cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegaciĂłn. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

🇪🇹Ethiopia🇪🇹🇪🇹 News🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

True Breaking News

Mostrar mĂĄs
El paĂ­s no estĂĄ especificadoEl idioma no estĂĄ especificadoLa categorĂ­a no estĂĄ especificada
Advertising posts
153Suscriptores
Sin datos24 hours
Sin datos7 days
Sin datos30 days

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ዶ/ር አብርሃም በላይ ለኢድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረችሁ መልዕክት አስተላለፉ --------------------------------- ግንቦት 05/2013 (ዋልታ) - የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር አብርሃም በላይ ለህዝበ ሙሰሊሙ እንኳን ለ1ሺህ 442ኛው የኢድ አልፈጥር በአል በሰላም አደረሳችሁ ብለዋል። ይህን በአል ስናከብር አንድነታችን ይበልጥ የምናጠናክርበትና በተለያዩ ቦታዎች የተፈናቀሉ ወገኖች የምናግዝበት በአል ሊሆን ይገባል ብለዋል። በተጨማሪም የተቸገረን በመርዳትና በመተሳሰብ መሆን አለበት ብለዋል ዶ/ር አብርሃም በላይ በመልእክታቸው፡፡
Mostrar todo...
ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለኢድ አልፈጥር በዓል የእንኳን አደረችሁ መልዕክት አስተላለፉ ------------------------- ግንቦት 05/2013 (ዋልታ) -ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ለ1ሺህ 442ኛው ዓመተ ሂጅራ የኢድ ዓልፈጥር በዓል እንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዚዳንቷ በትዊተር ገጻቸው ላይ ለመላው ሙስሊም ኢትዮጵያውያን እንኳን ለኢድ አል ፈጥር በዓል በደህና አደረሳችሁ ብለዋል። በዓሉን በቤታቸው ለማክበር ዕድሉን ያላገኙትን ወገኖቻችንን በማስታወስ ፣ በመደገፍና ያለንን በማካፈል ልናከብር ይገባል ብለዋል ። በዓሉ የሰላምና የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል፡፡
Mostrar todo...
ብሔራዊ ቡድኑ የማበረታቻ ሽልማት እና እውቅና ሊበረከትለት ነው -------------------------------------------- ግንቦት 04/2013 (ዋልታ) - የኢትዮጵያ ወንድ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ከ8 አመት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን ተከትሎ በመንግስት እና በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አማካኝነት የእውቅና እና ሽልማት ሊበረከትለት መሆኑን የኢፌዴሪ ስፖርት ኮሚሽን ኮምሽነር አቶ ኤሊያስ ሽኩር እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በጋራ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስታወቁ፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉን ተከትሎ በወቅቱ በተለያዩ ምክንያቶች የሽልማት እና የማበረታቻ ፕሮግራም ባይካሄድም የሀገራችን ህዝቦች በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች አደባባይ በመውጣት በከፍተኛ ድምቀት የጀግና አቀባበል በማድረግ ደስታቸውን እንደገለፁ ኮምሽነሩ በመግለጫቸው አንስተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ወንዶች እግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን ለ33ኛው የአፍሪካ ዋንጫ በማለፉ ሀገርንና ህዝብን በማኩራታቸው እና በቀጣይ ባለው አፍሪካ ዋንጫም ሆነ በሌሎች ውድድሮች ላይ ተፎካካሪ ሆኖ እንዲቀርብ የዝግጅት ስራ ለመስራት ዓላማ ተደርጎ የተዘጋጀ ፕሮግራም እንደሆነ ታውቋል፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፉ ለስፖርቱ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ፣ መነቃቃትን የፈጠረ ቢሆንም ቀጣይነት እንድኖረው ታዳጊ ወጣቶች ላይ መስራት እና ኤሊት ስፖርተኞችን በጥራትና በስፋት ማዘጋጀት ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ የገለፁት ኮምሽነሩ ብሄራዊ ቡድኑ ቀጣይ ባሉት ውድድሮች ላይ ጠንካራ እና ተፎካካሪ እንዲሆን የወዳጅነት ጨዋታዎችን ጨምሮ ሀብት ተመድቦ ... https://www.facebook.com/489211707826282/posts/4275772712503477/
Mostrar todo...