es
Feedback
Lovedface የተወደደ መልክ

Lovedface የተወደደ መልክ

Ir al canal en Telegram

ጌታን በማወቅና በክርስቶስ ፍቅር የሆነ ጥልቅ የመንፈስ ቅዱስ ህብረት @Lovedface @emanuellf

Mostrar más
1 052
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Canales Similares
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
diciembre '23
diciembre '23
+36
en 0 canales
noviembre '230
en 2 canales
Get PRO
octubre '230
en 0 canales
Get PRO
septiembre '230
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+11
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+12
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+15
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+7
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+9
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+11
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+6
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+27
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+23
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+27
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+90
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+33
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+17
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+28
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+12
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+19
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+20
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+27
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+26
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+114
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+23
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+12
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+33
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+34
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+26
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+63
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+9
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+11
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+63
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+42
en 0 canales
Get PRO
febrero '21
+43
en 0 canales
Get PRO
enero '21
+11
en 0 canales
Get PRO
diciembre '20
+1 002
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
20 diciembre0
19 diciembre0
Publicaciones del Canal
ቃል አጣሁ ጌታዬ ማን ልበልህ አሃሃ የምከፍልህ አጣሁ የምሰጠህ ኦሆሆ

2
🟠 በፅሁፉ እኔ የሚለው ቃልና ሃሳብ የሚወክለው አንባቢውን ነው።   🟠 አቤቱ በፊትህ እንዴት ሞገስን አገኘሁ? በአንተስ ዘንድ እንዴት ተወደድኩ? አቤቱ አምላኬና ንጉሴ ሆይ በአንተ የታወኩኝ ሆንኩኝ። ይህ ለእኔ እጅግ የበዛ ነው። መፅሀፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል “እግዚአብሔርም ምድርን ያናውጥ ዘንድ በተነሳ ጊዜ ሰዎች ከማስደንገጡና ከግርማው ክብር የተነሳ ወደ ደንጋይ ዋሻና ወደ ምድር ንቃቃት ውስጥ ይገባሉ… እስትንፋሱ በአንፍንጫው ያለበትን ሰው ተውት እርሱ ስለ ምን ይቆጠራል?” (ኢሳይያስ 2፡19-22)። ይህ እኮ እኔ ነበርኩኝ። “አካሌ እንደ ኢምንት ነው። ሕያው የሆነ ሰው ሁሉ በእውነት ከንቱ ብቻ ነው” (መዝ 39፡5)። አቤቱ እኔ ይህንን ነበርኩኝ። ታዲያ ስለምን በፊትህ ተቆጠርኩኝ? አንተም እየደጋግምክ በፊትህ ሞገስን እንዳገኘሁ ትነግረኛለህ። በስሜ እንዳወከኝ ትነግረኛለህ፤ የምለውን እንደምታደርግ ትነግረኛለህ (ዘፀአት 33፡17)። አቤቱ አምላኬና መድሃኒቴ ሆይ! አቤቱ!   🟠 ምህረትህ ከሕይወቴ እጅግ ይሻላል (መዝሙር 63፡3)። አቤቱ ለአንተ ባሪያ መሆኔ ለእኔ የሚበዛ ክብር ሆኖ ሳለ አንተ ግን ባሪያ እንዳልሆንኩ ደጋግመህ ትነግረኛለህ። ወዳጅ ብለህም ትጠራኛለህ። “ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ“ (ዮሐ 15፡15)። አንድ ጊዜ ዳዊት የተናገረው ነገር ትዝ ይለኛል። ዳዊት ከእረኝነት እግዚአብሔር የወሰደው፤ ወደ እስራኤል ጠባቂነትና ንግስና ያወጣው ሰው ነው። በሕይወቱም ደስተኛ ነበር። ከእግዚአብሔር የተደረገለት እንደማይገባውና በምህረቱ ብቻ እንዳደረገለት ያውቃል። መዝሙሮቹ ይህንን ይናገራሉ። እናም በንግስናው ወራት  ከጠላቶቹ ባረፈ ጊዜ ለእግዚአብሔር ቤትን መስራት አሰበ። እግዚአብሔርም አንተ የሰልፍ ሰው ነህና ልትሰራልኝ አትችልም፤ ነገር ግን “ጠላቶችህን ሁሉ ከፊትህ አጠፋለሁ… ታላቅ ስም አደርግልሃለሁ… ለህዝቤም ለእስራኤል ስፍራ አደርግለታለሁ፣ እተክለውማለሁ… ቤትን እሰራልሃለሁ… ከአባቶችህ ጋር ባንቀላፋህ ጊዜ ከወገብህ የሚወጣውን ዘርህን ከአንተ በኋላ አስነሳለሁ፤ መንግስቱንም አፀናለሁ…” አለው። ጌታ በነቢዩ በኩል ለዳዊት ይህን ሲለው ዳዊት ብቻውን መሆን ፈለገ። ወደ እግዚአብሔር ፊት ገባ፤ ተቀመጠና አስበ። ጌታን እንዲህ አለው “ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ እስከዚህ ያደረስከኝ እኔ ማን ነኝ? ቤቴስ ምንድነው? ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ ይህ በፊትህ ጥቂት ነበረ፤ ስለ ባሪያህም ቤት ደግሞ ለሩቅ ዘመን ተናገርህ፤ ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ…” (2ሳሙኤል 7)። ዳዊት ለጌታ የተደረገልኝ ብዙ፣ ከበቂ በላይ ቢሆንም እንተ ግን ያደረከውን እንደ ትንሽ ቆጥረህ ከዚያም አልፈህ ለሩቅ ዘመን ተናገርህ ይለዋል። አቤቱ ጌታ ሆይ መልካምነትህን ማን ተረድቶት ሊጨርስ ይችላል? ማንስ ዳርቻውን ሊያውቀው ይችላል?   🟠 ቁጭ ብዬ አስባለሁ እንደ ዳዊት… አቤቱ እኔ ማነኝ? አቤቱ በቀኝህ ያስቀመጥከኝ እኔ ማነኝ? በፊትህ ፃድቅና እጅግ የነፃሁ ሆንኩኝ። በአይኖችህ እጅግ የከበርኩና የተወደድኩ ሆንኩኝ። እኔ ማነኝ? አብ አንተን እንደሚያውቅ አንተም አብን እንደምታውቀው ያህል እንደምታውቀኝ ትነግረኛለህ (ዮሐንስ 10፡14)። የዘላለም መኖሪያዬ እንደሆንክ ትነግረኛለህ። አቤቱ እኔን ልታውቀኝ በየዕለቱም ከእኔ ጋር ልትነጋገር እኔ ማነኝ? በፊትህ ሞገስን አገኘሁ። አንተን የማወቅ ሞገስ ሰጠኸኝ። የምታከብረኝ ልጅህ ሆንኩኝ። በአይንህ ከበርኩ! አቤቱ እንዲህ ልትወደኝ እኔ ማነኝ? አንድ ልጅህንስ ለሞት አሳልፈህ ትሰጥልኝ ዘንድ እኔ ማነኝ? ዘላለምን ከእኔ ጋር ለመኖር ወደህ የመረጥከኝ፤ በእቅፍህም ያኖርከኝ አቤቱ እኔ ማነኝ? አምላኬና መድሃኒቴ ሆይ! አቤቱ አንተ እጅግ መልካም ነህ! አቤቱ አንተ መልካም ነህ! ህይወቴንና እድሜዬን ለአንተ ለመስጠት እጅግ ትንሽ ናት! አቤቱ!   📱 የአምላኬ ቃል አፕሊኬሽንን ለማውረድ @Lovedface በጣም እወዳችኋለሁ, የተወደደ አማኑኤል ከእግዚአብሔር ጋር ጥልቅ ፍቅር ዲቮሽናል የካቲት 25 2015
0
3
Sin texto...
0
4
አቤቱ አምላኬና ጌታዬ ሆይ አንተንና አንተን ብቻ ታመንኩ። ከእናቴም ማህፀን ጀምሮ በአንተ ላይ ተጣልኩ። አቤቱ አምላኬና ጌታዬ ሆይ! አቤቱ አንተ የዘላለም መጠጊያዬ ሆይ! https://youtu.be/sMnbqDQOtcU
0
5
❗️❗️❕በተለያየ አጋጣሚ በአካል የተገናኘን ጓደኞቼ ሁሉ! ከአንደኛ ደረጃ ት/ቤት ጀምሮ ኮሌጅ እስከነበርኩባቸው ጊዜዎች እንዲሁም በስራና በተለያየ አጋጣሚ በአካል ተገናኝተን የነበርን ሁላችሁ። ከእናንተ ጋር መገናኘቴ ለእኔ ደስታና ክብር ነው። እንደ አጋጣሚ ሳይሆን እግዚአብሔር ለእናንተ ወንጌልን አደርስ ዘንድ እድልን ሰጥቶኝ አግኝቻችኋለሁ። ለአብዛኞቻችሁ የክርስቶስ ኢየሱስን አዳኝነት በተለያየ መንገድ ነግሬያችኋለሁ። አሁን ለእናንተ በክብርና በፍቅር የምነግራችሁ ነገር አለኝ። የክርስቶስ ኢየሱስን ብቸኛ አዳኝነትና አማላጅነት እንዲሁም አምላክና ጌታ መሆኑን የማይቀበል ሃይማኖት ውስጥ ካላችሁ በእርግጥ ያ ሃይማኖት ወደ ሲኦል ይዟችሁ እየሄደ ነውና እባካችሁ አምልጡ! ከሀጢያትና ከዘላለም ሞት የሚያድነው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። ይሄን የምነግራችሁ እውነት ስለሆነና ለዘብ አድርጌ ልገልፀው የማልፈልገው ነገር ስለሆነ ነው። መፅሐፍ ቅዱስ ይህን እውነት አስረግጦ ያስረዳል። “መዳን በሌላ በማንም የለም፣ እንድንበት ዘንድ ለሰው ልጆች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና” ይላል (ሐዋርያት ስራ 4፡12)። እንዲሁም ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ሲናገር “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም” ብሏል (ዮሐንስ ወንጌል 14፡6)። ይህንን ግልፅ እውነት ያልተቀበለ የትኛውም ሃይማኖት የእግዚአብሔርን ስም ሊጠራ ይችላል፣ የአምላክን ስም በየዕለቱ ሊጠራ ይችላል፤ ነገር ግን በፍፁም ከእግዚአብሔር ጋር ሊታረቅም ሆነ የዘላለምን ህይወት ሊያገኝ አይችልም። አስታውሱ አይሁዳውያን እግዚአብሔርን ሲያመልኩ የኖሩ ህዝቦች ነበሩ የእግዚአብሔርን ስም ከማናችንም በላይ ይጠራሉ። ነገር ግን አልዳኑም። ይልቁን አዳኙን ኢየሱስን ሰቀሉት። አሁንም ከጥቂቶቹ በስተቀር ብዙዎቹ አልዳኑም። ነገር ግን የእግዚአብሔርን ስም ይጠራሉ። ያልዳኑበት ምክንያት የመዳን ቁልፉ ያለው ኢየሱስ ጋር እና ኢየሱስ ጋር ብቻ በመሆኑ ነው። ይሄ ጌታ ይወዳችኋል! ከሀጢያታችሁ ያነፃችኋል። አዲስ ሰው ያደርጋችኋል። በኦርቶዶክስ፣ በካቶሊክ፣ በይሓዋ ምስክር፣ በኢሬቻ አጋንንታዊ አምልኮ፣ በዋቄ ፈታ ውስጥ ያላችሁ እንዲሁም በግዴለሽነት አስተሳሰብ የምትኖሩ ሁላችሁ፤ የኢየሱስን ጥሪና ልመና ዛሬም እኔ ለእናንተ አቀርባለሁ። እባካችሁ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኑ! እርሱ የግድ ያስፈልጋችኋል! አባካችሁ ነፍሳችሁን አድኑ! አማኑኤል ከበደ
0
6
ወንጌላዊ ሬንሃርድ ቦንኬ - ስለሀጢያታችን የሞተው ኢየሱስ
ወንጌላዊ ሬንሃርድ ቦንኬ - ስለሀጢያታችን የሞተው ኢየሱስ
0
7
ናልኝ - ሳምራዊት ሲዛር.mp3
0
8
በስጋ ቤተሰቦቼ ለሆናችሁ በእናቴ እና በአባቴ በኩል የተዛመድን እንዲሁም በእህቶቼና በወንድሞቼ በኩል የተገናኘን ሁሉ እባካችሁ ይህንን መልዕክት አድምጡት። በክርስቶስ ፍቅር ወደሚወዳችሁ እውነተኛ አምላክ ፊታችሁን መልሱ። ጨለማ ከሆነው በውሸት ከተተበተበው ከኦርቶዶክስ ሃይማኖት ውጡ። ይህ ቪዲዮ ሁሉንም በትክክል ያስረዳችኋል። የዘላለም ሕይወት ሊሰጣችሁ የሚችለው ብቸኛው አዳኝ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። ብቻ! ይህ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት በፍፁም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዘላለም ህይወት ሊያደርሳችሁ አይችልም። በፍፁም! የያዛችሁት መንገድ የሚያደርሳችሁ ወደ ዘላለም ሞት ወደ ሲኦል ብቻ ነው። ይህንን መፅሐፍ ቅዱስ ነው የሚነግረን። ሰው እኮ በስራው እና በሃይማኖቱ አይደለም የሚፀድቀውና የሚድነው። በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን ብቻ ነው መፅደቅ የሚቻለው። ህይወታችሁን ለእርሱ ከሰጣችሁት ህይወታችሁንም እሱ ይመራዋል፣ ያስተካክለዋል። ቅዱሱን መንፈስ ይሰጣችኋል። ያጥባችኋል ይቀድሳችኋል። አንድ ነገር ግን እርግጠኛ ነኝ። ያላችሁት የተሳሳተ መንገድ ውስጥ ነው። ጉዳዩ ደግሞ የጊዜያዊ ነገር አይደለም። እንደዛ ቢሆን ምርጫችሁን ተቀብዬ ዝም ባልኩኝ ነበር። ነገር ግን ይህ የዘላለም ህይወታችሁን የሚወስን ጉዳይ ነው። ስለዚህ ይህ ያሳሳብኛል። ሁልጊዜ እየፀለይኩላችሁ ቢሆንም አባካችሁ ጆሮአችሁንና ልባችሁን ከፍታችሁ እውነተኛውን ወንጌል አዳምጡ። ከታች ያለውን የቪዲዮ መልዕክት ያስተላለፈው ቀድሞ የኦርቶዶክስ ዘማሪ የነበረው ትዝታው ነው። እናንተም ታውቁታላችሁ። አሁን እውነቱ በርቶለት ላልበራላቸው እያስረዳ ነው። እባካችሁ አዳምጡት። እባካችሁ ኢየሱስ ክርሰቶስን ተቀበሉና ድናችሁ የዘላለም ህይወት ወራሾች ሁኑ! እባካችሁ ከዘላለም ጥፋት አምልጡ! አባካችሁ አስተውሉ! ኩራትና ክብር ከሚወዳችሁ ጌታ አለያይቶ አያስቀራችሁ! እባካችሁ ልባችሁን ክፈቱ። መፅሐፍ ቅዱስ “መዳን በሌላ በማንም የለም፣ እንድንበት ዘንድ ለሰው ልጆች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና” ይላል (ሐዋርያት ስራ 4፡12)። እንዲሁም ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ ሲናገር “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም” ብሏል (ዮሐንስ ወንጌል 14፡6)። ይሄን ግልፅ እውነት ተቀበሉና ነፍሳችሁን አድኑ! ቤተሰባችሁን አድኑ! አምልጡ! አማኑኤል ከበደ https://www.youtube.com/live/qsp-ZEL16pA?feature=share
0
9
ኢየሱስን እንደ ብቸኛ አዳኝ በማይቀበሉ ሃይማኖት ውስጥ ላላችሁ፣ አምላክ የለም በማለት ለምታምኑ እንዱሁም በግዴለሽነት ለምትኖሩ ሁሉ ወደ ሲኦል እንዳትሄዱና ከእግዚአብሔር ጋር በመንግስቱ ለዘላለም መኖር እንድትችሉ መድሃኒት የሆነው ኢየሱስ ያስፈልጋችኋል። የሰው ልጆች ሁላችን ታመናል፣ የታመምነውም በሀጢያትና በሞት ነው። የተወለደልን፣ የሞተልንና ዳግመኛ የሚመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። እሱ ይወዳችኋልና ወደ እርሱ መጥታችሁ ዘላለምን ከእርሱ ጋር አብረን በፍስሃ እንኑር። እንባዎች ከአይኖቻችሁ ይታበሱ፤ እባካችሁ ወደ እርሱ ኑና የሚወዳችሁ ጌታ ለዘላለም ያሳርፋችሁ። የህይወትን ውሃ በነፃ ይሰጣችኋል። ዛሬም የፍቅር እጆቹ ለእናንተ የተከፈቱ ናቸው። ለመጨረሻው ጥሪ ምላሽ ስጡት! 📱 የአምላኬ ቃል አፕሊኬሽንን ለማውረድ @Lovedface በጣም እወዳችኋለሁ, የተወደደ አማኑኤል ከእግዚአብሔር ጋር ጥልቅ ፍቅር ዲቮሽናል ታህሳስ 30 2015
0
10
🟠 ጄሲ ዱፕላንቲስ ከአንድ መጋቢ ጋር ምሳ ለመብላት ካረፉበት ሞቴል ቅርብ ወደ ሆነ ወደ አንድ ሬስቶራንት ይገባሉ። የሚመገቡትን እንዳዘዙ ጄሲ ወደ ሞቴል ክፍላቸው በአስቸኳይ መመለስ እንዳለባቸው በውስጣቸው ተሰማቸው። አብሯቸው የነበረውን መጋቢ ይቅርታ ጠይቀው ሳይመገቡ ወዲያው ተነስተው ወደ ሞቴል ክፍላቸው በፍጥነት አመሩ። ገብተውም እግዚአብሔር አንድ ነገር ሊናገረኝ ይሆናል ብለው ክፍላቸውን ዘጉና ከአልጋቸው አጠገብ ተንበረከኩ። እንደተንበረከኩ ከክፍላቸው በሃይል ተስበው ወጡና ራሳቸውን ያገኙት በአንድ ሰማያዊ ሰረገላ ውስጥ ነበር። ቀና ብለው ሲመለከቱ አብሯቸው አንድ ከዚህ በፊት ጎብኝቷቸው የነበረ መልዓክ የሆነ ፍጡር አጠገባቸው አለ። “ወዴት ነው እየሄድን ያለነው?” ሲሉ ጠየቁት። እሱም ፈገግ ብሎ “ጌታ አምላክ ከሆነው ያህዌ ጋር ቀጠሮ አለህ” አላቸው። ሰማይ ሲደርሱ እጅግ ውብ ነበር። የተለያየ አይነት ሽታ ያላቸው አበቦች፣ ጅረቶችና በዙሪያቸው ዛፎች እንዲሁም ተራሮችን ተመለከቱ። አበቦቹ ረግጠዋቸው ሲያልፉ አይሰበሩም ነበር። እንደገና ያብባሉ። በዚያ መሰበር ወይም መሞት የለም። የጨለማ ጥላም የለም። ሁሉ ብርሃን ነው። ቀጠሮ ወደተያዘላቸው ወደ ኢየሱስ እየሄዱ በመንገድ ሲያልፉ የእምነት አባቶችን እንደ አብርሃምና ዳዊትን አገኙዋቸው፤ አናገሯቸውም። መልዓኩ ግን ወደ ቀጠሮዋቸው ያስቸኩላቸው ነበር። 🟠 እየሄዱ እያለ በድንገት መልዓኩ “ተንበርከክ ወደዚህ መጥቷል” አላቸው። በጉልበታቸው ተንበረከኩ። በጊዜው በሰማይ የነበሩ ህፃናት ለኢየሱስ እየዘመሩለት ነበር። እነሱን በደስታ ካቀፋቸው በኋላ ወደ ጄሲ ዱፕላንቲስ ዞረ። እሳቸውም ከእግሩ ስር ወደቁ። እግሩ የነጠረ ነሃስ ይመስል ነበር። እሳቸው በፊት እንደሚያስቡት እግሮቹ ላይ አነስተኛ ቁስል ወይም ጠባሳ ነገር ሳይሆን የተሰቀለበት ሚስማሮች ያለፉበት ትልልቅ ቀዳዳዎችን ተመለከቱ። ኢየሱስም እጁን በትከሻቸው ላይ አደረገና “ጄሲ፤ በእግሮችህ ቁም” አላቸው። ቆመውም ተመለከቱት። ኢየሱስ በክብር ያንፀባርቅ ነበር። “ተመልሰህ ሄደህ ለህዝቤ እየመጣሁ እንደሆነ ንገራቸው” አላቸው። እሳቸውም “ነገር ግን አያምኑኝም” አሉት። ጌታም “ከዚህም በፊት ለዘመናት አላመኑኝም ነበር ቢሆንም መጥቼ ነበር። እናም አሁንም በድጋሚ እየመጣሁ ነው” አላቸው። እሳቸውም “ይህንን ያውቃሉ” አሉት። ”አይ! አያውቁም። ወደዚህ ያመጣሁህ ሄደህ እየመጣሁ እንደሆነ እንድትነግራቸው ነው። ሰማኸኝ? እየመጣሁ ነው። ሂድና ንገራቸው” አላቸው። በንግግሩ ውስጥ የጉዳዩ አስቸኳይነት ይታይ ነበር። 🟠 በንግግራቸው መሃል ጄሲ እንዲህ አሉት “ጌታ ሆይ! ማድረግ የምችለውን ነገር ሁሉ አደርጋለሁ። በሙሉ ማንነቴ እወድሃለሁ። ነገር ግን በህይወቴ አንዳንድ ስህተቶችን ተሳስቻለሁ” ጌታም ”እኔ የተሳሳትካቸውን አላውቅም። አጥቤህ አስወግጃቸዋለሁ። ነፃ ነህ” ካላቸው በኋላ አይኖቹ በእንባ ተሞሉና አንድ ነገር ነገራቸው... ”የህይወቴ ደስ የማይል ቀን እየመጣ ነው… በመፅሀፍ ቅዱስ በሰማይ እንባን ሁሉ እንደማብስ የተናገርኩትን ቃል ታውቀዋለህ? እነዚያ እንባዎች በእኔ አይኖች ውስጥ ያሉትንም እንባዎች ያካትታሉ። ጄሲ፤ በዚያ ታላቅ የፍርድ ቀን ከምወዳቸው ፍጥረቶች ለአንዳንዶቹ ከእኔ እንዲለዩ መናገር ይኖርብኛል። ያንን ቀን አልወደውም! አልወደውም!” አላቸው። ኢየሱስ ይህንን ሲናገር አይኖቹ እንባ ተሞልተው ነበር። ሁልጊዜ ትኩረታችን እግዚአብሔር ከእኛ አይኖች ስለሚያብሳቸው እንባዎች ነው። ነገር ግን እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አልተረዳንም። ኢየሱስ ያለቀሰባቸው ሌሎች አጋጣሚዎችም ነበሩ። አንደኛው ለኢየሩሳሌም ነው፤ የኢየሩሳሌም ሁኔታ መለወጥ የሚችል ሁኔታ ነው። ሌላኛው ለአላዛር ያለቀሰለት ነው፤ ነገር ግን ከሞት አስነስቶት ሁኔታውን ለውጦታል። በመስቀል ላይ ሊሞት ሲልም አልቅሷል። ነገር ግን በትንሳኤ ሞትን ድል አድርጎ ሁኔታውን ለውጦታል። አሁን የሚያለቅስበትን ሁኔታ ግን ለዘላለም መለወጥ አይችልም። ኢየሱስ ለጄሲ እንዲህ አላቸው ”ጄሲ በዚያ ቀን የመጨረሻ ነው የሚሆነው! መለወጥ አልችልም። አዳም ሲወድቅ እንባ ከአይኖቼ ፈስሰዋል። ነገር ግን ለማዳን እንደምመጣ አውቅ ነበር። ሰዎችን እንደገና መንካት የምችልበት እድል ነበረኝ። ነገር ግን አሁን የመጨረሻው ቀን እየመጣ ነው። የመጨረሻ ነው። አንዴ ከተነገረ በኋላ ልለውጠው አልችልም። ጄሲ፤ እየመጣሁ እንደሆነ ንገራቸው።” 🟠 የእምነት አባት ጄሲ ዱፕላንቲስ በፃፉት “ሰማይ ከአምላክ ጋር ያደረኩት ግንኙነት” በሚል መፅሀፋቸው ላይ የነገሩን ነው። ኢየሱስ የተናገረው “እመጣለሁ” ብሎ አልነበረም። ያለው “እየመጣሁ ነው” ነው። ይህም ሌላ የእምነት አባት ደጋግመው የተናገሩትን ቃል ያስታውሰኛል። አንገስ በካን ይባላሉ። ብዙ ጊዜ እንዲህ ይላሉ… ”ኢየሱስ በቅርቡ ይመጣል አትበሉ፤ እሱ አሁን እየመጣ ነው። Jesus is not coming soon. He is on his way.” 🟠 ኢየሱስ ታማኝ እንደሆነ አውቃለሁ። በቃሉ እንዲህ ብሏል… “ድል የሚነሳ ይህንን ይወርሳል፤ አምላክም እሆነዋለሁ እርሱም ልጅ ይሆነኛል። ዳሩ ግን የሚፈሩና የማያምኑ የርኩሳንም የነፍሰ ገዳዮችም የሴሰኛዎችም የአስማተኞችም ጣዖትንም የሚያመልኩ የሐሰተኛዎችም ሁሉ ዕድላቸው በዲንና በእሳት በሚቃጠል ባሕር ነው፤ ይኸውም ሁለተኛው ሞት ነው” (ራዕ 21፡7-8)። በነዚህ ጊዜያት ጌታ በእንባ የመጨረሻውን ደውል እየደወለ ነው። ሰው እነዚህ መልካም ያልሆኑ ባህሪዎች ያለማቋረጥ በቀጣይነት ከታዩበት ከዳነ በኋላ የመጥፋቱ ወይም ዳግመኛ ያለመወለዱ ምልክት ነው። ሰው በኢየሱስ ሲያምን በደሙ፣ በስሙና በመንፈስ ቅዱስ ታጥቦና ነፅቶ ወራሽ ይሆናል። ህይወቱም እንደቃሉ ይሆናል። መፅሀፍ ቅዱስ ለዳንነው ለእኛ እንዳንስት ይነግረናል። አትሳቱ ወይም ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ ብሎናል። “ወይስ ዓመፀኞች የእግዚአብሔርን መንግስት እንዳይወርሱ አታውቁምን? አትሳቱ፤ ሴሰኞች ቢሆን ወይም ጣዖትን የሚያመልኩ ወይም አመንዝሮች ወይም ቀላጮች ወይም ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ ወይም ሌቦች ወይም ገንዘብን የሚመኙ ወይም ሰካሮች ወይም ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም” (1ቆሮ 6፡9)። ጳውሎስ ይሄንን የፃፈው አማኝ ለነበሩት የቆሮንቶስ ቤተክርስቲያን ነው። ለኤፌሶን ቤተክርስቲያንም በተመሳሳይ እንዲህ ይላል ”ከዚህ የተነሳ በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣልና ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ” (ኤፌ 5፡6)። አትታለሉ! 🟠 ደግሞ ጌታን ለማታውቁት ለእናንተ እላለሁ… በብዙ ሃይማኖት ጥላ ስር ያላችሁ በዚህ የመጨረሻ ጊዜ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኑ። ካቶሊክና ኦርቶዶክስ ወንድሞችና እህቶቼ ኢየሱስን እንደ ብቸኛ የዘላለም ህይወት አማላጅ (ከዘላለም ቁጣ በደሙ ከአብ ጋር አስታራቂ) አድርጋችሁ ካልተቀበላችሁና ዳግመኛ ካልተወለዳችሁ ፈፅሞ ልትድኑ አትችሉም። ፈፅሞ! መጨረሻችሁ ሲኦልና የእሳት ባህር ነው የሚሆነው። ሌላው ሁሉ ስርዓትና እውቀት አይጠቅማችሁም። ሙስሊም ወንድምና እህቶቼ ደግሞ ኢየሱስ ከነቢይነት ባለፈ አዳኝ መሲህ እንደሆነና እኛን ለማዳን ሞቶ እንደተነሳ እንዲሁም ጌታና አምላክ እንደሆነ ካላመናችሁና ዳግመኛ ካልተወለዳችሁ በጭራሽ መንግስተ ሰማይን ልትወርሷት አትችሉም። በጭራሽ! የዘላለም መኖሪያችሁ አሰቃቂው ሲኦልና የእሳት ባህር ነው የሚሆነው። በክፉ መንፈስ አምልኮ፣ በኢሬቻ የአጋንንት አምልኮ ስርዓት፣ በጥንቆላ፣ በዋቄ ፈታ እምነት እንዲሁም በሌሎች
0
11
Sin texto...
0
12
🟠 እህታችን ሊሊ ጥላሁን በቅርቡ (ህዳር 18 2015) በሲኤም ቤተክ/ን በተዘጋጀው የአምልኮ ምሽት ተገኝታ ነበር። ፕሮግራሙን ቀደም ብሎ በማወቄ የዝግጅት ፀሎት እያደረኩኝ ነበር። እግዚአብሔርን በሙሉ ማንነቴ የማምለክ ፍላጎት ስለነበረኝ በዚያን ቀን ያ እንዲሆን አስቀድሜ መፀለይ ጀመርኩኝ። ቀኑ ልዩ ይሆናልም ብዬ እጠብቅ ነበር። ምክንያቱም ሊሊ ጥላሁን ከእግዚአብሔር ጋር ያለን ጥልቅ ህብረት እንዳውቅ የረዳችኝ ናት። ከየትኛውም ትምህርት እና ስብከት ሁሉ ይልቅ የሷ አምልኮና መዝሙሮች በመልካም ቀይረውኛል። እናም ዳግመኛ ወደ ኢትዮጵያ የምትመጣበት ጊዜ በቀረበ ቁጥር በፀሎት እግዚአብሔርን መጠየቅ ጀመርኩኝ… “ጌታ ሆይ በዚያን ቀን በፍፁም ማንነቴ ላመልክህ እፈልጋለሁ። አቤቱ አምላኬ ሆይ ጥያቄ የሌለበት ፍፁም አምልኮ ልሰጥህ እፈልጋለሁ። እባክህ እርዳኝ! አንተ የምትቀበለውን ጥልቅ አምልኮ ልስጥህ” እያልኩኝ እፀልይ ነበር። ሌሎች የፀሎት ርዕሶቼን ወደ ጎን አደረኳቸው። የነበርኩበትን ችግር በዛ ቀን ማሰብ አልፈልግም፣ የህይወቴን ጥያቄ በዛ ቀን ማሰብ አልፈልግም ብዬ ለእግዚአብሔር ነገርኩት። 🟠 ስለዚህ ቀኑ ደረሰና በፕሮግራሙ ተገኘሁ። ፕሮግራሙም ተጀመረ። ፀሎቱን ከተካፈልን በኋላ የተባረከ ወንድማችን ፓ/ር ተስፋሁን ሊሊን ወደ መድረክ ጋበዛት። ከአምልኮ በፊት እንዲህ ያለ ሃሳብ ተናገረች “መወደድ ለእግዚአብሔር ትልቅ ነገር ነው። እሱ መወደድን ይፈልጋል። እኛ ስንወደው ደስ ይለዋል።” ከዚያም አምልኮ ተጀመረ። የጠለቀ አምልኮ ውስጥ ገባሁ። አይኔን መግለጥ እንባዬንም ማቆም አልተቻለኝም ነበር። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የእግዚአብሔር ሃይል በሰውነቴ ይመላለስ ጀመረ። ከታች ወደ ላይ፣ ወደ እግሬ፣ ወደ እጆቼ፣ ወደ ፊቴ፣ ወደ ከንፈሮቼ፣ ወደ ጭንቅላቴ፣ ከዛ መልሶ ወደ ታች፣ ወደ ላይ ይመላለስ ነበር። ምን እየሆነ ነው ብዬ እግዚአብሔርን ጠየኩት። እግዚአብሔርም “አምልኮህን ከሙሉ ማንነትህ እየተቀበልኩኝ ነው” አለኝ። በእርግጥም መቆም አልቻልኩም። ተንበረከኩኝ። ከዚህም በፊት በቤተክ/ን ሆኜ ሳመልክ የጠለቀ አምልኮ ውስጥ ስገባ አልፎ አልፎ እንበረከካለሁ። በዚያም ቀን ተንበረከኩኝ። ነገር መንበርከክም አቃተኝ። በፊት ለፌቴ መተኛት እንዳለብኝ እጆቼንም ወደፊት መዘርጋት እንዳለብኝ ከውስጤ ተሰማኝ። በህይወቴም ለመጀመሪያ ጊዜ እንደዛ አደረኩኝ። በዚህም ጊዜ የእግዚአብሔር ሃይል በሰውነቴ ውስጥ መመላሱ፣ እንባዬም ከአይኖቼ መውረዱ አልተቋረጠም ነበር። እያመለኩኝ በፊቴ ተደፍቼ እያለሁ እግዚአብሔር የማላውቀውን ነገር ነገረኝ “This is the highest form of worship/ ይህ የመጨረሻው የአምልኮ መልክ ነው” አለኝ። ሃሌሉያ! መልካምና ቸር የሆነው አምላካችን ስሙ ለዘላለም ይባረክ። ይህንን መልካም የሆነ አምላክ ማምለክ በመቻሌ ትልቅ እድለኝነት ይሰማኝ ነበር።  🟠 አምልኮው አልቆ ወደ ቤት ስመለስ ስልኬን ከፍቼ የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 4፡24ን አነበብኩት። እንዲህ ይላል “እግዚአብሔር መንፈስ ነው፤ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል”። ይህ ቃል እጅግ ብዙ ጊዜ ያጠናሁትና ሁልጊዜ፤ የዛን ቀንም ጨምሮ፤ ደጋግሜ የማነበው ቃል ነው። የግሪኩና የዕብራይስጥ ትርጉሙንም አጥንቼዋለሁ። ነገር የዚያን ቀን በታክሲ ውስጥ እያለሁ ከዚህ በፊት አስተውዬው የማላውቀውን የግሪክ ቃል ትርጉም አየሁኝ። የግሪኩ ቃል “Proskuneo ፕሮስኩኒዮ” ሲሆን ከዋና ትርጉሞቹ አንዱ “Prostrate/በፊት ለፊት መተኛት” ነው። ኦ ሃሌሉያ! 🟠 የእኔና የእናንተ ህይወት አምልኮ ነው። እግዚአብሔርን በጥልቀት ባወቅነው ቁጥር ለአምልኮ የምንሰጠው ቦታ ከየትኛውም ነገር በላይ ይሆናል። ምክንያቱም አምልኮ ከየትኛውም ነገር በላይ ከእግዚአብሔር ጋር ጥልቅ ግንኙነት የምናደርግበት ነው። በዮሐንስ ራዕይ ላይ ያሉት ሀያ አራት ሽማግሌዎች የእድሜ ሽማግሌዎች አይደሉም። በሰማይ ማርጀት የለም። ሽምግልና የጥበብንና የእውቀትን የማስተዋልን ጥልቀት መግለጫ ቃል ነው። መፅሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔርን በዘመናት የሸመገለ ይለዋል። “በሌሊት ራእይ አየሁ፤ እነሆም፣ የሰው ልጅ የሚመስል ከሰማይ ደመናት ጋር መጣ በዘመናት ወደ ሸመገለውም ደረሰ፤ ወደ ፊቱም አቀረቡት” (ዳን 7፡13)። የሰው ልጅ የተባለው ኢየሱስ፤ በዘመናት የሸመገለው ደግሞ አብ ነው። እነዚህ ሀያ አራት ሽማግሌዎች በጠለቀ ጥበባቸው፣ በበዛ ማስተዋላቸው፣ በእግዚአብሔር ህልውና ውስጥ መዋላቸው ያመጣው የመጨረሻ ውጤት በፊቱ መውደቅን ነው። “ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በዙፋን ላይ በተቀመጠው ፊት ወድቀው፣ ከዘላለም እስከ ዘላለም በሕይወት ለሚኖረው እየሰገዱ፤ ጌታችንና አምላካችን ሆይ፣ አንተ ሁሉን ፈጥረሃልና ስለ ፈቃድህም ሆነዋልና ተፈጥረውማልና ክብር ውዳሴ ኃይልም ልትቀበል ይገባሃል እያሉ በዙፋኑ ፊት አክሊላቸውን ያኖራሉ” (ራዕ 4፡10-11)። አዎን ጌታ ሆይ፤ በእርግጥም አንተ ይገባሃል። 🟠 ሀያ አራቱ ሽማግሌዎች በሰማይ በእግዚአብሔር ህልውና ቦታ ተሰጥቷቸው የክብሩ ተካፋይ ሲሆኑ፣ አክሊልም ሲደረግላቸው ከእግዚአብሔር ጋር ትከሻ አልተለካኩም። በፊቱ ወደቁ፣ ከዚያም ሰገዱ ወይም በፊት ለፊታቸው ተደፉ፤ የተሰጣቸውንም አክሊል አይገባንም ሲሉ ከእግሩ ስር አኖሩለት። እኛም ዛሬ የልጅነት ማንነታችን በእውነተኛው መንገድ በጥልቀት ሲገባን፣ የተሰጠን የኢየሱስ ክብር በእውነተኛው የፍቅር መነፅር ሲገለጥልን ከኢየሱስ ጋር ወይም አጠገባችን ካለ ወንድምና አገልጋይ ጋር ትከሻ አንለካካም። ይልቁን በአምልኮ በፊቱ እንደፋለን። ለጌታ የመገዛት፣ ለወንድማችን በፍቅር ባሪያ የመሆን ህይወታችን እየጠለቀ ይመጣል። 🟠 አቤቱ አምላኬና መድሃኒቴ ሆይ በፍፁም ልቤ፣ በፍፁም ነፍሴ፣ በፍፁም ሃሳቤም እንዳመልክህ እርዳኝ። አቤቱ አምልኮዬንም ተቀበልልኝ። ህይወቴ ፊትህ ይቅረብልህ፣ የሰጠኸኝ ክብሬም ከእግርህ ስር ይቀመጥልህ። አቤቱ አምላኬና መድሃኒቴ ሆይ ነፍሴ ታክብርህ። አቤቱ በመንፈሴ ላክብርህ። አሜን! 📱 የአምላኬ ቃል አፕሊኬሽንን ለማውረድ @Lovedface በጣም እወዳችኋለሁ, የተወደደ አማኑኤል ከእግዚአብሔር ጋር ጥልቅ ፍቅር ዲቮሽናል በየዕለቱ ታህሳስ 16 2015
0
13
Sin texto...
0
14
እኔ ግን አልችልም ያለሱ ባዶ ነኝ ያለ ኢየሱስ ህይወት እስትንፋስም የለኝ ባዶ ነኝ ግን አለኝ ወዳጅ አለኝ አለኝ አምላክ አለኝ አለኝ አባት አለኝ ኢየሱስ የሚባል የዘላለም ጥላ ፈውስ መዳኛዬ የህይወ
እኔ ግን አልችልም ያለሱ ባዶ ነኝ ያለ ኢየሱስ ህይወት እስትንፋስም የለኝ ባዶ ነኝ ግን አለኝ ወዳጅ አለኝ አለኝ አምላክ አለኝ አለኝ አባት አለኝ ኢየሱስ የሚባል የዘላለም ጥላ ፈውስ መዳኛዬ የህይወቴ ቤዛ አለኝ... የሱስ አለኝ!! ጌታዬ ሆይ እኔ እኮ እንደዚህ ነኝ! እንደዚህ ነኝ አባቴ ሆይ!
0
15
አባቴ ሆይ... ላምልክህ ... ጌታዬና አምላኬ ሆይ እኔ ላክብርህ ... ከእስትንፋሴ ይልቅ የምትቀርበኝ እንደ አይንህ ብሌን የምጠብቀኝ በልቤ ፅላት ላይ ያረፈው ፍቅርህ ይሰማኛል ... አባቴ ሆይ ላምልክህ!! ... አባቴ ሆይ... የቀረው ዘመኔ ይለቅ በፊትህ አንተን እያመለኩኝ እያከበርኩህ
0
16
በአማርኛ ቋንቋ https://www.facebook.com/100000517627353/posts/6273178759375983/?flite=scwspnss&mibextid=kIOpslkNPqsoFrHp
0
17
ጀመረ! የፈውስ ዥረት ከፓስተር ክሪስ ጋር https://youtu.be/KTof62tljJU
0
18
የፈውስ ዥረት የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ከፓስተር ክሪስ ጋር ዛሬ ጥቅምት 25 ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ይጀምራል። በተመሳሳይ ሰዓት ነገ ጥቅምት 26 ይቀጥላል። በእርግጥ እግዚአብሔር ለእናንተ ከየትኛውም
የፈውስ ዥረት የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም ከፓስተር ክሪስ ጋር ዛሬ ጥቅምት 25 ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ይጀምራል። በተመሳሳይ ሰዓት ነገ ጥቅምት 26 ይቀጥላል። በእርግጥ እግዚአብሔር ለእናንተ ከየትኛውም በሽታና ህመም ፈውስንና ተአምራትን የሚያደርግበት ጊዜ እንደሆነ አምኛለሁ። በሰዓቱ ከታች ባሉት አድራሻዎች በቀጥታ መከታተል ትችላላችሁ። የዩቲዩብና የፌስቡክ አድራሻዎችን ደግሞ ፕሮግራሙ በሚጀምርበት ሰዓት በቴሌግራም ቻናልና ፌስቡክ ገፅ የማስቀምጥ ይሆናል። 1. https://www.healingstreams.tv 2. https://www.ceflix.com +251912606346
0
19
ፀንታችሁ ቁሙ - ፓስተር ክሪስ በአማርኛ ትርጉም Hold on - Pastor Chris
ፀንታችሁ ቁሙ - ፓስተር ክሪስ በአማርኛ ትርጉም Hold on - Pastor Chris
0
20
እየው ልቤን እየው ውስጤ ይኸው እባክህ ማረው አይንህ ፍቅር ነው ይህን አውቃለሁ ውስጤ ሚጮኸው በኔ ክበር ነው... አይንህ ፍቅር ነው ይህን አውቃለሁ ልቤ ሚጮኸው በኔ ክበር ነው... ከፊቴ እያለ ተስሎ ውስጤ ማተቤ መስቀል ሆኖ እንዴት ይከብደኛል ስለእኔ የሞትከውን አንተን እሺ ማለትን?? እሺ ማለትን?? ጌታ ሆይ ስምህ ይባረክ!! https://youtu.be/rAtc_eYRr_o
0