es
Feedback
🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts

Ir al canal en Telegram

ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100

Mostrar mĂĄs
2 213
Suscriptores
-224 horas
-67 dĂ­as
-3430 dĂ­as
Archivo de publicaciones
ኡድሂያ ለማረድ ካቀዱ ከወዲሁ ጥፍርና ጸጉርዎን ከመቁረጥ ይቆጠቡ! ------------------- ☞ እንድ ሙስሊም ሀጅ የማያደርግ ከሆነና በዒድ አል አድሀ እለት ኡድሂያን ለማረድ ካሰበ የዙልሂጃ ወር ከገባበት የምጀመሪያዉ ቀን ጀምሮ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም፤ ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህም ተከታዩን የኡሙሰለማ ሀዲስ መሰረት ያደረገ ነው። عن أم سلمة رضي الله عنها أن النبي صلى الله عليه وسلّم قال : " إذا رأيتم هلال ذي الحجة ، وفي لفظ : "إذا دخلت العشر وأراد أحدكم أن يضحي فليمسك عن شعره وأظفاره ". رواه أحمد ومسلم ، وفي لفظ : " فلا يأخذ من شعره وأظفاره شيئاً حتى يضحي ". وفي لفظ : "فلا يمس من شعره ولا بشره شيئاً ". ከኡሙ ሰለማ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «የዙልሂጃ ወርን ጨረቃ ካያችሁና ከናንተ መካከል አንዱ ኡድሂያ ለማረድን ካቀደ፤ ፀጉሩንና ጥፍሩን ከመቁረጥ ይቆጠብ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል። በሌላም ዘገባም «ኡድሂያውን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩና ከጥፍሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። እንደዚሁ፤ «ከሰውነቱ ቆዳ ወይም ከፀጉሩ ምንንም አይቁረጥ» ብለዋል። ይህ ማንኛውም ሙስሊም እራሱን በሀጅ ላይ ካሉ ሰዎች ጋር የሚያመሳስልበት እና የተወሰኑ የኢህራም ክልከላዎችን ከነሱ ጋር የሚጋራበት ዲናዊ ስርአትና ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ☞ ጸጉርንና ጥፍርን ከመቁረጥ የሚከለከለው ለራሱ ወይም ለሰው በራሱ ገንዘብ የሚያርድ ሰው ብቻ ነው። ህጉ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው ሲባል፤ በወኪልነት ለሌላ ስው የሚያርድን ሰው አይጨምርም። ☞ እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም ማካካሻ ከፋራም የለበትም። አንዳንዶች እንደሚያስቡት ሳይሆን ወንጀሉን ቢፈፅምም ኡድሂያ ማረዱን መተው የለበትም። ☞ በስህተት ወይም በመርሳት ፀጉሩን ወይም ጥፍሩን የቆረጠ ሰው ምንም ወንጀል የለበትም። በተመሳሳይ መልኩ በጣም አስፈላጊ ሲሆን ቢቆርጥ ችግር የለውም። ለምሳሌ የተጎዳን የሰውነት ቆዳ ለማከም ወይም የተሰበረ ጥፍሩን ለማስተካከል መቁረጥ ይፈቀድለታል። ፠ ስለ ኡድሂያ ጥቂት ተጨማሪ ነጥቦች 1 - በዙልሂጃ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደ አላህ መቃረብ አንዱ ነው። 2- ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ صلى الله عليه وسلم ሱናዎች መካከል ነው። ኡድሂያ የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረግ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። 3- ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ ተቅዋና ታዛዥነት ግልጽ ማድረጋችንን ብቻ ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፤ {ﻟَﻦ ﻳَﻨَﺎﻝَ اﻟﻠَّﻪَ ﻟُﺤُﻮﻣُﻬَﺎ ﻭَﻻَ ﺩِﻣَﺎﺅُﻫَﺎ ﻭَﻟَٰﻜِﻦ ﻳَﻨَﺎﻟُﻪُ اﻟﺘَّﻘْﻮَﻯٰ ﻣِﻨﻜُﻢْ ۚ ﻛَﺬَٰﻟِﻚَ ﺳَﺨَّﺮَﻫَﺎ ﻟَﻜُﻢْ ﻟِﺘُﻜَﺒِّﺮُﻭا اﻟﻠَّﻪَ ﻋَﻠَﻰٰ ﻣَﺎ ﻫَﺪَاﻛُﻢْ ۗ ﻭَﺑَﺸِّﺮِ اﻟْﻤُﺤْﺴِﻨِﻴﻦَ} الحج 37 አላህን ሥጋዎቿም ደሞቿም ፈጽሞ አይደርሰውም፡፡ ግን ከእናንተ የሆነው ፍራቻ ይደርሰዋል፡፡ እንደዚሁ አላህን በመራችሁ ላይ ልታከብሩት ለእናንተ ገራት፡፡ በጎ ሠሪዎችንም አብስር፡፡» አል ሐጅ 37 4- ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። 5- ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። 6- ወንድም ይሁን ሴት ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። 7- የአላህ መልዕክተኛ صلى الله عليه وسلم እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣ ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ ወይም የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። 8- ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋራትም ይቻላል። 9- አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። 10- የኡድሂያውን ስጋ፣ ለቤት፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ ሶስት ቦታ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። አቡጁነይድ Http://www.t.me/abujunaidposts

10ቱ የዙልሒጃ ቀናት.pdf3.33 KB

🗞 ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው አስርቱ የዙልሂጃ ቀናት ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው፡፡ የአላህ ሰላምና እዝነት በታላቁ ነብይ በሙሀመድ በባልደረቦቻቸው እና በቤተሰቦቻቻው ሁሉ ላይ ይሁን፡፡ ከተከበሩት ወራት መካከል አንዱ የሀጅ ወር ዙልሂጃ ነው። ከቀናት ሁሉ አላህ ዘንድ የተወደዱት ደግሞ አስሩ የዙልሂጃ ቀናት ናቸው። እንደዉም ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው እነኝህ ቀናት ናቸው። የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፦ عن جَابِرِ بْنِ عَبْدِ اللهِ رَضِيَ الله عَنْهُ قَالَ: قَالَ رَسُولَ اللهِ صَلَّى الله عَلَيْهِ وَسَلَّمَ: "أَفْضَلُ أَيَّامِ الْدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ، يَعْنِي عَشْرُ ذِي الحْجَّةِ". صحيح الجامع ، رقم 1133 ጃቢር ኢብኑ ዓብዲላህ ባስተላለፉት ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል «ከዱንያ ቀናት ሁሉ ብልጫ ያላቸው፤ አስርቱ ቀናት ናቸው። ማለትም አስሩ የዙልሂጃ ቀናት» አልባኒ ሰሂሁል ጃሚዕ 1133 ላይ አስፍረውታል عن ابن عباس رضي الله عنهما، عن النبي صلى الله عليه وسلم قال: "ما من أيام العمل الصالح فيهن أحب إلى الله منه في هذه الأيام العشر. قالوا ولا الجهاد في سبيل الله !! قال : ولا الجهاد في سبيل الله، إلا رجل خرج بنفسه وماله ولم يرجع من ذلك بشيء" أخرجه البخاري ከኢብኑ ዓባስ በተዘገበ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል:‐ «በነዚህ አስር ቀናቶች ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች በበለጠ ስራዎች አላህ ዘንድ የተወደዱ የሚሆኑባቸው ቀናት የሉም፤ “በአላህ መንገድ ላይ የሚደረግ ጂሀድም ጭምር?” ተባሉ። እርሳቸውም፤ “ራሱንና ንብረቱን ይዞ ወጥቶ ምንም ያልተመለሰለት ሰው ሲቀር ጂሀድም ከዚህ አይበልጥም” አሉ።» ቡኻሪ ዘግበውታል በነዚህ ቀናቶች ትኩረት ልንሰጣቸው ከሚገቡ የዒባዳ አይነቶች መካከል:‐ 1. ጾም፦ ጾም ከስራዎች ሁሉ በላጭ ነውና በእነዚህ ቀናት መጾም እጅግ የተወደደ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ዘጠኙን የዙልሂጃ ቀናት ይጾሙ እንደነበር ተዘግቧል። (አስረኛው ቀን ግን ዒድ ስለሆነ አይጾምም) 2. ዚክሮችን ማብዛት፦ አላህን ማመስገን (አልሀምዱሊላህ) ፣ ተክቢር፣ ተስቢህ(ሱብሀነላህ) እና ተህሊል (ላ ኢላሀ ኢለላህ)፤ ኢባዳዉን ለማስታወስና የአላህን ስም ከፍ ለማድረግ በተለያዩ አጋጣሚዎች ድምጽን ከፍ አድርጎ እነዚህን ዚክሮች ማድረግ ይወደዳል። عن عبد الله بن عمر رضي الله عنهما عن النبي صلى الله عليه وسلم قال : "ما من أيام أعظم عند الله ولا أحب إليه العمل فيهن من هذه الأيام العشر فأكثروا فيهن من التهليل والتكبير والتحميد" أخرجه احمد 7/224 وصحّح إسناده أحمد شاكر ዓብዱላህ ኢብኑ ዑመር ባስተላለፉት ሀዲስ ነብዩ እንዲህ ብለዋል፤ «ከነዚህ አስር ቀናት በበለጠ አላህ ዘንድ ታላቅ የሆኑና መልካም ስራ እጅግ የተወደደባቸው ቀናት የሉም፤ ተህሊል ተክቢር እና ተህሚድ አብዙ» አል ኢማም አህመድ ዘግበውታል አህመድ ሻኪርም ሰሂህነቱን አረጋግጠዋል። ከተክቢር አደራረግ መካከል፤ الله أكبر ، الله أكبر لا إله إلا الله ، والله أكبر ولله الحمد “አላሁ አክበር፤ አላሁ አክበር፤ ላ ኢላሀ ኢለላህ ወላሁ አክበር ወሊላሂልሀምድ” የሚለው ዋነኛው ሲሆን ሌሎችም ይዘቶች አሉት። በእነዚህ ቀናት ውስጥ ሊደረግ የሚገባው ይህ ተክቢር ብዙ ሰዎች ስለማይፈጽሙት እየተረሱ ካሉ ሱናዎች መካከል ነው። ሰዎችን ለማስታወስ እና ሱናን ህያው ለማድረግ ድምጽን ከፍ አድርጎ ተክቢር ማድረግ ያስፈልጋል። ዓብዱላህ ኢብኑ ኡመር እና አቡሁረይራህ በነዚህ አስር ቀናት ገበያ ወጥተው ተክቢራ ሲያደርጉ ሰዎችም እያስታወሱ ተክቢራ ያደርጉ እንደነበር ተዘግቧል። ይህም፤ ሁሉም ሰው የራሱን ዚክር ያደርጋል ማለት ነው እንጂ ሰዎች እየተሰባሰቡ በአንድ ድምጽ ተክቢራ ያድርጉ ማለት አይደለም። ይህ መረጃ ያልተገኘለት የተሳሳተ አፈፃፀም ነው። 3. ሐጅና ዑምራ፦ በነዚህ ቀናት ውስጥ ከሚፈጸሙ መልካም ስራዎች መካከል ሐጅ ማድረግ ይገኝበታል፤ በነዚህ አስር ቀናት የሐጅ ዒባዳ ላይ ተገኝቶ በተገቢው መልኩ ከፈጸመው በአላህ ፍቃድ ከተከታዩ የአላህ መልዕክተኛ ብስራት ድርሻ ይኖረዋል፤ عن أبي هريرة رضي الله عنه قال: سمعته يقول: "الحج المبرور ليس له جزاء إلا الجنة" متفق عليه. ከአቡ ሁረይራ በተላለፈ ሀዲስ የአላህ መልዕክተኛ እንዲህ ብለዋል፤ «ከወንጀል የራቀና ተቀባይነት ያለው ሐጅ (አል-ሐጅ አል-መብሩር) ምንዳው ጀነት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡» ቡኻሪና ሙስሊም ተስማምተውበታል 4. ኡድሂያ፦ በነዚህ አስር ቀናት ከተወደዱ ተግባሮች መካከል ኡድሂያን በማረድ ወደአላህ መቃረብ ነው። የሚከተሉት ነጥቦች አጠር ያለ ግንዘቤን ይሰጣሉ፤ - ኡድሂያ በጣም ከጠነከሩ የነብዩ ሱናዎች መካከል ነው። የነብዩ ኢብራሂምን ሱና ህያው ከማድረጉ በተጨማሪ ለድሆች እና ችግረኞች መድረስ ነው። - ኡድሂያን በተመለከተ አላህ ከኛ የሚፈልገው ለእርሱ ያለንን ፍራቻ (ተቅዋ) ነው። - ኡድሂያ የሚታረደው ከዒድ ሰላት በኋላ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ከኢድ ሰላት በፊት ያረደ ሰው እንዲደግም አዘዋል። - ሚዛን በሚደፋው የኡለማዎች አቋም መሰረት የዒድ ሰላት ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሶስተኛው ቀን ጸሀይ እስክትጠልቅ ድረስ ኡድሂያን ማረድ ይቻላል። - ግመል፣ የቀንድ ከብቶች፣ በግና ፍየል ለኡድሂያ ይታረዱሉ። - የአላህ መልዕክተኛ እንከን ያለባቸውን እንስሳት እንዳናርድ ከልክለዋል። አንድ አይኑ የታወረ፣ ስብራት ያለበት፣ የከሳና የደከመ፣ የታመመ እንስሳ ለኡድሂያ አይሆንም። - ኡድሂያን ለብቻ ማረድ እንደሚቻለው ሁሉ ለሰባት ሆኖ አንድን ወይፈን ወይም በሬ መጋርትም ይቻላል። - አንድ ሰው ኡድሂያ ሲያርድ ለራሱ እና በህይወት ላሉም ይሁን በህይወት ለሌሉ ለቤተሰቦቹ አስቦ ሊያርድ ይችላል። - ኡድሂያውን ለራሱ፣ ለስጦታ እና ለሰደቃ አድርጎ መከፋፈሉ ሱና ነው። ይህ ማለት ግን እንደ አስፈላጊነቱ ለሶስቱም ያውለዋል ማለት እንጂ ሶስት እኩል ቦታዎች ይከፋፍለዋል ማለት አይደለም። - በዒድ ቀን ኡድሂያን ለማረድ አስቦ የዙልሂጃ ወር ከገባ ጥፍሩንና ጸጉሩን አይቆርጥም። ቆዳውንም አይቀርፍም። ይህ በሀጅ ላይ ያሉ ሰዎችን የሚመሳሰልበት ነብያዊ ትዕዛዝ ነው። ሆኖም ይህ የሚመለከተው የሚያርደዉን ሰው ብቻ ነው። እያወቀ ጥፍሩን ወይም ጸጉሩን የቆረጠ ወንጀል ፈጽሟልና ወደ አላህ በተውበት ሊመለስ ይገባዋል፤ ኡድሂያው ግን አይበላሽም። የመልካም ስራ በሮች ብዙ ናቸውና የቻልነዉን ሁሉ በመፈጸም ወደ አላህ መቃረብ ይገባል፤ የታሰረን ወይም የታመመን ሰው መጠየቅ፣ ዝምድናን መቀጠል፣ ሰደቃ ማብዛት፣ ሱና ሰላቶችን ማብዛት፣ ቁርዓን መቅራት፣ ዚክር ማብዛት፣ ዱዓን ማብዛት…ወዘተ ያስፈልጋል። አላህ በነዚህ ወርቃማ ጊዜያት ከሚጠቀሙና አላህ ዘንድ መልካም ምንዳን ከሚያገኙ ጠንካራና ብልህ የአላህ ባሮች ያድርገን። ✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ ህዳር 23/ 2004 ዓ.ል ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

እንዴ??? በዘመናችን ጣኦት ይመለካልን?? ------------------- በዚህ በሰለጠነ ዘመን ሰው ጣኦት ያመልካል ብዬ አላስብም ነበር? ሊባል ይችላል!!! ለመሆኑ ጣኦት ምንድን ነው? ክርስቶስን ማምለክና ጣኦት ማምለክ ይለያያሉን? ሮብን ለአብዶዪ አድርጎ ከሌላው ቀን የተለየ ተግባር መፈፀምስ ምንድን ነው? ሙታን አውሊያኦችን መማፀንና መለመን፣ ሀጃ እንዲፈፅሙልን መከጀልና ጣኦት ማምለክ ምን አገናኘው?? ለነዚህ ጥያቄዎች በቂ ምላሽን የያዘ አጭር መልእክት ነው። ይመልከቱት!! በሸይኽ ሳላህ አህመድ (አቡ ጁነይድ) 𒊹︎︎︎አጫጭርና ጠቃሚ መልዕክቶች ለማግኘት ይቀላቀሉን☟︎︎︎ ☟︎︎︎ 𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍𑁍 ❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀❀ ☀️ሁዳ መልቲሚዲያ ቴሌግራም 👇 t.me/huda4eth ፌስቡክ👇 fb.com/huda4eth ዩትዩብ👇 http://www.youtube.com/c/HudaMultimedia

{یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ ٱسۡتَعِینُوا۟ بِٱلصَّبۡرِ وَٱلصَّلَوٰةِۚ إِنَّ ٱللَّهَ مَعَ ٱلصَّـٰبِرِینَ} [እናንተ ያመናችሁ ሆ
{یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ ٱسۡتَعِینُوا۟ بِٱلصَّبۡرِ وَٱلصَّلَوٰةِۚ إِنَّ ٱللَّهَ مَعَ ٱلصَّـٰبِرِینَ} [እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በመታገስና በሶላት ተረዱ፡፡ አላህ ከታጋሾች ጋር ነውና] Surah Al-Baqarah: 153 @abujunaidposts

{یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ ٱسۡتَعِینُوا۟ بِٱلصَّبۡرِ وَٱلصَّلَوٰةِۚ إِنَّ ٱللَّهَ مَعَ ٱلصَّـٰبِرِینَ} [እናንተ ያመናችሁ ሆ
{یَـٰۤأَیُّهَا ٱلَّذِینَ ءَامَنُوا۟ ٱسۡتَعِینُوا۟ بِٱلصَّبۡرِ وَٱلصَّلَوٰةِۚ إِنَّ ٱللَّهَ مَعَ ٱلصَّـٰبِرِینَ} [እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በመታገስና በሶላት ተረዱ፡፡ አላህ ከታጋሾች ጋር ነውና] Surah Al-Baqarah: 153

ሐጅ ለመሄድ አስበዋልን? ለዝግጅት እንደዲሆንዎ ሐጅ እና ዑምራ App በነፃ አቅርበናል የሐጅ እና ዑምራን ድንጋጌዎች በቀላሉ ለመማር ይረዳ ዘንድ በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር የተዘጋጀው ይህ አፕ ነፃ፣ በመጠን አነስተኛ እና ብዙ ትምህርቶችን ያቀፈ መተግበሪያ አፕሊኬሽን ነው። ይጠቀሙበት ያስተዋውቁት፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=appinventor.ai_nesiha_org.Hajj ከጎግል ፕለይ ማውረድ ላልቻላችሁ Apk ፋይል አታች አድርገናል https://t.me/merkezuna/308 ___ ኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር www.nesiha.com

🔖 የእምነት ፈተና እና የኢማሙ አሕመድ ፅናት 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ ⌚️ 38:12 ደቂቃ 🍂 የአህሉሱና ኢማም አህመድ ኢብኑ ሀንበል በንጉሶች በታገዙ ጀህሚያዎች የደረሰባቸውን ከባድ ግፍና ፈተና ካለፉበት ፅናት የሚወሰዱ ትምህርቶች https://t.me/abujunaidposts/92 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

ክፍል 3- አብዛኛው ሙስሊም ማህበረሰብ አሽዓሪ ነውን? AUDIO (MP3) ____ 🏳️ የኡስታዝ ኢልያስ አህመድ የትምህርት መድረክ @ustazilyas

ክፍል 2-እውን ብዙሃኑ የኡማው ኡለማዎች አሽዓርያ ናቸውን? AUDIO (MP3) ____ 🏳️ የኡስታዝ ኢልያስ አህመድ የትምህርት መድረክ @ustazilyas

ክፍል 1- አሽዓሪያ ነባር ወይስ መጤ? AUDIO (MP3) ____ 🏳️ የኡስታዝ ኢልያስ አህመድ የትምህርት መድረክ @ustazilyas

"ነባሩ እስልምና" በሚል በነሲሓ ቲቪ በ 3 ክፍል የቀረበውን ፕሮግራም ለተከታታዮቻችን በኦዲዮ አቅርበናል ክፍል 1- አሽዓሪያ ነባር ወይስ መጤ? 🖇 የዳውንሎድ ሊንክ https://bit.ly/3zdi
"ነባሩ እስልምና" በሚል በነሲሓ ቲቪ በ 3 ክፍል የቀረበውን ፕሮግራም ለተከታታዮቻችን በኦዲዮ አቅርበናል ክፍል 1- አሽዓሪያ ነባር ወይስ መጤ? 🖇 የዳውንሎድ ሊንክ https://bit.ly/3zdiFk5 🔗 Telegram Link https://t.me/ustazilyas/695 🔗 Youtube Link https://youtu.be/OAYkzu036Mc ክፍል 2-እውን ብዙሃኑ የኡማው ኡለማዎች አሽዓርያ ናቸውን? 🖇 የዳውንሎድ ሊንክ https://bit.ly/3m46FK0 🔗 Telegram Link https://t.me/ustazilyas/696 🔗 Youtube Link https://youtu.be/Mfzqnj3ih7w ክፍል 3- አብዛኛው ሙስሊም ማህበረሰብ አሽዓሪ ነውን? 🖇 የዳውንሎድ ሊንክ https://bit.ly/3zdbcS0 🔗 Telegram Link https://t.me/ustazilyas/697 🔗 Youtube Link https://youtu.be/1h0uJ8YvR5k ____ 🏳️ የኡስታዝ ኢልያስ አህመድ የትምህርት መድረክ https://www.facebook.com/ustathilyas @ustazilyas

ነባሩ እስልምና - ክፍል 1 https://youtu.be/OAYkzu036Mc በመጅሊስ ተቋማዊ ለውጥ ዙርያ ተከታታይ ውይይት @ustazilyas
ነባሩ እስልምና - ክፍል 1 https://youtu.be/OAYkzu036Mc በመጅሊስ ተቋማዊ ለውጥ ዙርያ ተከታታይ ውይይት @ustazilyas

በመጅሊሱ ዙሪያ በኡዩብ ደርባቸው በኡስታዝ ሳላሕ እና በሸይኽ ኢልያስ አሕመድ መካከል ግንቦት 12/2014 በነሲሓ Tv ላይ የተቀረበ ውይይት

የተውሂድ_እውነታ_በቁርኣን.mp328.54 MB

የሸዋልን ፆም ለጀመሩ እህቶች አምስት አስፈላጊ ጥቆማዎች الحمد لله والصلاة والسلام على رسول الله وعلى آله وصحبه، أما بعـد: ከሸዋል ፆም ጋር በተያያዘ ብዙ እህቶች ከሚጠይቋቸው ጥያቄዎች በመነሳት አምስት ጥቆማዎች ይኖሩኛል፤ 1) ቀዳ ያለባት ሴት ከቀዳና ከሸዋል ሱና የትኛውን ታስቀድም? ☞ በሀይድ ወይም በወሊድ ደም ምክኒያት ረመዳንን አሟልታ ያልፆመች ሴት፤ ከሸዋል ስድስት ቀናት መፆምን አስመለክቶ በሀዲስ የተጠቀሰውን የአንድ አመት ፆም ምንዳ ለማግኘት አጅሩን እንደሚያገኝ ቃል የተገባለት ረመዳንን ካሟላ በኋላ የፆመው ሰው ስለሆነ፤ ቅድሚያ ረመዳንን መፆም ግድ ስለሚል በተቻላት መጠን ከሸዋል ሱና በፊት የረመዳንን ቀዷ ለማጠናቀቅ መሞከር ይኖርባታል። ይህ ከመጠራጠር ለመውጣት እና አጅሩን ከማግኘት አንፃር ኢባዳውን በአስተማማኝ መሰረት ላይ ለማሳረፍ ይረዳል። 📚 የሳውዲ ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ ይህንን በማስመልከት እንዲህ ብሏል፤ ¹ «ከረመዳን የተወሰኑ ቀናት ያሉበት ሰው በቅድሚያ እነሱን ሊፆምና ከዛ በኃላ ከሸዋል ወር ስድስት ቀናትን ሊፆም ይገባል፤ ምክኒያቱም ረመዳንን አስከትሎ ከሸዋል ስድስት ቀን ሊፆም የሚችለው ረመዳንን አሟልቶ ከፆመ ነው።» ፈታወለጅናህ 10/392 በተጨማሪን ሴቶች ይህንን መተግበራቸው ያለባችውን ቀዷ በጊዜ መክፈል ይችሉ ዘንድ ያበረታቸዋል። 2) የረመዳንን ወር በሙሉ ካልፆመችስ? 📚 ሸይኽ ኡሰይሚን እንደገለፁት² በወሊድ ወይም በተለያዩ በሽታዎች ምክኒያት ረመዳንን ሙሉዉን መፆም ያልቻለች ሴት ሸዋልን ቀዳ በማውጣት ከጨረሰችና ስድስቱን የሱና ቀናት መፆም የምትችልበት ጊዜ ሸዋል ውስጥ ካላገኘች የዘገየችው ከአቅም በላይ በሆነ ምክኒያት (ደሩራ) ስለሆነ ቀጣዩ የዙልቂእዳ ወር ከገባ በኃላም ቢሆን በሸዋል ሱና ነይታ ፆሟን ብታሟላው ኢን ሻ አላህ አጅሩን ታገኛለች። ይህንን መልእክት ያዘለውን የሸይኽ ኡሰይሚን ፈትዋ በመጅሙኡል ፈታዋ 20/19 ያገኙታል 3) ቀዳና የሸዋል ሱናን በአንድ ኒያ መፆም 📚 ሸይኽ ኢብኑ ባዝ ረሂመሁላህ (ኑሩን አለደርብ)² የጥያቄና መልስ ፕሮግራም ላይ ተጠይቀው ሲያብራሩ እንዲህ ብለዋል፤ «የስድስቱን ቀናት ፆም ከፈለገች በቅድሚያ ቀዳ አውጥታ በመቀጠል ሱናውን ፆም ትፁም። በሸዋል ወር ቀዳ አውጥታ ስድስቱን ቀናትም ከፆመች ትልቅ ኸይር ነው። የስድስቱን የሸዋል ቀናት ፆም ከቀዳ ጋር በአንድ ኒያ ብትፆም ግን የስድስቱን ቀናት አጅር ታገኛለች ብዬ አላስብም። የሸዋል ፆም የሚፆመው በተገደበ ጊዜ ሲሆን እራሱን የቻለ ኒያ ይፈልጋል።» ስለዚህም ሁለቱን በአንድ ላይ መፆም ሳይሆን ቅድሚያ ረመዳንን አሟልቶ ሱናውን ፆም መጀመር የተሻለ ነው። 4) የሸዋል ወር የመጀመሪያዎቹ ስድስት ቀናት ቢያልፉስ? ☞ ብዙ ሴቶች የሸዋል ፆም የሚባለው ወሩ እንደገባ ያሉት ስድስት ቀናት ብቻ ይመስሏቸዋል። ይህ ስህተት ነው። በሀዲሱ የተጠቀሰው ምንዳ ከሸዋል ወር ስድስት ቀናት የፆመን ሰው ሁሉ ይመለከታል። ይህ ደግሞ መጀመሪያም መጨረሻም በመካከልም ሊሆን ይችላል። 5) የሸዋልን ፆም አከታትሎ መፆም ☞ ሸዋል እንደገባ ብዙ ሰዎች አከታትለው በመፆም ይጨርሳሉ። ይህም ስንፍናን ለማስወገድና በረመዳን ያካበቱትን የመፆም ብቃት ላለማጣት ከማሰብ ነው። ነገር ግን በተቃራኒው ሰኞና ሀሙስ እንዲሁም አያመልቢድ በመፆም ሱና ፆም የመፆምን ልምድ ማዳበርም መልካም ነው። አንዳንድ ሴቶች አከታትለው መፆማቸው ግዴታ ስለሚመስላቸው ከመፆም ይሳነፋሉ። ይህ ሊታረም የሚገባው ግንዛቤ ነው። አላህ ፆማችንን ይቀበለን ዘንድ እማፀነዋለሁ! አቡጁነይድ ሸዋል 4/10/1436 ————// ———— ¹ فتاوى الجنة الدائمة 10/392 ² مجموع الفتاوى 20/19 ³ من موقع الشيخ http://www.binbaz.org.sa/node/13470 والله تعالى المسؤول أن يوفقنا لما يحب ويرضى t.me/abujunaidposts

የእናቶች ቀን... ሙስሊሞች እንዴት ያዩታል? እኛ ሙስሊሞች፤ እናትን በመታዘዝ፣ ለእናት መልካም በመዋልና አሷን በማስደሰት ታዘናል። እናትን ከመበደልና በሷ ላይ ከማመፅ በእጅጉ ተከልክለናል። ለእናት ክብር እንሰጥ ዘንድ በእርግዝና ወቅት ምን ያክል ድካምና እንግልት እንደሚገጥማት ቁርአን ያሳስበናል። (ﻭَﻭَﺻَّﻴْﻨَﺎ اﻹِْﻧﺴَﺎﻥَ ﺑِﻮَاﻟِﺪَﻳْﻪِ ﺣَﻤَﻠَﺘْﻪُ ﺃُﻣُّﻪُ ﻭَﻫْﻨًﺎ ﻋَﻠَﻰٰ ﻭَﻫْﻦٍ ﻭَﻓِﺼَﺎﻟُﻪُ ﻓِﻲ ﻋَﺎﻣَﻴْﻦِ ﺃَﻥِ اﺷْﻜُﺮْ ﻟِﻲ ﻭَﻟِﻮَاﻟِﺪَﻳْﻚَ ﺇِﻟَﻲَّ اﻟْﻤَﺼِﻴﺮُ) لقمان 14 «ሰውንም በወላጆቹ (በጎ እንዲያደርግ) በጥብቅ አዘዝነው፡፡ እናቱ ከድካም በላይ በሆነ ድካም አረገዘችው፡፡ ጡት መጣያውም በሁለት ዓመት ውስጥ ነው፡፡ ለእኔም ለወላጆችህም አመስግን በማለት አዘዝነው፡፡ መመለሻውም ወደኔ ነው፡፡» ሉቅማን 31:14 እኛ ዘንድ እናትን ማገልገል በህይወት ዘመኗ ብቻ ሳይሆን ከሞተችም በኃላ ይቀጥላል። አንድ ሙስሊም ለእናቱ ያለውን ክብር ከሚገልፅባቸው ተግባራት መካከል፤ የእናትን ኑዛዜ ተግባራዊ ማድረግ፣ ዱዓ ማድግ፣ ከአላህ ማርታን መጠየቅ፣ ቤተሰቧንና ጓደኞቿን ማክበር ይገኝበታል። በጥቅሉ እናትን ማስደሰት ለጀነት ከሚያበቁ ታላላቅ መልካም ስራዎች ይመደባል። በኢስላማዊ ሸሪዓ ለእናት የተሰጠውን ክብር በየትኛውም ምድራዊ ህግ ወይም ሀይማኖት አናገኘውም። እናትን አስመለክቶ የተጣለብን ሀላፊነት ከአባት የበለጠ መሆኑም ተገልፆልናል። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهُ قَالَ : [جَاءَ رَجُلٌ إِلَى رَسُولِ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَقَالَ : يَا رَسُولَ اللَّهِ ، مَنْ أَحَقُّ النَّاسِ بِحُسْنِ صَحَابَتِي ؟ قَالَ : أُمُّكَ . قَالَ : ثُمَّ مَنْ ؟ قَالَ : ثُمَّ أُمُّكَ . قَالَ : ثُمَّ مَنْ ؟ قَالَ : ثُمَّ أُمُّكَ . قَالَ : ثُمَّ مَنْ ؟ قَالَ : ثُمَّ أَبُوكَ] رواه البخاري ومسلم አቡ ሁረይራ እንዲህ ብለዋል፤ «አንድ ሰው የአላህ መልእክተኛ ﷺ ዘንድ መጣና እንዲህ አላቸው፤ የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ከማንም በላይ መልካም ልውልለት የሚገባ ሰው ማነው? በማለት ጠየቀ። "እናትህ" አሉት። ቀጥሎስ? አላቸው። "እናትህ" አሉት። ቀጥሎስ? አላቸው። "እናትህ" አሉት። ቀጥሎስ? አላቸው። "አባትህ" አሉት» ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል የእናቶች ቀንን ማክበር እንዴት ይታያል? ኢስላም ለእናት ታላቅ ክብርን አጎናፅፏል። ይሁንና "የእናቶች ቀን" በማለት በአመት አንድ ቀን ብቻ እንድትከበር አላዘዘም። ይህንንም ለማብራራት፤ 1) የእናቶችን ቀን በዓል አድርጎ ማክበር በዲናችን ያልነበረ እንግዳ ተግባር ነውና በዲን ውስጥ እንደተጨመረ ቢድዓ እንጂ እንደመልካም ስራ አይታይም። መልእክተኛው፤ እንዲሁም ሰሀቦችም ይሁኑ የዚህ ኡማ ታላላቅ መሪዎች ሁሉ አልፈፀሙትም። መልእክተኛው ﷺ ከቢድዓ ሲያስጠነቅቁ እንዲህ ብለዋል፤ وشَرُّ الْأُمُورِ مُحْدَثَاتُهَا ، وَكُلُّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ رواه مسلم والنسائي وزاد:وَكُلُّ ضَلَالَةٍ فِي النَّارِ. «የነገሮች ሁሉ ክፉ፤ (በዲን ውስጥ) አዳዲስ ፈጠራዎች ናቸው፤ ቢድዓ ሁሉ ጥመት ነው!» ሙስሊም ዘግበውታል። በነሳኢ ዘገባ ደግሞ «ጥመት ሁሉ ደግሞ የእሳት ነው» የሚለውን ጭማሪ እናገኛለን። ሆኖም፤ ቢድዓ በዲን ውስጥ መጨመር ነው። ይህ ተግባር ኢባዳ አይደለም በአሉም እንዲሁ ነውና ታዲያ ለምን ቢድአ ይሆናል የሚል ጥያቄ የሚያነሱ አሉ። በቅድሚያ፤ ለጉዳዩ ያለንን እይታ ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎች ዘንድ ባለው መልካም ስራ የመስራት ግንዛቤ ሳይሆን እንደ ኢስላም የመልካም ተግባራት ትርጓሜ ልናጤነው ይገባል። እንደ ኢስላም የሚታዩም ይሁን ልባዊ መልካም ስራዎች ሁሉ ኢባዳ ናቸው። እናትን ማስደሰት በአኼራ ታላቅ ደረጃን የሚያስገኝ የፅድቅ ዲናዊ ተግባር ኢባዳ መሆኑ ግልፅ ነው። አመታዊ በአሉም ቢሆን እንደሙስሊም ካሰብነው ለእናት መልካም በመዋል አጅር ለማግኘት ዲናዊ ስራ የሚሰራበት ቀን ነው። በዓል ማለት፤ በየአመቱ በሆነ ቀን በቋሚነት የሚደጋገምና ሰዎች በአልነቱን አስበውት የሚውሉት ቀን ነው። ቀናት ሁሉ የአላህ ናቸውና ለሆነ መልካም ስራ የሆነን ቀን በመምረጥ ቋሚ እና አመታዊ በአል አድርገን ስንደነግገው ከዲን ጋር የሚጋጭ ተግባር ይሆናል። በአል ማድረግ የምንችለው በዲናችን የታወቁትን አላህ የደነገጋቸውን የዒድ አልፊጥር እና የኢድ አል አድሐ በአላት ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ያሉ በአላት ወይ ከሌላ እምነቶች የተወሰዱ ወይም ደግሞ በዲን ውስጥ መሰረት የሌላቸው ፈጠራዎች ናቸውና አይፈቀዱም። ስለዚህም ታላላቅ ኡለማዎችን ያቀፈው ቋሚ የፈትዋ ኮሚቴ የእናቶች ቀንን ማክበር እንደማይፈቀድ ብይን ሰጥቷል (ፈታዋለጅናህ ቅፅ 3 ገፅ 86) 2) የእናቶች ቀን የተቀዳው ቤተሰባዊና ማህበራዊ ትስስራቸው በእጅጉ ከተጎዳ ካፊር ማህበረሰቦች ተግባር ስለሆነ ቢድዓ ከመሆኑ በተጨማሪ ከካፊሮች ጋር መመሳሰል ነው። ሙስሊም በማንነቱ ሊኮራና ምርጥ የሙስሊም ትውልዶችን አርአያ ሊያደርግ እንጂ የሌሎች ጭራ ሊሆን አይገባም። የሚገርመው ይህ በአል የመጣብን የወላጆች ክብር ከጠፋባቸውና በደል ከተንሰራፋባቸው ማህበረሰቦች መሆኑ ነው። ወላጆቻቸውን የአዛውንቶች መጦርያ ጥለው በአመት እንኳ ለመጠየቅ ፍቃደኛ የማይሆኑ ሰዎች ከበዙባቸው ሀገራት ነው። እነሱ ዘንድ ወላጆችን ማስከፋትና መበደል እጅጉን ተንሰራፍቷል። ይህም ስለሆነ እናታቸውን የሚያስታውሱበትን ቀን መመደባቸው አይገርምም። አለዚያማ ከብዙ አመታት መማፀን በኃላ ልጆቻቸው ሳያዩዋቸው የሚሞቱ ወላጆች በርካታ መሆናቸውን በነዚህ ሀገራት የሚኖሩ ወዳጆቻችን ያጫውቱናል። ለነሱ በእናቶች ቀን የሚፈፅሙት ዚያራና መልካም ስራ አመቱን ሙሉ ያሳዩትን ጉድለት የሚያካክስ ይመስላቸዋል። እኛ ሙስሊሞች ዘንድ ግን ሁኔታው ይለያል። አመቱን ሙሉ የእናትን ፍቅር ስናገኝና ስናገለግል ብንኖር ውለታዋን እንደማንመልስ ዲናችን ያስተምረናል። ታዲያ በአመት አንድ ቀን መርጦ እናት እናት ማለት እና ማሟሟቅ ምንም ትርጉም አይኖረውም። ሸይኽ ኡሰይሚን እንዲህ ብለዋል፤ «እናት፤ በአመት አንድ ቀን ብቻ ትኩረትን ከመቸሯ የበለጠ ሀቅ አላት። እንደውም ልጆች እናታቸውን የመንከባከብ ግዴታ አለባቸው። እንደዚሁ፤ ከአላህ ትእዛዝ ጋር እስካልተጋጨ ድረስ እናትን በማንኛውም ጊዜና ቦታ መታዘዝ ግዴታ ነው» መጅሙዑል ፈታዋ 2/301 እዝነትና መልካምነትን ያቀፈ ነውና ይህንን ታላቅ ዲን ጠንክረን እንያዝ! ከአዳዲስ ድንጋጌዎችም በርሱ እንብቃቃ፤ ስርአትና ድንጋጌዎቹንም እንተግብር። ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው! ወንድማቸሁ አቡጁነይድ ግንቦት 3/2007 --------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts

🍂 የትዕግስት ፍሬ በነብዩ አዩብ ታሪክ 🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ 🔗 Share Link https://t.me/abujunaidposts/356 ---------------- 📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች @abujunaidposts