Ethiopian Catholic Charismatic
Ir al canal en Telegram
805
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
-130 días
Archivo de publicaciones
#ለአላማ_ተጠርተናል
✅ ሁሉም ክርስቲያን እግዚአብሔር የወሰነለት አላማ በምድርም ላይ የሚፈፅመው ስራ አለው። ከመፈጠራችሁ በፊት አስቀድሞ መርጧችኋል መለኮታው ተልእኮ አዘጋጅቶላችኋል።
[ ወደ ሮሜ ሰዎች 8፥29-30 ]
-----------------
29፤ ልጁ በብዙ ወንድሞች መካከል በኵር ይሆን ዘንድ፥ አስቀድሞ ያወቃቸው የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቀድሞ ደግሞ ወስኖአልና፤
እኛ አድረገን ብለን ወይም ደግሞ መርጠን አይደለም የልጁን መልክ የመሰልነው መልካም የሆነው አባት ምን እንደሚበጀን ስለሚያውቅ ነው። እርሱን እንድንመስል ያደረገን።
30፤ አስቀድሞም የወሰናቸውን እነዚህን ደግሞ ጠራቸው፤ የጠራቸውንም እነዚህን ደግሞ አጸደቃቸው፤ ያጸደቃቸውንም እነዚህን ደግሞ አከበራቸው።
✅ ዳግም በመወለድ የመንግስቱ ወራሾች ተደርገናል። የተዋጀነው በከበረ ደሙ ነው። አስቡት ያዕቆብ በእግዚአብሔር ለመመረጥ ምን አደረገ! በፍፁም ምንም አላደረገም ከመወለዳችው በፊት እግዚአብሔር ያዕቆብን ወደድሁ ኤሳውን ግን ጠላሁ -ሮሜ 9፥13
✅ መልካም ዜና ያዕቆብ የእግዚአብሔር ምርጫ እንደነበረ እኛም እንደዚሁ ነን የሚል ነው። እኛ ባደረግነው ሳይሆን በመለኮታዊ ምርጫ እና ዕድል ነው። ተጠርታችኋል ከዛ በላይ ለአላማ እግዚአብሔር ለኤርምያስ ከመፀነሱ በፊት መመረጡን ነገረው። አኛም ስንፀነስ ጀምሮ በእግዚአብሔር ዓለማ ነው።
<<በሆድ ሳልሠራህ አውቅሃለሁ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።>> [ ኤር 1፥5 ]
✅ ሆኖም ከመወለዱ በፊት ለድህንነት መለየት ብቻ ሳይሆን ለአህዛብ ነብይ ተደርጎ መቀደሱንና መቀባቱን ታያላችሁ። በተመሳሳይ መንገድ እያንዳንዱ ክርስቲያን ለዓላማ ተለይቷል ራዕይ የምንለው ያንን ዓላማ ነው። የአላማ ሰዎች ለምን በምድር ላይ እንዳሉ ያውቃሉ። እኔና እናንተም በዚህ ምድር እግዚአብሔር ያስቀመጠልንን መልካም ስራ ለማድረግ በዓላማ ተፈጠርን።
“እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”
— ኤፌሶን 2፥10
ማንኛውም ሰው እንደሚኖረው ኑሮ ኖረን በፍጹም አናልፍም። ምንም ዋጋ ቢያስከፍል በእግዚአብሔር ፀጋ ራዕያችንን እና ጥሪያችንን አሳክተን እናልፋለን።
#አዋጅ የእግዚአብሔርን ስራ ልሰራ በዓላማ ተፈጥሪያለው ብላችሁ አውጁ!!!
የእግዚአብሔርን ዓላማ ማስፈፀም መመረጥ መታደል ነው።
መልካም የተባረከ ቀን
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#መንፈስ_ቅዱስን
ለመግባት ሲፈልግ አትቃወመው
በልብህ ሲያድር አታሳዝነው
በሕይወትህ ሲሰራ አታዳፍነው
ሊገባ ሲመጣ ክፈትና አስገባው
በልብህ ውስጥ ሲያድር አስደስተው
በአንተም ይሁን በሌላ ሰው ስለ ክርስቶስ ሲያስረዳህ ታዘዘው።
በየዕለቱ በሚኖርህ ሕይወት ደስተኛ እና ሰላማዊ ትሆናለህ።
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#ምዝገባ_ጀምረናል
1ኛ ዙር 2014 ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ ሰሚናር መስከረም 23 ከቀኑ 5:30- 7:00 በጎተራ ዶንቦስኮ ቤተፀሎት ይሰጣል።
ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ መነቃቃት ሰሚናር
ይህ የማነቃቂያ ሰሚናር የተዘጋጀበት ዓላማ አዲስ ነገር ለመፍጠር ሳይሆን ክርስቲያኖች ዳግም በመወለድ ከመንፈስ ቅዱስ የተቀበሉትን ማንነት እና የፀጋ ስጦታዎች በእግዚአብሔር ቃል ተረድተው አኚህን ስጦታዎች በማነቃቃት እና በማደስ በተለወጠ ማንነት እና ሰላማዊ ሕይወት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንዲኖሩ ማስቻል ነው።
ይህ ማነቃቂያ ሰሚናር
1 የተፈጠርንበትን ዓላማ ያሳየናል
2 የቃሉን መረዳት እንድናገኝ ይረዳናል
3 በመንፈስ የሆነ የፀሎት ሕይወት ይሰጠናል
4 የደህንነታችንን ምስጢር ያስረዳናል
5 የምስጢረ ንስሐ ፍሬያማነት ያሳየናል።
6 የመንፈስ ፍሬ እንድናፈራ ይረዳናል።
7 ስጦታዎቻችንን ለይተን እንድናገለግል ይረዳናል።
8 የልቦናችንን ዓይኖች ያበራልናል
ሌሎችም ያልተዘረዘሩ ብዙ ጥቅሞች
“ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ።”
— ሆሴዕ 4፥6
ለመመዝገብ
+251916584487
+251936960959
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#ምዝገባ_ጀምረናል
1ኛ ዙር 2014 ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ ሰሚናር መስከረም 23 ከቀኑ 5:30- 7:00 በጎተራ ዶንቦስኮ ቤተፀሎት ይሰጣል።
ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ መነቃቃት ሰሚናር
ይህ የማነቃቂያ ሰሚናር የተዘጋጀበት ዓላማ አዲስ ነገር ለመፍጠር ሳይሆን ክርስቲያኖች ዳግም በመወለድ ከመንፈስ ቅዱስ የተቀበሉትን ማንነት እና የፀጋ ስጦታዎች በእግዚአብሔር ቃል ተረድተው አኚህን ስጦታዎች በማነቃቃት እና በማደስ በተለወጠ ማንነት እና ሰላማዊ ሕይወት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንዲኖሩ ማስቻል ነው።
ይህ ማነቃቂያ ሰሚናር
1 የተፈጠርንበትን ዓላማ ያሳየናል
2 የቃሉን መረዳት እንድናገኝ ይረዳናል
3 በመንፈስ የሆነ የፀሎት ሕይወት ይሰጠናል
4 የደህንነታችንን ምስጢር ያስረዳናል
5 የምስጢረ ንስሐ ፍሬያማነት ያሳየናል።
6 የመንፈስ ፍሬ እንድናፈራ ይረዳናል።
7 ስጦታዎቻችንን ለይተን እንድናገለግል ይረዳናል።
8 የልቦናችንን ዓይኖች ያበራልናል
ሌሎችም ያልተዘረዘሩ ብዙ ጥቅሞች
“ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ።”
— ሆሴዕ 4፥6
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#ምዝገባ_ጀምረናል
1ኛ ዙር 2014 ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ ሰሚናር መስከረም 23 ከቀኑ 5:30- 7:00 በጎተራ ዶንቦስኮ ቤተፀሎት ይሰጣል።
ሕይወት በመንፈስ ቅዱስ መነቃቃት ሰሚናር
ይህ የማነቃቂያ ሰሚናር የተዘጋጀበት ዓላማ አዲስ ነገር ለመፍጠር ሳይሆን ክርስቲያኖች ዳግም በመወለድ ከመንፈስ ቅዱስ የተቀበሉትን ማንነት እና የፀጋ ስጦታዎች በእግዚአብሔር ቃል ተረድተው አኚህን ስጦታዎች በማነቃቃት እና በማደስ በተለወጠ ማንነት እና ሰላማዊ ሕይወት እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ እንዲኖሩ ማስቻል ነው።
ይህ ማነቃቂያ ሰሚናር
1 የተፈጠርንበትን ዓላማ ያሳየናል
2 የቃሉን መረዳት እንድናገኝ ይረዳናል
3 በመንፈስ የሆነ የፀሎት ሕይወት ይሰጠናል
4 የደህንነታችንን ምስጢር ያስረዳናል
5 የምስጢረ ንስሐ ፍሬያማነት ያሳየናል።
6 የመንፈስ ፍሬ እንድናፈራ ይረዳናል።
7 ስጦታዎቻችንን ለይተን እንድናገለግል ይረዳናል።
8 የልቦናችንን ዓይኖች ያበራልናል
ሌሎችም ያልተዘረዘሩ ብዙ ጥቅሞች
“ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል፤ አንተም እውቀትን ጠልተሃልና እኔ ካህን እንዳትሆነኝ እጠላሃለሁ፤ የአምላክህንም ሕግ ረስተሃልና እኔ ደግሞ ልጆችህን እረሳለሁ።”
— ሆሴዕ 4፥6
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#ጤናማ_መንፈሳዊነት
የሰውነት መብራት ዓይን ናት። ዓይንህ እንግዲህ ጤናማ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፤ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን፥ ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል። እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ፥ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ! (የማቴዎስ ወንጌል 6 : 22-23)
በዚህ አዲስ ዓመት ለራሳችን አንድ ጥያቄ እንጠይቀው መንፈሳዊነቴ ጤናማ ነው አይደለም። መልሱ ሩቅ አይደለም ልባችን አኗኗራችን ድርጊታችን ይመሰክርልናል። ከመልሱ በኋላ ራሳችንን ለመለወጥ እንዘጋጅ።
በሕይወታችን ጤናማነት የጎደለው የትኛውም አይነት ሕይወት መጨረሻው ሀዘን እና ውድቀት ነው። ስለዚህ አስተውለን በሕይወታችን የሚሆነውን ነገር ቆም ብለን ልንረዳ ይገባል። ብዙ ክርስቲያን ሳይቆም የቆመ መስሎታል። ስለዚህ ሕይወታችንን በእግዚአብሔር ቃል አይተን በትክክለኛው ሕይወት ልንመራ ይገባናል።
ጌታ ኢየሱስ ስለ አይንና ስለ መንፈሳዊ እይታ ሲያስተምር አይን የሰውነት መብራት ናት በማለት ገልጿል። ዓይን ጤነኛ ከሆነ ሰውነት ሁሉ ብሩህ ይሆናል። ዓይን ታማሚ ከሆነች ግን ሰውነት ሁሉ የጨለመ ይሆናል።
የስጋ አይን ከሚታየው አለም የመንፈስ አይን ደግሞ ከመንፈስ አለም መልዕክት ይቀበሉና ለአዕምሮ ያስተላልፋሉ። በአይን በኩል ወደ አይምሯችን የሚገባ የትኛውም የምናየው ነገር በጎ አሊያም ጎጂ ተፅዕኖ አለው።አይን ሲያይ ወዲያው አይምሮ በምናየው ነገር ቁጥጥር ስር መሆን ይጀምራል።በዚህ ጊዜ አዕምሮ በአይን በኩል የተቀበለውን ነገር ለማድረግ፣ወይም ለሚያየው ነገር አዎንታዊ/አሉታዊ ምላሽ ለመስጠት ፈጣንና ቀልጣፋ መሆን ይጀምራል።
ስለዚህ ለእይታችን ከፍተኛ ግምት ልንሰጥ ይገባል።መንፈሳዊ እይታችን ምን ይመስላል? አጥርተን እንድናይ የእግዚአብሔር ቃል ተሰጥቶናል ስለዚህ ቃሉን በመጠቀም ጤናማ የሆነ እይታ ልናይ ይገባል።
መልካም የተባረከ ቀን!!!
በክርስቶስ የተወደዳችሁ እናቶች አባቶች እህቱችና ወንድሙች በቅድሚያ 2013 በሰላም አስጨርሱ ወደ 2014 አዲስ የተስፈ አመት ያሻገረን ልዑል እግዚአብሔርን እናመሰግናለን። በመቀጠል የካራዠማቲክ እንቅስቃሴ ንቁ እና ታማኝ አባል ስለሆናችሁ እናመሰግናለን።
በየወሩ ለእንቅስቃሴው በመስጠት እንቅስቃሴዉ በልባችሁ ውስጥ ትርጉም ያለው ቦታ እንዳላዉ እያሳያችሁ ነው።
በየወሩ ለእንቅስቃሴው በምታደርጉት መዋጮ ወንጌልን እንድንሰብክ ፣ ደቀ መዛሙርት እንድናደርግ ፣የማነቃቂያ ,የምስጋና የሱባኤን ፕሮግራሞች እና እርዳታ የሚያስፈልጋቸውንበማኅበረሰባችን ውስጥ ሌሎች እንድንረዳ ያስችለናል። እና በእናንተ የገንዘብ ድጋፍ ለውጥ እያደረጋችሁ ነው።
ስለዚህም ቀጣይነት ያለው ድጋፍዎን ከልብ እናደንቃለን።
ሰለዚህም የመስከረም 2014 ወርሀዊ መዋጮውን በዚሁ በጌታ ፍቅር ለማስታወስ እንወዳለን።
እሁድ በሚደረገው የአመቱ መክፈቻ የምስጋና ፕሮግራም ላይ መዋጮውን በፖስታ ዉስጥ አርገዉ እንዲሁም ስሙትን ፅፈውበት እንዲሰጡ እናሳስባለን። በባንክ ቀጥታ ዲፑዚት ማረግ የምትፈልጉም ይቻላል። የተባረከ ቀን ተባረኩ።
ማቴዎስ 14
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁸ ጴጥሮስም መልሶ፦ ጌታ ሆይ፥ አንተስ ከሆንህ በውኃው ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዘኝ አለው።
²⁹ እርሱም፦ ና አለው። ጴጥሮስም ከታንኳይቱ ወርዶ ወደ ኢየሱስ ሊደርስ በውኃው ላይ ሄደ።
³⁰ ነገር ግን የነፋሱን ኃይል አይቶ ፈራ፥ ሊሰጥምም በጀመረ ጊዜ፦ ጌታ ሆይ፥ አድነኝ ብሎ ጮኸ።
³¹ ወዲያውም ኢየሱስ እጁን ዘርግቶ ያዘውና፦ አንተ እምነት የጎደለህ፥ ስለምን ተጠራጠርህ? አለው።
እንግዲህ ክፍሉን እንዳነበባችሁት ጴጥሮስ ብቻ አልነበረም መርከቡ ላይ የነበረው ሐዋርያት ብቻ እንኳን ከነበሩ 12 ነበሩ ማለት ነው። ዛሬ መርከብ በሆነች ዓለም ላይ እየኖርን ነው። ሁልግዜም ነውጥ አለ ችግር አለ ዋናው ነገር ግን ቁጭ ብለን እያየን ነው? ታዛቢ ነን? ወይስ በችግር ላይ ተራማጅ ነን? እንግዲህ በዚህ ዘመን ቁጭ ብሎ አስተያየት ሰጪ ፣ ተቺ፣ ነቃፊ የበዛበት ዘመን ነው። ሚዲያው በሙሉ ሀሳብ ሰጪ በዝቶበታል አዋቂ ነን ባይ በዝቷል። በችግር ላይ የሚራመዱ ተግባራዊ ሰዎች ይህች ምድር በናፍቆት እና በጉጉት ትጠብቃለች። እኔን ፣ አንተን ፣ አንቺን። መርከብ ላይ ከነበሩት የተራመደው አንድ ሰው የዚህ ዘመን አንተ ነህ አንቺ ነሽ።
ስለዚህ እኛም ዛሬ መርከብ ላይ እንደቀሩት ተመልካች እና ሀሳብ ሰጪ መሆኑን ትተን ጌታን አይተን በችግር ላይ ለመራመድ ደፋር ልንሆን ይገባል። እድለኛ ትውልድ እኛ ነን ስለዚህ ዛሬ ቆርጠን በእምነት እርምጃ መጀመር አለብን። ጳውሎስና ጴጥሮስ በዘመናቸው የሚጠበቅባቸውን አድርገው አልፈዋል። የዘመኑ ጴጥሮስ ጳውሎስ እኛ ነን። ዘመኑ እኛን ይጠብቃል። የክርስቶስ ወታደሮች ተነሱ በውሀ ላይ መራመድ እንጀምር።
ቤተክርስቲያንም ሀገራችንም የሚያወራ ሳይሆን እውነተኛ የተግባር እና የለውጥ ሰዎች ትፈልጋለች።
2014 በውሀ ላይ የመራመድ ዘመን ይሁንልን መልካምን አድራጊ በጎ ተፅእኖ ፈጣሪዎች ይብዙልን።
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
#የኢትዮጵያ_ካቶሊክ_ካርዝማቲክ_እንቅስቃሴ
ያለፈውን ዓመት ሸኝተን አዲሱን ዓመት ስንቀበል በዚህም ዓመት ብዙ ኃላፊነቶችን እንድንወጣ ነው።
“እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።” — ኤፌሶን 2፥10
ከብዙ በጥቂቱ
1 ካለፈው ዓመት በተሻለ መልኩ በግልም ሆነ በሕብረት የምንሰራበት
“ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና።”
— ፊልጵስዩስ 2፥13
2 የጀመርናቸውን አገልግሎቶች አጠናክረን የምንቀጥልበት
“በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤”
— ፊልጵስዩስ 1፥6
3 የአባላቶቻችንን ሕይወት በትኩረት የምንከታተልበት
“በእናንተ ዘንድ ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በውድ እንጂ በግድ ሳይሆን፥ በበጎ ፈቃድ እንጂ መጥፎውን ረብ በመመኘት ሳይሆን ጐብኙት፤”— 1ኛ ጴጥሮስ 5፥2
4 ጠንካራ እና ጤናማ አገልጋዮችን በብዛት የምናፈራበት
“አላቸውም፦ መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ለመከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት።”
— ሉቃስ 10፥2
5 የፀጋ ስጦታ አገልግሎቶች በይበልጥ የሚገለጡበት
“የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤”— 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥4
6 የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ቡድኖች ተጠናክረው የሚቀጥሉበት።
“የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ፤— ቆላስይስ 3፥16
ብዙ እቅዶችን ይዘን ዓመቱን
በእምነት: በደስታ: በፍቅር: ጀመርን
“እኔም መልሼ፦ የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን— ነሀምያ 2፥20
https://t.me/eccrm
#የኢትዮጵያ_ካቶሊክ_ካርዝማቲክ_እንቅስቃሴ
ከብዙ በጥቂቱ
ያለፈውን ዓመት ሸኝተን አዲሱን ዓመት ስንቀበል በዚህም ዓመት ብዙ ኃላፊነቶችን እንድንወጣ ነው።
“እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።” — ኤፌሶን 2፥10
1 ካለፈው ዓመት በተሻለ መልኩ በግልም ሆነ በሕብረት የምንሰራበት
“ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና።”
— ፊልጵስዩስ 2፥13
2 የጀመርናቸውን አገልግሎቶች አጠናክረን የምንቀጥልበት
“በእናንተ መልካምን ሥራ የጀመረው እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ድረስ እንዲፈጽመው ይህን ተረድቼአለሁና፤”
— ፊልጵስዩስ 1፥6
3 የአባላቶቻችንን ሕይወት በትኩረት የምንከታተልበት
“በእናንተ ዘንድ ያለውን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በውድ እንጂ በግድ ሳይሆን፥ በበጎ ፈቃድ እንጂ መጥፎውን ረብ በመመኘት ሳይሆን ጐብኙት፤”— 1ኛ ጴጥሮስ 5፥2
4 ጠንካራ እና ጤናማ አገልጋዮችን በብዛት የምናፈራበት
“አላቸውም፦ መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ለመከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት።”
— ሉቃስ 10፥2
5 የፀጋ ስጦታ አገልግሎቶች በይበልጥ የሚገለጡበት
“የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤”— 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥4
6 የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ቡድኖች ተጠናክረው የሚቀጥሉበት።
“የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ፤ በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ፤— ቆላስይስ 3፥16
ብዙ እቅዶችን ይዘን ዓመቱን
በእምነት: በደስታ: በፍቅር: ጀመርን
“እኔም መልሼ፦ የሰማይ አምላክ ያከናውንልናል፥ እኛም ባሪያዎቹ ተነሥተን እንሠራለን— ነሀምያ 2፥20
https://t.me/eccrm
#የኢትዮጵያ_ካቶሊክ_ካርዝማቲክ_እንቅስቃሴ
“እግዚአብሔር ታላቅ ነገርን አደረገልን፥ ደስም አለን።”
— መዝሙር 126፥3
እንኳን ደስ ያለን 2013 በስኬት እና በድል አለፍነው።
2013 ከእቅዳችን በላይ እግዚአብሔር አደረገልን።
ብዙ ምርኮ የሰበሰብንበት ዓመት
ብዙ አገልጋዮች ያገኘንበት ዓመት
ብዙ ለጋሶችን ያገኘንበት ዓመት
ሙሉ ሳውንድ ሲስተም የገዛንበት ዓመት
በልዩነት የተገለጥንበት ዓመት ነበር
የቱን ተናግረን የቱን እንተወው
ብቻ እግዚአብሔር ይመስገን።
ታላቅ ነገር ሆነ። እልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልልል👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏👏
2014 በትልቅ ድል ምርኮ በምርኮ የምንሆንበት የመንፈስ ቅዱስ ኃይል የሚገለጥበት ልዩ ዓመት ሆነልን በኢየሱስ ስም!!!
https://t.me/eccrm
https://t.me/eccrm
