es
Feedback
🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

🗞 ዹ አቡጁነይድ መልዕክቶቜ Abujunaid posts

Ir al canal en Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ ዚቀሚቡ ዚድምፅና ዹፅሁፍ መልዕክቶቜ ዚሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ኚመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

Mostrar más
2 174
Suscriptores
Sin datos24 horas
-27 días
-1930 días
Archivo de publicaciones
أَما وَاللَهُ إِنَّ ال؞ُلمَ ؎ُ؀مٌ وَلا زالَ المُسيءُ هُوَ ال؞َلومُ إِلى الديّانِ يَومُ الدينِ نَمضي وَعِندَ اللَهِ تَجتَمِعُ الخُصومُ سَتَعلَمُ في الحِساؚِ إِذا الِتَقَينا غَداً عِندَ المَليكِ مَنِ الغَ؎ومُ @abujunaidposts

🔖 5 ምክሮቜ ለቁርአን ሐፊዞቜ 🎁 ለመርኹዝ ኢብኑ መስኡድ ተመራቂ ተማሪዎቜ ዹቀሹበ ሙሀደራ 🎙 አቡ ጁነይድ ሳላህ አሕመድ ---------------- 📮ዚአቡጁነይድ መልዕክቶቜ @abujunaidposts

‏اللذات منها روحانيه ومنها حيوانية ومنها ؎يطانية قال اؚن القيم رحمه الله: (...ولذة العلم لذةٌ عقلية روحانية من جنس لذة الملا؊كة، ولذةُ ؎هوات الأكل وال؎راؚ والنكاح لذةٌ حيوانية ي؎ارك الإنسانَ فيها الحيوانُ، ولذة ال؎ر وال؞لم والفساد والعلو في الأرض ’لذة‘ ؎يطانيةٌ ي؎ارك صاحؚها فيها إؚليسُ وجنوده) ‏مفتاح دار السعادة Ù¡/ ــ٧ @abujunaidposts

دَعِ اﻷَحْزَانَ وَ اهْجُرْهَا مَلِيَّا وَ عَانِقْ ؚِالرِّضَا وَهْجَ الثُّرَيَّا هِيَ الدُّنْيَا فَلاَ تَأْسَفْ عَلَيْهَا وَ إِنْ خَاَؚتْ ؞ُنُونُكَ يَا أُخَيَّا فَلَوْ دَامَتْ لِغَيْرِكَ أَوْ لِغَيْرِي لَمَا وَصَلَتْ إِلَيْكَ وَ لاَ إِلَيَّا فَسَلْ تِلْكَ القُُؚورَ وَ سَاكِنِيهَا فَقِيرًا كَانَ أَمْ مَلِكًا ثَرِيَّا فَسِرْ يَا صَاحِ ِفي ؚِرٍّ وَ تَقْوَى وَ عِ؎ْ حُرًّا عَلَى الدُّنْيَا أَؚِيَّا @abujunaidposts

ስለ "እንኳን አደሚሳቜሁ" ባቀሚብኩት ፅሁፍ መጠቆም ዚፈለኩት ምንም አይነት ማህበራዊ ግንኙነት ሀራም ነው ዹሚል መልእክት አይደለም። በተለይም ኚክርስቲያን እና አይሁዶቜ ጋር ባለን ማህበራዊ ግንኙነቶቜ ላይ ዚተፈቀዱ ብዙ በመልካም ዹመኗኗር እሎቶቜ አሉን። ሆኖም ሀይማኖታዊ ወሰኖቜ ዹሉም ማለት አይደለም። ዹተፈቀደውን ስንተገብር እንደ ያልተፈቀደ ጋብቻ፣ በአላት ላይ መሳተፍ፣ ለሞቱት ዹአላህን ማርታ መለመንና ባጠቃላይ በዲን መመሳሰልን ግን በፍፁም አንፈፅምም። ይህንን ዚእምነትና ዚሀይማኖት ወሰን መናድ አይቻልም። ማንነታቜንን ማክበር፣ ግንኙነታቜንን በዲናዊ ገደቊቜ ማጠር ብሎም አለመሟሟት ለሌሎቜ ሞራል ዲንና ማንነት ኹመጹነቅ ይቀድማል። ዲን ኹምንም በላይ ነውና ኹመሾማቀቅ እንውጣ። ይህ ዚዲናቜን መገለጫ ነውና እንደ ማክሹርና ፅንፈኝነት ማዚት አይቻልም። በነገራቜን ላይ ዚአንድ እምነት ተኚታይ ኚሌሎቜ ለመቀራሚብ ብሎ ኚእምነቱ ጋር ዚሚጣላበት ሁኔታ ድሮ ቀርቷል። ሌሎቹም ቢሆኑ ይህ በኛ ሀይማኖት አልፈቀድም እና ይቅርታ ይሉሀል። (فَلَا تُطِعِ ٱلۡمُكَذِؚِّینَ * وَدُّوا۟ لَوۡ تُدۡهِنُ فَیُدۡهِنُونَ * وَلَا تُطِعۡ كُلَّ حَلَّافࣲ مَّهِینٍ) አስተባባዮቜንም አትታዝዙ፡፡ ብትመሳሰላ቞ውና ቢመሳሰሉህ ተመኙ፡፡ [Surah Al-Qalam 8 - 10] ወላሁ አዕለም https://islamqa.info/en/answers/106668/greeting-christians-on-the-occasion-of-their-festivals @abujunaidposts

በካፊሮቜ በዓል እንኳን አደሚሳቜሁ ማለት ይፈቀዳልን? በበአላት ሰሞን በተደጋጋሚ እገሌና እገሌ ላይክ አድርገውታል ኹሚለን ፖስቶቜ መካኚል ኚፊሎቹ ዚእንኳን አደሚሳቜሁ መልእክቶቜ ና቞ው። ለጌታ መወለድ፣ ለጌታ መሰቀል፣ ለጌታ ሞቶ መነሳት (ትንሳኀና) መሰል ክስተቶቜ እንኳን አደሚሳቜሁ ሲባል ሌር ወይም ላይክ ዚሚያደርጉ ብዙ እህትና ወንድሞቜን አስተውያለው። አንዳንዎ በስህተት ሌላ ግዜም ነገሩን እንደቀላል በመውሰድ ዹሚፈፀም ሊሆን ይቜላል። ሆኖም እጅግ ኚባድና በአኌራ ዋጋ ዚሚያስኚፍል መዘናጋት ነው!! በካፊሮቜ በአልፀ እንኳን አደሚሳቜሁ... እንኳን ደስ አላቜሁ... እንኳን አብሮ አደሹሰን ማለት እነሱን ለማስደሰትም ይሁን ለመመሳሰል ኹአላህ ዲን መንሞራተት እና ዚካፊሮቜን ኩፍር ዹመናገር ስነልቊና መካብ ስለሆነ ክልክል ነው። መኚባበር እና አብሮነትን ለማሳዚት ኚእምነታቜን መንሞራተት አይጠበቅብንም። ዲን ኹምንም በላይ ነውና ሞሪዓን መተላለፍ ፍፁም ጥፋት ነው!! ፈጣሪ ወለደ ተወለደ ዹሚለው አስተምህሮ ዚጥፋትነቱ ክብደት ሰማያትንና ምድርን ሊሰነጥቅ እንደሚቀርብ ቁርአን ይነግሚናል። አላህን ዚሚያስቆጣ ተግባር በመፈፀማቾው እንኳን ደስ ያላቜሁ ማለት ኚሙስሊም አይጠበቅም!! (وَقَالُوا۟ ٱتَّخَذَ ٱلرَّحۡمَـٰنُ وَلَدࣰا * لَّقَدۡ جِ؊ۡتُمۡ ؎َیۡـًٔا إِدࣰّا * تَكَادُ ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تُ یَتَفَطَّرۡنَ مِنۡهُ وَتَن؎َقُّ ٱلۡأَرۡضُ وَتَخِرُّ ٱلۡجَِؚالُ هَدًّا * أَن دَعَوۡا۟ لِلرَّحۡمَـٰنِ وَلَدࣰا * وَمَا یَنَؚۢغِی لِلرَّحۡمَـٰنِ أَن یَتَّخِذَ وَلَدًا * إِن كُلُّ مَن فِی ٱلسَّمَـٰوَ ٰ⁠تِ وَٱلۡأَرۡضِ إِلَّاۀ ءَاتِی ٱلرَّحۡمَـٰنِ عَؚۡدࣰا * لَّقَدۡ أَحۡصَىٰهُمۡ وَعَدَّهُمۡ عَدࣰّا * وَكُلُّهُمۡ ءَاتِیهِ یَوۡمَ ٱلۡقِیَـٰمَةِ فَرۡدًا) [«አልሚሕማንም ልጅን ያዘ (ወለደ)» አሉ፡፡ ኚባድ መጥፎን ነገር በእርግጥ አመጣቜሁ፡፡ በእርሱ (በንግግራ቞ው ምክንያት) ሰማያት ሊቀደዱ፣ ምድርም ልትሰነጠቅ፣ ጋራዎቜም ተንደው ሊወድቁ ይቃሚባሉ፡፡ ለአልሹሕማን ልጅ አለው ስለአሉ፡፡ ለአልሹሕማን ልጅን መያዝ አይገባውም!! በሰማያትና በምድር ያለው ሁሉ (በትንሣኀ ቀን) ለአልራሕማን ባሪያ ኟነው ዚሚመጡ እንጂ ሌላ አይደሉም] Surah Maryam 88 - 95 ለመሆኑ አንድን ካፊር ለሀይማኖታዊ በአል እንኳን አደሹሰህ ስትለውፀ ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ አይደለምን? እንኳን አደሹሰህ... ጌታ ተወልዶ ተሰቅሎ ሞቷል ብለህ ለማወጅ፣ ለመስቀል ለመስገድና ዚፈጣሪን ክብር ዚሚነኩ ንግግሮቜን ለመናገር እንኳን በቃህ! እንኳን አደሹሰህ... ማርያም ፈጣሪዋን ወለደቜውፀ በመጠቅለያም ጠቀለለቜው እያልክ ለመዘመር እንኳን በቃህ! ዚኩፍር ተግባርን ለመኹወን ኹሆነ ዹደሹሰው ለምንስ እንኳን አብሮ አደሹሰን እንላለን? እውቁ አሊም ኢብኑል ቀይም ሹሂመሁላህ ይህ ተግባር ዹተኹለኹለ ስለመሆኑ ዚኡለማዎቜ ዚጋራ አቋም መሆኑን በመጠቆም እንዲህ ብለዋልፀ «ኩፍርን ብቻ በሚያንፀባርቁ ዚሀይማኖታ቞ው መገለጫዎቜ እንኳን አደሚሳቜሁ...እንኳን ደስ ያለቜሁ ማለት ሀራም መሆኑ ዹሁሉም ሊቃውንት ስምምነት ያለበት ነው። ለምሳሌ አንድ ሙስሊም በነሱ በዓላትና ፆም ጊዜፀ «በአሉን ዚተባሚኚ ያድርግልህ» ወይም «መልካም ዚደስታ በአል ያድርግልህ» እና መሰል ዚደስታ መግለጫዎቜን ቢያስተላልፍፀ ተናጋሪው ኚኩፍር ቢድን እንኳ ኚባድ ወንጀል ነው ዚፈፀመው። ይህምፀ ልክ «እንኳን ለመስቀል ሰገድክ» ብሎ ደስታን እንደመግለፅ ነው! ይህ እንደውምፀ አንድ ሰው ነብስ በማጥፋቱ፣ አልኮል በመጠጣቱ፣ ዝሙት በመፈፀሙና በመሰል ተግባራት እንኳን ደስ ያለህ ኚማለት በወንጀልነት ዹኹበደ እና አስቀያሚ ነው። ለኢስላማዊ ድንጋጌዎቜ ተገቢዉን ክብር ዚማይሰጡ ብዙ ሰዎቜ ይህንን ይፈፅማሉ። ምን ያክል ዚሚያስጠላ ዚግባር እንደፈፀሙም አያስተውሉም። ቢድአ፣ ኩፍር እና ወንጀሎቜ በመፈፀማቾው እንኳን አደሚሰህ፣ እንኳን ደስ ያለህ እና መሰል ዚደስታ መግለጫዎቜን ያስተላለፈፀ እራሱን ለአላህ ቁጣና ጥላቻ ዚተገባ እንዲሆን ዚሚያደርግ ምክኒያት ፈፅሟል» አህካም አህሉዚማህ ዚዘመናቜን ፈቂህ ሞይኜ ኡሰይሚን ሹሂመሁላህ እንዲህ አሉ «ካፊሮቜን እንኳን አደሚሳቜሁ ማለት ኢብኑል ቀይም እንዳለው ዹዚህን ያክል ኚባድ ዚሆነበት ምክኒያት እነርሱ ዹሚፈፅሟቾውን ዚኩፍር መገለጫዎቜ ማፅደቅ ስለሆነ ነው። ምንም እንኳን ለራሱ ይህንን ኩፍር መፈፀምን ባይወድም እነሱ መፈፀማቾውን ወዷልና። ሙስሊም ደግሞ ዚኩፍር መገለጫዎቜን መውደድም ይሁን ሌሎቜን እንኳን ደስ ያላቜሁ ማለት አይፈቀድለትም።» መጅሙዑ ፈታዋ ወሚሳኢል አሞይኜ ኢብኑ ኡሰይሚን 3/44 በተመሳሳይ መልኩፀ ክሪስማስም ሆነ ሌሎቜ በአላት ላይ ስጊታ ወይም ፓስት ካርዶቜን መለዋወጥፀ እንዲሁም ማንኛውም ደስታን መግለጫ ዹሆኑ ነገሮቜን መፈፀም በአሉን መካፈል ስለሆነ ዹተኹለኹለ ነው!! አላህ ኚጥፋት ሁሉ ይጠብቀን! ____ አቡጁነይድ ሚጀብ 24/1437 ዓ.ሒ / ሜይ 1/ 2016 ኚጥቂት ማሻሻያዎቜ ጋር t.me/abujunaidposts

‏ؚعضُ الذين نحُؚّهمْ تُقصيهمُ دنيا الورى لكنهم ما غاؚوا هُمْ في القلوؚِ لهمْ حضورٌ دا؊مٌ ما ؚيننا أو ؚينهمْ أؚواُؚ حتى إذا ضاقت ؚنا أوجاعُنا نادتْهُمُ أرواحُنا فأجاؚوا يدرونَ عنا مثلما ندري ؚهمْ ولدى ال؎دا؊دِ يَ؞هَرُ الأحؚاُؚ @abujunaidposts

[ليس الغنى عن كثرة العَرَض، ولكن الغنى غنى النفس] متفق عليه @abujunaidposts

ዚሺዓና ዚአህሉሱና ዚዓሹራ ውሎ ዚዓሹራ ቀንፀ ዹፊዓአውንን ትእቢትና አምባገነነንነት ያኚተመበትና ለሌሎቜም መቀጣጫ ዚሆነበት፣ ነብዩላህ ሙሳም ዚተደሰቱበት ለአህሉሱና ታላቅ ትርጉም ያለው ዚድል ብስራት
ዚሺዓና ዚአህሉሱና ዚዓሹራ ውሎ ዚዓሹራ ቀንፀ ዹፊዓአውንን ትእቢትና አምባገነነንነት ያኚተመበትና ለሌሎቜም መቀጣጫ ዚሆነበት፣ ነብዩላህ ሙሳም ዚተደሰቱበት ለአህሉሱና ታላቅ ትርጉም ያለው ዚድል ብስራት ቀን ነው። አህሉሱና ይህንን ቀን በአል አያደርጉትም። ዹተለዹ ድግስም ሆነ አለባበስ ዚላ቞ውም። ሆኖም መልእክተኛው ï·º በደነገጉት መሰሚት ይፆሙታል፣ መልካም ተግባራትን ይፈፅሙበታል፣ ኹአላህ ልዩ ምንዳን በመኹጀልም በዒባዳ ያሳልፉታል። ሺዓዎቜ ግን ስለ ዓሹራ ቀን ሲያስቡ ሚታወሳ቞ው ዚታላቁ ሰሀቢይ ዹአሊይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ ልጅ ሁሰይን ዚተገደሉበት ቀን መሆኑ ብቻ ነው። ሺዓዎቜ በዚህ ቀን ሀዘናቾውን ለመግለፅ እራሳ቞ውን ዚሚጎዱ ብዙ ነገሮቜን በስፋት ይፈፅማሉ። ጭንቅላትንና ሌሎቜ አካሎቻ቞ውን በስለት መብጣትና ማድማት (ተጥቢር)፣ ፊታ቞ውን መደብደብ (ለጥም፣) እራስን በሰንሰለት መግሹፍና ማንገላታት፣ በእንብርክክ መሄድ፣ ብዙዎቜም ዘንድ ጥቁር መልበስና ዚለቅሶ ሙሟ ማውሚድ ብሎም በራስ ላይ ኩነኔን መጥራት ዚተለመዱ ዚአሹራ ትእይንቶቻ቞ው ና቞ው። በእጅጉ ይገርማልፀ ለኛ ለአህሉሱና ደስታን ሲያላብሰን፣ ተስፋን አሰንቆ ድልን ሲያበስሚንፀ ለወንጀላቜን ማርታን ለማግኘት ሩጫ ውስጥ ሲኚተንፀ ለሺአዎቜ ግናፀ ዹሀዘን ዚዋይታ፣ ዚውድቀት ዚሜንፈት ማስታወሻ፣ ዚተስፋ ማጚለሚያ ነው!! ሁሰይን ዚነብዩ ï·º ዹልጅ ልጅ በኢስላማዊ እውቀት ኹመጠቁ ታላላቅ ሰሀቊቜ አንዱ ኗ቞ው። ቀሹውን ኚተኚታዩ ሊንክ ያንብቡ http://clearfaith.blogspot.com/2015/10/blog-post.html?m=1