7 203
Suscriptores
+224 horas
-17 días
-1530 días
Archivo de publicaciones
7 203
Repost from ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ
"የምንኖረው ቀብር ከሟቹ ይበልጥ ፣ ሰርግ ከፍቅር ይበልጥ በሚያሳስብበት እና ቁሳዊ ነገሮች ከአእምሮ ብስለት ይበልጥ የሚከበርበት ዓለም ውስጥ ነው።
ይዘቱን በሚንቅ የማሸጊያ ባህል ውስጥ ነው የምንኖረው።"
ኤድዋርዶ ጋሊያኖ
@zephilosophy
7 203
Repost from አርምሞ🧘🏽♂
ሩሲያዊው ጸሃፊ አንቶን ቼኮቭ ስለወደቁ ማህበረሰቦች ተፈጥሮ ሲጠየቅ እንዲህ ሲል መልስ ሰጥቶ ነበር፡-
‹‹በወደቁ ማህበረሰቦች ውስጥ ለእያንዳንዱ ጥበበኛ አእምሮ አንድ ሺህ ሞኞች እና ለእያንዳንዱ አስተዋይ ቃል አንድ ሺህ ደደብ ቃላት አሉ። ብዙሃኑ ሁል ጊዜ ሞኞች ሆነው ይቆያሉ። በዚህም ምክንያታዊውን ሰው ያለማቋረጥ ያሸንፋሉ። በህብረተሰብ ውስጥ ለውይይት ግንባር ቀደም የሆኑ ተራ ርእሶችን ካየንና ተራ ሰዎች ዋናውን መድረክን ከተቆጣጠሩ ለእናንተ የሚያወሩት ከራሳቸው ማኀበረሰብ ያመጡትን ተራ ውድቀት ነው።
ለምሳሌ በዘፈኖች ውስጥ ትርጉም የለሽ ቃላት እየተዘፈነ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ሲጨፍሩ እና ደጋግመው ሲያዳምጡ ይታያሉ። እናም የዘፈኑ ባለቤት ታዋቂ፣ ዝነኛ እና ተወዳጅ ይሆናል። ሰው እንኳን በህብረተሰብ እና በህይወት ጉዳዮች ላይ የራሱ አስተያየት አለው።
ጸሃፊዎች እና ደራሲዎች ግን ማንም አያውቃቸውም፤ ከእቁብ ባለመቁጠር ዋጋ እንኳን ሳይሰጣቸው ሲያልፉ ይስተዋላል። አብዛኛው ሰዎች ስካርን ብሎም በከንቱ ወሬ መፍዘዝን ይወዳሉ። አዕምሯችንን እንድንስት የሚያደነዝዝና በማይረባ ነገር የሚያስቀን ሰው ደግሞ ወደ እውነት ከሚነቃንና እውነትን በመናገር ከሚጎዳን ሰው የተሻለ ቦታን ያገኛል። ስለዚህም ነው ዲሞክራሲ እና ሎጂክ ለደናቁርት ማህበረሰቦች የማይመቸው!። ምክንያቱም ብዙሃን አላዋቂዎች የብዙሃኑን እጣ ፈንታ ይወስናሉ!።››
@Armemo_offical
7 203
የሆነ ጊዜ መንግስት ኦሮሚያ ውስጥ በተደረገ ውጊያ ማረኳቸው ያላቸውን ወጣቶች አቅርቧቸው በቲቪ እየተናገሩ ነው
የሰራዊቱ የምርኮኛ አያያዝ እንዴት ነው?
"እንደልባችን ገላችንን እየታጠብን፣ ስጋም ዳቦም በቀን እንደፈለግን እየበላን ነው ...ተንከባክበውናል ሌሎችም ከኛ ተምረው እጅ በሰላም ይስጡ"
ሕዝቡ በኮሜንት
"ተምረናል ...መንግስት እኛንም ይማርከን"👐
አሌክስ አብርሀም
7 203
Repost from አርምሞ🧘🏽♂
ኤሊቶች እንዴት ነው የሰዎችን አዕምሮ የሚቆጣጠሩት?። የምትጠቋማቸው ሚዲያዎች ከአስፈላጊ ጉዳዮች የሚያደናቅፉ ወጥመዶች ናቸው ብላችሁ ታስባላችሁ?፤ በህይወታችሁ ላይ ተፅዕኖ የሚፈጥሩ ውሳኔዎች በጠቅላላ እናንተ ሳታስተውሉ ቀስ በቀስ በላያችሁ ላይ ቤታቸውን እየሰሩ እንደሆነ አስተውላችኋል?። እስቲ ዛሬ አንድ ነገር ላጋራችሁ፦
1(Distraction strategy–ያለመረጋጋት ስትራቴጂ)
«Keeping the public occupied and diverted from important issues»
ማህበረሰቦችን በመቆጣጠር ውስጥ ወሳኝ ንጥረ ነገር ያልተገመቱ ክስተቶችን ደጋግሞ መፍጠር መቻል ነው። ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ኤሊት የሆኑ ታላላቅ ሰዎች ውሳኔያቸው፣ ለውጥ እና ነውጣቸው ጭምር ቀጣይነት ባለው የዜና እና የሚዲያ አገልግሎት ባርነት ስር ይወድቃል። በዚች ቀላል ምክንያት ያስችላቸዋል። በየቀኑ ሰዎች በማይረቡ ስራዎች እንዲጠመዱ በማድረግ ለማሰብና ለመተንተን ግዜ ባለመስጠት ውስጥ ሌላ አዳዲስ ኢኮኖሚካሊ እና ፖለቲካዊ ለውጦችን ደጋግሞ መፍጠር።
2(Create a Problem, Then Offer a Solution –ችግርን ፍጠር ከዛ መፍትሄ ስጥ)
«Manufacturing crises to justify pre-planned measures»
ይህን እንዲህ ይከፈላል፦
#ችግር_ምላሽ_መፍትሔ
የሚባል ስትራቴጂ ሲሆን ሰዎች ወደኛ እንዲመጡ ሳይሆን እኛን ፈልገውን እንዲመጡ የማድረግ ብልሃት ነው። በቀላሉ በእነሱ ላይ ችግር እንፈጥርባቸዋለን እነሱም ለችግሩ መፍትሔ ፍለጋ ላይ ይጠመዳሉ። ይህ ብዙ ግዜ ከመዳኒት ንግድ አኳያ ሜዲኬሽን ላይ ሪሰርቸር የሚያደርጉ ኤሊቶች ብዙ ገንዘብ ለመስራት አስችሏቸዋል።
ለምሳሌ ነፃነትን የሚገድቡ ህጎችን በማጽደቅ ደህነታቸውን ስጋትን ውስጥ ማስገባት ብሎም ማህበራዊ መብቶችን በመገደብ የኢኮኖሚ ቀውስን ማስፋፋት መቻል ነው።
3(Gradual Strategy / Strategy of Gradualism–የደረጃ ስትራቴጂ)
«Introducing unacceptable changes slowly to make them seem normal»
የተበላሸ የአገዛዝ ስርዓትን ለማራመድ ከፈለግን..ከፈጣን ኃይል ይልቅ በማያስተውሉት ደረጃ ቀስ በቀስና ለረጅም ግዜ በተተገበረ መልኩ በሌሎች ላይ መፈጸም ነው። ቀስ በቀስ የተለወጠ ስርዓት ያደነዝዛል ፈጽሞ አገዛዙን አለመቀበል አይቻልም። የሆነ ግዜ ላይ ከዛ ስርዓት ጋር የተዋሃደ ማንነት ሆነው እናገኛቸዋለን።
4(የፕሮክራስቴሽን ስትራቴጂ)
«Presenting harsh measures as necessary in the future to soften acceptance»
ከባድ ውሳኔዎችን ያለማመንታት እንዲወስዱ «የወደፊቱን አስፈላጊነት» ደጋግሞ መስበክ። ሰው የዛሬን መስዋትነት ለመቀበል የሚደፍረው ነገ የተሻለ ይሆናል በሚል ተስፋ ነው። ያለፈው ወቅት የተኖረና የሚታወቅ ነው፤ ስለዚህ የሰው ልጅን የመቆጣጠርያ መሳርያ ያልተኖረ ግዜ ብቻ ነው።
5(Addressing the Public as Children – ህዝቡን ወደህፃናዊ ባህሪ መለወጥ)
«Using simplified, emotional language to weaken critical thinking.»
ቀላል፣ ስሜታዊ እና የዋህ ንግግሮች እየበዙ ሲሄዱ የማሰብ አቅም በዛው ልክ እየደከመ ይመጣል። የምንጠቀመው ቃላት የአዕምሮ መዋቅር ስርዓትን ይቀርጻል።
6(Stimulate Emotion Instead of Reason–በሃሳብ ፋንታ ስሜትን መፍጠር)
«Appealing to feelings to bypass logical analysis»
የስሜት መነቃቃት ሎጂካሊ አስተሳሰብን ያበላሻል። ፍርሃት፣ ጭንቀት፣ ጉጉትን መፍጠር ከእውነታው ይልቅ ምናባዊና ያልተጨበጠ ውጤቶችን ያስከትላል።
7(Keep the Public Ignorant–ሰዎችን አላዋቂ ማድረግ)
«Maintaining gaps in knowledge and awareness to prevent understanding»
የትምህርት ድክመት፣ የጠቅላላ እውቀት ማነስ እና በማዕረግ መካከል ሰፊ የሆነ የአእምሮ ልዩነት ላይ ያሉ ግለሰቦችን ይህን ድክመታቸውን ደጋግሞ መንገር።
8(ደግነትን እና ትህትናን የያየዘ የሚመስል የጭቃ ውስጥ እሾህ)
ከፍተኛ የሆነ የአዕምሮ ማደንዘዣ ልምዶችን ኖርማላይዜሽን በማድረግ ማርኬቲንጉን መቆጣጠር መቻል። ባህላዊና ወግ አዘል ልምዶችን በፌዝና በመዝናናት ፈንታ ቀይሮ ማህበራዊ ተቀባይነት እንዲኖረው ማድረግ።
9(የጋራ አመፅን ወደግል ጥፋተኝነት መቀየር)
አንድን ግለሰብ ውድቀቱ የግል ጉድለቱ እንጂ የአገዛዙ ስርዓት አለመሆኑን ማሳመን መቻል። ልክ እንደ ኒው ኤጅ አይነት «ድሃ የሆንከው የገዛ የአዕምሮ ውቅርህ በስበት ህግ አምጥቶት ነው፤ ስለዚህ ኢኮኖሚካሊ የአገር ውድቀትን መተቸት የለብህም» እንደማለት ያለ። ስለዚህ ይህ ግለሰብ መንግስትን ከመቃወም ይልቅ እራስን ወደመውቀስ ድምዳሜ ይገባል።
10(ግለሰቦችን ከራሳቸው በላይ ማወቅ)
ምስጋና ለሳይኮሎጂ ይሁንና በኒውሮባይሎጂ እና በመረጃ ትንተና ስርአቶች የሰውን ልጅ ባህሪ በቀላሉ በትክክል ለመረዳት ተችሏል። አንድ ሰውን ወይም አንድ ማኀበረሰብን ከመገናኘታችን በፊት ደካማና ጠንካራ ጎኑን በማጥናት ካርታውን በቀላሉ ማግኘት የቅድመ ማሸነፍ ብልሃት ነው።
እነዚህ ስትራጂዎች በትክክል ቢሰሩም ባይሰሩም ወደ አንድ ነገር ይወስዱናል። እሱም ንቃተ ህሊናችን እንደገና ለማግኘት እራሳችንን መጠየቅ መቻል ነው።
«ትኩረቴን የገዛው ማነው?»
«በእኔ ማጣት የሚያገኘው ማነው?»
አዎን ማስተዋል ወደ ነፃነት የምንወጣበት የመጀመርያው እርምጃ ነው።
@Armemo_offical7 203
“እስኪ ንገሩኝ ሰው ሳይጮህና ሳይሰበር ስንት ስቃይ ይታገሳል?። ይህን ሁሉ ብቸኝነት፣ ይህን ሁሉ ፍርሃት በልቡ ተሸክሞ ምንም እንዳልተፈጠረ መቆም ይችላልንህ?።
ውስጣችን እየተቃጠለ ፈገግ ማለታችን አያስገርምም? ቀስ በቀስ እየሞትን እንዴት ነው ህይወትን የምንኖረው?።
ዙሪያችሁን ተመልከቱ.. ሁሉም ሰው ጭንብል ለብሷል፤ ሁሉም ሰው መናገር የማይደፍረው ታሪክ ማንም ሊሰማው የማይችለው ቁስል በውስጡ ተሸክሟል።
ወዳጆቼ ሆይ የምንኖረው ሳይሆን እስከመጨረሻው ድረስ የሚገድለንን ጨዋታ በደማቁ እንጫወታለን። ይህ የሕይወት ትወናችን ሲያልቅና መጋረጃው ሲዘጋ ምንም አይነት ጭብጨባ የለም፤ ማንም አያስታውሰንም!።”
፦The Idiots 📖―Dostoyevsky
7 203
የስፔን የፓርላማ አባል ኢሬን ሞንቴሮ ለትራምፕ የላኩት መልዕክት፦
"ትራምፕ ሆይ፤ ጦርነት ከፈለግክ የገዛ ልጅህን ላክ። ሂድና በጣም የምትወዳቸውን ሰዎች ወደ ግንባር ስደድ። እኛ ግን ልጆቻችንን፣ ሴት ልጆቻችንንና የምንወዳቸውን ሰዎች እቤት ውስጥ ሆነው በጤና እና በሰላም እንዲኖሩ እንፈልጋለን፤ እንወዳቸዋለን። ከእንግዲህ ጦርነት አንፈልግም፤ ምክንያቱም ጦርነት ነፃነታችንን እንደሚሰርቀንና ማህበረሰባችንም በፍርሃት የተሞላ፣ ራስ ወዳድ እና በቀላሉ የሚጠመዘዝ እንዲሆን እንደሚያደርገው እናውቃለን... ይህ ደግሞ እኩልነትን ያጠፋል።
ጦርነት አንፈልግም፤ ምክንያቱም ጦርነት የሚታዘዘው በቅንጡ ቢሮዎች ውስጥ ሆኖ ነው፤ ዋጋውን ግን ሁልጊዜ የሚከፍለው ህዝብ ነው። የሌሎችን ልጆች ለሞት መላክ በጣም ቀላል ነው። ስለዚህ በግልጽ እንናገራለን፦ የእኛ ወንዶችና ሴቶች ልጆች፣ ባልደረቦቻችን እና ጓደኞቻችን—እዚህ እቤታቸው ይቆዩ፤ ምክንያቱም ከፊታቸው የሚጠብቃቸው ሙሉ ህይወት አለ። "
7 203
Repost from ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ
▌የብርሃን ብቸኝነት©
መንቃት ጉዞ ነው እንጂ መድረሻ አይደለም። ማታለያዎችን መግፈፍ፣ የማይመቹ እውነቶችን መጋፈጥ እና ጥያቄ ከማይቀርብባቸውን እምነቶች የጋራ ግዴለሽነት ባለፈ መራመድ ነው።
ሆኖም ታሪክ አንድ ከባድ እውነት በጆሯችን ያንሻኮሻኩል—ብርሃንን የሚሹ ሁልጊዜ በጥላ ውስጥ በሚቀሩት ይገፋሉ!
ብርሃናቸው የእውቀትን፣ የግንዛቤን እና ምናልባትም መንፈሳዊ መሻገርን፣ ዕድገትን የማምጣት ሃይል አለው። ነገር ግን ያ ብርሃናቸው የመገለላቸው ምክንያት ሲሆን ማየት ያማል።
ማህበረሰቡ የራሱን ፈጠራ የለመደና የራሱን ውሸት የሚያምን በመሆኑ የእምነቶቹን ክፍተት እና ስህተት የሚያሳዩትን አይወድም። ይልቁንም ይፈራቸዋል፣ ይጠላቸዋል፣ ያፌዝባቸዋል፣ እና ድምፃቸውን ለማፈን ይፈልጋል።
ይህንን እውነት በታሪክ ውስጥ በግልጽ ማየት እንችላለን። ሶቅራጥስ ወጣቶችን በማበላሸት ተወገዘ። ጋሊልዮ ዶግማን በመቃወም ተሰደደ። ኒቼ ሀሳቦቹ የተለመደ አስተሳሰብን ያናወጡ እና ያወኩ ናቸው ተብለው ተነቅፏል።
እነዚህ አእምሮዎች ብርሃንን ቢያንጸባርቁም ግን በዙሪያቸው ያለው ማህበረሰብ የጨለማነትን ምቾት በመምረጡ ወደ ኋላ ተገፍተዋል።...
ዮናታን በጋሻው
@zephilosophy
7 203
Repost from Tesfaab Teshome
የቃልኪዳን አገር ፥ ኢትዮጵያ...
ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር የተመረጠች ናት እንላለን። መለኮታዊ ኪዳን እንዳለን እንናገራለን። በአይናችን ከምናየው መራራ እውነት ይልቅ በምናባችን የሳልነውን ጣፋጭ ተረት እናምናለን።... ቅድስት አገር ኢትዮጵያ እንላለን።
ስለየትኛዋ ኢትዮጵያ ነው የምናወራው?
ልጅ እያለሁ ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር ምርጥ ትመስለኝ ነበር። ጣፋጩን ውሸቴን አምኜ ሀሴት አድርጌያለሁ። እግዚአብሔር በተለየ ሁኔታ እንደሚወደን ሳስብ ደስ ይለኝ ነበረ። ጎምዛዛውን እውነት መቀበል አልፈግም ነበር።
ከጣፋጭ ውሸት ጎምዛዛ እውነት ይሻላል።
መጽሐፍ ቅዱስ ኢትዮጵያን ከአለም የተለየች አድርጎ አይስላትም። በመጽሐፍ ቅዱስ መጠቀስ የቅድስና ምልክት አይደለም። በመጽሐፍ ቅዱስ ፅህፈት ዘመን የነበሩ አገራትን በተለያየ አውድ ተጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ በመጽሐፍ ቅዱስ ተደጋግማ ብትጠቀስም ፥ እኛ በምኞታችን እንደሳልነው "ከአለም ህዝብ ሁሉ የላቅን" እንደሆንን ለማሳየት አይደለም።
ከመጽሐፍ ቅዱስ ጥቂት ምሳሌ እናንሳ ፥
"... እናንተም ኢትዮጵያውያን ደግሞ፥ በሰይፌ ትገደላ^ላችሁ"
(ይህ ጥቅስ ያለው በትንቢተ ሶፈኒያስ ነው። ምዕራፍ ሁለት ቁጥር 12 ላይ ታገኙታላችሁ)
"... የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨ^ነቁ አየሁ፤ የምድያም አገር መጋረጃዎች ተንቀጠቀጡ።
(ይህ ደግሞ በዕንባቆም 3፥ 7 ላይ የሚገኝ ምንባብ ነው። )
ትንቢተ ሕዝቄል ምዕራፍ 30 ቁጥር 4 ደግሞ እንዲህ ይላል፥ "... ሁከትም በኢትዮጵያ ይሆናል፤ የተገ^ደሉትም በግብፅ ውስጥ ይወድቃሉ፥ ብዛትዋንም ይወስዳሉ፥ መሠረትዋም ይፈርሳል"
ከሕዝቄል መጽሐፍ አንድ እንጨምር ፥
"... እስከ ኢትዮጵያ ዳርቻ ድረስ ውድማና ባድማ አደርጋታለሁ"
(ሕዝቄል 20 ፥10)
ተጨማሪ ከዜና ካልዕ እንውሰድ
"እግዚአብሔርም በአሳና በይሁዳ ፊት ኢትዮጵያውያንን መታ፤ ኢትዮጵያውያንም ሸሹ"
(2ኛ ዜና 14፥12)
ከላይ ያሉት ጥቅሶች ምን ይነግሩናል?
እርግጥ መሰረታዊ የሄርሚኒትክስ ሕግ ልንከተል ይገባል። መጽሐፍ ቅዱስ ስናነብ ጥንቃቄ ይፈልጋል። የትንቢት መጽሐፍና የታሪክ መጽሐፍ የሚተረጎሙበት መንገድ አንድ አይደለም። የመዝሙር መጽሐፍትና የሕግ መጽሐፍት የተለያዩ ባህሪያት አላቸው። ይህ ሁሉ ቢሆንም ፥ ለሚያስተውል ሰው ከላይ ለናሙና የተቀመጡ ጥቅሶች ጥሩ ማሳያ ናቸው።
ኢትዮጵያ የተለየች አገር ናት ብሎ ማሰብ ጥሩ ነው። አገራት ተረት ያስፈልጋቸዋል። ከማንም የላቅን ነን ብሎ ማሰብ ብሔራዊ ኩራትን ይጨምራል። ለአገር የመስራት ተነሳሽነት ይፈጥራል። ይህ ግን ለእኛ አይሆንም።
ያለንበት ነባራዊ ሁኔታ ለምናባዊ ኩራት አይፈቅድም። እንደ አገር አደጋ ውስጥ ነን። በየለቱ ብዙ አሳሳቢ ጉዳዮች ይፈጠራሉ። ብሔራዊ ህልውናችን ፈተና ውስጥ ነው። ስለዚህ ከምናባዊው ነገር ይልቅ መራራውን እውነት እንጋፈጥ።
ለኛ የሚያስፈልገን "እግዚአብሔር የሚወደን ልዩ ህዝቦች ነን" የሚል ስብከት አይደለም። ለኛ የሚያስፈልገን "ከማንም አንበልጥም" የሚል መራራ ኪኒን ነው።
"ከማንም አንበልጥም። ከፈ^ረሱ አገሮች የተለየ ነገር የለንም። አምላክ ይጠብቀናል የሚለውን መመፃደቅ አቁመን የቤት ስራችንን ካልሰራን የፈረ^ሱት አገሮች እጣ ይገጥመናል" ብሎ ማሰብ ነው የሚጠቅመን
ሃሳቤን ሳልጨርስ ፅሁፉ ረዘመብኝ...
ለማንኛው ጎምዛዛውን እውነት እንቀበል
Via ተስፋኣብ ተሾመ
https://t.me/Tfanos
7 203
« በዓለም ላይ ያሉ ፖለቲከኞች በጫካ ውስጥ እንዳሉ፡ ዝንጀሮዎች ናቸው፤ ከተጣሉ አዝመራውን ያበላሻሉ፡ ቢታረቁ አዝመራውን ይበላሉ!
-
© George Orwell
Animal farm 📚
@sebleworkbooks
7 203
Repost from ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ
‹‹ለማወቅ የሚኖርንም ሰው እወዳለሁ . . .የማወቅ ፍላጎቱም በምድር ላይ ታላቅ ሰው ይኖር ዘንድ ምክንያት ሁኗልና . . .ምንም እንኳን በዚያ ሂደት የራሱን ውድቀት እንደሚያፋጥን ባውቅም እውቀትን የሚፈልጋት እሱ ታላቅ ሰው ነው፡፡ከመልካም ስራው በፊት መልካም ቃላት የሚናገርና ከተናገረውም በላይ የሚሰራ ሰው እወዳለሁ . . . ቢያንስ ቃሉን አክባሪ ነውና . . .የቱንም ያህል አምላኩ ቢቀጣው አምላኩን የሚወድ ሰው ደግሞ አከብራለሁ፤ ምክንያቱም አምላኩን የሚወድ ሰው በቁጣው ውስጥም ማለፍ ይችላልና . . . ነፍሱ እየደማች ጥንካሬ ያልተለያትን ሰው እወዳለሁ፣ ድልድዩ የተሰራው ለእንደሱ ዓይነቱ ነውና . . .ከጠቆረው ደመና ዕለት ዕለት ‹ጠብታወች› ወደምድር ይወርዳሉ . . . እነዚህ ጠብታወች ሰዎች ቢሆኑም የሚናገሩት የምስራች ግን የመብረቁን መምጣት ነው . . . እነሆ መብረቁ ደግሞ ታላቅ ሰው ነው . . . ››
ዛራቱስትራ
ፍሬድሪክ ኒቼ
@zephilosophy
7 203
Repost from ሰማዐያዊ
በተፈጥሮ በንቃተ አእምሮና በዉስጠ አእምሮ መኻከል ያለዉ በር የሚከፈተዉ ጠዋትና ማታ ሲኾን ሴራቶኒን (የቀን የአንጎል መረጃ አስተላላፊ) በቀን እንድንነቃ፤ ሜላቶኒን (የማታ የአንጎል መረጃ አስተላላፊ) ተዝናኖት ዉስጥ በመክተት ወደ እንቅልፍ በመምራት ይሠራሉ። ምርጡ ጊዜ ለአርምሞ ጠዋት ከእንቅልፍ ስንነቃና ማታ ከእንቅልፍ በፊት ነዉ። ምክንያቱም መረጃን በመሸከም ወደ ዉስጠ አእምሮ ዘልቆ ለመግባት የሚያግዙንን አልፍና ጤት የአንጎል ሞገድን በቀላሉ ለመጠቀም ስለሚረዳ።
የአርምሞ ግብ መኾን ያለበት የተዝናና አካል ዉስጥ የነቃ አእምሮን መፍጠር ነዉ። ሕብረ ብሔራዊ የአንጎል ሞገድን በማጣመር የተፈለገ መረጃ ወደ ዉስጠ አእምሮ በማድረስ ሙሉ ትዉዉቅን ከራስ ጋር መፍጠርን ነዉ። በዚኽ ወቅት የልብና የአንጎል፤ የመንፈስና የአእምሮ መጣመር በመፈጠር ሙሉነት የመላበስ ልምምድ በመኾን ያገለግላል።
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
