es
Feedback
NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

Canal cerrado

NISIR International Broadcasting Co. is an impartial and independent media agency operates as social media & multimedia production. Voice of voices ንሥር ኢንተርናሽናል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የማያዳላ እና ገለልተኛ የመገናኛ ተቋም ነዉ። ማህበራዊ ሚዲያ እና መልታይሚዲያ እምራች ሁኖ ይሰራል። አማራ ድምፅ!

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel)

El canal NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 28 384 suscriptores, ocupando la posición 8 809 en la categoría Noticias y medios y el puesto 1 162 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 28 384 suscriptores.

Según los últimos datos del 10 marzo, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -552, y en las últimas 24 horas de 0, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 0%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener N/A% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 0 visualizaciones. En el primer día suele acumular 0 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
NISIR International Broadcasting Co. is an impartial and independent media agency operates as social media & multimedia production. Voice of voices ንሥር ኢንተርናሽናል ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የማያዳላ እና ገለልተኛ የመገናኛ ተቋም ነዉ። ማህበራዊ ሚዲያ እና መልታይሚዲያ እምራች ሁኖ ይሰራል። አማራ ድምፅ...

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 11 marzo, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.

28 384
Suscriptores
Sin datos24 horas
-1017 días
-55230 días
Archivo de publicaciones
እነኳን ለ2018 ዓ.ም አደረሳችሁ! ************** *የአማራ ህዝብ ዋስትና ለሆንከው ለመላው የአማራ ፋኖ! *በየ እስር ቤቱ ታጉራችሁ በስቃይ ለምትገኙ የአማራ ልጆች! *ለአማራ ፋኖ ወላጆችና
እነኳን ለ2018 ዓ.ም አደረሳችሁ! ************** *የአማራ ህዝብ ዋስትና ለሆንከው ለመላው የአማራ ፋኖ! *በየ እስር ቤቱ ታጉራችሁ በስቃይ ለምትገኙ የአማራ ልጆች! *ለአማራ ፋኖ ወላጆችና የታጋይ ቤተሰቦች! *ለመላው የአማራ ትግል ደጋፊወችና ኢትዮጵያውያን በሙሉ! እንኳን ለ2018 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ! አዲሱ አመት የአማራ ህዝብ ትግል በድል የሚጠናቀቅበት እንዲሆን እንመኛለን። እንደሚታወቀው የአማራ ህዝብ ለአመታት በጦርነት ቀንበር ውስጥ ሆኖ ኑሮውን እየገፋ ይገኛል። ንሥር ብሮድካስት ኮርፖሬሽንም በአማራ ህዝብ ላይ የተፈፀመውን እና እየተፈፀ ያለውን ጥቃት አስመልክቶ አማራው እራሱን እንዲያነቃና እራሱን ከጥቃት መከላከል እንዲችል ከ2013 ዓ. ም ጀምሮ ላለፍት አመታት እለታዊ መረጃወችን በየቀኑ በማቅረብ አስተዋጽኦ ሲያደርግ ቆይቷል። ይህን አረመኔና አገር አጥፊ ስርዓት በማጋለጥና ወገናችን ላይ የሚፈፀመውን ጥቃት ለማስቆም በሚደረገው እርብርብ ንሥር ብሮድካስት የራሱን ሚና ተጫውቷል። ሆኖም ከ2018 ጀምሮ የእለታዊ ዜና ስርጭት ፕሮግራማችን ስለማይኖር እሰከ አሁን ስትከተሉን የነበራችሁ ተከታዮቻችንና እንዲሁም መረጃ ስታደርሱን የነበራችሁ ምንጮቻችንን ከልብ እያመሰገን ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ሌሎች ተመሳሳይ የትግል ሚዲያወችን እንድትጠቀሙና እንድትከተሉ በአክብሮት እናሳስባለን። ለወደፊትም ከድል በሗላ በሌሎች የአማራ ትግል ታሪክ ዶክመንታሪወች እና ለነፃነት የተዋደቁ ወገኖቻችን በሚዘክሩ ፕሮግራሞች ተመልሰን እንደምንገናኝ ለማስታወስ እንወዳለን። በመጨረሻም የተጀመረው የህልውና ትግል ከግብ እንዲደርስ እና በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ ሁሉም አማራ እና የአማራ ትግል ደጋፊ በጋራ እንዲቆም፣ በአንድነትና በህብረት እንዲታገል እናሳስባለን። ድል ለጀግናው የአማራ ፋኖ! ድል ለአማራ ህዝብ! መልካም አዲስ ዓመት! ንሥር ብሮድካስት ኮርፖሬሽን ዕረቡ ዻጉሜ 5/2017 ዓ.ም

1/ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኀ) ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዘለቀ ዕዝ ዳ/ቴዎድሮስ ፭ኛ ኮር ታድሎ ብርሃን ክ/ጦር ጅባስራ ብርጌድ እና ከጎንደሬ በጋሻው ፋሲለደስ ብርጌድ  ጳጉሜ 1/2017 ዓ.ም ጎንደር ዙሪያ ወረዳ ከባህሪ ግንብ እስከ ብርቧክስ እና አርሴማ ድረስ የሸፈነ ከጠላት ጋር ውጊያ በማድረግ በጠላት ላይ ሰብዓዊና ቁሳዊ ጉዳት አድርሰውበታል።    ከ10 በላይ ሙትና ቁስለኛ የሆነው የብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ሸሽቶ ወደ ጎንደር ከተማ ገብቷል።     2/ በስርዓት አልበኞች ላይ ርምጃ መሰድ ተጀመረ! ከጎንደር ደባርቅ ዋና አውራ ጎዳና አሽከርካሪዎችንና መንገደኞችን በመዝረፍ የውንብድና ተግባር ተሰማርተው በነበሩ ወሮበሎች ላይ ዛሬ ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም ጠዋት ጀምሮ ርምጃ መውሰድ ተጀምሯል። በተለይም ከአምባጊዮርጊስ ደባርቅ መስመሮች ላይ ሲዘርፉ፣ሲያግቱ እና የውንብድና እኩይ ድርጊት ለመፈፀም ተሰማርተው በነበሩ ስርዓት አልበኞች ላይ እየተወሰደ በሚገኘው የተጠና ኦፕሬሽን መስመሩን ለጊዜው ከወሮበሎች ማፅዳት የተቻለ ሲሆን በዘላቂነት ችግሩን ለመቅረፍ ጠላት በሰፈረባቸው አካባቢዎች ድረስ ዘልቆ ማፅዳት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበታል።     ተበትነው የተሰወሩ ወንበዴዎች እጅ እየሰጡ ሲሆን ህዝቡ እየተወሰደ ለሚገኘው ስርዓት የማስያዝ ርምጃ እየተሳተፈ ይገኛል።       3/ የአደረጃጀት መረጃ የ ዘራይ አዝመራው ክፍለ ጦር አዲስ ዓመትን”ውስጣዊ ችግር በመፍታት ሃይል እንገንባ!መሪ እንፍጠር” በሚል መሪቃል ለሁለት ዓመታት  በአርበኛ ኢንጅነር በየነ አለማው እና አርበኛ አስምሮ ፍቃዴ ሲመራ የቆየው ዘራይ ክፍለ ጦር ሙሉ ሪፎርም አድርጓል። አውናዊ የክፍለ ጦሩ ቁመና መደበኛ የብርጌድ ስታዳርድ ባሞሉ አምስት ብርጌዶች የተዋቀረ ነው። እነዚሁ ብርጌዶች፦ 1. ቆራጡ ገብሬ አቡሃይ ፩ኛ ብርጌድ 2. ሸጋው ውበት ፪ኛ ብርጌድ 3. ሃይሌ ማሞ ፫ኛ ብርጌድ 4. ንግስቷ ሰላም ጥላሁን ፬ኛ ብርጌድ 5. ሞላ ደጀን ማይካድራ ብርጌድ ሲሆኑ የዘራይ ክፍለ ጦር እንደሚከተለው ሁኖ ተዋቅሯል። 1. የዘራይ ክፍለ ጦር ሰብሳቢ-አርበኛ እሱባለው ይርጋ 2. ወታደራዊ አዛዥ-አርበኛ ፻ዓለቃ የሽበር አስማማው 3. ም/ል ወታደራዊ አዛዥ-አርበኛ አምሳሉ ዘሪሁን 4. ዘመቻ-አርበኛ ሙሉቀን ያለው 5. ም/ል ዘመቻ-አርበኛ አማኑኤል አጥናፉ 6. አስተዳደር-አርበኛ ፶ዓለቃ ትግስት ተረፈ 7. ሎጅስቲክ አስተዳደር-አርበኛ ጋሻው መሰለ 8. ልዩ ተልዕኮ-አርበኛ ገብሬ ሸቴ 9. ስለጠና-አርበኛ አሜሪካው አለባ 10. ኦርዲናስ-አርበኛ ይበልጣል ጌታቸው 11. ገንዘብ አስተዳደር-አርበኛ ጌታቸው ዘሪሁን 12. ፖለቲከ ዘርፍ-አርበኛ ላቀው ፈረደ 13. ህዝብ ግንኙነት-አርበኛ ፍቅሩ የማታው 14. መረጃ እና ደህንነት———- 15. ህዝባዊ አስተዳደር-አርበኛ ቃቀይ ጌትነት 16. ህግ እና ስነ-ምግባር-መምህር አስቻለው አግንቸ      በመሆን ዘራይ ክ/ጦር አመራር አዋቅሯል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !! አፋብኃ ምዕ/አማራ ቀጠና ቴወድሮስ እዝ ቃል አቀባይ ማርሸት ፀሃው ጳግሜ 4/2017/

የአፋብኅ ምዕራብ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ  ፫ኛ ጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር ፲/አ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ እና ቢትወደድ መንገሻ ጀምበሬ ብርጌድ ድማማ ማንጉዳ ላይ ተከማችቶ ከነበረዉ የአድማ ብተና ሚሊሻ እና የፖሊስ ታጣቂ ላይ በወሰደዱት በለሊት ጠላትን የማፅዳት ኦፕሬሽን ተሻለ ዳኘዉ የተባለን ከሀዲ ጨምሮ                                                             9 የሚሆነዉን በመደምሰስ ከ12 በላዩን ቁስለኛ አድርገዉ 3 ክላሽንኮቭ                                                          1 ሲሶ ክላሽ                                                           370 የክላሽ ተተኳሽ ተረክበዋል።   በተደጋጋሚ  በደረሰበት ምት የአረመኔው ሰራዊት ለፋኖ  እጅ እየሰጠ  ይገኛል ። ቢቸና ከተማ መሽጎ የሚገኘው የሚሊሻ ካንፕ በመክዳት ፋኖን ከተቀላቀሉት መካከል 1ኛ.ተሾመ ክብሬ አድራሻ ሸበል በረንታ ሌዲ ቀበሌ 2ኛ. ውድ አቡ ሸበል በረንታ ወቦ ወሬ ቀበሌ ተወላጅ የነበሩ  8ኛ በላይ ዘለቀ ክ/ጦር ሽፈራው ገርባው ብርጌድ ተቀላቅለዋል። በተመሳሳይ ቀረብህ ሲሳይ የተባለው ሚሊሻ ለቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ከፍለ ጦር ኢንጅነር ክበር ተመስገን ብርጌድ እጁን በሰላም ሰጥቷል። ሌሎቻችሁም የምሕረት ጥሪያችንን በመቀበል ራሳችሁን ከከንቱ መስዋዕትነት አድኑ ስንል  መልዕክታችን  ኦናስተላልፋለን። ከሕዝባችን ጋር የምናደርገው ውይይት በተጠናከረ መንገድ ቀጥሏል። የአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር የስናን አባጅሜ ብርጌድ ከሸዋ ኪዳነ ምሕረት ቀበሌ ማሕበረሰብ ጋር ሰፋ ያለ ውይይት አድርገዋል። በውይይቱ የአማራ ትግል የደረሰበት የልዕልና ጥግ ለማሕበረሰቡ የተገለጸ ሲሆን በመልካም አስተዳደርና በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፋ ያለ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምሕርት ተሰጥቷል። ሕዝባችን የምንሞትለት የምንሰዋለት፣ ዝቅ ብለን የምናገለግለው በቀደመ የአርበኝነት ታሪኩ አንጸባራቂ ድል ሰርቶበት ለታሪክ ምስክር ያስቀመጠውን አልቬን፣ቤልጅግ፣ ምንሽር...መሳሪያውን አስታጥቆ በደሙ ላወረሰን ታሪኩ ፣ማንነቱ፣ ዕምነቱና ሕልውናው እንድንዋደቅ እስከ ደም ጠብታና እስከ ሕይወት መስዋዕትነት እንድንታገል ለዛና በረከት ባለው አንደበቱ ባርኮና መርቆ የሸኘን ነው። ሕዝባችን ጥላችን ሁሉ ነገራችን ነው። ሕዝባችን ቀይ መስመራችን ነው። አዲስ ትውልድ ፣  አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ! አፋብኃ| ቴዎድሮስ ዕዝ       ጳጒሜ 03/2017ዓ.ም

በአዲሱ ዓመት አማራነትን ፀረ-አማራነት ከማይደርስበት ሰገነት እናስቀምጠዋለን ! ምላጭ የመዋጥ ያክል ከብዶ የነበረው አማራዊ አንድነት በአንድ ማንኪያ ቅንነት ጥሩ የአዲስ አመት ዋዜማ ላይ እንድንገኝ አድርጎናል ። ይሔ አማራዊ አንድነት በፍጥነት እየተጎዘ በሚሄድበት ወቅት ከሚፈለገው ቦታ ለመድረስ በአንድነት ጉዞ ውስጥ የሚገኙ መንገደኞች የኋላ እና የፊት መስታውት በመመልከት ፣ አቅጣጫ በመጠቆም ፣ መስታውት በመወልወል ወይም ፀሎት በማድረግ ማገዝ አማራዊ ግዴታው ነው ። ነገር ግን የባሱን መሪ ፣ ፍሬን እና ነዳጅ መቆጣጠሪያውን ለሹፌሩ መተው ደግሞ ጉዞውን ሙሉ ጤነኛ እንዲሆን ያደርጋዋል ። በዚህ ጉዞ ላይ ለተሳፋሪዎችም ሆነ ለሹፌሩ ሳይናገር ለመውረድ የሚሞክር ካለ ግን ፈጣሪ ፣ ህዝብ ፣ጊዜ እና ታሪክ የትውልዱ መሣቂያ እና መሣለቂያ ያደርጉታል ። የአማራነት ሰይፍም ይበላዋል ። የድንጋይ ዘመን አስተሳሰብ ባለቤቶች አማራነትን በብዙ ሰው ሰራሽ እና ስርዓት መር ችግሮች ከቀበሩበት የብረት በርሚል ውስጥ አዲሱ ትውልድ ከቀበሩበት አውጥቶ ለዓለም ህዝብ እያሣየው ይገኛል ። ከዚህ ስንደርስ ግን እልፍ አይተኬ የጀግኖች ህይወትን ገብረንበት፣ እልፎች አካለ ጎደሎ ሁነውበት፣ እልፎች ወሕኒ ቤት ታጉረውበት፣ እልፎች ሀብት ንብረታቸውን አጠው በስደት አገር ሰሪ አገር አልባ ሁነውበታል ። በነዚህ አስቸጋሪ የአማራው ዓመታቶች ፈጣሪ ፣ ታሪክ ፣ ጊዜ እና ህዝብ በደንብ እየታዘቡን ወየም እየመዘኑን ይገኛሉ ። ከአራቱ ሚዛኖች በአንዱ ተመዝኖ የወደቀ ሰው ደግሞ በፍፁም ዋጋ የማያወጣበት ወድቆ የማይነሳበት ደረጃ ላይ ይደርሳል ። ምንም አይነት ሰዋዊ ልዩነቶች ቢኖሩብንም እንኳን እንደ ህዝብ ላለመጥፋት ቤት ንብረታችን ጥለን የወጣን የአማራ ልጆች አንድ ለመሆን የሚያስቸግረን ጉዳይ ይኖራል ተብሎ አይገመትም ። ወቅቱ ምንም በዓይንህ ማየት ማትፈልገው ሰው እንኳን ቢሆን ለህዝባችን አንድነት ሲባል ቀድመህ ይቅርታ ጠይቀህ ወደ ስራ ምትገባበት ጊዜ ነው ። በነፃ ለነፃነት የሚታገል ታጋይ እና አታጋይ ትልቁ ደሞዙ ' ነፃነት ' ነው ። ነፃነት ደግሞ በነፃ አይገኝም ። ነፃነት ጨርሶ የሚያጠፋ ወይም የሚያም 'ዱላ' አለው ። ዱላው የወንድም ከሆነ ደግሞ ቢያምም ያድናል ። አማራነት ወደ ባለቤቱ የአማራ ህዝብ እንዲመለስ ደግሞ አዲሱ ትውልድ አንድ አማራ እና አንድ የጥይት ፍሬ እስክትቀረው ድረስ ታግሎ ያስከብረዋል ። አማራነትን ፀረ አማራነት ከማይደርስበት ሰገነት ከፍ አድርጎ ያስቀምጠዋል ። አማራነትን ባለቤቱ ብቻ ሊያውቀው በሚችለው መፍቻ ተቆልፎ ይቀመጣል ። ምክንያቱም አማራነት የባለቤቱ ውድ ንብረት ስለሆነ እና በአደራ ለሌሎች የማይሰጥ ማንነት ስለሆነ ። ፈጣሪ ሁሌም ጥሩ ዘመኖችን ሲሰጠን ቆይቷል ። እነዚያን ዘመናቶች ጥሩ ወይም መጥፎ ምናደርጋቸው እኛው የእርሱ ፍጥረቶች ነን ። አሁን ግን ፈጣሪ ጥሩ ዘመን ብቻ አይደለም የሠጠን ጥሩ መሪ እና መልካም አጋጣሚዎችን ፈጥሮልናል ። የተሠጡንን መልካም አጋጣሚዎች ለአማራው እና ለፍትሕ ወዳድ ሀገሬው የሚበጅ አድርጎ መጠቀም ወይም መስራት ደግሞ የዚህ ትውልድ ለነገ የማይባል አሁናዊ ስራው ተደርጎ መታወጅ አለበት ። ይሔን ጊዜ እና መልካም አጋጣሚ በአግባቡ ሳንጠቀም ከቀረነ እና እንደ ህዝብ ካልጠፋነ ሌላ 500 ዓመት ከመከራ እና ጭቆና ጋር ለመጠበቅ እንገደዳለን ። እኛ ደግሞ ይህ እንዲሆን የማንፈልግ ትውልዶች ነን ። በጳጉሜ ውሐ መንፃት ለሠውነታችን እና ለልብሶቻችን ብቻ ሳይሆን ለአስተሳሰባችንም ስለሚጠቅም በደንብ እንጠቀምበት ። ' እጅ ከለቀቀ ብልሐት አለቀ ' የሚለው የሕፃናት የብይ ጨዋታ ህግ ለአሁኑ ጊዜ የፖለቲካ አሰላለፍም ይሰራል ። እጃችን ላይ ያለውን መልካም አጋጣሚ ሁሉ በማስተዋል መጠቀም ለነገ ቤታችን ማማር ትልቅ ጉልበት ስለሚኖረው ለመጠቀም ግዴለሽ መሆን አያስፈልግም ። ሰገነቱ ላይ እንገናኝ ! መልካም ዓዲስ ዓመት ! አዲስ ትውልድ ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣ አዲስ ተስፋ ! አርበኛ ግሩም ምሳሌ

‎መልካም ዜና! ‎የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የኮር ምስረታ አካሄደ ‎ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ አምስት ክ/ጦሮችን ወደ አንድ በማሰባሰብ ግዙፉን የፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር አንድ መስርቷል:: ‎ ‎ይህንን ኮር አፄይኩኖ አምላክ፥ ሰባት ለሰባ፥ ነጎድጓድ፥ ናደው እና በፍቃዱ በላይ ክ/ጦሮች በአንድ ላይ ሁነው ነው የመሰረቱት :: ‎ ‎ይህ የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር ምስረታ ሥነ ስርዓት የአሳምነው እዝ አመራሮች፥ የየክ/ጦር መሪዎች፥ የፋኖ አባላት፥ አባት አርበኞች፥ የሀይማኖት አባቶች፥ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በኤፍራታና ግድም ወረዳ በደራሲና አርበኛ አሰገድ መኮነን መቀመጫ ማጀቴ ተካሄዷል:: ‎ ‎በዚህ የኮር ምስረታ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው እዝ አፄ ይኩኖ አምላክ፥ ሰባት ለሰባ ፥ነጎድጓድ ፥ ናደው እና በፍቃዱ በላይ ክ/ጦር የፋኖ አባላት በወታደራዊ ሰልፍ ተመው በመምጣት ተሳታፊ ሁነዋል:: ‎ ‎የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር ምስረታ ፕሮግራም ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአፋብኃ ሴንትራል ኮማንድ አባል እና ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ዋና መሪ አርበኛ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ እስካሁን የገጠሙንን በርካታ ተግዳሮቶች በፋኖ አርበኞቻችን እና በማህበረሰባችን ጥንካሬ ተወጥተን የጋራ መሰባሰቢያ ቤታችንን ከሸንኮራ እስከ ቋራ ተጉዘን ገንብተን በመጣን ማግስት ታላቁን የፄ ዘርያይቆብ ኮር መመስረት መቻላችን ጥንካሬያችን የታየበት በመሆኑ ሁላችንም ደስ ሊለን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል:: ‎ ‎በኮር ምስረታው የተገኙት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ሴንትራል ኮማንድ አባል እና የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ዋና ወታደራዊ አዛዥ ፊት አውራሪ ድርሳን ብረሀኔ ከአሳምነው ዕዝ ጋር በጋራ በመስራት የጥላትን ቅስም የምንሰብርበት ወቅት ሩቅ አይደለም ብለዋል:: ‎ ‎ይህንን የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ አንደኛ ኮር ምስረታ በተመለከተ የስም ስያሜ በአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የድርጅት ጉዳዮች ኃላፊ አርበኛ አሸናፊ ምንዳ በኩል ማብራሪያ ተሰጥቶ የዕዙ የድርጅት ጉዳዮች  የቀጣይ እቅድ የሚያመላክቱ መልእክቶች ተላልፈዋል:: ‎ ‎በዚህ የኮር ምስረታ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ወታደራዊ ዋና አዛዥ ፊት አውራሪ ባዩ አለባቸው የፋኖ ኃይል ሊከተላቸው የሚገቡ የቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችና ወታደራዊ መመሪያ ምን መምሰል እንዳለባቸው መልእክት አስተላልፈዋል:: ‎ ‎የኮር ምስረታ ፕሮግራሙም በተለያዩ መጣጥፎች፥ ግጥሞች፥ ሽለላና ቀረርቶ በድምቀት ከተካሄደ በኋላ  የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል እንዲመሰረት ከሸንኮራ እስከ ቋራ ተራራ ሸንተረሩ ቁርና ብርዱ እንዲሁም የጠላት ሀይል ሳይበግራቸው አንድ የአማራ ቤት ሰርተው ለተመለሱት የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች የቃል ኪዳን ምልክት የሆነችውን የአባቶቻችን የቃል ኪዳን አርማ የሆነችውን ሰንደቅ ዓላማ በማበርከት ለቀጣይ መሪነት ዝግጁ እንዲሆኑ ተደርጓል:: ‎ ‎በመጨረሻም የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ም/ል መሪ በአርበኛ ኢሳያስ ደመቀ የአፄ ዘርአያዕቆብ ኮር አንድ መሪ ሁነው የተመደቡ የፋኖ አመራሮች ቃለመሀላ እንዲፈጽሙ ተደርጎ የተመደቡ አመራሮች የአማራ ህዝብ የጣለባቸውን አደራ በብቃት እንዲወጡ ጭምር መልእክት በማስተላለፍ እና ከብልጽግና ጋር ወግነው ለሚሰሩ አመራሮች፥ የአድማ ብተና ፥የሚኒሻ ፥ እና የመከላከያ አባላት የፋኖን ትግል እንዲደግፉ ጥሪ በማስተላለፍ ፕሮግራሙ ተጠናቋል:: ‎የኮሩን አመራሮች ዝርዝር ሙሉ መረጃ እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።    "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን" አፋብኃ ደቡብ  አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝየህዝብ ግንኙነት ዜና ክፍል        ጳጉሜ 03/2017 ዓ.ም

የአረመኔ ስርዓት ጦር እየፈረሰ ነው አፋብኃ የምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 5ኛ ክፍለ ጦር ወርቅ አባይ ብርጌድን የአረመኔው ስርዓት ወንበር ጠባቂ የነበሩ የመከላከያ ወታደሮች ቀን በቀን እየፈረ
የአረመኔ ስርዓት ጦር እየፈረሰ ነው አፋብኃ የምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 5ኛ ክፍለ ጦር ወርቅ አባይ ብርጌድን የአረመኔው ስርዓት ወንበር ጠባቂ የነበሩ የመከላከያ ወታደሮች ቀን በቀን እየፈረሱ ወርቅ አባይን ተቀላቀሉ።ስርዓቱን ሲያገለግሉ እና ሲታገሉ የነበሩ ወታደሮች በአማራ ህዝብ ላይ የመከላከያ ሰራዊቱ  የሚፈፀመው ግፍ እና ሰቆቃ መቋቋም ስላቃተን ነው የወጣነው በማለት ሁለት የመከላከያ ወታደሮች ሁለት ጥቁር ክላሽ ይዘው ከእነ ሙሉ ትጥቃችን ፋኖን የተቀላቀልን ብለዋል። አገዛዙ በድጉ እና በሰፊው ህዝብ ላይ እየፈጸመው ያለው ጅምላ ጭፍጨፋ እና ማንነትን ተኮር ያደረግ  በመዝረፍ እና ቤታቸውን በማቃጠል ከሚኖሩበት አካባቢ መፈናቀል፣መግደል እና ሴቶችን መድፈር የተሰጠን ተልዕኮ ቢሆንም ለአማራ ህዝብ የማይገባ መሆኑን ስለተረዳን ከአገዛዙ ከድተን ፋኖን ተቀላቅለናል ሲሉ የኦሮሚያ ተወላጅ የሆኑት ወ/ር ካሱ ወልዱ እና ጋዲሳ መገርሳ ተናግረዋል። ንጹሃን አርሷደሮችን ከቤት እያወጡ እና የቀን ሰራተኞቹን በግፍ እና በሰቆቃ እረሽነዋል አስረዋል። እንዲሁም በእሁዲት ከተማ በማህበረሰቡ ላይ የፈጸሙት በድል ለአማራ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ህዝብም ጥቁር ታሪክ ሁኖ የሚቀመጥ ይሆናልም በለው አክለው ገልጸዋል።ጠላትን ስቦ በማስከዳት እና በመደምሰስ አፋብኃ የምዕራብ አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ 5ኛ ክፍለ ጦር አጠናክሮ ቀጥሎበታል። ፲/አ እ/ር ዘመኑ አማረ 5ኛ ክ/ጦር ህ/ግ መምሪያ ኃላፊ ጳግሜ 3/2017/

የፋኖ ቤተሰቦችን ያነጣጠረ ጥቃት ተፈፀመ በአፋብኃ ምዕራብ አማራ ቀጠና ቴወድሮስ ዕዝ 2ኛ /ተፈራ ዳምጤ/ ክፍለ ጦር  መዝገበ ጮቄ ብርጌድ  በደብረ ሰላም ቀበሌ ኑዋሪ በሆኑት አቶ ጌትነት እንየው ላይ ሰዴ ከተማ  ቤተ-ክርስቲያን በሄዱበት ፋኖ ልጅ አለህ በማለት በዚህ መልኩ ተደብድበው ህክምና ላይ ይገኛል ። አቶ ጌትነት እንየው የ72  ዓመት ሽማግሌ ሲሆኑ በግብርና የሚተዳደሩና  አርሶ ከማደር ውጭ ወቅታዊ  የፖለቲካ ሁኔታ እንኳን በቅጡ  ለይተው የማይረዱ በርካታ ቤተሰብ በመምራትና  ታዋቂ የሀገር  ሽማግሌ የሆኑ ምስጉን አርሶ አደር ናቸው።ነገር ግን አማራ ከመሆናቸውና በተጨማሪ  ታደለ ጌትነት የሚባል ልጃቸው  መዝገበ ጮቄ ብርጌድ ውስጥ የአማራን ህዝብ ከመጥፋት ለመታደግ እንደ ሁሉም አማራ ወጣት እየታገለ ስለሚገኝ ለመደብደባቸው ትልቁ ምክንያት መሆኑን ማረጋገጥ ችለናል ። የአቶ ጌትነት እንየው የመኖሪያ ቤት ለከተማው ቅርብ በመሆኑ የተወሰኑ የሚኒሻ አባላት ወደ ቤት በመሄድ የቦንብ ጥቃት ለማድረስ ሙከራ ቢያደርጉም የመዝገበ ጮቄ ብርጌድ ሻለቃ ሶስት መረጃ ስለደረሳት ተከታትላ ጥቃቱን በማክሸፍ ጥቃት አድራሾችን ወደ መጡበት በማባረር መልሳለች ። ከዚህ በፊት በርካታ ጊዜ የፋኖ ቤተሰቦችን ማሰር፣ ማንገላታት ፣ መግረፍ እንዲሁም ከማዳበሪያና  ምርጥ ዘር እንዲሁም ከየትኛም የማህበረሰብ አግልግሎት  ውጭ  በማድረግ እንደ አማራ ህዝብ ከሚደርሰው ግፍ በተጨማሪ የተለየ ጭቆናና አፈና ሲፈፀም ቆይቷል። ሁኖም ግን በፋኖ በኩል በሆደ ሰፊነትና  በአስተዋይነት ከሚገባው በላይ ትግስትን ተላብሰን ሆድ አደር ሚኒሻና የብልፅግና አመራር  በእኛ ቤተሰቦች ላይ የሚያደርሰውን በእነሱ ላይ ከማድረግ ተቆጠበን ቀይተናል ። ከዚህ በኋላ ግን ለየትኛውም ቤተሰቦቻችን ላይ ለሚደርስ ጥቃት ትይዩ ዕርምጃ የምንወስድ መሆኑን ማሳወቅ እንወዳለን ። በመጨረሻም የተከበራችሁና የተወደዳችሁ የባንዳ ቤተሰቦች ይህንን አስነዋሪ ድርጅት የሚሰሩ የቅርብ ቤተሰቦቻችሁን ጥብቅ ምክርና ማሳሰቢያ እንድትሰጡ ከወዲሁ እናሳስባለን። መዝገበ ጮቄ ብርጌድ ጳግሜ 3/2017/

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ "የፖለቲካ መኮንኖችን" በድምቀት አስመረቀ:: የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ "ፀሃፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሃብተወልድ የፖለቲካ መኮንን ማሰለጠኛ ማዕከል" የሚል ፕሮጀክት በማቋቋም የመጀመሪያ ዙር የፖለቲካ መኮንኖችን ለበርካታ ቀናት ሲያሰለጥን ቆይቶ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በድምቀት አስመርቋል። የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምንሊክ ዕዝ የፖለቲካ ዘርፍ ሥር የተቋቋመው የፖለቲካ መኮንኖች ማሰልጠኛ ማዕከል በኢትዮጵያ የፖለቲካና የድፕሎማት ታሪክ ደማቅ አሻራ ባለቤት በሆነው ፀሃፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሃብተወልድ ስም በመታሰቢያነት ተሰይሟል። ከሁሉም ኮሮች የተመለመሉ ሰልጣኝ የፖለቲካ መኮንኖች በርካታ ዉጣዉረዶችን አልፈው ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ለምረቃ በመብቃታቸው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት በድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች የተላለፈ ሲሆን የመኮንን ተመራቂዎቹ በሰለጠኑት መሰረት በአማራ ብሔርተኝነት መስመር ትግሉን በትጋትና በንቃት ለማገልገል፣ ድርጅታችን አፋብኃን ለመጠበቅ፣ ፖለቲካዊ ሥራዎችን ለመስራት ቃል ገብተዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ጳጉሜ 3/2017 ዓ.ም

‎መልካም ዜና! ‎የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የኮር ምስረታ አካሄደ ‎================ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ አምስት ክ/ጦሮችን ወደ አንድ በማሰባሰብ ግዙፉን የፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር አንድ መስርቷል:: ‎ ‎ይህንን ኮር አፄይኩኖ አምላክ፥ ሰባት ለሰባ፥ ነጎድጓድ፥ ናደው እና በፍቃዱ በላይ ክ/ጦሮች በአንድ ላይ ሁነው ነው የመሰረቱት :: ‎ ‎ይህ የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር ምስረታ ሥነ ስርዓት የአሳምነው እዝ አመራሮች፥ የየክ/ጦር መሪዎች፥ የፋኖ አባላት፥ አባት አርበኞች፥ የሀይማኖት አባቶች፥ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በኤፍራታና ግድም ወረዳ በደራሲና አርበኛ አሰገድ መኮነን መቀመጫ ማጀቴ ተካሄዷል:: ‎ ‎በዚህ የኮር ምስረታ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው እዝ አፄ ይኩኖ አምላክ፥ ሰባት ለሰባ ፥ነጎድጓድ ፥ ናደው እና በፍቃዱ በላይ ክ/ጦር የፋኖ አባላት በወታደራዊ ሰልፍ ተመው በመምጣት ተሳታፊ ሁነዋል:: ‎ ‎የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ ኮር ምስረታ ፕሮግራም ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአፋብኃ ሴንትራል ኮማንድ አባል እና ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ዋና መሪ አርበኛ ኢንጅነር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ እስካሁን የገጠሙንን በርካታ ተግዳሮቶች በፋኖ አርበኞቻችን እና በማህበረሰባችን ጥንካሬ ተወጥተን የጋራ መሰባሰቢያ ቤታችንን ከሸንኮራ እስከ ቋራ ተጉዘን ገንብተን በመጣን ማግስት ታላቁን የፄ ዘርያይቆብ ኮር መመስረት መቻላችን ጥንካሬያችን የታየበት በመሆኑ ሁላችንም ደስ ሊለን ይገባል ሲሉ ተናግረዋል:: ‎ ‎በኮር ምስረታው የተገኙት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ሴንትራል ኮማንድ አባል እና የአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ዋና ወታደራዊ አዛዥ ፊት አውራሪ ድርሳን ብረሀኔ ከአሳምነው ዕዝ ጋር በጋራ በመስራት የጥላትን ቅስም የምንሰብርበት ወቅት ሩቅ አይደለም ብለዋል:: ‎ ‎ይህንን የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ አንደኛ ኮር ምስረታ በተመለከተ የስም ስያሜ በአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የድርጅት ጉዳዮች ኃላፊ አርበኛ አሸናፊ ምንዳ በኩል ማብራሪያ ተሰጥቶ የዕዙ የድርጅት ጉዳዮች  የቀጣይ እቅድ የሚያመላክቱ መልእክቶች ተላልፈዋል:: ‎ ‎በዚህ የኮር ምስረታ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ወታደራዊ ዋና አዛዥ ፊት አውራሪ ባዩ አለባቸው የፋኖ ኃይል ሊከተላቸው የሚገቡ የቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችና ወታደራዊ መመሪያ ምን መምሰል እንዳለባቸው መልእክት አስተላልፈዋል:: ‎ ‎የኮር ምስረታ ፕሮግራሙም በተለያዩ መጣጥፎች፥ ግጥሞች፥ ሽለላና ቀረርቶ በድምቀት ከተካሄደ በኋላ  የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል እንዲመሰረት ከሸንኮራ እስከ ቋራ ተራራ ሸንተረሩ ቁርና ብርዱ እንዲሁም የጠላት ሀይል ሳይበግራቸው አንድ የአማራ ቤት ሰርተው ለተመለሱት የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች የቃል ኪዳን ምልክት የሆነችውን የአባቶቻችን የቃል ኪዳን አርማ የሆነችውን ሰንደቅ ዓላማ በማበርከት ለቀጣይ መሪነት ዝግጁ እንዲሆኑ ተደርጓል:: ‎ ‎በመጨረሻም የአፋብኃ ደቡብ አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ ም/ል መሪ በአርበኛ ኢሳያስ ደመቀ የአፄ ዘርአያዕቆብ ኮር አንድ መሪ ሁነው የተመደቡ የፋኖ አመራሮች ቃለመሀላ እንዲፈጽሙ ተደርጎ የተመደቡ አመራሮች የአማራ ህዝብ የጣለባቸውን አደራ በብቃት እንዲወጡ ጭምር መልእክት በማስተላለፍ እና ከብልጽግና ጋር ወግነው ለሚሰሩ አመራሮች፥ የአድማ ብተና ፥የሚኒሻ ፥ እና የመከላከያ አባላት የፋኖን ትግል እንዲደግፉ ጥሪ በማስተላለፍ ፕሮግራሙ ተጠናቋል:: ‎የኮሩን አመራሮች ዝርዝር ሙሉ መረጃ እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።             "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን" አፋብኃ ደቡብ  አማራ ቀጠና አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ዜና ክፍል        ጳጉሜ 03/2017 ዓ.ም ‎

አማኑኤል ከተማ ላይ ኦፐሬሽን ተሠርቷል። በአፋብኃ ምዕራብም አማራ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ የቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር በላይ ዘለቀ ብርጌድ ጳጉሜን 02 ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ አማኑኤል ከተማ ላይ በሰራው ኦፐሬሽን ወርቄ አታላይ የሚበል የስርአቱ ተላላኪ ባንደ እስከመጨረሻው የሸኘ ሲሆን  አራት የወራሪውን ኃይሎች ቆስለኛ ማድረግ ችሏል። ጳጉሜን 03/13/2017 ዓ.ም

ሰበር_ዜና አማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የልጅ እያሱ ኮር ክፍለጦሮች በጋራ በከፈቱት ጠንካራ ውጊያ የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ የሆነችውን #ውጫሌ ከተማን ተቆጣጥረው ታላቅ ድል ተጎናፀፉ:: ዛሬ ጳጉሜ 03/2017 ዓ.ም አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ በልጅ እያሱ ኮር ስር ያሉ ክፍለ ጦሮች የደቡብ ወሎ ዞን የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ውጫሌ ከተማ ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ በቀጠለው ተጋድሎ እስከ መሀል ከተማ በመግባት የየጁ ክፍለ ጦር ራስ አሊ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ እና ራምቦ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ በጋራ በመሆን በተናበበ ፍፁም በተቀናጀ መልኩ የተሳካ ውጊያ በማድረግ ጠላትን ሙት እና ቁስለኛ ሲያደርጉት ውለዋል ። እስካሁን ከ10 በላይ ፖሊስ እና ሚሊሻ ሲገደል በቁጥር ያልተረጋገጠ የወራሪው መንግስት ወታደር ሚሊሻ አድማ ብተና አና ፖሊስ ቁስለኛ ሆኗል:: በተጨማሪም ሶስት የሚሊሻ አባላት ምርኮኛ በማድረግ ውጊያው እንደ ተፋፋመ ቀጥሏል:: በዚህ ውጊያ የልጅ እያሱ ኮር የበቀል በትሩን አጠናክሮ በመቀጠል ውጫሌ ከተማ ያለውን የብልፅግና ግብስብሰ የፀጥታ ኀይል እና ካድሬ እያጠራ ይገኛል፡፡ የአብይ ሠራዊት ከወልድያ እና ከደሴ ሁለት ዙ23 እና አንድ መድፍ ያመጣ ቢሆንም ከብዙ ኪ.ሜ ርቀት ቆሞ ከመተኮስ በዘለለ ምንም ፋይዳ ያለው ተግባር ሊፈፅሙ አልቻሉም፡፡ በተጨማሪም በተደረገው ከፍተኛ የከበባ ውጊያ አንድ ከፍተኛ (ኮሎኔል ሊሆን እንደሚችል ይገመታል) የመከላከያ አመራርም ጭምር ተገድሏል። ጠላትን ከበባ ውስጥ በማስገባት ውጊያው አሁንም የቀጠለ ሲሆን ከዚህ የተሻለ ጮቤ የሚያስረግጥ ድል እየጠበቅን ከበባውን አጠናክረን ይዘናል፡፡ መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ©አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የልጅ እያሱ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል 03/13/2017 ዓ.ም

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን ህዝባዊ ውይይቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል(አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙ
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን ህዝባዊ ውይይቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል(አፋብኃ)  ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ከሚያስተዳድራቸው ወረዳዎች አንዱ በዋግኸምራ አስተዳደር ዞን ጋዝጊብላ ወረዳ ላልኪው ቀበሌ አንዱ ሲሆን ከቀበሌው ማህበረሰብ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ማድረጉ ተነገረ። ጷግሜ 02/2017ዓ.ም የኮሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በተደረገው ህዝባዊ ውይይት የፋኖ ሰራዊት ከማህብተሰቡ ጋር ያለው ግንኙነት፣የሲቪል አስተዳደሩ ከህብረተሰቡ  እና ከሰራዊቱ ጋር ያለው ግንኙነት እንዲሁም የፍትህ አሰጣጥን በተመለከተ ሃሳቦች የተነሱ ሲሆን በተነሱ የመወያያ ሀሳቦች ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ በመድረስና የቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መጠናቀቁ ታውቋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የኮሩ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ  ቢሆነኝ ቢያበይን መረጃውን አድርሷል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ        ጷግሜ 03 / 2017 ዓ.ም

151 የአገዛዙ ወታደር እጅ ሰጠ በጎንደር ቀጠና 151 ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው እጃቸውን ለፋኖ ሲሰጡ፡ አገዛዙ ደግሞ የከዱትንና የሞቱበትን ለመተካት መጠነሰፊ የግዳጅ አፈሳ እያካሄደ ይገኛል። እስካሁን ባለው ሁነት ከጎንደር ከተማና አካባቢዋ በርካታ ወጣቶች በአገዛዙ ሀይሎች በግዳጅ ታፍሰዋል። ጳግሜ 2/2017/

ሰበር የድል ዜና ዛሬ ጳጉሜ 02/2017 ዓ.ም አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ በልጅ እያሱ ኮር ስር ያሉ ክፍለ ጦሮች  የደቡብ ወሎ ዞን የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ውጫሌ ከተማ ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ በቀጠለው ተጋድሎ እስከ መሀል ከተማ በመግባት የየጁ ክፍለ ጦር ራስ አሊ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ እና ራምቦ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ በጋራ በመሆን በተናበበ ፍፁም በተቀናጀ መልኩ የተሳካ ውጊያ በማድረግ ጠላትን ሙት እና ቁስለኛ ሲያደርጉት ውለዋል ። እስካሁን ከ 10  በላይ ፖሊስ እና ሚሊሻ ሲገደል በቁጥር ያልተረጋገጠ የወራሪው መንግስት ወታደር ሚሊሻ አድማ ብተና አና ፖሊስ  ቁስለኛ ሆኗል በተጨማሪም ሶስት የሚሊሻ አባላት ምርኮኛ በማድረግ ውጊያው እንደ ተፋፋመ ቀጥሏል:: በዚህ ውጊያ የልጅ እያሱ ኮር የበቀል በትሩን አጠናክሮ በመቀጠል ውጫሌ ከተማ ያለውን የብልፅግና ግብስብሰ የፀጥታ ኀይል እና ካድሬ እያጠራ ይገኛል፡፡ የአብይ ሠራዊት ከወልድያ እና ከ ከደሴ ሁለት ዙ23 እና አንድ መድፍ ያመጣ ቢሆንም ከብዙ ኪ.ሜ ርቀት ቆሞ ከመተኮስ በዘለለ ምንም ፋይዳ ያለው ተግባር ሊፈፅሙ አልቻሉም፡፡በተጨማሪም በተደረገው ከፍተኛ የከበባ ውጊያ አንድ ከፍተኛ የመከላከያ አመራርም ጭምር ተገድሏል።የከበባ ውጊያው አሁንም  የቀጠለ ሲሆን ከዚህ የተሻለ ጮቤ የሚያስረግጥ ድል እየጠበቅን ከበባውን አጠናክረን ይዘናል፡፡ አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ የልጅ እያሱ ኮር ህዝብ ግንኙነት ጳግሜ 2/2017/

ሰበር የድል ዜና ዛሬ ጳጉሜ 02/2017 ዓ.ም አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ በልጅ እያሱ ኮር ስር ያሉ ክፍለ ጦሮች  የደቡብ ወሎ ዞን የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ውጫሌ ከተማ ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ በቀጠለው ተጋድሎ እስከ መሀል ከተማ በመግባት የየጁ ክፍለ ጦር ራስ አሊ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ እና ራምቦ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ በጋራ በመሆን በተናበበ ፍፁም በተቀናጀ መልኩ የተሳካ ውጊያ በማድረግ ጠላትን ሙት እና ቁስለኛ ሲያደርጉት ውለዋል ። እስካሁን ከ 10  በላይ ፖሊስ እና ሚሊሻ ሲገደል በቁጥር ያልተረጋገጠ የወራሪው መንግስት ወታደር ሚሊሻ አድማ ብተና አና ፖሊስ  ቁስለኛ ሆኗል በተጨማሪም ሶስት የሚሊሻ አባላት ምርኮኛ በማድረግ ውጊያው እንደ ተፋፋመ ቀጥሏል:: በዚህ ውጊያ የልጅ እያሱ ኮር የበቀል በትሩን አጠናክሮ በመቀጠል ውጫሌ ከተማ ያለውን የብልፅግና ግብስብሰ የፀጥታ ኀይል እና ካድሬ እያጠራ ይገኛል፡፡ የአብይ ሠራዊት ከወልድያ እና ከ ከደሴ ሁለት ዙ23 እና አንድ መድፍ ያመጣ ቢሆንም ከብዙ ኪ.ሜ ርቀት ቆሞ ከመተኮስ በዘለለ ምንም ፋይዳ ያለው ተግባር ሊፈፅሙ አልቻሉም፡፡ በተጨማሪም በተደረገው ከፍተኛ የከበባ ውጊያ አንድ ከፍተኛ የመከላከያ አመራርም ጭምር ተገድሏል። የከበባ ውጊያው አሁንም  የቀጠለ ሲሆን ከዚህ የተሻለ ጮቤ የሚያስረግጥ ድል እየጠበቅን ከበባውን አጠናክረን ይዘናል፡፡ አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ የልጅ እያሱ ኮር ህዝብ ግንኙነት ጳግሜ 2/2017/

ሰበር የድል ዜና ዛሬ ጳጉሜ 02/2017 ዓ.ም አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ በልጅ እያሱ ኮር ስር ያሉ ክፍለ ጦሮች  የደቡብ ወሎ ዞን የአምባሰል ወረዳ መቀመጫ በሆነችው ውጫሌ ከተማ ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ በቀጠለው ተጋድሎ እስከ መሀል ከተማ በመግባት የየጁ ክፍለ ጦር ራስ አሊ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ እና ራምቦ ክፍለ ጦር ሁለተኛ ሻለቃ በጋራ በመሆን በተናበበ ፍፁም በተቀናጀ መልኩ የተሳካ ውጊያ በማድረግ ጠላትን ሙት እና ቁስለኛ ሲያደርጉት ውለዋል ። እስካሁን ከ 10  በላይ ፖሊስ እና ሚሊሻ ሲገደል በቁጥር ያልተረጋገጠ የወራሪው መንግስት ወታደር ሚሊሻ አድማ ብተና አና ፖሊስ  ቁስለኛ ሆኗል በተጨማሪም ሶስት የሚሊሻ አባላት ምርኮኛ በማድረግ ውጊያው እንደ ተፋፋመ ቀጥሏል::በዚህ ውጊያ የልጅ እያሱ ኮር የበቀል በትሩን አጠናክሮ በመቀጠል ውጫሌ ከተማ ያለውን የብልፅግና ግብስብሰ የፀጥታ ኀይል እና ካድሬ እያጠራ ይገኛል፡፡ የአብይ ሠራዊት ከወልድያ እና ከ ከደሴ ሁለት ዙ23 እና አንድ መድፍ ያመጣ ቢሆንም ከብዙ ኪ.ሜ ርቀት ቆሞ ከመተኮስ በዘለለ ምንም ፋይዳ ያለው ተግባር ሊፈፅሙ አልቻሉም፡፡በተጨማሪም በተደረገው ከፍተኛ የከበባ ውጊያ አንድ ከፍተኛ የመከላከያ አመራርም ጭምር ተገድሏል።የከበባ ውጊያው አሁንም  የቀጠለ ሲሆን ከዚህ የተሻለ ጮቤ የሚያስረግጥ ድል እየጠበቅን ከበባውን አጠናክረን ይዘናል፡፡ አፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ እዝ የልጅ እያሱ ኮር ህዝብ ግንኙነት ጳግሜ 2/2017/

NiSiR Int. Broadcasting Co. (Official Telegram Channel) - Estadísticas y analítica del canal de Telegram