es
Feedback
Protestant mezmur collection

Protestant mezmur collection

Ir al canal en Telegram

Protestant song ethio

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Protestant mezmur collection

El canal Protestant mezmur collection (@protestantmezmurcollection) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 13 376 suscriptores, ocupando la posición 5 465 en la categoría Música y el puesto 2 526 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 13 376 suscriptores.

Según los últimos datos del 19 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -73, y en las últimas 24 horas de 0, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 20.05%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 6.00% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 2 683 visualizaciones. En el primer día suele acumular 803 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
Protestant song ethio

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 20 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Música.

13 376
Suscriptores
Sin datos24 horas
-207 días
-7330 días
Archivo de publicaciones
photo content

👉 "ኩርፊያ የጊዜ ሌባ ነው!" ባልና ሚስት ለ40 ዓመታት በትዳር አብረው ኖረዋል። አንድ ቀን ግን በሆነ ትንሽ ነገር ተጣልተው "የዝምታ ጦርነት" ውስጥ ገቡ። ሁለቱም ኩሩ ስለነበሩ "ለምን እኔ ቀድሜ አናግራለሁ?" በሚል እልህ ለሳምንታት ሳይነጋገሩ ቆዩ። አንድ ቀን ባልየው ከቤት ወጥቶ ሲመለስ ለሚስቱ በጣም የሚያምር አበባና ደብዳቤ ይዞ መጣ። ነገር ግን ኩርፊያው ስላልበረደለት አበባውን ጠረጴዛ ላይ አስቀምጦ፣ ደብዳቤውን ከስሩ አድርጎ ምንም ቃል ሳይተነፍስ ወደ መኝታ ክፍሉ ገባ። ሚስትየው "አሁንም በጽሁፍ ነው የሚነግረኝ? በአፉ መናገር አቅቶት ነው?" ብላ በንዴት አበባውንም ሆነ ደብዳቤውን ሳታየው ወደ መኝታ ክፍሏ ገባች። ለቀናት ያ ደብዳቤ እዛው ጠረጴዛ ላይ ተቀምጦ ቀረ። እሷም አላነበበችውም፣ እሱም "አንብቢው" አላላትም። ከሳምንት በኋላ ባል በድንገት በሞት ተለየ። ሚስት በሀዘን ተሰባብራ ቀናት አለፉ።አንድ ቀን ቤቷን ስታስተካክል ያን የደረቀ አበባና ከስሩ ያለውን ደብዳቤ አገኘች። ቶሎ ከፈተችው። ደብዳቤው እንዲህ ይል ነበር፦ "የኔ አለም፣ ዝምታችንን ልሰብረው ፈለግኩ። ዛሬ ዶክተር ጋር ሄጄ ነበር፤ የልብ ህመሜ እየጸና መሆኑንና ብዙ ጊዜ እንደማይቀረኝ ነገረኝ። የቀሩኝን ጥቂት ቀናት ካንቺ ጋር እየሳቅኩና እየተጨዋወትኩ ማሳለፍ እፈልጋለሁ። እባክሽን ይቅር በይኝና አናግሪኝ። እወድሻለሁ።" ሚስት ደብዳቤውን አንብባ ስትጨርስ በለቅሶ ተዝለፈለፈች። ነገር ግን የሚሰማት አልነበረም። ያ ሁሉ ቀን በከንቱ በዝምታ መባከኑ፣ የመጨረሻ ቃላቱን ሳይነግራት ማለፉ የዘላለም ቁስል ሆነባት። ብዙዎቻችን ነገ የምንኖር ይመስለንና ዛሬን በኩርፊያና በዝምታ እናባክናለን። ቂም መያዝ ሰውን አይቀጣም፣ የሚቀጣው የራሳችንን ሰላምና አብሮነት ነው። • "ይቅርታ" ማለት ዝቅ ማለት አይደለም፤ ለግንኙነታችሁ ትልቅ ዋጋ መስጠት እንጂ። • ሳታወሩ የምታሳልፉት እያንዳንዱ ደቂቃ ተመልሶ አይመጣም። • ያላችሁን ፍቅር ዛሬውኑ ግለጹ፤ ነገ ላይኖር ይችላልና። ሰው ከሞተ በኋላ ከመቆጨት፣ በህይወት እያለ ይቅርታ መጠየቅ የትኛው ይከብዳል? እናንተስ በኩርፊያ ምክንያት ያመለጣችሁ ትልቅ ዕድል አለ?

✍️ከዕለታት አንድ ቀን፣ በአንድ መንደር ውስጥ የሚኖር ዮናስ የተባለ ሰው ነበረ። ዮናስ መጥፎ ሰው ባይሆንም፣ በአንድ መጥፎ ልማዱ ግን በመንደሩ ይታወቃል፤ እሱም የሰማውን ወሬ ሁሉ እውነትነቱን ሳይመረምር ወዲያና ወዲህ ማውራትና ማናፈስ ነበር። አንድ ቀን ዮናስ ስለ መንደሩ መምህር አንድ ያልተረጋገጠ መጥፎ አሉባልታ ሰማ። ወዲያውኑም ሳይገታ ለጓደኞቹ፣ ለጎረቤቶቹና ለአገኘው ሰው ሁሉ አወራው። ወሬው ልክ እንደ ሰደድ እሳት በመንደሩ ተሰራጭቶ የመምህሩን መልካም ስም ሙሉ በሙሉ አጠፋው፤ ቤተሰቦቹም በትልቅ ሀዘን ላይ ወደቁ። ከጥቂት ቀናት በኋላ ግን፣ ዮናስ ያወራው ወሬ ፍጹም ውሸትና አሉባልታ መሆኑ በግልጽ ታወቀ። ዮናስ ባደረገው ነገር ክፉኛ ተጸጸተ፤ ሕሊናውም እረፍት ነሳው። የተናገረው ወሬ ያደረሰውን ጉዳት እንዴት ማስተካከል እንዳለበት ለመጠየቅ በመንደሩ ወደሚኖሩት አንድ ትልቅ ጥበበኛ ሽማግሌ ዘንድ ሄደ። ሽማግሌው ዘንድ ቀርቦም፦ አባቴ፣ እባክዎትን ይርዱኝ! እውነትነቱን ሳላውቅ ባወራሁት አሉባልታ ምክንያት የአንድን ንጹህ ሰው ስም አጥፍቻለሁ። አሁን ግን በጣም ተረድቼዋለሁ፤ ይህንን ስህተቴን እንዴት ማረም እችላለሁ? ሲል በለቅሶ ጠየቃቸው።ሽማግሌው የዮናስን የንስሃ ልብ ተመለከቱና እንዲህ አሉት፦ ልጄ ሆይ፣ ያጠፋኸውን ስም መልሰህ ማስተካከል የምትችልበት አንድ መንገድ አለ። ነገር ግን መጀመሪያ የምነግርህን ነገር በትክክል መፈጸም አለብህ።ዮናስም ለማድረግ ተስማማ። ሽማግሌው ቀጠሉ፦ አሁን ወደ ቤትህ ሂድና አንድ ትልቅ የትራስ ከረጢት ሙሉ በሙሉ የወፍ ላባዎችን ሙላው። ከዚያም በከተማው መሀል ባለው አደባባይ ላይ ቁም፤ የከረጢቱን አፍ ከፍተህ ላባዎቹን በሙሉ በነፋሱ ላይ በትናቸው። ይህንን አድርገህ ስትጨርስ ተመልሰህ ና።ዮናስ በሽማግሌው ትዕዛዝ ቢገረምም፣ የተባለውን ለማድረግ ፈጠነ። አንድ ከረጢት ሙሉ ላባ አዘጋጅቶ ወደ አደባባዩ በመሄድ በነፋሱ ላይ በትነው። ነፋሱም ላባዎቹን እየወሰደ ወደ ተለያዩ አቅጣጫዎች፣ ወደ ሩቅ ጫካዎች፣ ወደ ቤቶች ጣሪያና ወደ ገደላገደሉ በታተናቸው። ዮናስ ከረጢቱ ሲባዶ ወደ ሽማግሌው ተመለሰ። ዮናስ በደስታ፡- አባቴ፣ የተባለውን በሙሉ ፈጽሜያለሁ፤ ላባዎቹን በነፋስ በትኛቸዋለሁ አላቸው።ሽማግሌው ግን ረጋ ብለው አይኑን እያዩ እንዲህ አሉት፦በጣም ጥሩ ልጄ! አሁን ደግሞ ሁለተኛውና ዋናው ሥራህ ይቀራል። አሁኑኑ ተመልሰህ ሂድና በነፋስ የበተንካቸውን ላባዎች በሙሉ አንድ በአንድ ለቅመህ ወደዚህ ከረጢት ውስጥ መልሳቸው። አንድም ላባ መቅረት የለበትም። ዮናስ ደነገጠ! ራሱንም እየነቀነቀ፡- አባቴ! ይህ እኮ ፍጹም የማይቻል ነገር ነው! ነፋሱ ላባዎቹን ወደ የት እንደወሰዳቸው አላውቅም፤ አብዛኞቹ እኮ በጣም ርቀው ሄደዋል፣ መቼም ቢሆን ተለቅመው አያልቁም! አላቸው።በዚህ ጊዜ ሽማግሌው በጥልቀት ተነፈሱና በትልቅ ማስተማሪያ ድምፅ እንዲህ አሉት፦እንግዲህ እወቀው ልጄ! አንተ የምታወራው አሉባልታና የሰው ሀሜትም ልክ እንደነዚህ ላባዎች ናቸው። ከአፍህ አውጥተህ በሰዎች ጆሮ ላይ ስትበትናቸው ነፋስ እንደወሰዳቸው ላባዎች በየቦታው ይበተናሉ፤ የት እንደደረሱም አታውቅም። በኋላ ላይ ብትጸጸትና ‘ውሸት ነው’ ብለህ ብታስተባብል እንኳ፣ የሰዎችን አእምሮ አዳርሰህ የተበላሸውን ስም እንደ ድሮው ሙሉ በሙሉ ማስተካከል አትችልም። ስለዚህ ላባውን ከመበተንህ በፊት (ቃላትን ከአፍህ ከማውጣትህ በፊት) ሁልጊዜ አስብበት። 👉 አሉባልታ አንዴ ከተናገሩት በኋላ የሚያስከትለውን ጉዳት መልሶ ማረም በጣም ከባድ አልፎ ተርፎም የማይቻል ይሆናል። 👉 አሉባልታን አለማውራት ብቻ ሳይሆን፣ ሌሎች ሲያወሩም አለመስማትና ቦታ አለመስጠት እራስንና ሌሎችን ከጥፋት ይታደጋል። 👉 እውነተኛ «ክብር ያለው ሰው» የሰዎችን ስም ልክ እንደ ራሱ ስም በጥንቃቄ ይጠብቃል። ማረጋገጫ የሌለውን ወሬ ከመበተን ይልቅ ዝምታን ይመርጣል።✍️

መንፈሳዊ ኮንፍራንስ የመዳን ድምፅ አለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን አሰላ ከግንቦት 14 - 16 አርብ ቅዳሜ እሁድ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል አድራሻ:- አሰላ ከተማ ሀንቁ ቀበሌ ፊት
መንፈሳዊ  ኮንፍራንስ  የመዳን ድምፅ አለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን አሰላ ከግንቦት 14 - 16  አርብ ቅዳሜ እሁድ  ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል አድራሻ:-  አሰላ ከተማ ሀንቁ ቀበሌ ፊት ለፊት

መንፈሳዊ ኮንፍራንስ የመዳን ድምፅ አለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን አሰላ ከግንቦት 14 - 16 አርብ ቅዳሜ እሁድ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል አድራሻ:- አሰላ ከተማ ሀንቁ ቀበሌ ፊት
መንፈሳዊ  ኮንፍራንስ  የመዳን ድምፅ አለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን አሰላ ከግንቦት 14 - 16  አርብ ቅዳሜ እሁድ  ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል አድራሻ:-  አሰላ ከተማ ሀንቁ ቀበሌ ፊት ለፊት

የወንጌል ስርጭት በአሰላ ከተማ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
የወንጌል ስርጭት በአሰላ ከተማ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል

አንድ ቅቤ አምራች ገበሬና ዳቦ አምራች ነጋዴ እንደ አጋጣሚ ድግስ ላይ ተገናኝተው ያወራሉ፡፡ በጨዋታቸው በጣም ስለተግባቡ ከዚህ በኋላ አጋጣሚ ፈጥረው ለመገናኘት ይስማማሉ፡፡ ነጋዴው ጠዋት ጠዋት 300 ግራም ዳቦ ሲልክለት ገበሬው ደግሞ ማታ ማታ 300 ግራም ቅቤ ሊልክለት ተስማሙ፡፡ በዚህ መልኩ ብዙ ጊዜ ከቆዩ በኋላ ነጋዴ የቅቤ መጠን እየቀነሰ መሄዱን አየ፡፡ በመጨረሻም ሚዛን ላይ ሲያስቀምጠው 150 ግራም ሆኖ አገኘው፡፡ በዚህም በጣም አዘነ፤ ተበሳጨም፡፡ ገበሬውንም አስጠራው፡፡ ሌሎች ሰዎች እንዲያዳምጡት አድርጎ ‹ከተስማማነው ውጭ የቅቤውን መጠን ለምን ቀነስከው?› ሲል ጠየቀው፡፡ ገበሬውም ‹እኔ ፈጽሞ አልቀነስኩትም› ሲል በአግራሞት መለሰ፡፡ ነጋዴውም ቅቤውን በሚዛን ለክቶ አሳየው፡፡ 150 ግራም ነው፡፡ ገበሬውም አዘነ፡፡ ‹እኔ ቤት ውስጥ የ300 ግራም መለኪያ የለኝም፡፡ አንተ ጠዋት ዳቦውን ስትልክልኝ በእጅ ሚዛኑ አንደኛው ሰሐን ላይ አደርገዋለሁ፤ ከዚያም ቅቤውን በሌላኛው ሚዛን አስቀምጠዋለሁ፡፡ ልክ ከዳቦው ጋር እኩል ሲመዝኑ በዕቃ አዘጋጅቼ እልክልሃለሁ› አለው፡፡ ወዲያውም ጠዋት የላከለትን ዳቦ አውጥቶ ሚዛኑ ላይ አስቀመጠው፡፡ ዳቦው 150 ግራም ነበር የሚመዝነው፡፡ ነጋዴው አፈረ፡፡ ‹የምታገኘው ለሌላው ባደረግከው ልክ ነው፡፡ 150 ሰጥተህ 300 ልታገኝ አትችልም፤ እባብ ሰጥተህ ርግብ፣ ድንጋይ ሰጥተህ ዳቦ፣ እሬት ሰጥተህ ማር ልታገኝ አትችልም፤ አንተ ብቻ ብልጥ ልትሆን አትችልም፤ ማሾውን አጥፍተህ ብርሃን ልታገኝ አትችልም፤ ሌላው ገድለህ አንተ በሰላም ልትኖር አትችልም› አለው ገበሬው፡፡ ማንኛውም ድርጊት ተመሳሳይና ተመጣጣኝ የሆነ ምላሽ አለው፡፡ አንተ እዚህ ለብቻህ ቤትህ ውስጥ ሆነህ ክፉ ስታደርግ ሌላውም በቤቱ ብቻውን ሆኖ ክፉውን ይመልስሃል፡፡ ‹እዛም ቤት እሳት አለ› እንዳሉት ነው አለቃ ገብረ ሐና፡፡ አንተ ጎመድ ይዘህ ከወጣህ ሌላውም አያቅተውም፤ አንተ ገጀራህን ከሳልክ ሌላውም ይስላል፤ አንተ የሌላውን ወገን ስታፈናቅል፣ ያኛውም ያንተን ወገን ያፈናቅላል፡፡ ዛፍ ቆርጠህ ዝናብ፣ በካይ ጋዝ እየለቀቅክ የተስተካከለ የአየር ንብረት አትጠብቅ፡፡ ተፈጥሮም በሰጠሃት መጠን ነው የምትመልስህ፡፡ በዓለም ላይ ሚዛኑ አንድ ነው፤ ተመዛኞቹ ግን ይለያያሉ፡፡ እዚህ ካጎደልክ፣ እዚያም ያጎድሉብሃል፡፡

መንፈሳዊ ኮንፍራንስ በአለ - ኤል ቤተ ክርስቲያን አሰላ ከሚያዝያ 22 - 25 ሐሙስ አርብ ቅዳሜ እሁድ ሙሉ ቀን ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል መቅረት አይቻልም አድራሻ ቀበሌ 1 ከት
መንፈሳዊ  ኮንፍራንስ  በአለ - ኤል ቤተ ክርስቲያን አሰላ ከሚያዝያ 22 - 25 ሐሙስ አርብ ቅዳሜ እሁድ ሙሉ ቀን ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል መቅረት አይቻልም አድራሻ  ቀበሌ 1 ከትንቢት ሆቴል ጀርባ

photo content

OROMOO & AMHARIC WEDDING SONG የሠርግ መዝሙር FAARFANNAA CIDHAA @ProtestantWeddingsong @protestantmezmurcollection @protestantsongn
OROMOO & AMHARIC WEDDING SONG የሠርግ መዝሙር FAARFANNAA CIDHAA @ProtestantWeddingsong @protestantmezmurcollection @protestantsongnew @protestantmezmurcollection

OROMOO & AMHARIC WEDDING SONG የሠርግ መዝሙር FAARFANNAA CIDHAA @ProtestantWeddingsong @protestantmezmurcollection @protestantsongn
OROMOO & AMHARIC WEDDING SONG የሠርግ መዝሙር FAARFANNAA CIDHAA @ProtestantWeddingsong @protestantmezmurcollection @protestantsongnew @protestantmezmurcollection

photo content

photo content

sagantaa ayyaana du'a ka'uu sababeeffachuun kan qophaa'e
sagantaa ayyaana du'a ka'uu sababeeffachuun kan qophaa'e