ᴛʜᴏᴜɢʜs.ᴘʟᴄ🔥
Ir al canal en Telegram
...Quotes from different societies. Also👉https://t.me/LilOriIII
Mostrar más856
Suscriptores
Sin datos24 horas
-17 días
-1530 días
Archivo de publicaciones
856
Repost from ☦️ዜማ ዘቅዱስ ያሬድ®
እኸ ሰዎች እኛ ክርስቲያኖች በመስቀል ምሳሌ እናማትባለን አይደል? በነገራችን ላይ ምስጢራት ሲፈፀሙ ግድ ነው ማማተብ፣ ይህ ልምድ የመጣው ከሐዋርያት እንደሆነ እና እንዲሁ ተራ ነገር አለመሆኑን ከአባቶች በጥቂቱ ላሳያችሁ
ሊቁ ጠርጡለስ 160 – 240 A.D. )De Corona (The Crown), chapter 3
በእያንዳንዱ እርምጃ እና እንቅስቃሴ፣ በመውጣትና በመግባት፣ ልብስና ጫማ ስንለብስ፣ ስንታጠብ፣ ጠረጴዛ ላይ ስንቀመጥ፣ መብራቶቹን ስናበራ፣ ስንቀመጥ፣ በእለት ተዕለት ህይወታችን ውስጥ ባሉ ተግባራት ውስጥ እናማትባለን።ቅዱስ ቄርሎስ የኢየሩሳሌም 315–387 (Catechetical Lectures 13.36)
እንኪያስ የተሰቀለውን ለመናዘዝ አናፍርም።መስቀል በጣቶቻችን በድፍረት የተሠራ ማኅተማችን ይሁን፣ በሁሉም ነገር፣ በምንበላው እንጀራ በምንጠጣውም ጽዋ ላይ። በመግቢያችን እና በመውጣት; ከመተኛታችን በፊት, ስንተኛ እና ስንነሳ; በመንገድ ላይ ስንሆን እናማትብ…..ማማተብ የምእመናን ምልክት እና የሰይጣናት ፍርሃት ነው።ታላቁ ቅዱስ ባስሊዮስ (c. 330–379) On the Holy Spirit 27,66
በቤተክርስቲያን ውስጥ ተጠብቀው ከሚገኙት በአጠቃላይ ተቀባይነት ያላቸውም ሆነ በይፋ ከታዘዙት እምነቶች እና ልማዶች አንዳንዶቹነእከጽሑፍ ትምህርት የተገኘን ሲሆን ሌሎቹን ደግሞ በሐዋርያት ትውፊት ‘በምሥጢር’ ተላልፎልን ደርሶናል: ከእውነተኛው ሃይማኖት ጋር በተያያዘ ሁለቱም አንድ ዓይነት ኃይል አላቸው። ለምሳሌ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የታመኑትን በመስቀል ምልክት እንዲያማትቡ ነው ።ይህን ትውፊት ሲተገብሩ የማናያቸው ጭሶች ሐዋርያት ስራ ምዕራፍ 2 ላይ ነው የተመሰረትነው ሲሉ ያስቀኛል ድንቄም ዸንጤቆስጤ……ሎል
856
Repost from የህይወት ቅኔ🥀
ለማወቅ ከመሞከር አላውቅም ማለት የሚያሳፍረን ድንቅ ፍጥረታት..ምንም ማለት አይደለም አላውቅም ማለት ለዛውም ትልቁ እውቀት አለማወቅን ማወቅ ነው.. ካወቁት እውቀታቸውን ከማይሰስቱ ለመምከር ከበረቱ ለመናገር ከማይፈሩ ለማስተማር ከተዘጋጁት መማር መስማት እና ማወቅን የመሰለ ሰውን የማይጎዳ ብልጠት የለም..
አውቃለሁ ብለህ ሳታውቅ ቀርተህ ሰው ፊት ሰው መሃል ምን አሳቀቀህ ምን አስጨነቀህ ጓድ ቢቀርስ
ቀዳማዊ ዘ አቢሲኒያ ⚜GREETINGS 🚬 ቀኃስ
856
Repost from አሀዱ Thoughts
ዛሬ ረቡዕ ማታ 3 ሰዓት በኃይለኛው የሚያሸልም Game night አሀዱ ላይ ተዘጋጅቷል ፣ ሁላችሁም ተሳተፉ፣
join, share, post,
Let's gooo 👌👍🙌
https://t.me/ahadu_thought
856
Repost from ☦️ዜማ ዘቅዱስ ያሬድ®
+1
በቁርባን የተጋባች አንድ እህታችን “ብር ከሌለው ለምን ያገባል “ ስትል ሰማሁ ከዚ በላይ የጌታን ስጋ መዳፈር እና ጌታ ላይ ማመጽ የለም
በጋብቻው ጊዜ በክርስቶስና በጌታ መሰዊያ(ታቦት) ፊት ሴቷ እንዲ ብላ ትምላለች
እኔ (እገሊት:እገሌን) የሕግ ባል ይሆነኝ ዘንድ ወድጄ ተቀብየዋለሁ ስለዚህ ከዛሬ ጀምሮ በተቻለኝ መጠን በሥራው ሁሉ እረዳዋለሁ፣ በሀዘኑና በደስታው ፣በጤናውና በሕመሙ ጊዜ ከእርሱ ጋር እሆናለው …….
አንዳንዴ በአለም ሰዎች አንወሰድ
856
Repost from አሀዱ Thoughts
ዛሬ እሁድ ማታ the biggest giveaways ለድምፃዊያን ተወዳዳሪዎች ፣ ተዘጋጅቷል፣ ከምሽቱ 3 እሰከ 5 ሰዓት ይሳተፉ፣ ከአንድ ደቂቃ በታች ድምፆዎን record አርገው፣ post ያድርጉ፣
ከ 1 አሰከ 10 የወጡትን እንሸልማለን
🙌🙏👌👏👏
856
Repost from አሀዱ Thoughts
ዛሬ እሁድ ማታ the biggest giveaways ለድምፃዊያን ተወዳዳሪዎች ፣ ተዘጋጅቷል፣ ከምሽቱ 3 እሰከ 5 ሰዓት ይሳተፉ፣ ከአንድ ደቂቃ በታች ድምፆዎን record አርገው፣ post ያድርጉ፣
ከ 1 አሰከ 10 የወጡትን እንሸልማለን
🙌🙏👌👏👏
856
Repost from አሀዱ Thoughts
ተረት ተረት:
በድሮ ጊዜ ነው አሉ
ሰውየው በዘመድ አዝማድ ሚስት አፈላልጎ አፈላልጎ አንዷን በቅርቡ ከባሏ ጋር የተፋታች ሴትዮ አጋቡት አሉ።
ያገባት ሴትዮ ደግሞ የቀድሞው ባሏን የፈታችው ዱላውና ንቀቱ ምርር አድርጓት ነበር።
እናላችሁ ሰውዬ ሆዬ
አንድ ምሽት ላይ ከመሬት ተነስቶ አዲሷን ሚስቱን እግሩን ማሳጠብ መቀነቷን አስወልቆ መግረፍ አማረው።የአዲስ አባውራ ነገር በቃ ወቢ ተፋው
አባዎራ:-ተነሺ መቀነትሽን ፍቺ
አዲስ ሚስት:- ወደ አልጋ አብረን ሄደን ነው እንጂ አንተ ሱሪ ታጥቀህ እኔን መቀነት ፍች የምትለኝ ምን ሆነሃል አንተው ትለዋለች።
አባዎራ:-ኧረ ጥጋብ ቀዩ በይ ተነሺ እግሬን እጠቢኝ ያለዚያ የቀድሞው ባልሽ የሰበረሽ ቦታ ላይ እሰብርሻለሁ
አዲስ ሚስት:-እርሶ ሰውዬ ይከበሩ!
አባዎራ:-በአምስት ደቂቃ ልክ አስገባሽ አደል ብሎ ሚስቱን ሊገርፍ አለንጋውን ከግድግዳው አውርዶ ጠጋ
አዲሷ ሚስት:-ብድግ አድርጋ ከምድጃው ስር ታጋድመውና ሶስቴ በክርን ድቁስ
አባዎራ:-ከስር ሆኖ ኡኡ የሰው ያለህ ተጋደልነ
አዲሷ ሚስት:-ሁለቴ በቡጢ ነርታው ለይተህ ጩህ
አባዎራ:-ኡኡ ገደለችኝ
ጩኸቱን የሰሙ ጎረቤቶች እየተሯሯጡ መጥተው በሩን በርግደው ሊገቡ ሲሉ ሚስት ሆዬ ባሏን ደበደበች ተብዬ ከምታማ እሱም ሚስቱ ደበደበችው ከሚባል ትልና ከስር የነበረው ባሏን ገልብጣው እሷ ከስር እሱን ከላይ እንዳደረገችው ጎረቤት ግብት።
ጎረቤቶቹም ሰወዬውን ልቀቅ ብለው እሷንም ልቀቂ ብለው መገላገል ሲጀምሩ
አባዎራ ሆዬ:-ኡኡ እኔን ልቀቁኝ አዲስ ግልብጥ ነኝ
ተረቴን መልሱ አፌን በሰልፍ አብሱ🙏
856
Repost from የህይወት ቅኔ🥀
ፍቅራችን አልቆ ጫፍ ላይ እንዳለ ሊገባ ገደል
እኔ እንደገባኝ ገብቶሀል አይደል
ሳንነጋገር ሳይወጣን ክፉ
እንዲሁ ብቻ ግን ፍቅራችን ሄዷል ወደ አፋፉ
እንደፊታችን ልክ እንደድሮ ደስ አይለንም
ተቃቅፈን ማደር ቀን መዋል አብሮ
አንተም ታውቆሀል እኔም ታውቆኛል
አናውራው እንጂ ሰልችቼለሀው ሰልችተኸኛል
አንዳንዴ እንዲ ነው
የህይወት እድል የህይወት እጣ
ትለያያለህ እንለያይ የሚል ቃል ሳታወጣ🥀
856
On Today's episode of እርሶ ቢሆኑ ምን ያደርጋሉ:
"ተበድያለው ኸረ በምን ሀጢያቴ ነው? ምን በድዬ ይሄን ያህል የሚደርስብኝ? በመላ ቱሉ ዲምቱ እንዲ ያለ ነገር አልተሰማም አዪ .... እሺ እሺ እረጋገለው። ታሪኬን ልንገራችሁ።
ከ9 ወር በፊት ለብዙ ዓመታት አፍቅሬ ለ 2 ዓመት አጭቼ ከ 1 ዓመት በፊት ያገባዋት ሚስቴ አረገዘች። በውነት ደስ አለኝ ሙት። በደስተኛ ደስ አለኝ። ስንት ዓመት የቋጠርኳትን ፣ ከእጅ ድብደባ እና በሌሊት ፈተና አንሶላ ከማርጠብ የተረፈ ዘሬን ለተልኮ ልኬ ተሳክቶልኝ ነበረ። አረገዝኩ ያለቺኝ ቀን ትዝ ይለኛል በሀይገር ከ ቱዲዬ(ቱሉ ዲምቱ) ወደ መገናኛ እየሄድኩ አንድ ወላቃ ብርሀኔ አደሬ እና ታዬ ደንድአ ተዳቅለው የመሰለ ረዳት በላይ በላይ ጠቅጥቆን ነበር። በአንድ ቆጥ የሚያክል እና አንዲት ቦርጫም ሴትዮ(ከላይ ብትጠመጥም ከበሮ የያዘች ደብተራ ነበር የምትመስለው) መሀል ገብቼ መከራዬን እያየው ነበር። መንገዱ ሲንገጫገጭ የሴትዮዋ ቦርጭ ከኃላ ሲገፋኝ ረጅሙ ሰውዬ ደሞ ሊደግፍ እጁን ሲያነሳ ብብቱ ሂዶ ፊቴን ይስማል። (በያንዳንዱ ብብት ወ ፊት ፅግበራ 60000 ምናምን ህዋሰ አዕምሮዬ ሲሞቱ ይታወቀኝ ነበር።) ታድያ በዚ መሀል ነበር ደውላ አረገዝኩ ስትለኝ በደስታ ዘልዬ(በሰው በታጨቀ ሀይገር ላይ ቁመህ እየሄድክ እንዴት ዘለልክ ካልከኝ አስረግዘህ እየው ነው መልሴ) ረጅሙን ሰው ላቅፈው ስል የዛች ቀፈት ሲገፋኝ ሰውዬውም እጁን ሲያነሳ ሂጄ የብብቱን ላበት ሳምኩት። እንደዛም ሁኖ ደስታዬ አልደፈረሰም ነበር።
በእርግዝናዋ ወቅት ያማራትን አቅርቢያለው። ( አንዴ ለማርያም ዝክር ለየኔ ቢጤ የሚሰጥ ምግብ አምሮኛል ብላኝ ከለማኝ ጋር ተጋፍቼ ስቀበል ድሮ ኮርቼባት የተለየዋት ኤክሴ አይታኝ እጇን አንስታ "እልልልል እሰይ ስለቴ ሰመረ እሰይ እመቤቴ እንደው ምን ላርግሽ ፀሎቴን ሰማሽኚ ድሮም አመዳም ነበር ይባስ አመዳም አረግሺልኝ ይሄ መናጢ" እያለች ሰግዳለች)።
እንደ "ሰውዬው" ሚለዋወጥ ባህሪዋን ታግሺያለው።
የወልቂጤ ድንች ያስመሰላት ውፍረቷ እንኳን ይማርከኝ ነበር። ዝሆኔ የያዛው ሚመስለውን እግሯን ማታ ማታ ሳላቋርጥ አሽቺያለው። አረ ስንቱ...
ግዴታዬን ሀላፊነቴን ተወጥቼ አይደርስ የለ የመውለጃዋ ቀን ደረሰ። መቼ ?ትናንትና! በእድር አስለፍፌ ፣ ኑ አጅቡኝ ብዬ ፣ ዘመድ አዝማድ እና ለ'ይቺ ናት ኢትዮጵያ' ካፕሽን ብዬ ከየ ቤተእምነቱ ሁለት ሁለት አባቶች ይዤ ተግተልትለን የታምራትን ዓይኔን ላይ ነው እየዘፈንኩ ሄድን። ሆስፒታሉን ባ'ንዴ ለገዢው ፓርቲ የወጣ የድጋፍ ሰልፍ አስመሰልነው። አብሬያት ማርያም ማርያም እያልኩ አማጥኩ። ቀበቶዬን አላልቼ ድጋፌን ሰጠው።ተንቆራጠጥኩ። (አልዋሽም ሌላ ምክንያትም አለኝ ቁርስ የበላሁት ቂንጬም ስላልተስማማኝ ነው)። በመጨረሻም ወንድ ልጅ ወለደች ተባለ። በደስታ ተጨፈረ። (የሰፈር ልጆች ጩኸቱ ስቧቸው ቦታውን ረስተው 'ወያላው ዝም' እያሉ ነበር) ባለቤቷ መጥተህ ማየት ትችላለህ ሲባል በፉጨት እና ጭብጨባ ታጅቤ ወደ ክፍሏ ገባው።
ፊቴ ጥርስ በጥርስ ሁኖ በኩራት ጀነን ብዬ ነርሷን "የታል የኔ ልዑል" አልኳት። ውስጥ ያሉት ባለሙያዎች በሽሙጥ ያዩኛል። ችላ ብዬው ድጋሚ ጠየኩ። "ይኸው" ብላ በእጇ የያዘችውን ዘረጋቺልኝ። በግርታ "ልጄን እኮ ነው ያልኩት ያረረ ዳቦ ምን ያረግልኛል" አልኳት። በአዘኔታ "እንግዲህ ምድጃው የሚያወጣው ያዘዝከውን የሰጠውን ነው" አለች ወደ ሚስቴ ማህፀን እያሳየች። ሚስቴን ሳያት ዓይኔን ትሸሻለች። አሁንም ባለማመን "እኮ እኔ ወለደች ተብዬ ልጄን ላቅፍ ነው የገባሁት። ምናልባት ስታምጥ የገፋችውን ሰገራ እንዳይሆን የያዥው አልኳት።" ነርሷ ሁኔታው ገብቷት በሀዘኔታ እያየች ዝም አለች። ይታይህ ሚስቴ ክልስ የመሰለች ቀይ ነች እኔም ጠይም አሳ መሳይ የተባለልኝ ነኝ ታድያ እንዴት እሙሙዋን የመሰለ ልጅ ትወልዳለች? በህክምና ባላብራራውም የጥቁር ሰዎች ጨቅላዎች እንኳን እንደተወለዱ አይጠቁሩም። ቅስሜ እንክትክት አለ። ይሄን መሸጦ ጎማ ከለር ምን ላርገው? ሚካኤልን የመሰለ ልጅ ስጠብቅ የረገጠውን ሰጠቺኝ! ንጋቷ ከልካይን የመሰለ ልጅ ስጠብቅ ንጎሎ ካንቴን ሰጠቺኝ። 'የማርያም አራስ ናት ተው!' ብለውኝ ነው እንጂ 3 ቁጥር 4 ቁጥር ልገባላት ነበር።ይኸው ከትናንት ጀምሮ በዙሪያዬ ያለ የማውቀው ባሪያ እየፈለኩ ነው።
ፍረዱኝ ጦቢያ ህዝብ እንዲ ይደረጋል ወይ ?ከታምራት ዘፈን አሁን ወደ ቴዲ መጥቼ ጉድ ሰራቺኝን እየዘፈንኩ ነው ቢያንስ ምን አለ ልጁ የሆነ ነገር ሁኖ የአብነትን ልጄ አትናፍቀኝ ብታዘፍነኝ...
B ነኝ ከ TD"
