Ethiopian Catholic Charismatic
Ir al canal en Telegram
805
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
-130 días
Archivo de publicaciones
የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር
በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ
የ21 ቀን ፀሎት ፕሮግራም።
በየቀኑ #ፀሎት #አምልኮ #ትምህርት ይኖረናል
👉3ኛ ቀን የፀሎት ርዕስ
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ዮሐንስ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁰ ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።
¹¹ መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
በክርስቶስ የተገኘው ሕይወት መረዳት እንዲሆንልን እና በዚህ ሕይወት መመላለስ እንዲሆን እንፀልያለን።
የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር
በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ
የ21 ቀን ፀሎት ፕሮግራም።
በየቀኑ #ፀሎት #አምልኮ #ትምህርት ይኖረናል
👉2ኛ ቀን የፀሎት ርዕስ
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
“ሰባሪው በፊታቸው ወጥቶአል፤ እነርሱም ሰብረው ወደ በሩ አልፈዋል፥ በእርሱም በኩል ወጥተዋል፤ ንጉሣቸውም በፊታቸው አልፎአል፥ እግዚአብሔርም በራሳቸው ላይ ነው።”
— ሚክያስ 2፥13
የ2ኛ ዙር #ሕይወት_በመንፈስ _ቅዱስ _ሰሚናር
በሞጆ ሱባኤ ሴንተር ለምናደርገው ሱባኤ
የ21 ቀን ፀሎት ፕሮግራም ዛሬ ይጀምራል።
በየቀኑ #ፀሎት #አምልኮ #ትምህርት ይኖረናል
👉1ኛ ቀን የፀሎት ርዕስ
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ዳንኤል 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² እርሱም እንዲህ አለኝ፦ ዳንኤል ሆይ፥ አትፍራ፤ ልብህ ያስተውል ዘንድ፥ ሰውነትህም በአምላክህ ፊት ይዋረድ ዘንድ ካደረግህበት ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ቃልህ ተሰምቶአል፤ እኔም ስለ ቃልህ መጥቻለሁ።
¹³ የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ፤ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ፤ እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት።
መጽሐፍ-ቅዱስ
🙏🏻🙏🏻ሰላም፣ ሰላም፣ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቅ የቤዛነት ሥራ፣ በእግዚአብሔር አብ ፍቅር በመንፈስ-ቅዱስ ፀጋ እንዲያው ተመርጣችሁ የተወደዳችሁ ቅዱሳን የአባቴ ልጆች፣ የጌታ ጸጋ እና ሰላም ከናንተ ጋር ይሁን። በዛሬው ዝግጅታችን በሁላችንም እጅ ስለሚገኘው ነገር ግን የሚገባውን ትኩረት እና መሻት ስላልሰጠነው ስለ ታላቁ መጽሐፍ፣ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ በጥቂቱ እናያለን።
🖊🖊መጽሐፍ-ቅዱስ ምንድነው?
መጽሐፍ-ቅዱስ ሰዎች በእግዚአብሔር መንፈስ ተመርተው/ተነድተው የጻፉት የእግዚአብሔር ቃል ነው። 2ጢሞቴዎስ 3:16-17 ''የእግዚአብሔር ሰው ፍጹምና ለበጎ ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ ይሆን ዘንድ፥ የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ሁሉ ለትምህርትና ለተግሣጽ ልብንም ለማቅናት በጽድቅም ላለው ምክር ደግሞ ይጠቅማል።'' ይህ <የእግዚአብሔር መንፈስ ያለበት> የሚለውን በግሪክ ትርጉም <የእግዚአብሔር እስትንፋስ> ይለዋል፤ ይህም ማለት እግዚአብሔር ሰውን አበጅቶ የሕይወት እስትንፋስ እፍ እንዳለበትና ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው እንደሆነ ሁሉ በተጻፈው ቃሉም እግዚአብሔር ሕይወትንና ጥበብን እፍ ብሎበታል፣ ስለዚህ የሚያነበው ሁሉ በዚህ በእግዚአብሔር እስትንፋስ ይዳሰሳል፣ ይነካል፣ ይለወጣል እንዲሁም እንደ አዲስ ይሰራል(ይፈጠራል) ማለት ነው።
ይህ ቅዱስ መጽሐፍ ማንም ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ሊመገበው የሚገባ ሕይወትን የሚሰጥ መንፈስ ያለበት የአባታችን ቃል ነው።(ዮሐ.6:63) እንዲሁም የእግዚአብሔር ሰው -ፍጹም፣ -ለበጎም ሥራ ሁሉ የተዘጋጀ እንዲሆን የሚጠቅም፣የሚመክር ቅዱስ መጽሐፍ ነው።
🖊🖊የመጽሐፍ-ቅዱስ ይዘት
እንግዲህ የአባቴ ምርጦች፣ ከላይ ለማየት እንደሞከርነው፡ መጽሐፍ-ቅዱስ የእግዚአብሔር እስትንፋስ ወይም መንፈስ ያለበት መጽሐፍ ነው። ታዲያ የእግዚአብሔር የአባታችንን የዘላለማዊ ስልጣኑን እና የልቡን አሳብም በሙላት የምናውቅበት ቅዱስ እና ድንቅም መጽሐፍ ነው። ይህን ስንል ግን የእግዚአብሔር አሳብ በ66,73,ወይም 81 መጽሐፍት ብቻ አልቋል ወይም ያልቃል ማለት ሳይሆን ነገር ግን ለእኛ ሰዎች የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ ኃይሉን እና ክብሩን እናውቅ ዘንድ ግን በቂ እንዲሆኑ በመንፈስ-ቅዱስ ምሪት የቀደመችው ቤተ-ክርስቲያን በቀኖና(ልኬት) ቅዱሳን መጽሐፍትን በማሰባሰብ ለሰዎች መዳን የሚረዳውን ጸጋ ይሰጥ ዘንድ የሚያስፈልጉትን መጽሐፍት በአንድ ጥራዝ በማድረግ <መጽሐፍ-ቅዱስ> ብላ ሰይማቸዋለች።
የዚህ የመጽሐፍ-ቅዱስ ይዘት ወይም ቀኖናዊ አካሄዶች የተለያዩ ምልከታዎች አሏቸው። እነዚህ ምልከታዎች በቀደመው ቀኖና ማለትም አይሁዳውያን በተቀበሏቸው ከብሉይ ኪዳን 39 በእብራይስጥ ቋንቋ ብቻ የተጻፉትን እንዲሁም ከአዲስ ኪዳን 27 በግሪክ ቋንቋ ብቻ የተጻፉትን በአጠቃላይ 66 መጽሐፍትን የያዘ ሲሆን፥ ከዚህ ቡኃላ ግን በ381ዓ.ም ላይ የቀደመችው የቤተክርስቲያን አባቶች በመሰባሰብ በብሉይ ኪዳን መጽሐፍት ላይ ሌሎች ከእብራይስጥ ቋንቋ ውጪ የተጻፉ 7 መጽሐፍትን በማከል መጽሐፍ-ቅዱስ ከብሉይ 46 እና ከአዲስ 27 በአጠቃላይ 73 መጽሐፍት እንዲሆኑ ደንግጋለች፣ እነዚህ 7 የብሉይ-ኪዳናት መጽሐፍት ድሕረ-ቀኖና(Deuterocanonical) በማለት ይታወቃሉ። ቡኃላ ላይ በ 16ኛው ክ.ዘመን የሪፎርሜሽን ጀማሪው ማርቲን ሉተር በቀደመው የአይሁድ ቀኖና ላይ ብቻ በመስማማት 66 መጽሐፍትን ብቻ የተቀበለ መሆኑን እናውቃለን።
እዚህ ላይ ልብ ማለት ያለብን የድህረ-ቀኖና መጽሐፍት የእግዚአብሔር እስትንፋስ ያለባቸው የአይሁዳውያን የራሳቸው ታሪክ ቢሆንም በኢየሱስ ዘመን እንዲሁም በመጀመሪያይቱ ቤ/ክ ዘመን የነበሩ አይሁዳውያን በራሳቸው ቋንቋ ተጽፈው ስላልተገኙ እንደማይቀበሏቸው ነው።
በአጠቃላይ መጽሐፍ ቅዱስ ሁለት የተለያዩ የማይነጣጠሉ ክፍሎች አሉት፥
1. ብሉይ ኪዳን
2. አዲስ ኪዳን
ብሉይ ኪዳን 39 መጽሐፍቱ 4 ክፍሎች አሉት
A. የህግ መጽሐፍት (ከኦሪት ዘፍጥረት-ዘዳግም 5 መጽሐፍት)
B. የታሪክ መጽሐፍት (ከመ/ኢያሱ-መ/አስቴር 12 መጽሐፍት)
C. የጥበብ መጽሐፍት (ከመ/ኢዮብ - መ/መኃልይ 5 መጽሐፍት)
D. የትንቢት መጽሐፍት (ከት/ኢሳያስ-ት/ሚልክያስ 17 መጽሐፍት)
እንዲሁም 7ቱ የድህረ ቀኖና መጽሐፍት
መጽሐፈ-ጦቢት (የታሪክ መጽሐፍ)
መጽሐፈ-ዮዲት (የታሪክ መጽሐፍ)
1ኛ መ/መቃብያን(የታሪክ መጽሐፍ)
2ኛ መ/መቃብያን (የታሪክ መጽሐፍ)
መጽሐፈ-ጥበብ (የጥበብ መጽሐፍ)
መጽሐፈ ሲራክ (የጥበብ መጽሐፍ)
መጽሐፈ ባሮክ (የትንቢት መጽሐፍ)
አዲስ-ኪዳንም 27ቱ መጽሐፍት 4 ክፍሎች አሉት፡
1. ወንጌላት(የህግ መጽሐፍት) (የማቴዎስ፣የማርቆስ፣የሉቃስ እና የዮሐንስ ወንጌል 4 መጽሐፍት)
2. የሐዋርያት ሥራ(የታሪክ መጽሐፍ 1 መጽሐፍ)
3. አለም-አቀፍ መልዕክቶች (የጥበብ መጽሐፍት ከ ሮሜ-ይሁዳ 21 መጽሐፍት)
4. የዮሐንስ ራዕይ(የትንቢት መጽሐፍ፣ 1 መጽሐፍ)
🖊🖊መጽሐፍ-ቅዱስን እንዴት እናንብብ?
መጽሐፍ-ቅዱስ በእግዚአብሔር መንፈስ ምሪት ከሆነ የተጻፈው ሙሉ መረዳቱንና ለህይወትም የሚሆን ምሪት እናገኝበት ዘንድ በመንፈስ-ቅዱስ ምሪት ሆነን ማንበብ እና ማጥናት ይኖርብናል። ለዚህም የሚረዳን ቅዱሳን መጽሐፍትን እንድንረዳ እና እንዳንስት መጸለይ፣ ኃይል መጠየቅ ይገባናል።(ማቴ 22፥29,፣ ሉቃ 24:45)
እንዲሁም ቃሉ ላይ ጊዜ በመውሰድ ከላይ ባየናቸው ክፍፍሎች ላይ በመመርኮዝ ማጥናት ቀላል ይሆናል።
እንደኔ ግን የአባቴ ልጆች መጽሐፍ-ቅዱስን ለማንበብ እና በህይወት ለመተርጎም 4 ደረጃዎችን ብንጠቀም እመክራለው፦
1. ማንበብ (ቃሉ ወደ እኔ መጣ)
2. ማሰላሰል (የቃሉን ትርጉም መረዳት)
3. መጸለይ (በቃሉ ትርጉም ላይ እኔ የምሰጠው ምላሽ)
a. ይቅርታ መጠየቅ(ከዚህ በፊት ለቃሉ ምላሽ ስላልሰጠሁ)
b. ምስጋና መስጠት(አሁን ግን እድል አግኝቻለው)
c. መንፈስ-ቅዱስን መለመን(ምላሽ ለመስጠት ኃይል እና ፀጋ እንዳገኝ)
4. መመሰጥ (ቃሉ ወደ ልቤ ወረደ፣ የቃሉን መገለጥ የማግኝበት ደረጃ ነው)
5. ማካፈል (በቃል እና በስራ ምስክር መሆን)
ተባርካቹሃል!!!!! የጌታ ጸጋ እና ሰላም ብዝዝዝዝዝት ይበልላችሁ።🙏🏻🙏🏻🙏🏻🙏🏻🙏🏻
ጌታ ኢየሱስ ይወዳቹኃል!!
2ኛ ዙር ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ ሴሚናር
በሞጆ ሱባኤ ሴንተር
ምዝገባ ተጀመረ
#ከነሐሴ_17_እስከ_21
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ቅዳሴ የትምህርት ግዜ የውይይት ግዜ የቅዱስ ቁርባን ስግደት
“የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን አጠገብኸኝ፥ በቀኝህም የዘላለም ፍሥሐ አለ።”
— መዝሙር 16፥11
አዘጋጅ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ካርዝማቲክ እንቅስቃሴ
ከአዲስ አበባ ለምትነሱ 1400
ከክፍለሀገር ለምትመጡ 1000
ለመመዝገብ 0911958019
የ2014 በሞጆ ሱባኤ ሴንተር የሚካሄደው ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ ሴሚናር መሪ ቃል
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
#ታያላችሁ፥ ልባችሁም ሐሤት ታደርጋለች፥ አጥንታችሁም እንደ ለምለም ሣር ትበቅላለች፤ የእግዚአብሔርም እጅ ለሚፈሩት ትታወቃለች፥ በጠላቶቹም ላይ ይቈጣል።
ታያላችሁ፥ ልባችሁም ሐሤት ታደርጋለች፥ አጥንታችሁም እንደ ለምለም ሣር ትበቅላለች፤ የእግዚአብሔርም እጅ ለሚፈሩት ትታወቃለች፥ በጠላቶቹም ላይ ይቈጣል።
#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_ሰሚናር
ከሐምሌ 12 እሰከ ሐምሌ 16
በሞጆ ሱባኤ ሴንተር
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ቅዳሴ የትምህርት ግዜ የውይይት ግዜ
የቅዱስ ቁርባን ስግደት
“ገመድ ባማረ ስፍራ ወደቀችልኝ፥ ርስቴም ተዋበችልኝ።”
— መዝሙር 16፥6
#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_ሰሚናር
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ከሐምሌ 12 እሰከ ሐምሌ 16
በሞጆ ሱባኤ ሴንተር
ቅዳሴ የትምህርት ግዜ የውይይት ግዜ
የቅዱስ ቁርባን ስግደት
“የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን አጠገብኸኝ፥ በቀኝህም የዘላለም ፍሥሐ አለ።”
— መዝሙር 16፥11
#ሕይወት_በመንፈስ_ቅዱስ_ሰሚናር
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥#
ከሐምሌ 12 እሰከ ሐምሌ 16
በሞጆ ሱባኤ ሴንተር
🍀ቅዳሴ የትምህርት ግዜ የውይይት ግዜ
የቅዱስ ቁርባን ስግደት
“የሕይወትን መንገድ አሳየኸኝ፤ ከፊትህ ጋር ደስታን አጠገብኸኝ፥ በቀኝህም የዘላለም ፍሥሐ አለ።”
— መዝሙር 16፥11
አዘጋጅ የኢትዮጵያ ካቶሊክ ካርዝማቲክ እንቅስቃሴ
#12ኛ_ቀን_የፀሎት_ርዕስ
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
በብዙ ረሀብ እና ጥማት ውስጥ ያሉ ሕይወታቸው ምን እንደሚያስፈልገው ላልተረዱ የእግዚአብሔር ነገር ስላልገባቸው በዓለም ሕይወት እየተጎዱ ላሉ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር ገብተው እንዲያርፉ እንፀልያለን።
ኢሳይያስ 55
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁ ኑና ግዙ ብሉም፤ ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅና ወተት ግዙ።
² ገንዘብን እንጀራ ላይደለ፥ የድካማችሁንም ዋጋ ለማያጠግብ ነገር ለምን ትመዝናላችሁ? አድምጡኝ፥ በረከትንም ብሉ፥ ሰውነታችሁም በጮማ ደስ ይበለው።
³ ጆሮአችሁን አዘንብሉ ወደ እኔም ቅረቡ፤ ስሙ ሰውነታችሁም በሕይወት ትኖራለች፤ የታመነችይቱን የዳዊትን ምሕረት፥ የዘላለምን ቃል ኪዳን ከእናንተ ጋር አደርጋለሁ።
ምሽት 3:30 live አብረን በሕብረት እንፀልያለን
እግዚአብሔርን በአንድነት እናመልከዋለን።
#12ኛ_ቀን_የፀሎት_ርዕስ
በብዙ ረሀብ እና ጥማት ውስጥ ያሉ ሕይወታቸው ምን እንደሚያስፈልገው ላልተረዱ የእግዚአብሔር ነገር ስላልገባቸው በዓለም ሕይወት እየተጎዱ ላሉ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር ገብተው እንዲያርፉ እንፀልያለን።
ኢሳይያስ 55
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እናንተ የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁ ኑና ግዙ ብሉም፤ ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅና ወተት ግዙ።
² ገንዘብን እንጀራ ላይደለ፥ የድካማችሁንም ዋጋ ለማያጠግብ ነገር ለምን ትመዝናላችሁ? አድምጡኝ፥ በረከትንም ብሉ፥ ሰውነታችሁም በጮማ ደስ ይበለው።
³ ጆሮአችሁን አዘንብሉ ወደ እኔም ቅረቡ፤ ስሙ ሰውነታችሁም በሕይወት ትኖራለች፤ የታመነችይቱን የዳዊትን ምሕረት፥ የዘላለምን ቃል ኪዳን ከእናንተ ጋር አደርጋለሁ።
#5ኛ_ቀን_የፀሎት_ርዕስ
ሮሜ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና።
…
⁸ ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል።
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
ለመውደድ ምንም አይነት ምክንያት የማያስፈልገው አጋፔ የሆነው የእግዚአብሔር ፍቅር የበለጠ እንዲገለጥልን የእግዚአብሔርን ፍቅር በሙላት እንድንረዳ እንፀልያለን።
በውሎአችን እያሰላሰልን እየፀለይንበት በጌታ ፊት እንሁን። ምሽት 3:00 በአንድ ላይ በቀጥታ እንፀልያለን።
#4ኛ_ቀን_የፀሎት_ርዕስ
“ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።”
— 1ኛ ዮሐንስ 4፥10
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥
በብዙ የኃጢአት ክስ ውስጥ ገብተው የእግዚአብሔርን ምህረትና ፍቅር ለዘነጉ በእግዚአብሔር መውደዳቸውን ለሚጠራጠሩ የኃጢአት ክስ ለሚያስጨንቃቸው እይኖቻቸው እንዲበራ ፍቅሩን መረዳት እንዲሆንላቸው እንፀልያለን።
