ኮዬ ፈጬ ፕሮጀክት 12 እና አዲስ ከተማ እድለኞች
Ir al canal en Telegram
Mostrar más
998
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
Repost from ለኮዬ ነዋሪዎች ዝርዝርና ተአማኒ ወሳኝ መረጃ መለዋወጫ ቻናል
የጣሪያና ግድግዳ ግብር ክፍያ ተፈጻሚነት ጋር በተያያዘ ዛሬ በሸገር ከተማ ከንቲባ ቢሮና በሸገር ከተማ የገቢዎች ቢሮ የሔደው የነዋሪ ተወካይ ያገኘውን መረጃ እናጋራችሁ
ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ በወዴሳ ወረዳ ከኮዩ ፈጩ 2 የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች/ ዕድለኞች እየተሰበሰበ ስላለው የጣራና ግድግዳ ግብር ግልፅ መረጃ ከሚመለከተው አካል እስካሁን ባለመሰጠቱ ነዋሪው በመረጃ ክፍተት የማህበራዊ ሚዲያ ሰለባ ሆኖል፡፡ እንደ ነዋሪ ተወካይ ከሚመለከተው አካል ተዓማኒና ተጨባጭ መረጃ በማግኘት ህብረተሰቡን ካላስፈላጊ መንገላታት ለመታደግ ጥረት ተደርጓል፡፡
በነዋሪ ተወካይ የተደረጉ ጥረቶችን ለማሳየት ያህል፡-
1. እሮብ ነሃሴ 24 ቀን 2015 ዓ.ም. ጠዋት ዩሴፍ ቤተክርስቲያን አካባቢ ወደሚገኘው የሸገር ከተማ ከንቲባ ቢሮ የተወሰኑ የነዋሪ ተወካይ በመሔድ ክቡር ከንቲባ ደ/ር ተሾመ አዱኛን ለማግኘት ጥረት አድርገዋል፡፡ ክቡር ከንቲባው በወቅቱ ቢሮ አልነበሩም፤ ከንቲባው የወከሏቸው አመራርም እንዲሁ በቢሮ ስላልነበሩ የነዋሪው ተወካዮች የሚመለከታቸውን አመራር ሳያገኝ ለመመለስ እያሰቡ እንዳሉ በግቢው ውስጥ የፋይናንስና ገቢዎች ቢሮ የሚል አንድ ታፔላ ያያሉ፡፡
2. የነዋሪ ተወካዮቹም በሸገር ከንቲባ ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ የፋይናንስና ገቢዎች ቢሮ በመሔድ ስለ ኮዩ ፈጩ 2 የጣራና ግድግዳ ግብር መረጃ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ እዛም እንዲሁ ጥርት የለ መረጃ የሚሰጣቸው የሚመለከተው አካል አላገኙም፡፡ መረጃ የሚሰጥ አካል ባይገኝም ከኮዩ ፈጬ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ለስራ የመጣ አንድ ተወካይ ስላለ ስለጉዳዩ መረጃ ካለው እንዲጠይቁት ይጠቁሟቸዋል፡፡ የነዋሪዎቹ ተወካዮችም በተጠቆሙት መሰረት ወደ ከንቲባ ቢሮ ለስራ ወደሔዱት የኮዩ ፈጩ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ተወካይ በመቅረብ ሰላምታ ከተለወመጡ በኋላ ፈቃደኝነታቸውን ጠይቀው ከዚህ የሚከተለውን ጥያቄ አቅርበውላቸዋል፡-
1. በኮዩ ፈጩ 2 ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን የጣራና ግድግዳ ግብር ለመሰብሰብ መነሻ የሆነ እንደ ሸገር ከተማ የወጣ አዋጅ፣ ደንብ ወይም መመሪያ መኖር/ አለመኖሩን ጠይቀዋል?
2. የኮዩ ፈጩ 2 የጋራ መኖሪያ ቤት በሚያፈስ ጣሪያ፣ ገና ብዙ ያልተጠናቀቀ የግንባታ፣ አስፈላጊ መሰረተ ልማት ባልተሟላበት ሁኔታ የጋራ መኖሪያ ቤቱን የጣራና ግድግዳ ግብር ግምት/ የሬቱን ጉዳይ በምን አግባብ እንደተወሰነ ትክክለኛውን መረጃ እንዲነግሯቸው ጠይቀዋል?
3. የኮዬ ፈጨ ኮንዶሚንየም በአዲስ አበባ ኮንዶሚንም ደረጃ ሲታይ ደረጃው ስንት ነው? ከዚሁ ጋር ተያይዞ በውዴሳ ወረዳ ከኮዩ ፈጩ 2 የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪው እየተሰበሰበ ያለው የጣራና ግድግዳ ግብር አሁን ላይ እንዲሰበሰብ መደረጉ ወቅቱንና ጊዜውን የዋጀ ነውይ? የሚሉና ከዚህ ጋር ተያያዥ የሆኑ ጥያቄዎችን የነዋሪ ተወካዩቹ አቅርበውላቸዋል፡፡
ከኮዩ ፈጩ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ቢሮ ለስራ ሸገር ከንቲባ ግቢ የተገኙት ተወካይ ምላሽ፡-
1. ባለሙያው ለመጀመሪያው ጥያቄ የሰጡት ምላሽ ምንም ዓይነት መነሻ አዋጅ እና መመሪያ እንደ ሸገር ከተማ አልተዘጋጀም ብለዋል፡፡ ነገር ግን የከተማ ቦታ ኪራይ እና የከተማ ቤት ግብር አዋጅ ቁጥር 80/1968 አንቀፅ 6/2 መሰረት አድርጎ የሸገር ከተማ ካቢኔ ተወያይተው በቃለጉባኤ ያፀደቁት መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡
2. የነዋሪ ተወካዩቹ በተራ ቁጥር ሁለት ላቀረቡላቸው ጥያቄ የኮዩ ፈጩ የገቢዎች ቢሮ ተወካይ ምላሽ ሬቱን ለመወሰን በኮዩ ፈጩ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ጥናት መጠናቱን ተናግረዋል፡፡ በጥናቱ እንደ ሳምፕል ሰርቬ የተወሰደው የለሙትን የቱሉዲምቱን እና የኮዩ ፈጬ አንድ የጋራ መኖሪያ ቤት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በቱሉዲምቱ አንድ መኝታ ቤት እስከ 12 ሺ ብር ሲከራይ፤ በኮዩ ፈጩ አንድ መንገድ ዳር ያሉ የለሙ ሳይቶች ደግሞ እስከ 7 ሺ ብር እንደሚከራይ ታሳቢ ተደርጎ ነው ለኮዬ ፈጨ 2 ኮንዶሚንየም 133.38 ተባዝቶ እንድትከፍሉ የተደረገው ብለዋል፡፡ ይህም በአዲስ አበባ የኮንዶሚንም የጣራና የግድግዳ ግብር ለመገመት በጥናት ላይ ተመርኩዞ ለ1ኛ ደረጃ የተቀመጠውን በካሬ 247 ብርን በካሬ ተባዝቶ ነው ተፈጻሚ የተደረገው፡፡
3. በተራ ቁጥር ሁለት ላቀረቡላቸው ጥያቄ የኮዩ ፈጩ የገቢዎች ቢሮ ተወካይ ምላሽ ለኮዩ ፈጩ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ኃላፊ ለሆኑት ለአቶ መልካሙ የኮዩ ፈጩ 2 ነዋሪዎች ቅሬታ ተገልፆ ቢቀርብላቸው ቅሬታዎቻችሁን ለካቢኒው ያቀርባሉ የሚል ምልከታ ሰጥተዋቸዋል፡፡
ዛሬ ማለትም ነሃሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ከጠዋት ሳር ቤት አካባቢ ወደሚገኘው የሸገር ከተማ ገቢዎች ቢሮ የተወሰኑ የነዋሪ ተወካዩች በመሔድ የሸገር ከተማ የገቢዎች ኃላፊ ቢሮ ሔደው ነበር፡፡ ዛሬ ጠዋት የሸገር ከተማ የገቢዎች ኃላፊ በስብሰባ ምክንያት ቢሮ ባለመሆናቸው በሸገር ከተማ አሰተዳደር ገቢዎች ቢሮ የገቢ አሰባሰብ ክፍል ምክትል ኃላፊ የሆኑትን አቶ ኑሪ ሁሴን አግኝተው አነጋግረው ተመልሰዋል፡፡
የኮዩ 2 የነዋሪ ተወካዩቹ ለአቶ ኑሪ ሁሴን ከላይ ለኮዩ ፈጩ ክፍለ ከተማ ገቢዎች ጽ/ቤት ባለሙያ ያቀረቡትን ጥያቄ አቅርበውላቸዋል፡፡ በሸገር ከተማ የገቢ አሰባሰብ ክፍል ምክትል ኃላፊ የሆኑትን አቶ ኑሪ ሁሴንም የነዋሪ ተወካዩቹን አቤቱታ በጽሞና ካደመጡ በኋላ የጣራና የግድግዳ ግብር እንደሚከፈል ማወቅ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ይሁንና
በወዴሳ ወረዳ ከኮዩ ፈጩ 2 የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪዎች እየተሰበሰበ ስላለው የጣራና የግድግዳ ግብር ማስከፈል መጀመራቸውን መረጃው እንደሌላቸው ነግረውናል፡፡
አቶ ኑሪ ሁሴን በሸገር ከተማ ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በስብሰባ ምክንያት ቢሮ ስለሌሉ ሰኞ ቢሮ ሲገቡ በጉዳዩ ዙሪያ ተነጋግረን የደረስንበትን እናሳውቃችኋለን ብለዋቸዋል፡፡ አቶ ኑሪ እስከዛ ድረስ ያለውን ነገር ወደ ሸገር ከተማ አመራሮች ጋር ተነጋግረው፣ የሔዱበትን አግባብ እና ይህንን ለሚመለከተው አካል አሳውቃችኋል ወይ? የሚሉትን መረጃዎች እንደሚያጣሩ ለነዋሪ ተወካዩቹ አረጋግጠውላቸዋል፡፡ በመጨረሻም አቶ ኑሪ ሁሴን በሸገር ከተማ ገቢዎች ቢሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ሰኞ ስራ ሲገቡ ተነጋግረውበት፣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋርም ከተነጋገሩ በኋላ የደረሱበትን መደምደሚያ እናሳውቃችኋለን ብለዋቸው የሔዱትን የነዋሪ ተወካይ የእጅ ስልክ ተቀብለው ተወካዩቹ ተመልሰዋል፡፡
በቀጣይም ከነዋሪ ተወካዮች የሚሰጡንን መረጃዎች ለማጋራት እንሞክራለን። ደህና እደሩ….
ይህን የጣሪያና ግድግዳ ግብር ክፍያ ተፈጻሚ የሚሆነው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብቻ ነው። ምክንያቱም አስተዳደሩ ይህን ገቢ ለመሰብሰብ የወጣ መመሪያ ስላለ ነው።
ከአዲስ አበባ ውጭ ያሉ የክልል ከተሞች እንደዚህ ዓይነት የህግ ማዕቀፍ የላቸውም።
በኦሮሚያ ክልል ያሉ ከተሞች ከቤት ባለቤቶች በዓመት የሚሰበስቡት ገቢ የአፈር ግብር ብቻ ነው። በሸገር ከተማ የተካለሉት የሰበታ፣ የቡራዩ፣ የለገጣፎ ለገዳዲ፣ የሱሉልታና የአቃቂ አካባቢዎች ያሉ ኮንዶሚኒየም ቤቶች የጣራና ግድግዳ ግብር አይከፍሉም። በተመሳሳይ የገላን አካባቢ ብቻ ይህን ሊያደርግ አይችልም።
እኔ ባደረኩት ማጣራት በኦሮሚያ ክልል የጣራና ግድግዳ ግብር ለመሰብሰብ የወጣ አዋጅ፣ ደንብ ወይም መመሪያ የለም። በተመሳሳይ የሸገር ከተማም ያወጣው ህግ የለም። ስለዚህ ህጋዊ የሆነ ህግ ሳይወጣ ገቢ መሰብሰብ ተገቢ አይደለም።
ምናልባት ህግ ሳይወጣ ገቢ በመሰብሰብ ወደፊት ህጋዊ ለማድረግ የሚመች ስላልሆነ ጥንቃቄ ብናደርግ ጥሩ ነው። በተረፈ እኔ ያገኘሁትን መረጃ ይበልጥ ለማረጋገጥ የኦሮሚያ ክልል ገቢዎች ቢሮን ጨምሮ ሁሉም ሴክተር ቢሮዎች ሳር ቤት ስለሆኑ በአካል ሄዶ ማጣራት ይቻላል።
ለ ኘሮጀክት 12 እና አዲስ ከተማ የ13ተኛ ዙር የቤት እድለኞች በሙሉ የመፀዳጃ ቤት እቃዎችን ለመውሠድ የምትመጡ ከነገ 29 /10/2015 በአመታዊ ንብረት ቆጠራ ምክንያት ላልተወሰነ ጊዜ መስተንግዶ የማንሠጥ መሆኑን እንገልፃለን። ፅ/ቤቱ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለቤት ሽያጭ በካሬ ሜትር ቁርጥ ተመን አወጣ ።
…
ሰሞኑን ፋይናንስ ቢሮ የቀረበለትን አዲስ ቀመር በመቀበሉ የመሬት ስሪት መስሪያ ቤት ባለሙያዎች አዲሱን ቀመር ተግባራዊ ለማድረግ እየተዘጋጁ መሆኑ ታውቋል።
የውሳኔው ማጠንጠኛ በቤት ግብይት ወቅት ዕውነታው እና የሚቀርበው የሽያጭ ውል እጅግ የተራራቀ በመሆኑ - በውሉ ላይ ተመስርቶ የሚገኘው ካፒታል ጌን 15 % ፣ቫት 15% ፣ የቴምብር ቀረጥ 2 % ፣ አሹራ 4% ፣ እንደየ ገቢው ሁኔታ ከ10- 35 % ትርፍ ግብር በተሰኙ የገቢ አርዕስቶች ላይ የተለያዩ ውጫዊና ውስጣዊ ምክንያቶች አየተደረደሩ ሽያጭ ገቢ እንዲደበቅ ተደርጓል የሚል ነው።
በቤት ግብይት ዙሪያ አሳንሶ መዋዋል ፣ አሳንሶ መገመት ፣የስም ዝውውር ማዘግየት ፣ ቤቱ በርካታ ጊዜ ግብይት ቢፈፀምበትም በመንደር ውል እየተዋዋሉ ስም ዝውውር አገልግሎት ሳይጠይቁ ግብይቱን አለማሳወቅ ተጠቃሽ ችግሮች መሆናቸው ተመልክቷል።
የከተማው አስተዳደር አሰራሩን በማስተካከል - ዕውነተኛው የሽያጭ ፍሬ ገንዘብ ላይ ያደርሰኛል በማለት እንደየ ቦታው ደረጃ - አንድ ይዞታ በካሬ ሜትር ሊሸጥ የሚችልበትን ዋጋ ወስኗል።
በአዲሱ ቀመር ቤት ሻጭ እና ገዥ የሚያቀርቡት ውል ላይ የጠቀሱት ገንዘብ ከተቀመጠው የካሬ ሜትር ዋጋ ከበለጠ ተቀባይነት የሚያገኝ ሲሆን ካነሰ ደግሞ አስተዳደሩ ባቀረበው የካሬ ሜትር ዋጋ ብቻ ይስተናገዳል።
የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን በቦታው ስፋት በማባዛት የሚገኘው ውጤት ከሽያጭ ውሉ ጋር በማነፃፀር ብልጫ ባለው ዋጋ ስመ - ንብረት ዝውውሩ ተፈፃሚ እንዲሆን ዶ/ር ቀንዓ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።
የመብራት እና ውሃ የመሰረተ-ልማት አቅርቦት በተሟላ ሁኔታ ማቅረብ አለመቻሉ፣ የመንገድ መሰረተ-ልማት አቅርቦት በጣም የተጓተተ እና በሙሉ አቅሙ ያለመስራት ችግር ስላለ ነዋሪው በክረምትም ሆነ በበጋ ለብዙ ችግር መዳረጋቸውን፣ አሁንም የነዋሪው ቅሬታ ያልተፈታባቸው ችግሮች ጋር በተያያዘም የውስጥ ለውስጥ መስመር ዝርጋታ የተሰራ ቢሆንም ከዋናው መስመር ጋር አለመገናኘቱ፣ ወ.ዘ.ተ.…
በሌላ በኩል ደግሞ ከህገ-ወጥ ግንባታ፣ የአከራይ ተከራይ ውል ማዋዋል ጉዳይ፣ ከጋራ አጥር ፈቃድ መስጠት፣..ወ.ዘ.ተ.. ክፍለ ከተማው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ችግሩ የሚፈታበት ሁኔታ እንዲፈጠር ወሳኝ ወሳኝ የሆኑ የነዋሪውን የጋራ አንገብጋቢ ጥያቄዎችን አቅርበዋል፡፡
በመጨረሻም በፓርሴል ሰብሳቢዎች ለተነሱ ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና ሀሳቦች ላይ አቶ ተሾመ ጥላሁን እና አቶ ቱሬ አለሙ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
አቶ ተሾመ ጥላሁን በማጠናቀቂያ ንግግራቸው ከነዋሪ ተወካዮች ለሚነሱ ጥያቄዎች የክ/ከተማው ቤቶች ብቻውን የሚመልሰው ባለመሆኑ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን የአ/አበባ ሴክተር መ/ቤት፣የወረዳ እና ሌሎች አካላትን ያሳተፈ የጋራ መድረክ የሚፈጠርበትን ሁኔታ በቅርቡ እንፈጥራለን ብለዋል፡፡
ከቤቶች ርክክብ ጋር በተያያዘም የፓርሴል ሰብሳቢዎች የነዋሪ ተወካይ ብቻቸውን የሚረከቡበት ሁኔታ አይኖርም ብለዋል፡፡ አቶ ተሾመ ህገ-ወጥነትን ለመከላከል የፕሮጀክት፣ የፓርሴል፣ የብሎክ ኮሚቴ አባላት ጥንካሬ ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል፡፡
ከህገ-ወጥ ግንባታ ስራ ጋር በተያያዘ አሁንም ያሉ ካሉ የነዋሪ ተወካዮች መረጃ ስጡ ብለዋል፡፡
የአከራይ ተከራይ ጉዳይ በመላው ኦሮሚያ በቤቶች ፅ/ቤት ስራ ነው ብለዋል፡፡ የአከራይ ተከራይ ውል የማዋዋል ስራ ለመስራት ከመንግስት ሃላፊነት የተሰጠው አካል የክፍለ ከተማ ቤቶች በመሆኑ ውል የማዋዋል ስራው የሚሰራው በክ/ከተማው ቤቶች ስር ባለ የስራ ክፍል ነው ብለዋል፡፡
አቶ ተሾመ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴንና ህገ-ወጥነትን በመከላከል ረገድ ምንም የምንታገሰው ነገር የለም፤ ስለሆነም በጋራ መኖሪያ ቤት ሳይቶች አካባቢ የሚስተዋለውን ህገ-ወጥነት ወደ ህጋዊ ስርዓት ለማስገባት የሚሰሩ ስራዎች አጠናክረን የምንሔድበት ይሆናል ብለዋል፡፡
ሽርፍራፊ ሳንቲም የሚለቅሙ የሚሊሻ አባላት ካሉ በመረጃና በማስረጃ አስደግፋችሁ አቅርቡ የማስተካከያ እርምጃ ይወሰዳል ጠቁመዋል፡፡
ቤታቸውን አድሰው በማይገቡ የቤት ዕድለኞች ጋር በተያዘም የጊዜ ገደብ መቀመጡ የማይቀር ጉዳይ ነው ብለዋል፡፡
የቤት ለቤት ቆጠራ ማጠናቀቂያ ሪፓርትና አጠር ያለ የእውቅና መርሃ-ግብር በቀጣይ ሳምንት እናደርጋለን ብለዋል፡፡ ሁሉም የድርሻውን ስራ ወስዶ በጋራ ኃላፊነት መወጣት እዳለበት የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ መድረኩ ተጠናቋል፡፡
የኮዩ ፈጩ ክፍለ ከተማው ቤቶች ፅ/ቤት ባዘጋጀው የኮዩ ፈጩ 1 እና 2 ውስጥ ያሉ የፓርሲል ሰብሳቢዎች ከክፍለ ከተማው ቤቶች የስራ ሃላፊዎች ጋር በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ሰፋ ያለ ውጤታማ ውይይት አድርገናል::
ስብሰባውን የመሩት የክፍለ ከተማው ቤቶች ፅ//ቤት ሃላፊ አቶ ተሾመ ጥላሁን እና የክፍለ ከተማው ቤቶች አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ቱሬ አለሙ ናቸው፡፡
የተነሱ ሀሳቦች
1. አጠቃላይ የኮዩ ፈጩ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በተመለከተ፣
2. ሁለተኛውና ደግሞ በቀጣይ ስለሚዘጋጁ መድረኮች ሁሉም የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት በተመለከተ ተወያይተናል፡፡
1.1 አጠቃላይ የኮዩ ፈጩ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በተመለከተ፣
አቶ ቱሬ በገለፃቸው ያለምንም በጀት በበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በኮዩ ፈጩ የስልሳ ስምንት ሺ አራት መቶ አስር (68,410) የጋራ መኖሪያ ቤቶችን የቤት ለቤት ቆጠራ በማድረግ መረጃዎችን በለተለያየ አግባብ ለማደራጀት ተችሏል ብለዋል፡፡ በዚህ የቤት ለቤት ቆጠራ መርሃ-ግብር ክፍለ ከተማው ብዙ ግብዓት እንዳገኘበትም አብራርተዋል፡፡
ዕጣ የወጣላቸው /ህጋዊ ቤቶች/ በአግባቡ ተለይተው በመረጃ ዳታ ቤዝ ተደራጅቷል፣
1.2 የመንግስት ቤቶች ማለትም እስካሁን በተለያየ ምክንያት ዕጣ ያልወጣላቸው ቤቶች የተጠናከረ መረጃ ተደራጅቷል
1.3 በህገ-ወጥ መንገድ ቤት ሰብረው የገቡ1,798 ህገ-ወጦች ተለይተዋል....ከዚህ ውስጥ ወደ 300 ቤቶች እንዲለቀቁ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ቀሪዎቹ በቅርቡ ኦፐሬሽናል ፕላን አውጥተን ወደ ስራ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንዳሉ ተናግረዋል፡፡
1.4 አቶ ቱሬ ለከተማው የፀጥታ ኮሚቴ ዛሬ ከሰዓት በኋላ የኮዩ ፈጩ የጋራ መኖሪያ ቤት ህገ-ወጥ ቤት ሰበራንና ህገ-ወጥ እንቅስቃሴዎች በተመለከተ ሪፓርት ቀርቦላቸው ዳይሬክሽን ይቀመጣል ብለዋል፡፡ በቅርቡ በህገ-ወጥ መንገድ የተያዙ ቤቶችን ከነዋሪ ተወካዩች ጋር በተቀናጀ አግባብ እናስወጣለን ብለዋል፡፡ በዚህ ኦፐሬሽን አስፈላጊ የሆኑ የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎች ሁሉ ይሰራሉ ብለዋል፡፡
1.5 የቤት ለቤት ቆጠራ ከተጠናቀቀ በኋላ የተፈጠሩ ህገ-ወጥ ተግባራት መረጃ በየወቅቱ እንደሚደረርሳቸው፣ እሳቸው ስብሰባ እየመሩ ባሉበት ጊዜ ፕሮጀክት 16 የሕንፃ ቁጥር 30፣ የቤት ቁጥር 34 በህገ-ወጥ መንገድ ቤቱ እየተሰበረ እንዳለ መረጃው በዛው ቅፅበት እንደደረሳቸው ተናግረዋል፡፡
1.6 አቶ ቱሬ በኮዩ ፈጩ 17ኛ ዙር በጨረታ የተላለፉ የንግድ ቤቶች “ሳይወለዱ ነው የተበላሹት” ብለዋል፡፡ የንግድ ቤቶቹ የአ/አበባ ቤቶች ያወጣውን ጨረታ አሸንፈው ወዲያውኑ ወደ ህገ-ወጥ ተግባር ነው የተሰማሩት ብለዋል፡፡
ከዚሁ ጋር አያይዘው 70 በመቶ የሚሆኑት የጨረታ አሸናፊዎች ጨረታውን እንዳሸነፉ አየር ባየር ሸጠው መውጣታቸውን ጠቁመዋል፡፡
በኮዩ-ፈጩ 2 የጋራ የመኖሪያ ሕንፃዎች ስር ያሉ የሱቅ ጨረታ አሸናፊዎች ካርታ ሳይሰጣቸው፣ የቁልፍ ርክክብ ባልተፈጸመበትና የብድር ውሉ ባላለቀበት ሁኔታ የጨረታው አሸናፊዎቹ የፓርሴል ኮሚቴ አባላትንም ሆነ ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትን ሃሳብ ሳይጠይቁ በማናለብኝነት የሱቁን ዲዛይን በመቀየር፣ የጋራ መጠቀሚያ ቦታን በመቀራመት የግለሰብ በማድረግ፣ የጋራ ቦታን በግል በማጠር፣ ከG+7 የሰባቱም ፍሎር የሽንት ቤት መቀበያ ባለ160PVC እየነቀሉ በባለ 110PVC እየቀረሩ፣ የፍሳሽ መሽመር ላይ የሽንት ቤት PVC መሰመር የማገናኘት፣ አንደኛ ፎቅ ላይ ያሉ ቤቶችን አላግባብ የማፍረስ እና የመሳሰሉትን ህገ-ወጥ ተግባራት መስተዋላቸው ይታወቃል፡፡
በጨረታ የተላለፉ ሱቆች ያለ እድሳት ፈቃድ ሲታደሱ እጅግ በሚዘገንን ሁኔታ የጋራ ሕንፃውን መሰረት የተሸከሙ ፒላሮችና ቢሞች እያፈረሱ በዙ ችግር እንዳስከተሉ መሬት ላይ ያለ ሃቅ ነው፡፡ ይህ ህገ-ወጥ ተግባር በሚመለከተው አካል በቅርቡ የዕርምት እርምጃ እየተወሰደ እንዳለ ይታወቃል፡፡
አቶ ቱሬ እንዳሉት አፍራሽ ግብር ሃይሉ ህገ-ወጥ ግንባታው ተጠናቋል የሚል መረጃቸ ካልደረሰን በስተቀር የንግድ ቤቶች የዕድሳትና የግንባታ ፈቃድ አገልግሎት አንሰጥም ብለዋል፡፡
ህገ-ወጥ የጋራ መኖሪያ ቤት ዕድሳት ጋር በተያያዘ እየተፈጠሩ ያለ ችግር ከዘመቻ ስራ ባለፈ ቀጣይነት ባለው መንገድ በሚመለከተው አካልጥብቅ ቁጥጥር ካልተደረገበት በስተቀር ለጋራ መኖሪያ ቤቱ ትልቅ ችግር መፍጠሩ አይቀሬ ነው፡፡
አቶ ቱሬ ከሃምሌ 1ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ የንግድ ሱቆች ህጋዊ የስራ ፈቃድ የሌላቸው የንግድ ድርጅቶች ፍቃድ እንዲያወጡ ይደረጋል ብለዋል::
1.7 አቶ ቱሬ የጋራ መኖሪያ ቤቱን ከዝናብ፣ ከወጨፎ፣ ከፀሃይ ለመከላከል 1.5 ወጥ የሆነ ዲዛይን ተዘጋጅቶ ወደ ሕንፃው ውሃ እንዳይሰርግና የወጨፎ መከላከያ እንዲኖራቸው ይደረጋል ብለዋል፡፡
1.8 ከአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፓሬሽን የቅርንጫፍ 07 የአንድ ማዕከል በኮዩ ፈጩ እና ሌሎች የመሰረተ-ልማት አቅራቢ ተቋማት ጋር በተያያዘም ሰኔ 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ይወጣሉ እየተባለ ያለው ጥድፊያ ተግባራዊ የሚሆን እንዳልሆነ ጠቁመዋል፡፡
1.9 ሰሞኑን እንደ ከተማ የመነጋገሪያ አጀንዳ የነበረውና ብዙዎቻችሁ እየጠየቃችሁ የነበረው የጣሪያና የግድግዳ ግብር ክፍያን በተመለከተ እኛን የ13ኛ ዙር የጋራ መኖሪያ ቤት እድለኞችን ይመለከታል ወይስ አይመለከትም ለሚለው ጥያቄ? የአቶ ቱሬ ምላሽ "የ13ኛ ዙር 20/80 ባለ ቤቶች እንደ ሸገር ከተማ ሰው ወደ ቤቱ ስላልገባ የቤት ግብር በ2015 ዓ.ም ስለማይከፍል አይመለከተውም::" በ2016 ዓ.ም. በኮዩ 2 የጋራ መኖሪያ ቤት የጣሪያና የግድግዳ ግብር ክፍያ እደሚጀመርም ጠቁመዋል.....
2.0 አቶ ቱሬ የክ/ከተማው ቤቶች በወረዳው የማዘጋጃ ቤት አገልግሎት ውስጥ ተግባሩ አለ፤ከዛ ውጪ በወረዳ ደረጃ ቢሮ የለውም ብለዋል፡፡ ስለሆነም የክ/ከተማው ቤቶች ፅ/ቤት ከነዋሪ ተወካዩች ከፓርሴል ሰብሳቢዎች ጋር አብሮ መስራት አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
2. ሁለተኛውና የመጨረሻው አጀንዳ ደግሞ በቀጣይ ስለሚዘጋጁ መድረኮች ሁሉም የነቃ ተሳትፎ ማድረግ እንዳለበት በተመለከተ፣
ሸገር ከተማ የተቋቋመችው እንደ ሀገር በተቋማት የቀጣይ ዓመት በጀት ከተለቀቀ በኋላ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ምንም ዓይነት በጀት አለመመደቡን ተናግረዋል፡፡
አብዛኞቹ አመራርና ሠራተኞችም ስራቸውን የሚያከነውኑት ያለደሞዝ መሆኑን ተጠቁሟል፡፡
በቀጣይ ሳምንት የጋራ መኖሪያ ቤቶች የቤት ለቤት ቆጠራ መርሃ-ግብር የተጠቃለለ ሪፓርት የሚቀርብበት የጋራ መድረክ ለማዘጋጀት በጀት እንደሚያስፈልጋቸው፤ መርሃ-ግብሩን ለማስኬድ የበጀት ድጋፍ አስፈላጊ በመሆኑ የጋራ መኖሪያ ቤት ነዋሪ ትብብር ወሳኝ ነው፡፡
እንደ ኮዩ 1 እና 2 የጋራ መኖሪያ ቤት ሳይት የነዋሪ ተወካይ በመድረኩ ላይ የተሳተፉ የፓርሴል ሰብሳቢዎች እንደ ነዋሪ ተወካይነታቸው እንደ ኮዩ በጣም በጣም ብዙ ተደራራቢ ችግሮች ያሉበት ሳይት በመሆኑ የሚመለከተው መንግስታዊ ተቋማት ሁሉ ተገቢውን ትኩረት ተደርጎ ያልተጠናቀቁ ቀሪ ግንባታ የተቋራጮችና ማህበራት ስራዎች፣ ከሮቶና የፓምፕ አቅርቦት ጋር በተያያዘ፣ የመሰረተ-ልማት አቅርቦቶች እንዲሟሉልን የተሻለ ትኩረት ተሰጥቶት የሚሰራበት ሁኔታ ሊፈጠርልን ይገባል::
