀልንና ማዕጠንቶችን ይዘው ሔዱ ወደ እቶኑም በደረሱ ጊዜ ጸሎትን አድርገው ዮሴፍን ከማሠሪያው ፈትተው አወጡት። አባቱ ማኅውም በሰማ ጊዜ መጥቶ ከሊቀ ጳጳሳቱ እግር በታች ወድቆ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ የክርስትና ጥምቀትንም ያጠምቀው ዘንድ ለመነውና ከቤተ ሰቦቹ ሁሉ ጋር አጠመቀው።

❤ ከጥቂት ቀኖች በኋላ በአውሲም ከተማ መኰንኑ አርያኖስ ደረሰ፡፡ የሀገሩን ታላላቅ ሰዎችንም አቅርቦ ስለከበረ ቅዱስ ቢፋሞን ጠየቃቸው፡፡ የአገር ሽማግሎችም ስለእርሱ አዘኑ-እርሱ ተአምራትን የሚያደርግ አማልክትንም የሚረግም መሆኑን ያውቃሉና፡፡ ወዲያውም ቅዱስ ቢፋሞን ቤተሰቦቹን ተሰናብቶ ያማሩ ልብሶቹን ለብሶ ፈረስ ጋልቦ የሀገሩ ሽማግሎችና መኮንኑ ካሉበት ቦታ ደረሰ፡፡ መኮንኑ አርያኖስም ባየው ጊዜ ደስ ብሎት በክብር ሰላምታ ሰጠው፡፡ ❤ ቅዱስ ቢፋሞንም "የሰላም ትርጓሜው ደስታ ነው፣ እኔ በጌታዬና በፈጣሪዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ደስታ አለኝ አንተና ባልንጀሮችህ ግን በሰማያት ደስታ የላችሁም" አለው፡፡ አርያኖስም "እኔ ክፉ ነገርን እንድትነግረኝ አልመጣሁም፣ ለአማልክት እንድትሠዋ በንጉሡ ደብዳቤ ታዝዤ መጣሁ እንጂ" አለው፡፡ ቅዱስ ቢፋሞንም "አማልክቶቻችሁ አፍ እያላቸው የማይናገሩ፣ እጅ እያላቸው የማይዳስሱ፣ ጆሮ እያላቸው የማይሰሙ፣ ዐይን እያላቸው የማያዩ፣ አፍ እያላቸው የማይተነፍሱ ናቸውና የሠሩአቸውና የሚያመልኳቻም እንደ እነርሱ ይሁኑ፡፡ እኔ ግን ሰማይንና ምድርን በውስጣቸውም ያለውን ሁሉ ለፈጠረ ለጌታዬ ለፈጣሪዬ ለኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ አሰግዳለሁ" አለው፡፡ መኰንኑ አርያኖስም ይህንን ነገር ከቅዱስ ቢፋሞን አፍ በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ፡፡ ጽኑ በሆኑ ልዩ ልዩ ማሠቃያዎችም አሠቃየው፡፡ ዳግመኛም በፈረሶች ላይ አሥሮ መሬት ለመሬት እየጎተተ ከተማውን ሁሉ አዞረው፡፡ የቅዱስ ቢፋሞን እናቱና አገልጋዩ በመጡ ጊዜ በከበረች የወንጌል ቃል አጽናናቸው፡፡ እነርሱና ሌሎችም የከተማው ሰዎች "እኛም በቅዱስ ቢፋሞን አምላክ የምናምን ነን፣ ሰማዕትም እንሆን ዘንድ እንወዳለን" ብለው ጮኹና የመኰንኑን ለወንበር ገለበጡት፡፡ መኰንኑም ጥልቅ ጉድጓድ አስቆሮ እሳት አስነድዶ ከዚ ውስጥ ጨመራቸውና ሰማዕትነታቸውን በድል ፈጽመው የድል አክልሊን ተቀዳጁ፡፡ ቁጥራቸውም አምስት መቶ ሆነ፡፡ እነዚህም 500 ቅዱሳን ምስክርነታቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ቅዱስ ቢፋሞን ያጽናናቸውና ያበረታቸው ነበር፡፡ የከበረች እናቱም በላይዋ ላይ እንዲጸልይ ለመነችው፣ እርሱም በመስቀል ምልክት በላይዋ አማተበና በሰላም ሂጂ አላት፡፡ እርሷም ወዲያው ማንም ሳይነካት ዘላ ከእሳቱ ገባች፡፡ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለች፡፡ ❤ የከበረ ቅዱስ ቢፋሞንን ግን አርያኖስ ወደ ንጉሡ መክስምያኖስ ሰደደው፡፡ ንጉሡም "የነገሥታቱን ትእዛዝ የምትተላፍ ለአማልክት የማትሠግድ ሥራየኛው ቢፋሞን አንተ ነህን?" አለው፡፡ ቅዱሱም "እኔ ሥራይን አላውቅም፣ ለረከሱ አማልክትህ ግን አልሰግድም፣ አንተም እነርሱም በአንድነት ወደ ገሃነመ እሳት ትወርዳላችሁ" አለው፡፡ ንጉሡም ይዞ በእጅጉ አሠቃው፡፡ ማሠቃየትም በሰለቸው ጊዜ ወደ መኮንኑ ኄሬኔዎስ ላከው፡፡ እርሱም ካሠቃው በኋላ መልሶ ለአርያኖስ ላከው፡፡ በእነዚህም ጊዜ ቅዱስ ቢፋሞን ምንም አልበላም ነበር፡፡ አርያኖስም በብረት ችንካሮች ቸነከረውና "ለአማልክት ካልሰገድክ አጠፋሃለሁ" አለው፡፡ ቅዱሱም ንጉሡንና አማልክቱን ረገማቸው፡፡ መኰንኑም በዚህ ጊዜ አሥሮ እየጎተተ በከተማው ሁሉ አዞረው፡፡ ከእንዴና ከተማ ውጭ አውጥቶ በእሳት አቃጠለው፤ ነገር ግን ጌታችን ቅዱስ ቢፋሞንን ከእሳቱ ውስጥ ያለምንም ጉዳት በደህና አወጣው፡፡ ቅዱሱም በእሳት ቆሞ ሳለ ከእግሮቹ ብዙ ደም ፈሰሰ፡፡ በዚያም ቦታ አንድ ዐይነ ሥውርና ለምጻም ሰው ነበረ፡፡ እርሱም ከቅዱስ ቢፋሞን ደም ወስዶ ዐይኑን ቢቀባው ወዲያው ማየት ቻለ፣ ከለምጹም ነጻ፡፡ ከዚህም በኋላ "እኔም በቅዱስ ቢፋሞን አምላክ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኛለሁ" ብሎ ጮኸ፡፡ ወዲያውም መኰንኑ ተናዶ ራሱን በሰይፍ አስቆረጠውና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ መኰንኑ አርያኖስ የቅዱስ ቢፋሞንንም አንገት በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ ቅዱስ ቢፋሞንም አገልጋዩን ዲዮጋኖስን ወደ እርሱ አቅርቦ ሥጋውን በስውር እንዲጠብቅ ደሙንም በበፍታ ልብስ እንዲቀበል ይኸውም ከመከራው ዘመን በኋላ ለበረከት እንዲሆን ነገረው፡፡ ገድሉንም ለምእመናን እንዲነገር ከነገረው በኋላ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብሎ በመስቀል ምልክት አማተበና ወደ ጭፍሮቹ ሄዶ "የታዘዛችሁትን ፈጽሙ" በማለት እንዲሰይፉት ራሱን አሳልፎ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ወደ ላይኛው ግብጽ አጥማ አውራጃ ወስደው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና የሰማዕትነት ፍጻሜው ሆነ፡፡ የተዘጋጀለትንና አስቀድሞ ያየውን የክብር አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ፡፡ ከአንገቱም ብዙ ደም በፈሰሰ ጊዜ አገልጋዩ ዲዮጋኖስ በፍታውን ዘርግቶ ደሙን ተቀበለ፡፡ በቦታው መዓዛው እጅግ ጣፋጭ የሆነ ሽታ በሸተተ ጊዜ ችፍሮቹ ደንግጣና ፈርተው ከቦታው ሸሹ፡፡ ምእመናንም መጥተው ሥጋውን ወስደው በክብር ገንዘው ቀበሩት፡፡ ከመቃብሩም ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ፡፡ ❤ አገልጋዩም ያችን በፍታ ወደ አገሩ ወስዶ ምን እንደሚያደርግ እያሰበ ሳለ ቅዱስ ቢፋሞን ተገለጠለትና ለወዳጁ ለቴዎድሮስና ለአገሩ ሰዎችም ሁሉ ገድሉን እንዲነግር አዘዘው፡፡ እርሱም በመርከብ ተሳፍሮ ሲሄድ በመርከብ ሳለ ጌታችን በዚያች በቅዱስ ቢፋሞን ደም በታለለች በፍታ ብዙ ተአምር አደረገ፡፡ ዲዮጋኖስም የቅዱሱን ገድል ነገራቸው፡፡ እነርሱም እያደነቁ ወደ አገሩ አውሲም አደረሱት፡፡ ዲዮጋኖስም አውሲም እንደደረሰ ለቅዱስ ቴዎድሮስና ለአገሩ ሰዎች ሁሉ የቅዱስ ቢፋሞንን ገድል ነገራቸው፣ ያችንም በደሙ የታለለች በፍታ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ብዙ ተአምራት እያደረገችላቸው ከእነርሱ ጋር በክብር አኖሯት፡፡ ❤ የመከራው ዘመን አልፎ ደገኛው ንጉሥ ቆስጠንጢኖስ ከነገሠ በኋላ እግዚአብሔርም የከበረ የቅዱስ ቢፋሞንን ሥጋ ለምእመናን አለኝታና መጽናኛ ለበሽተኞችም የሚፈውስ ኃይል እንዲሆን ሊገልጠው ወደደና ገለጠው እርሱም በላይኛው ግቡጽ በጥማ አውራጃ በቃው ከተማ በጥር ሃያ ሰባት በዚች ቀን በሰማዕትነት የሞተ ነው ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በተጋዳይ በቅዱስ ቢፋሞን ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን፡፡ ምንጭ፦ የጥር 27 ስንክሳር።                                                         ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለከ_እንተ_ረከብከ_ሞገሰ። ኅቡአተ ትፍትን ወዘማዕቅት ከርሠ። #ሱርያል_መልአክ እንዘ ትስእል መንፈሰ። ፍጥረታተ ኵሎ አመ በማየ አይኅ ደምሰሰ። እግዚአብሔር አትረፈ ሰማኒተ ነፍሰ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥር _27።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ኵሉ ማዕበልከ ወሞገድከ እንተ ላዕሌየ ኃለፈ። ዓልተ ይኤዝዝ እግዚአብሔር ሣህሎ ወሌሊተ ይነግር። እምኀቤየ ብፅዐተ ሕይወትየ ለእግዚአብሔር"። መዝ 41፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 5፥1-6፣ ይሁ 1፥20-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 14፥21-24። የሚበበው ወንጌል ማቴ 16፥1-5። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የመልአኩ የቅዱስ ሱርያል የመታሰቢያ በዓልና የቅዱስ ኄኖክ የዕርገቱ መታሰቢያ በዓል፣ የጾም፣ የጸሎት፣ የምህላ ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።                  

❤ ከዚህም በኋላ የከበረ ሰራብዮንን ወደ አገሩ ከእርሱ ጋር ወስዶ ያሠቃየው ዘንድ ከኀሳቡም ካልተመለሰ ራሱን በሰይፍ ይቆርጥ ዘንድ ኄሬኔዎስ አንዱን መኰንን አዘዘው። መኰንኑም ከርሱ ጋር በመርከብ ወሰደው ሌሊትም በሆነ ጊዜ ወደ አንድ ወደብ ደርሰው በዚያ ተኙ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ያቺ መርከብ ወደ ቅዱስ ሰራብዮን አገር ደረሰች በጥዋትም በነቁ ጊዜ የመሔጃቸው አቅጣጫ ተለውጦ አገኙ እጅግም አደነቁ ወደ ሰራብዮንም "እነሆ ይቺ አገርህ ናት" የሚል ቃል ከሰማይ መጣ ከመርከብም አውርደው ታላቅ ሥቃይን አሠቃይተው ጥር27 ቀን ራሱን በሰይፍ ቆረጡት በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ። መኰንኑም ልብሶቹን አውጥቶ ገንዞ ለዘመዶቹ ሰጠው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕቱ በቅዱስ ሰራብዮን በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ቢፋሞን፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ድንግል የሆነ እግዚአብሔርን የሚወድ ለድኆችና ለችግረኞች የማሚመጸውት ይህንንም ዓለም ንቆ የተወ ነው። አባቱም ከከበሩ ወገኖች የሆነ ስሙ አንስጣስዮስ የእናቱም ስም ሶስና ነው። እነርሱም መመጽወትን የሚወዱ ክርስቲያኖች ናቸው የጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የእመቤታችንን ድንግል ማርያምን የከበሩ ሰማዕታትንም ሁሉ በዓላት ለድኆችና ለምስኪኖች ምጽዋትን በመስጠት ያከብራሉ የሚኖሩትም በምስር አውራጃ አውሲም በሚባል አገር ውስጥ ነው። ❤ እግዚአብሔርም ደግነታቸውን ተመልክቶ መልኩ እጅግ ያማረ ልጅ ቅዱስ ቢፋሞንን ሰጣቸው፡፡ እነርሱም ገና ሲወልድ ጀምሮ ብዙ ተአምራት አድጎላቸዋልና እጅግ አላቸው፡፡ በሃይማኖት በምግባር ኮትኩተው አሳደጉት፡፡ ዘጠኝ ዓመትም በሆነው ጊዜ ሃይማኖትንና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እንዲማር ለአንድ መምህር ሰጡት፡፡ ከመምህሩም ዘንድ ጥበብንና ተግሣጽን የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት ሁሉ አጠና፡፡ ከልጅነቱም ጀምሮ በጾም በጸሎት በስግደት ይጋደል ነበር፡፡ እግዚአብሔር ለቅዱስ ቢፋሞን ገና በልጅነቱ በእጆቹ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን የማድረግ ጸጋ ሰጠው፡፡ በቁስል ደዌ እጆቹንና እግሮቹን የታመመ አንድ ድኃ ቅዱስ ቢፋሞንን ምጽዋት ቢለምነውና ቅዱሱም በእጆቹ ቢነካው ወዲያው ከደዌው ድኖ ጤነኛ ሆነ፡፡ ❤ ሁለተኛም በሌላ ጊዜ በቅዱስ ዳዊት መዝሙር ሲያመሰግን ከዚያ አንድ ጋኔን የሚጥለው ሰው ነበረና "የእግዚአብሔር ቅዱስ ሆይ ተወኝ፣ ከዚህ ቦታ ልጥፋ" ብሎ ጮኸ፡፡ ቅዱስ ቢፋሞን ወደ ጌታችን ጸልዮ ያንን ጋኔን ያደረበትን ሰው አዳነው፡፡ መምህሩም ይህን አይቶ በዚህ ሕፃን ልጅ ያደረውን ጸጋ አደነቀ አከበረውም፡፡ በመምህሩም ዘንድ 8 ዓመት ኖረ፡፡ ጌታችንም ቅድስት እናቱን ድንግል ማርያምንና ቅዱሳኑን እያስከተለ እየመጣ ይገለጥለት ነበር፡፡ ❤ ቅዱስ ቢፋሞን በየሰባት ቀን በመጾም ተጋድሎውን ጨመረ፡፡ ከሰንበት በቀር አይበላም ነበር፡፡ ዕድሜው ከፍ ሲል ወላጆቹ ሚስት ሊያጋቡት አሰቡ፡፡ እርሱ ግን "በዚህ እንደጤዛ በሚያልፍ ዓለም ከሴት ጋር መኖር ለእኔ ምኔ ነው? ፍላጎቱም ዓለሙም ሁሉም ያልፋል" አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ በሰባተኛው ወር አባቱ ሲያርፍ ቅዱስ ቢፋሞን ንብረቱን ሁሉ አውጥቶ ለጦም አዳሪዎች ሰጣቸውና በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የተጠመደ ሆነ፡፡ በዚያም ወራት የፋርስ ሰዎች በሮም ሰዎች ላይ ጦርነት አስነሥተው ነበር፡፡ የሮሙ ንጉሥ በጦርነቱ ስለሞተ ሮም ያለንጉሥ ቀረች፡፡ መኳንንቱና የመንግሥት ታላላቅ ሰዎችም ተሰብስበው ከአገሮች ሁሉ ተዋጊዎች የሆኑ አርበኞችን ይሰበስቧቸው ዘንድ በየአገሩ አዘዙ፡፡ ከላይኛው ግብፅ ልበ ደንዳና የሆነ ስሙ አግሪጳዳ የሚባል ሰይጣን በልቡ ያደረበት ፍየል ይጠብቅ የነበረ ኃይለኛ ሰው ተገኘ፡፡ እርሱንም ወደ አንጾኪያ አገር ወስደው የፈረሶች ባልደራስ አድርገው ሾሙት፡፡ ❤ በአንዲት ዕለትም ሸንበቆ አንሥቶ ዋሽንት ሠርቶ ሲነፋ በፈረሶቹ ላይ ሰይጣን አደረባቸውና ፈረሶቹም እያሽካኩ ይጨፍሩ ጀመር፡፡ በጦርነት የሞተው ንጉሥ ሴት ልጅም በቤተ መንግሥት አዳራሽ ሆና ሲዘፍንና ዋሽንት ሲነፋ አግሪጳዳን አይታ ወደደችው፡፡ ሰይጣንም በልቧ የዝሙትን ፍላጻ ጨመረባትና ወደ እርሷ አስመጣችውና አገባችው፡፡ ስሙንም ዲዮቅልጥያኖስ ብላ ሰየመችውና አነገሠችው፡፡ ታናሽ እኅቷም በእርሷ ቀንታ መክስምያኖስ የሚባለውን አንዱን መኮንን መልምላ አገባችና ልብሰ መንግሥት አልብሳ አነገሠችው፡፡ መክስምያኖስና ዲዮቅልጥያኖስም በአንጾኪያና በሮም ተስተካከለው ነገሡ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ሰይጣን ተገለጠላቸውና እንዲህ አላቸው፡- "በንጉሡ ሴቶች ልጆች ላይ የዝሙትን ፍቅር በልባቸው ላይ አሳድሬ እንዲወዷችሁና እንዲያገቧችሁ ያደረኩት እኔ ነኝ፤ አሁንም ትእዛዜን ከሰማችሁ በምድር የሚኖረውን ሕዝብ ሁሉ በእጃችሁ ውስጥ አደርግላችኋለሁ፤ እናንተም ስገዱልኝ የብርና የወርቅ ምስልም ሠርታችሁ አማልክት በሏቸው፡፡ ስማቸውንም አጵሎን አርዳሚስ ብላችሁ ጥሯቸው፡፡ ሰዎችም ሁሉ ዕጣን እንዲያሳርጉላቸውና እንዲሰግዱላቸው እዘዙ፤ ያልሰገዱላቸውንም ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ ቁረጡ፤ ይህን ካደረጋችሁ መንግሥታችሁን አሰፋላችኋለሁ ካለዚያ ግን መንግሥታችሁ ታልፋለች" አላቸው፡፡ እነዚህም ሁለት ሰነፎች መክስምያኖስና ዲዮቅልጥያኖስም ለሰይጣን ሰገዱለትና "ያዘዝከንን ሁሉ እናደርጋለን ብቻ መንግሥታችንን አጽናልን" አሉት፡፡ በዚህም ጊዜ ኄሬኔዎስንና አርያኖስን በግብጽ አገር ላይ መኳንንት አድርገው ሾሟቸው፡፡ ለጣዖት የማይሰግዱትን ሁሉ እንዲገድሉ አዘዟቸው፡፡ የከበረ ቅዱስ ቢፋሞንም ይህንን ትእዛዝ በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ፡፡ ወዳጁን ቴዎድሮስን ጠራውና በክብር ባለቤት በጌታችን ስም ደማቸው አፍስሰው ሰማዕት ይሆኑ ዘንድ በምክር ተስማሙ፡፡ ❤ የቅዱስ ቢፋሞን ዜናው በሁሉ ዘንድ የታወቀ ነውና ወሬው ከሃዲው ንጉሥ መክስምያኖስ ዘንድ ተሰማ፡፡ መኳንንቶቹም "በምስር አውራጃ በአውሲም ከተማ የሚኖር ስሙ ቢፋሞን የሚባል ሰው አለ፣ እርሱም የነገሥታትን ትእዛዝ የሚተላለፍ አማልክትን የሚረግምና የሚያቃልል ነው" ብለው ለንጉሥ መክስምያኖስ ነገሩት፡፡ በዚህም ጊዜ ንጉሡ ቅዱስ ቢፋሞን ለአማልክት ካልሰገደ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጠው ትእዛዝ ጽፎ ለጨካኙ መኮንን ለአርያኖስ ላከለት፡፡ ደብዳቤውም ከመኮንኑ ዘንድ ሳይደርስ የታዘዘ የእግዚአብሔር መልአክ ለቅዱስ ቢፋሞን ተገልጠለትና በሰማዕትነት እንደሚሞት እናቱና አገልጋዩ ዲዮጋንዮስም አብረውት እንደሚሞቱ ከነገረው በኋላ ሰማዕትነቱን በትዕግስት እንዲፈጽም ነገረው፡፡ የተዘጋጀላቸውንም የክብር አክሊላት አሳየው፡፡ ቅዱስ ቢፋሞን ተነሥቶ ለእናቱ መልአኩ የነገረውን ነገራት፡፡ መልአኩ ለእርሷም ተልጦ ይህንኑ እንደነገራት ለልጇ ነገረችውና ለሰማዕትነት በመመረጣቸው በአንድነት እጅግ አላቸው፡፡ ሲጸልዩ አደሩና በነጋታው ቅዱስ ቢፋሞን ወዳጁን ቴዎድሮስን አስጠራውና ሁሉን ነገረው፡፡ ቀጥሎም "የመከራው ጊዜ ካለፈ በኋላ አንተ በዚህች አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ትሾማለህ ያንጊዜም በስሜ ቤተ ክርስቲያን ትሠራለህ" ብሎ ትንቢት ነገረው፡፡ ወዲያም ሰላምታ ተሰጣጡና ተሳስመው ተለያዩ፡፡

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤               ❤ #ጥር ፳፯ (27) ቀን። ❤ እንኳን #ሳፍራ_ለሚባል_ለመልአክ_ለቅዱስ_ሱርያል ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል፣ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ በሞት ፋንታ ለተሰውረው #ለነቢዩ_ቅዱስ_ኄኖክ ለዕርገቱ መታሰቢያ በዓል፣ ለከበረ ሐዋርያ #ለቅዱስ_ጢሞቴዎስ ከኤፌሶን አገር ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ ለሥጋው ፍልሰት በዓል፣ ከግብጽ ደቡብ ከታችኛዪቱ ምስር አውራጃ በብኑዲ ከምትባል መንደር ለሆነ ለከበረ #ቅዱስ_ሰራብዮን ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ከታናሽነቱ ድንግል ለሆነ እግዚአብሔርን ለሚወድ ለድኆችና ለችግረኞች ለሚመጸውት ይህንንም ዓለም ንቆ ለተወ በእሳት ተቃጥሎ ሰማዕትነት ለተቀበለ ለከበረ #ቅዱስ_ቢፋሞን ለዕረፍቱ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቸሩ_መድኃኔዓለም_ከስቅለቱ ከወራዊ መታሰቢያ፣ #ከሰማዕታት_ትውፍሎን_ከዮስና_ከሰርኒስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                               ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን #ሳፍራ_የሚባል_የመልአክ_ሱርያል በዓል ነው እርሱም #ከነቢይ_እዝራ ጋር የኖረ የተሠወረ ምሥጢርንም የገለጠለት ነው እርሱም ስለ ሰው ልጆች ወደ እግዚአብሔር የሚለምን ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሱርያል አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ በዚችም ዕለት #የያሬድ_ልጅ_ኄኖክን የመላልኤል ልጅ #የቃይናን_ልጅ_የኄኖስ_ልጅ_የሴት_ልጅ #የአዳም_ልጅ_ኄኖክን_መላእክት ይዘው አሳረጉት ይኸውም በመባርቅትና በነፋሳት ላይ ተጭኖ በመብረር ወደ ሰማይ ወስደው ከረቂቃን መላእክት ጋር አኖሩት የእግዚአብሔርም ትእዛዝ ጸሐፊ ተባለ። ❤ እንዲህም አለ "ከማደሪያው ከሚወጣው ከቅዱሱና ከገናናው በጸናች ኃይሉ ከሠራዊቱ ጋር በሲና ተራራ ከሚገለበጠው ጋር በመነጋገር ተመላለስኩ። ሁሉም ይፈሩ ነበር በውኃ ዳርም ሳለሁ የልመናቸውን መታሰቢያ ጻፍኩ እስከ አንጎላቸሁና ሕልም እንደሚያይ እስከምሆን ይችም በአርሞን ግራና ቀኝ ያለች አገር ናት"። በደብር ቅዱስ ለነበሩ ለኃጢአት ለሚተጉ ለሴት ልጆች ይዘልፋቸው ዘንድ ቃል እንደጠራውና እንዳሳየው ተናገረ። ❤ እንዲህ አለ "በበረድ ደንጊያ ወደ ተሠራ ታላቅ ቤት ቀረብኩ በበረድ ደንጊያ የተሠራ የዚያ ቤት ግድግዳ እንደ ሳንቃ ልዝብ ነው ከዚህ ቤት የሚበልጥም ሌላ ቤት አየሁ ደጃፉም የተከፈተ ነው በእሳት ቅጽርም የተሠራ በክብር ከሁሉ የሚበልጥ ነው። በውስጡም ከፍ ያለ የእግዚአብሔርን ዙፋን አየሁ መልኩም እንደ ውርጭ ነው አጎበሩም እንደሚያበራ ፀሐይ ነው ከዙፋኑም በታች የኪሩቤል ድምፅ ይሰማል። ዳግመኛም ወደ ሰባት ተራራዎች ደረስኩ ሦስቱ በምሥራቅ በኵል ሦስቱ በአዜብ በኵል ናቸው የመካከለኛው ግን ሰማይ ጠቀስ ነው የመላእክትም ጌታ በላዩ አለ"። ሌሎች አራት ገጾች ኪሩቤልን አየ ስለ ክርስቶስም እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "የዘመናት አለቃ ወደ ሆነው የሰው ልጅ ተጠራ ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ የነበረ ሆነ" ሁለተኛም "ለጻድቃን የጽድቅ በትር ለአሕዛብም ብርሃን ተስፋ ለሌላቸወሰ አለኝታ ይሆናል" አለ። ❤ በሰማይ ገጽ ስለሚመላለሱ ብርሃናት እንዲህ አለ "አንዱም አንዱ በየወገናቸው በሠለጠኑበትና በተሠየሙበት ጸንተው ይኖራሉ" ስለ ነፋሳትም መውጫዎች እንዲህ ብሎ ተናገረ "ሦስቱ በሰማይ ገጽ ሦስቱ በምድር ገጽ ሦስቱ በግራ ናቸው"። ስለ አዳምም እንዲህ አለ "እነሆ በሬ ከምድር ወጣ ፀዓዳም ሆነ" ስለ ሔዋንም "ሴት እምቦሳ ከርሱ ወጣች" አለ። ❤ ስለ ምኵራብም "ያንን አሮጌ ቤት እስከሚአሳንሰው ድረስ አየሁ አለ ምሰሶዎቹንም ከውስጡ አወጣ"። ስለ ቤተ ክርስቲያንም "ጌንን አሮጌ ቤት እስከሚአሳንሰው ድረስ አየሁ አለ ምሰሶዎቹንም ከውስጡ አወጣ"። ስለ ቤተ ክርስቲያንም "ጌታ አዲስ የበጎች ቤት አምጥቶ እስቲሠራ ድረስ አየሁ ከቀድሞውም ቤት የበለጠ ነው በጎችም ሁሉ በውስጧ ይሠማራሉ" አለ። ስለ ምእመናንም "የእሊህም በጎች ፀጒራቸው ንጹሕ ነጭ ነው የተበተኑትም ከአራዊት ጋራ ይሠማራሉ ሁሉም በአንድነት ተሰብስበው ገራሞች ሁነዋልና"። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ኄኖክ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የሐዋርያው_ቅዱስ_ጢሞቴዎስ ከኤፌሶን አገር ወደ #ቊስጥንጥንያ_ከተማ_የሥጋው_ፍልሰት፦ ጻድቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስም መንግሥትን በያዘ ጊዜ የከበሩ የሐዋርያትን ሥጋቸውን ከሰማዕታትም ብዙዎችን ከቦታቸው ሁሉ ወደ ቊስጥንጥንያ አፈለሳቸው ስለ ሐዋርያ ጢሞቴዎስም ሥጋ በኤፌሶን አገር እንዳለ ሰምቶ ካህናትንና ምእመናንን ላከ እነርሱም አፍልሰው ወደ ቊስጥንጥንያ አድርሰው በከበሩ ሐዋርያት ቤተ መቅደስ ውስጥ አኖሩት። በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ሰራብዮን፦ ይህም ቅዱስ ከግብጽ ደቡብ ከታችዪቱ ምስር አውራጃ በብኑዲ ከምትባል መንደር ነው። ቅዱሱም ብዙ የገንዘብ ጥሪት እንስሳትም አሉት አብዝቶ መመጽወትንም የሚወድ ነው ስደትም በሆነ ጊዜ የክርስቲያን ወገኖችን ፈልጎ ያሠቃይ ዘንድ መኰንኑ ኄሬኔዎስ በየአገሩ እንደሚዞር ሰማ ለርሱም ስማቸው ቴዎድሮስና ሁለተኛውም በግ አርቢ ሰርማ የሚባሉ ወዳጆች ነበሩት እነርሱም ተከተሉት ይህም ቅዱስ መኰንኑን ሊገናኘው ከአገሩ ወጣ መኲንኑንም በአገኘው ጊዜ በፊቱ ቁሞ ከወገኖቹ ጋር በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ መኰንኑም ሁሉንም አሠራቸው። ❤ የአገር ሰዎችም በሰሙ ጊዜ ሁሉንም ተሰበሰቡ መኰንኑን ገድለው ቅዱስ ሰራብዮንን ከእጁ ሊወስዱ ሽተው የጦር መሣሪያ በመያዝ ለጦርነት የተሰለፉ ሠራዊት ሁነው ደረሱ ቅዱሱ ግን ከለከላቸው እንዲህም አላቸው "እኔ በጌታዬ ክርስቶስ ስም ደሜን አፈስ ዘንድ በፈቃዴ የመጣሁ አይደለምን" መኰንኑም በመርከብ ተሳፍሮ ከዚያ ሔደ ቅዱሳኑም አብረውት ሔዱ። ወደ እስክንድርያ አገርም በደረሰ ጊዜ የከበረ ሰራብዮንን በመንኰራኵር ውስጥ ጽኑዕ ሥቃይ እንዲአሠቃዩት ወደ እሳት ማንደጃም ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ። ከዚህም በኋላ ከነዳጅ ድፍድፍና ቅመማ ቅመም ጋር በወጭት ውስጥ ቀቀሉት የሥጋውንም ሥሮች ቆረጡ በብረት ዐልጋ ላይም አስተኝተው በችንካር ቸነከሩት ይሁን ሁሉ ሥቃይም የሚታገሥ ሆነ የእግዚአብሔርም መልአክ ሥቃዩን ከላዩ ይቀበልለት ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ ከእንጨት ላይ ሰቅለው በፍላፃዎች ነደፉት የእግዚአብሔርም መልአክ እርሱን ከተሰቀለበት አውርዶ በእርሱ ፈንታ መኰንኑን አሥሮ ሰቀለው። የከበረ ሰራብዮንም እንዲህ አለው "ሕያው እግዚአብሔርን በክርስቶስ ስም የታሠሩትን ሁሉንም እስከምታወጣቸውና የሞታቸውን ፍጻሜ እስከምታዝዝ አንተ ከእዚህ ከተሰቀልክበት ዕንጨት እንደማትወርድ ዕወቅ"። በዚያንም ጊዜ ሁሉንም አውጥተው ራሷቻቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ የእሊህም ሰዎች ቊጥራቸው አምስት መቶ አርባ ነፍስ ሆነ።

✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስ በዓለ ንግስ በደብራችን እንዲህ ባለ ሁኔታ ተከብሮ አልፏል ።
+7
✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስ በዓለ ንግስ በደብራችን እንዲህ ባለ ሁኔታ ተከብሮ አልፏል ።