es
Feedback
Fit Corner Sport- ፊት ኮርነር ስፖርት

Fit Corner Sport- ፊት ኮርነር ስፖርት

Ir al canal en Telegram

Will provide different Training & Consultancy on fitness & wellness industry.

Mostrar más
1 572
Suscriptores
+224 horas
+47 días
-730 días
Archivo de publicaciones
As usual, we showed up and got it done! 🔥 Mass sport + amazing people + unstoppable energy = perfect day. 💪🏽🙌🏽 # fit cor
+7
As usual, we showed up and got it done! 🔥 Mass sport + amazing people + unstoppable energy = perfect day. 💪🏽🙌🏽 # fit corner sport

ያበሎ ከተማ የቦረና ህዝብ የእንግዳ ተቀባይነት መለያ ናት። ወደ ቦረና ሲመጡ ሰውን እንደ እንግዳ ሳይሆን እንደ ቤተሰብ ይቀበላሉ። ፍቅር፣ ክብር፣ ባህል እና መተሳሰብ በየቤቱ የሚታይበት ምድር ነው።
+6
ያበሎ ከተማ የቦረና ህዝብ የእንግዳ ተቀባይነት መለያ ናት። ወደ ቦረና ሲመጡ ሰውን እንደ እንግዳ ሳይሆን እንደ ቤተሰብ ይቀበላሉ። ፍቅር፣ ክብር፣ ባህል እና መተሳሰብ በየቤቱ የሚታይበት ምድር ነው። የቦረና ህዝብ ፈገግታ፣ እና እንክብካቤ ለማንም የማይረሳ ትውስታ ይሆናል። እየተደረገልን ያለው አቀባበል የእውነት ልዩና ከልብ ነው:: #Yabelo #Borena #Oromia #Hospitalit

Saturday morning workouts are ON tomorrow — get ready, guys! 💪🔥 Let’s start the weekend strong, sweat together, and crush o
Saturday morning workouts are ON tomorrow — get ready, guys! 💪🔥 Let’s start the weekend strong, sweat together, and crush our goals. See you in the gym!”

#ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ # አዳማ ዩኒቨርስቲ # የኢፌድሪ ህብረት ሰራ ማህበራት ከፊት ኮርነር ሰፖርት ጋር በመተባበር ላለፉት ስምንት ቀናት በአዳማና በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች ስሰጡ የነበሩ የአካል ብቃት ሰል
+7
#ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ # አዳማ ዩኒቨርስቲ # የኢፌድሪ ህብረት ሰራ ማህበራት ከፊት ኮርነር ሰፖርት ጋር በመተባበር ላለፉት ስምንት ቀናት በአዳማና በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲዎች ስሰጡ የነበሩ የአካል ብቃት ሰልጠናዎች በስኬት ተጠናቀቁ:: # ፊት ኮርነር ስፖርት # ህብረት ሥራ ምህበራት

የስፖርታዊ እንቅስቃሴና የትጥቅ ድጋፍ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ ለሚገኙ ወጣቶች ተደረገ ። በኢፌዴሪ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር በዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌና በፊት ኮርነር
+9
የስፖርታዊ እንቅስቃሴና የትጥቅ ድጋፍ በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ ለሚገኙ ወጣቶች ተደረገ ። በኢፌዴሪ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር በዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌና በፊት ኮርነር ኮንሰልታንሲ የተመራው ልዑክ በሣውላ ከተማ ያለውን የ "ኑኒ እስ አይ ናይታ" የወጣቶች ስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራን ጎብኝተዋል:: ኑኒ እስ አይ ናይታ በሚል ስያሜ የሚታወቁት በሣውላ ከተማ በሰውነት ቅርፅ ስፖርት የሚታወቁት እና የጎፋን አከባቢ በማህበራዊ ሚዲያ በማስተዋወቅ ላይ የሚገኙ ወጣቶችን ልዑካኑ ምልከታ አድርገዋል። በጉብኝቱ ወቅት በኢፌዴሪ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌ እንደተናገሩት ስፖርት የአንድን አከባቢ መልካም ገፅታን ከመገንባት አኳያ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል። አክለውም ወጣቶች ከሚሰሩት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ባሻገር፤ በመልካም ስብዕና ታንፀው በማህበራዊ ሚዲያ አካባቢያቸውን ለማስተዋወቅ የጀመሩት መልካም ተግባር ከፍተኛ እንደሆነም አብራርተዋል። በዕለቱም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አሰልጣኝና ታዋቂው ኢንስትራክተር ነፃነት ካሳ ለኑኒ እስ አይ ናይታ ወጣቶች የትጥቅ ድጋፍ አድርገዋል። ወጣቶችም በቦታው በመገኘት ስለተደረገላቸው ድጋፍና ጉብኝት በማመስገን ፍቅራቸውን ገልፀዋል ። በስተመጨረሻም በቦታው የተገኙት አጠቃላይ አመራሮች እና ወጣቶች የማስ ስፖርት በመስራት ወጣቶችን አበረታተዋል።

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለመከላከል የሚያስችል የማህበረሰብ አቀፍ ስፖርት በአድዋ ድል መታሰቢያ ፊት ለፊት ተጀመረ። የካቲት 29/2018 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ *** በዛሬ
+7
ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን በአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለመከላከል የሚያስችል የማህበረሰብ አቀፍ ስፖርት በአድዋ ድል መታሰቢያ ፊት ለፊት ተጀመረ። የካቲት 29/2018 ዓ.ም፤ አዲስ አበባ፤ *** በዛሬው ዕለት ከማለዳ ጀምሮ የጤና ሚኒስቴር ሰራተኞችና የስራ ሃላፊዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንዲሁምእንግዶች፣ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት ደማቅ የማህበረሰብ ዓቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተከናውኗል። ይህ የማህበረሰብ አቀፍ እንቅስቃሴ ''ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን በአካል ብቃት እንቅስቃሴ እንከላከል'' በሚል መሪ ቃል በጤና ሚኒስቴር፣ የአ/አ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮና በፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ በትብብር የተዘጋጀ ሲሆን በተከታታይ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የሚከናዎን መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። በተጨማሪም የተለያዩ አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶችና አምራች ድርጅቶች የተሳተፋበት የጤናና የስፖርት አውደርዕይ የተከፈተ ሲሆን የደም ግፊት፣ የስኳርና የአይን ምርመራ በነፃ ለማህበረሰቡ እየተሰ ይገኛል። ይህ የጤና እና ስፖርት አውደ ርዕይ አሁንም በድምቀት የቀጠለ ሲሆን እስከምሽቱ ድረስ እንደሚቀጥል በአስተባባሪዎቹ ተገልጿል። ===//=== #የጤና_ሚኒስቴር #የአዲስ_አበባ_ወጣቶችና_ስፖርት_ቢሮ #ፊት_ኮርነር_ስፖርት_አማካሪ

ታላቅ የኢፍጣር ዝግጅት በአድዋ ጂም ተካሄደ፤ የካቲት 28/2018 ዓ.ም፤ 🧎‍♂️🧎🧎‍♂️🧎 አድዋ ጂም አባላትና ለወዳጅ ዘመድ የእስልምና እምነት ተከታዮች በትናንትናው ዕለት ከምሽቱ 1:00 ሰ
+8
ታላቅ የኢፍጣር ዝግጅት በአድዋ ጂም ተካሄደ፤ የካቲት 28/2018 ዓ.ም፤ 🧎‍♂️🧎🧎‍♂️🧎 አድዋ ጂም አባላትና ለወዳጅ ዘመድ የእስልምና እምነት ተከታዮች በትናንትናው ዕለት ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ የኢፍጣር ዝግጅት በድምቀት ተከናውኗል። የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ መስራችና ባለቤት፣ ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተከናወነው የኢፍጣር መርሃ ግብር አንድነትን፣ መተሳሰብንና በሕብር አብሮ የመኖር ማሳያ መሆኑ ተገልጿል። **//*

የጎፈሬ-ፊት የጉብኝት ጉዞ (Gofere_Fit Tour) ዛሬ በይፋ በአድዋ ድል መታሰቢያ ይጀምራል። የካቲት 21/2018 ዓ.ም 🎽 🩳 ዛሬ ተሳታፊዎች በስጦታ የሚንበሻበሹበት ቀን ነው! እርስዎም ተ
የጎፈሬ-ፊት የጉብኝት ጉዞ (Gofere_Fit Tour) ዛሬ በይፋ በአድዋ ድል መታሰቢያ ይጀምራል። የካቲት 21/2018 ዓ.ም 🎽 🩳 ዛሬ ተሳታፊዎች በስጦታ የሚንበሻበሹበት ቀን ነው! እርስዎም ተጋብዘዋል! ፊት ኮርነር ስፖርት፣ ጎፈሬና የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት የተፈራረሙት የሦስትዮሽ መግባቢያ ሰነድ ተከትሎ የስፖርታዊ ጉዞው ዛሬ በአራዳ ክፍለ ከተማ፥ በአድዋ ድል መታሰቢያ ፊት ለፊት ከቀኑ 11:00 ጀምሮ ይከናወናል። ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣን ጨምሮ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው አሰልጣኞች፣ የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ተወካዮችና በርካታ ታዋቂ ሰዎች ይገኙበታል። ጎፈሬ ጥራት ያላቸውን አዘጋጅቷል። ጤናዎን እየጠበቁ ስጦታ የሚያገኙበት መድረክ ተመቻችቷል። ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ የአካላዊ፣ ማሕበራዊና አዕምሯዊ ጤናዎት የሚጠብቁበት መድረክ ተመቻችቷል። ቦታ:- ፒያሳ፥ አድዋ ድል መታሰቢያ ፊት ለፊት

በድጋሚ!! የጎፈሬ-ፊት የስፖርታዊ ጉዞ (Gofere_Fit Tour) በአድዋ ድል መታሰቢያ ረቡዕ፥ የካቲት 25/2018 ዓ.ም 🎽 🩳 ነገም ተሳታፊዎች በስጦታ የሚንበሻበሹበት ቀን ነው! እርስዎም ተ
+4
በድጋሚ!! የጎፈሬ-ፊት የስፖርታዊ ጉዞ (Gofere_Fit Tour) በአድዋ ድል መታሰቢያ ረቡዕ፥ የካቲት 25/2018 ዓ.ም 🎽 🩳 ነገም ተሳታፊዎች በስጦታ የሚንበሻበሹበት ቀን ነው! እርስዎም ተጋብዘዋል! ፊት ኮርነር ስፖርት፣ ጎፈሬና የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት የተፈራረሙት የሦስትዮሽ መግባቢያ ሰነድ ተከትሎ የስፖርታዊ ጉዞው ቀጥሎ፥ በአድዋ ድል መታሰቢያ ፊት ለፊት ከቀኑ 11:00 ጀምሮ ይከናወናል። ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣን ጨምሮ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው አሰልጣኞች፣ የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ተወካዮችና በርካታ ታዋቂ ሰዎች ይገኙበታል። ጎፈሬ ጥራት ያላቸውን የስፖርት ትጥቆች ዛሬም አዘጋጅቷል። ጤናዎን እየጠበቁ ስጦታ የሚያገኙበት መድረክ ተመቻችቷል። ነገ ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ የአካላዊ፣ ማሕበራዊና አዕምሯዊ ጤናዎት የሚጠብቁበት መድረክ ተመቻችቷል። ቦታ:- ፒያሳ፥ አድዋ ድል መታሰቢያ ፊት ለፊት **** #ፊት_ኮርነር_ስፖርት_አማካሪ #የአዲስ_አበባ_ወጣቶችና_ስፖርት_ቢሮ #ጎፈሬ

🌙✨ ልዩ የረመዳን ኢፍጣር ምሽት ✨🌙 ለክቡራንና ክቡራት ደንበኞቻችን የተባረከውን የረመዳን ወር በአክብሮትና በአንድነት ለማክበር፣ በሚመጣው 📅 ቅዳሜ 28/06/2018 ዓ.ም ⏰ ከምሽቱ 1፡00
🌙✨ ልዩ የረመዳን ኢፍጣር ምሽት ✨🌙 ለክቡራንና ክቡራት ደንበኞቻችን የተባረከውን የረመዳን ወር በአክብሮትና በአንድነት ለማክበር፣ በሚመጣው 📅 ቅዳሜ 28/06/2018 ዓ.ምከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ 📍 በጂማችን የተለየ እና የማይረሳ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅተናል። በዚህ ውብ ምሽት ታላላቅ እንግዶች፣ ሚኒስትሮች፣ ታዋቂ የከተማችን ሰዎች፣ እና የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ተገኝተው ምሽቱን ያደምቃሉ። እርስዎም ከነቤተሰቦት በክብር ተጋብዘዋል።

የጎፈሬ-ፊት የጉብኝት ጉዞ (Gofere_Fit Tour) ዛሬ በይፋ በአድዋ ድል መታሰቢያ ይጀምራል። የካቲት 21/2018 ዓ.ም 🎽 🩳 ዛሬ ተሳታፊዎች በስጦታ የሚንበሻበሹበት ቀን ነው! እርስዎም ተ
+7
የጎፈሬ-ፊት የጉብኝት ጉዞ (Gofere_Fit Tour) ዛሬ በይፋ በአድዋ ድል መታሰቢያ ይጀምራል። የካቲት 21/2018 ዓ.ም 🎽 🩳 ዛሬ ተሳታፊዎች በስጦታ የሚንበሻበሹበት ቀን ነው! እርስዎም ተጋብዘዋል! ፊት ኮርነር ስፖርት፣ ጎፈሬና የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት የተፈራረሙት የሦስትዮሽ መግባቢያ ሰነድ ተከትሎ የስፖርታዊ ጉዞው ዛሬ በአራዳ ክፍለ ከተማ፥ በአድዋ ድል መታሰቢያ ፊት ለፊት ከቀኑ 11:00 ጀምሮ ይከናወናል። ኢንስትራክተር ነፃነት ካሣን ጨምሮ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው አሰልጣኞች፣ የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ተወካዮችና በርካታ ታዋቂ ሰዎች ይገኙበታል። ጎፈሬ ጥራት ያላቸውን አዘጋጅቷል። ጤናዎን እየጠበቁ ስጦታ የሚያገኙበት መድረክ ተመቻችቷል። ከቀኑ 11:00 ሰዓት ጀምሮ የአካላዊ፣ ማሕበራዊና አዕምሯዊ ጤናዎት የሚጠብቁበት መድረክ ተመቻችቷል። ቦታ:- ፒያሳ፥ አድዋ ድል መታሰቢያ ፊት ለፊት **** #ፊት_ኮርነር_ስፖርት_አማካሪ #የአዲስ_አበባ_ወጣቶችና_ስፖርት_ቢሮ #ጎፈሬ

ስለ ጤናዎ ሲባል... የሰው ልጅ በሕይወት ዘመኑ በአማካይ 104,600 ኪ.ሜ ያህል በእግሩ ይጓዛል፡፡ እርምጃ በሰዓት ከ200 – 300 ኪሎ ካሎሪ ለማቃጠል ይረዳል፡፡ በየቀኑ ከምናደርገው ጉዞ ላይ
+9
ስለ ጤናዎ ሲባል... የሰው ልጅ በሕይወት ዘመኑ በአማካይ 104,600 ኪ.ሜ ያህል በእግሩ ይጓዛል፡፡ እርምጃ በሰዓት ከ200 – 300 ኪሎ ካሎሪ ለማቃጠል ይረዳል፡፡ በየቀኑ ከምናደርገው ጉዞ ላይ 5 ደቂቃውን ፈጠን ያለ እርምጃ እንዲሆን ብናደርገው ገዳይ ለሆኑ በሽታዎች የመጋለጥ እድልን በ10% መቀነስ ይቻላል፡፡ በተጨማሪም በቀን 7,000 እርምጃዎችን መጓዝ ወይም ከ60 – 75 ደቂቃዎች የእግር ጉዞ ማድረግ የሚከተሉትን የጤና ጠቀሜታዎች ያስገኛል፦ • ገዳይ የሆኑ በሽታዎችን በ 47% ይቀንሳል • የመርሳት በሽታ (Dementia) በ38% ይቀንሳል • በካንሰር የመያዝ እድል በ37% ይቀንሳል • የልብና ተያያዥ በሽታዎች በ25% ይቀንሳል • የስኳር በሽታ (Type 2) በ14% ይቀንሳል፡፡ አሁን በከተሞች ውስጥ በወንዞች ዳርቻ ልማትና በኮሪደር ልማት ምቹ የሆኑ የእግረኛ መንገዶች በከፍተኛ ጥራት መገንባታቸው ለሁሉም የሕብረተሰብ ክፍል መልካም አጋጣሚ ነው፡፡ ፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪም ይህንን መልካም አጋጣሚ ሕብረተሰቡ እንዲጠቀምበትና ጤናውን እንዲጠበቅ ሙያዊ ምክሩን ይለግሳል፡፡ በቀን 7,000 እርምጃ ወይም ከ60 – 75 ደቂቃ በእግር መጓዝ የእለት ግብ በማድረግ ጤናችን እንጠብቅ፡፡ በኮሪደር ልማትና በወንዞች ዳርቻ ልማት አካባቢ በሚገኙ የእግረኛ መንገዶች ላይ የፊት ኮርነር ስፖርት አማካሪ ከተለያዩ የመንግስት ኃላፊዎች፣ አምባሳደሮችና እንግዶች ጋር የእግር ጉዞዎችን በማድረግ አርዓያነታቸውን አሳይተዋል፡፡ ====//== 👇ከታች ያሉትን ማስፈንጠሪያዎች በመጫን ከእኛ ጋር ወዳጅ ይሁኑ። Tik Tok: https://www.tiktok.com/@netsisport?_t=8oMpNHC40DW&_r=1 YouTube: https://youtube.com/@netsisport?si=GY0w80TrUxw12rjU