es
Feedback
የደብረ ምህረት ቅድስት ድንግል ማርያም እና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት

የደብረ ምህረት ቅድስት ድንግል ማርያም እና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት

Ir al canal en Telegram

👉የቦንጋ ደ/ም/ቅ/ድ/ማርያም እና አ/ገ/መንፈስ ቅዱስ ቤ/ን ሰንበት ት/ቤት አባላት እና ምዕመናን የቴሌግራም ቻናል ነው። 👉በውስጡ የተለያዩ ስርዓተ ቤተ ክ/ን የጠበቁ ትምህርቶች፣ዝማሬዎች፣ስነፅሁፎች እና ወቅታዊ መረጃዎች ይቀርቡበታል። 👉በተጨማሪም ለተጋቢ ሙሽሮች ደረጃውን የጠበቀ ካባ በተመጣጣ ዋጋ እናከራያለን። 👉ሀሳብ ጥያቄ እና አባል መሆን ከፈለጋችሁ @debremhiret👈ያግኙን

Mostrar más
427
Suscriptores
Sin datos24 horas
+37 días
+2130 días

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
enero '25
enero '25
+16
en 0 canales
diciembre '24
+29
en 0 canales
Get PRO
noviembre '24
+67
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+49
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+1
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+3
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+9
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+18
en 0 canales
Get PRO
mayo '24
+276
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
16 enero+1
15 enero+1
14 enero0
13 enero0
12 enero0
11 enero+1
10 enero+2
09 enero+2
08 enero+3
07 enero+1
06 enero+1
05 enero+1
04 enero+2
03 enero0
02 enero+1
01 enero0
Publicaciones del Canal
ቀረ'ባት¡ በኤፍራታ በጎል በከብቶች በረት የጌቶችን ጌታ የአለምን መድኃኒት የተናገሩለት ነቢያት በትንቢት የአማልክትን አምላክ  ወለደችው በእውነት አልፋና ኦሜጋ ያለ'ና የነበረ ከአለም ፍጥረት በፊት ህያው ሆኖ የኖረ አዳምን ለማዳን ዘመን አስቆጠረ ብስራታዊው መልዓክ ሄደ እየበረረ የጌታን መወለድ ለእረኞች ነገረ። እነርሱም በደስታ ሄደው ሰገዱለት ከመላዕክት ጋራ ሆነው ዘመሩለት በሰማይ መላዕክት ታላቅ ደስታ ሆነ ሰላምም በምድር ለሰው ልጅ ሰፈነ ይገርማል! ኧረ እንዴት ያለ ነው አምላክ ሰው መውደዱ በከብቶች ማደርያ ግርግም መወለዱ ምን አይነት ፍቅር ነው ምን አይነት ትህትና የኃያላን ኃያል ህፃን ሆኗልና እንደምን ቢወደን እንዴት ቢያፈቅረን ነው በጨርቅ ተጠቅልሎ ከግርግም የተኛው ያ'ማኑኤል እናት! አሁንም እንጠይቅሽ! መልሱ በልብሽ ነው ቢሆንም እንጠይቅሽ! የፍጠረቱን እንባ የሚያብስን ጌታ እሹሩሩ ስትይው ያለቀሰ 'ለታ አለምን የጨበጠውን በእጆችሽ ስታቅፊው መጋቢውን ጌታ ጡትሽን ስታጠቢው እንዴት ነበር ድንግል ፈጣሪን ስትወልጂው እንዴት ነበር! አእላፍ መላዕክት ዝማሬን ሲያሰሙ ሰሎሜና ዮሴፍ ያኔ ሲደመሙ ላ'ምላክ ሲዘምሩ እረኛች በደስታ ሰብአ ሰገል መጥተው ሲያቀርቡ ስጦታ ምን አሰበ ልብሽ ድንግል የዚያን 'ለታ ምን አሰበ?... ግሩም ነው እኮ! ጥልቅ ነው ይህ ምስጢር ከቶ ማይነገር ማርያም ግን በልቧ ትጠብቀው ነበር እፁብ እንላለን እኛም በትህትና የአብ ልጅ እግዚአብሔር ከኛ ጋር ነውና አዳምን ከአሳሩ ሊያድነው ወደደ ፍቅር አስገድዶት ከሰማይ ወረደ ረቂቁ አምላክ ስጋን ተዋሀደ አማኑኤል ጌታ ዛሬ ተወለደ ዲያቢሎስ አፈረ ጠላት ተዋረደ ጥልቅ ነው ይህ ምስጢር ከቶ ማይነገር ማርያም ግን በልቧ ትጠብቀው ነበር።!!!! <<ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ በልቧ እያሰበች ትጠብቀው ነበር።>> ሉቃ2፥19 👉ታህሳስ 23/24-2015 ዓ.ም ተጻፈ ✍በደብረ ምህረት ቅድስት ማርያም እና አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ(የተጻፈ)    •➢ ሼር // SHARE      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret

2
ልዩ የልደት(የገና) በዓል ግጥም 🌿ማርያም ግን በልቧ ትጠብቀው ነበር።!!!🌿 መፈጸሚያው ሲደርስ ተስፋቸው የአበው እግዚአብሔር ከሰማይ ገብርኤልን ላከው ደስተኛው መልአክ ምስራቹን ይዞ ወደ ማርያም
ልዩ የልደት(የገና) በዓል ግጥም 🌿ማርያም ግን በልቧ ትጠብቀው ነበር።!!!🌿 መፈጸሚያው ሲደርስ ተስፋቸው የአበው እግዚአብሔር ከሰማይ ገብርኤልን ላከው ደስተኛው መልአክ ምስራቹን ይዞ ወደ ማርያም መጣ ከአምላኩ ታዞ 'ያለምን መድኃኒት የጌቶችን ጌታ ትፀንሻለሽ አላት በፍፁም ደስታ በእርጋታ ሆና ድንግልም ሰማችው <<እንደምን ይሆናል>> ብላ ጠየቀችው ማስረዳት ቢከብደው ይህን ታላቅ ምስጢር <<እስመ አልቦ ነገር ዘይሰዓኖ ለእግዚአብሔር>> ብሎ ንግግሩን ገብርኤል ፈጸመው ቸሩ እግዚአብሔርን የለም የሚሳነው አሁንም በእርጋታ ሆና ሰማችና "እነሆኝ የጌታ ባርያ ይሁንልኝ" አለች ድንግል በትህትና ይህን ጊዜ ነበር ቃል የተፀነሰው የሰው ለጆች ድህነት ጅማሮው የሆነው። እንጠይቃት እስኪ ይቺን ብላቴና ሰማይ ያልቻለውን ችላዋለችና ድንግል ሆይ! የመለኮት እሳት ባደረብሽ ጊዜ እንዴት አላቃጠለሽ ልብሱ ቀሚሱ እሳት እንደምን አልፈጀሽ የ'ሳት መጋረጆች በየት ተከለሉ ሰባቱ ብርሀናት ወዴት ተተከሉ ነገደ ኪሩቤል እሳታዊያኑ 'ሚሸከሙት ዙፋን ወዴት ነው በውኑ ከጠባቡ ሆድሽ በግራ ነውን ወይንስ በሌላኛው በቀኝሽ ይሆን ማርያም ሆይ! ከስፋትም ጋራ የሆድሽ መጥበብ ከድንግልና ጋር አንድ የሆነ ሀሊብ የመፅነስሽን ነገር እንዴት እንለፈው እንግዳ ነው ለኛ ሰምተን የማናውቀው _እንዴት እንለፈው? ባ'ንቺ እኮ ነው ድንግል ቃል ስጋ የለበሰው አባ ህርያቆስ እንኳ ያልቻለውን ምስጢር ምን ቃላት አምጥጠን ስላንቺ እንናገር ማርያም ግን! በልቧ ጠብቃው ይህን ታላቅ ምስጢር ወደ ቤተልሔም ሄደች ልትቆጠር ምድረ ቤተልሔም በእንግዶች ተሞልታ ለድንግል ማርያም ግን የለም አለች ቦታ ቀረ'ባት¡ ......ይቀጥላል
459
3
🌿ድንግል ሆይ🌿 ወደ አንቺ መጥቶ "ጸጋን የተሞላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ" ያለሽ መልአክ ዛሬም ወደ እኔ ይምጣ...... (የብርሃን እናት ከተሰኘው መጽሐፍ) ✍ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ •➢ ሼር // SHAR
🌿ድንግል ሆይ🌿 ወደ አንቺ መጥቶ "ጸጋን የተሞላሽ ሆይ ደስ ይበልሽ" ያለሽ መልአክ ዛሬም ወደ እኔ ይምጣ...... (የብርሃን እናት ከተሰኘው መጽሐፍ) ✍ዲያቆን ሄኖክ ሃይሌ     •➢ ሼር // SHARE      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret
504
4
እናቴ ፳፩ "ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አ
እናቴ ፳፩ "ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ ኅብስትን የተመገብሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ኅብስትን ነው እንጂ፤ ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም፤ ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን ነው እንጂ፤ ድንግል ሆይ ከአንቺ አስቀድሞ ከአንቺም በኋላ እንዳሉ ሴቶች መተዳደፍን የምታውቂ አይደለም፤ በንጽሕና በቅድስና ያጌጥሽ ነሽ እንጂ፤ ድንግል ሆይ የሚያታልሉ ጐልማሶች ያረጋጉሽ አይደለም የሰማይ መላእክት ጐበኙሽ እንጂ እንደተነገረ ካህናትና የካህናት አለቆች አመሰገኑሽ እንጂ....." (አባ ሕርያቆስ - ቅዳሴ ማርያም)     •➢ ሼር // SHARE      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret
469
5
እናቴ ፳፩ " ድንግል_ሆይ ! በበደል ምሳር የማትቆረጪ ከኃጢኣት አውሎ ነፋስ የተነሣ የማትነዋወጪ ዘወትር ፍጹም የምትለመልሚ በዘመኑ ኹሉ የምታፈሪ በወሮች ኹሉ የምትለቀሚ ከእጽዋት ኹሉ ይልቅ የምታም
እናቴ ፳፩ " ድንግል_ሆይ ! በበደል ምሳር የማትቆረጪ ከኃጢኣት አውሎ ነፋስ የተነሣ የማትነዋወጪ ዘወትር ፍጹም የምትለመልሚ በዘመኑ ኹሉ የምታፈሪ በወሮች ኹሉ የምትለቀሚ ከእጽዋት ኹሉ ይልቅ የምታምሪ እመቤቴ ማርያም ኾይ የተባረክሽ ዕፅ ነሽ።" ✍አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ እናቴ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም ክብር ላንቺ ይሁን ። የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን አማላጅነቷ አይለየን :: መልካም ቀን ተመኘን     •➢ ሼር // SHARE      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret
367
6
#ገብርኤል የንጉስ ጭካኔ ፥ ክንዱ ቢበረታ፤ ለጣዖት ሳንሰግድ፥ እኛ ሳንረታ፡፡ የምናምነው አምላክ፥ ሊያድነን ወደደ፤ ገብርኤል መጣና፥ እሳቱ በረደ፡፡ ፤ ፍላፃና ሠይፉን፥ አጠፈው መላኩ፤ ሰላም ይዞ
#ገብርኤል የንጉስ ጭካኔ ፥ ክንዱ ቢበረታ፤ ለጣዖት ሳንሰግድ፥ እኛ ሳንረታ፡፡ የምናምነው አምላክ፥ ሊያድነን ወደደ፤ ገብርኤል መጣና፥  እሳቱ በረደ፡፡ ፤ ፍላፃና ሠይፉን፥ አጠፈው መላኩ፤ ሰላም ይዞ መጣ፥ ባለም ለታወኩ፡፡ አትጠራጠሩ፥ ምልጃው ያስምረናል፤ የሚነደው እሳት፥ ሳይነካን ወተናል፡፡ ፤ የሰልስቱ ደቂቅ፥ የእጠሉጣ ብርታት፤ የድንግል አብሳሪ፥ የቂርቆስ ረዳት፡፡ በሚመጣው አለም፥ እንዳይበላኝ እሳት፤ አማልደኝ ከጌታ፥ ነፍሴን እንዲምራት፡፡ ፤ የነገርኩህ ሁሉ፥ በቀኑ ደረሰ ፤ በዘብር ገብርኤል፥ እንባዬ ታበሰ፡፡ ና ልጄ ስትለኝ፥ አልልህም እንቢ፤ ስለቴን ተቀበል፥ አባቴ ቁልቢ፡፡ ፤ የልቤን ነግሬህ፥ የቁልቢው ገብርኤል፤ ሳትረሳ ፈፀምከው፥ ስለቴን  ተቀበል፡፡ ለንግስ እንመጣለን፥ አንተ አትረሳምና፤ ደሞ የዛሬ አመት፥ አድርሰን በደህና፡፡ +++++++     •➢ ሼር // SHARE      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret
428
7
🌿እንኳን ለሊቀ መለአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!🌿 እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ። ሉቃስ 1:19 "በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩት ብ
🌿እንኳን ለሊቀ መለአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!🌿 እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ። ሉቃስ 1:19 "በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩት ብርሀንን የገለፀና የሰበከ ይህ ገብርኤል ነው" ድርሳነ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልዕኮ አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን (ሠለስቱ ደቂቅን) ከእቶነ እሳት ያደነው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል፣ እመቤታችን አምላክን እንደምትወልድ ታላቁን የምሥራች ያበሰረው፣ በባቢሎን ምርኮ የነበረውን ስለ ሕዝቡ የሚያለቅሰውን የነቢዩ ዳንኤልን የጸሎት መልስ ይዞ የመጣው፣ ራእዩንም ያብራራለት ቅዱስ ገብርኤል ካለንበት ችግር እንድንወጣ ከገጠመን ፈተና እንድናልፍ የመወጫ መንገድ ያሳየን ሀገራችንንም ካለችበት ችግር ያውጣልን። በምልጃው አይለየን አሜን።🙏 መልካም በዓል     •➢ ሼር // SHARE      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret      🔸 @yedebremhret
367
8
#ሊቀ_መላእክት_ቅዱስ_ገብርኤል (#ታኅሣሥ_19) ታኅሣሥ ዐስራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅ ያዳነበት ነው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር ከአባታቸው ከይሁዳው ንጉሥ ከኢዮአቄም ጋር የማረካቸው አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ እግዚአብሔር በዚህች ዕለት መልአኩን ልኮ ታላቅ ተአምር አድርጎላቸዋል፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ጥበብን እያስተማረ ካሳደጋቸው በኋላ በባቢሎን ሀገሮች ሁሉ ውስጥ ሾማቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ ለዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ ለጣዖቱ ባለመስገድ እግዚአብሔርን ብቻ በማምለክ የጸኑት እነዚህ ሦስት ወጣቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ስለ እነርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡- ‹‹ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፡፡ ንጉሡም ናቡከደነፆር መኳንንትንና ሹማምቶችን፥ አዛዦችንና አዛውንቶችን፥ በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን፣ መጋቢዎችንም፣ አውራጃ ገዦችንም ሁሉ ይሰበስቡ ዘንድ፣ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፡፡ በዚያን ጊዜም መኳንንቱና ሹማምቶቹ፣ አዛዦቹና አዛውንቶቹ፣ በጅሮንዶቹና አማካሪዎቹ፣ መጋቢዎቹና አውራጃ ገዦቹ ሁሉ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ተሰበሰቡ፤ ናቡከደነፆርም ባቆመው ምስል ፊት ቆሙ፡፡ አዋጅ ነጋሪውም እየጮኸ እንዲህ አለ፡- ‹ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ! የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፣ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል፡፡ ተደፍቶም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል፡፡› ስለዚህ በዚያን ጊዜ አሕዛብ ሁሉ የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ፣ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የተናገሩ ሁሉ ተደፉ፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ሰገዱ፡፡ በዚያን ጊዜም ከለዳውያን ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፡፡ ለንጉሡም ለናቡከደነፆር ተናገሩ እንዲህም አሉ ‹ንጉሥ ሆይ! ሺህ ዓመት ንገሥ፡፡ አንተ ንጉሥ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ የሚሰማ ሰው ሁሉ ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ይስገድ፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል ብለህ አዘዝህ፡፡ በባቢሎን አውራጃ ሥራ ላይ የሾምሃቸው ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም የሚባሉ አይሁድ አሉ፤ ንጉሥ ሆይ! እነዚህ ሰዎች ትእዛዝህን እንቢ ብለዋል፤ አማልክትህን አያመልኩም፥ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል አይሰግዱም፡፡› ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ያመጡ ዘንድ አዘዘ፤ እነዚህንም ሰዎች ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው፡፡ ናቡከደነፆርም ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ሆይ! አምላኬን አለማምለካችሁ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን? አሁንም የመለከቱንና የእንቢልታውን የመሰንቆውንና የክራሩን የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ ተደፍታችሁ ላሠራሁት ምስል ብትሰግዱ መልካም ነው፤ ባትሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው?›› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡን ‹ናቡከደነፆር ሆይ! በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም፡፡ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ! እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ› አሉት፡፡ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፡፡ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፡፡ እርሱም ተናገረ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት አዘዘ፡፡ ሲድራቅንና ሚሳቅንም አብደናጎንም ያስሩ ዘንድ ወደሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ፡፡ የዚያን ጊዜም እነዚህ ሰዎች ከሰናፊላቸውና ከቀሚሳቸው ከመጐናጸፊያቸውም ከቀረውም ልብሳቸው ጋር ታስረው በሚነድድ በእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ፡፡ የንጉሡም ትእዛዝ አስቸኳይ ስለሆነ የእቶኑም እሳት እጅግ ስለሚነድድ፣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም የጣሉአቸውን ሰዎች የእሳቱ ወላፈን ገደላቸው፡፡ እነዚህም ሦስቱ ሰዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ታስረው በሚነድደው በእቶኑ እሳት ውስጥ ወደቁ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም ‹ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን?› ብሎ ተናገራቸው፡፡ እነርሱም ‹ንጉሥ ሆይ! እውነት ነው› ብለው ለንጉሡ መለሱለት፡፡ እርሱም ‹እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል› ብሎ መለሰ፡፡ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ ‹እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም! ኑ ውጡ› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ፡፡ መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፣ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፣ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ፡፡ ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ፡፡ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፣ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ› አለ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡›› ትንቢተ ዳንኤል 3፡1-30፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በመልአኩ አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ( ስንክሳር ዘተዋሕዶ ) ለተዋሕዶ ልጆች👇                 •➢ ሼር // SHARE      🔸 @yedebremhret 🔸 @yedebremhret 🔸 @yedebremhret
364
9
ተወዳጆች እግዚአብሔርን እንደ ማመስገን ምንም በጎ ነገር የለም፡፡ የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ እንደ ማንሣትም (እንደ ማማረርም) ምንም ክፉ ነገር የለም፡፡ ✅መንፈሳዊ ነገሮችን ማድረግ ስናበዛ መከራ
ተወዳጆች እግዚአብሔርን እንደ ማመስገን ምንም በጎ ነገር የለም፡፡ የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ እንደ ማንሣትም (እንደ ማማረርም) ምንም ክፉ ነገር የለም፡፡ ✅መንፈሳዊ ነገሮችን ማድረግ ስናበዛ መከራው ቢበረታብን ምንም ልንደነቅ አይገባንም፡፡ ✅ሌቦች ወርቅና ብር ያለውን እንጂ ድርቆሽና ገለባ እንዲሁም ሰንበሌጥ ያለውን ቤት አይበረብሩምና፡፡ ዲያብሎስም የሚያጠቃው መንፈሳዊ ምግባራትን የሚያበዙትን ሰዎች ነው፡፡ በጎ ምግባር ባለበት ኹሉ ብዙ ወጥመዶች አሉ! ቸርነት ባለበት ቅንአት አለ! ✅ እነዚህን ኹሉ ከንቱ የሚያደርግ አንድ ፍቱን የጦር ዕቃ መሣሪያ ግን አለ፤ ስለ ኹሉም ነገር እግዚአብሔርን ማመስገን! ✍ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 🌈ቀናችንን በምስጋና እንጀምር 🙏ሰናይ ቀን Channel group @yedebremhret @bdebremhret
514
10
ስሜት ወረተኛ ፍቅረኛ ማለት ነው ..... ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም ሰናይ ጊዜ🙏
ስሜት ወረተኛ ፍቅረኛ ማለት ነው ..... ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም ሰናይ ጊዜ🙏
393
11
በንስሐ ሕይወት ለመኖር የምንሻ ከሆነ ለወደቅንበት ኃጢአት ምክንያት መደርደርና ለራሳችን ይቅርታን ለመስጠት መሞከር የለብንም። ኃጢአትን ከፈጸሙና ከሠሩ በኋላ ለኃጢአት ያበቃ ሌላ ምክንያት ማቅረብና
በንስሐ ሕይወት ለመኖር የምንሻ ከሆነ ለወደቅንበት ኃጢአት ምክንያት መደርደርና ለራሳችን ይቅርታን ለመስጠት መሞከር የለብንም። ኃጢአትን ከፈጸሙና ከሠሩ በኋላ ለኃጢአት ያበቃ ሌላ ምክንያት ማቅረብና በዚያም አንፃር ለመጽናናት መሞከር በራሱ ኃጢአት ነው። በዚህ አይነት ለኃጢአቱ ምክንያት እየደረደረ የሚጽናና ሰው ኃጢአትን እየለመደ ወደ ባሰ አዘቅት ከመውረድ በቀር ንስሐ ለመግባት አይችልም። ምንም ምክንያት ቢደረድር ኃጢአት ምን ጊዜም ኃጢአት ነውና። ለሠራነወ ኃጢአት የተለያዩ ምክንያቶችን በማበጀት ራሳችንን እያጽናናን ነፃ ለመሆን መጣር የለብንም ። ስለ ሰሩት ኃጢአት ምክንያትን የደረደሩ አዳምና ሔዋንም ባቀረቡት ምክንያት ከመቀጣት አልዳኑም ። እግዚአብሔርም አዳም ስለ አቀረበው ምክንያት "የሚስትህን ቃል ሰምተኻልና ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዘዝኩህ ዛፍም በልተኻልና " በማለት ለኃጢአቱ የሚገባውን ቅጣት ሰጠው እንጂ አልተወውም። [ዘፍ3፥17] ይባስ ብሎ በእነርሱ ምክንያት በመጣው መርገም ቅጣቱ በትውልዳችን ሁሉ ሆነ እንደ እነርሱ ሁሉ እኛም ዘወትር ምክንያት በመደርደር ከኃጢአታችን የተነሣ ከሚመጣው ቅጣት ለማምለጥ የምንሞክር ሆንን ስለዚህ ንስሐ ለመግባት በጣም ስንቸገር እንታያለን ። አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ 👉የተወደዳችሁ ከዚህ በኋላ በግሩፑ ከመጻህፍት የተመረጡ ጽሁፎችን በቻልን መጠን እናጋራችኋለን
504
12
https://www.youtube.com/live/EOE07cxv8zo?si=hKOHMsR3XwlxcPP5
296
13
ጉባኤውን በቀጥታ ስርጭት መከታተል የምትፈልጉ በዚህ channel 👉@yedebremhret በሚለው ስር ባለው ሊንክ ገብታችሁ እንድትከታተሉ አስቀምጠንላችኋል ኦርቶዶክሳዊያን☝☝☝☝☝
739
14
https://www.youtube.com/live/2ld8xE-mBLE?si=b9IoSZOvnpf5f535
224
15
🌿የሚገርም ልዩ አቀባበል!🌿 እጅግ ደግሞ አስደማሚ ጉባኤ ነበር።🥰 የናታኔም የወጣቶች ማህበር አባላት እና የከተማው ምርጥ ሾፌሮች ላሳያችሁን ፍቅር የእመቤታችን ልጅ በሰማይ ያክብራችሁ።🙏🙏🙏+4
🌿የሚገርም ልዩ አቀባበል!🌿 እጅግ ደግሞ አስደማሚ ጉባኤ ነበር።🥰 የናታኔም የወጣቶች ማህበር አባላት እና የከተማው ምርጥ ሾፌሮች ላሳያችሁን ፍቅር የእመቤታችን ልጅ በሰማይ ያክብራችሁ።🙏🙏🙏 ነገም ከነገ ወዲያም አብረን እንዳማረብን እንቀጥላለን😍 የነገ ሰው ይበለን 👇join👇 👇group👇                👇channel👇 @bdebremhret      @yedebremhret @bdebremhret      @yedebremhret
972
16
የቤተክርስቲያን ውድ ልጆች እንኳን ለጉባኤያችን ቀን አደረሳችሁ። እነሆ 1ድ ቀን ብቻ ቀረን አብረን በአምላክ ቤት ልንዘምር🥰🥰🥰 እንደተለመደው እጅግ በጣም ልዩ ድምቅ ያለ አቀባበል ለእንግዶቻችን+3
የቤተክርስቲያን ውድ ልጆች እንኳን ለጉባኤያችን ቀን አደረሳችሁ። እነሆ 1ድ ቀን ብቻ ቀረን አብረን በአምላክ ቤት ልንዘምር🥰🥰🥰 እንደተለመደው እጅግ በጣም ልዩ ድምቅ ያለ አቀባበል ለእንግዶቻችን ለማድረግ በመኪና በባጃጅ በሞተር ጊንቦ ድረስ እንሄዳለን🫠 🌿 ነገ ልዩ ቀን ነው🌿 🙏ያድርሰን🙏 share ስለምታደርጉልን እናመሰግናለን🙏🙏 👇join👇 👇group👇                👇channel👇 @bdebremhret      @yedebremhret @bdebremhret      @yedebremhret
837
17
☝☝ከ330 በላይ እይታ share ስለምታደርጉልን እናመሰግናለን🙏🙏 👇join👇 👇group👇                👇channel👇 @bdebremhret      @yedebremhret @bdebremhret        @yedebremh
777
18
🙏የተወደዳችሁ ተቃበበሉልን እስቲ ሁላችንም በዚህ profile አችንን እናጥለቅልቀው🙏 🥰ታህሣስ 11/2017🥰 🥰በደብረ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን🥰 🥰ከቀኑ 9:00 እንገናኝ።🥰
🙏የተወደዳችሁ ተቃበበሉልን እስቲ ሁላችንም በዚህ profile አችንን እናጥለቅልቀው🙏 🥰ታህሣስ 11/2017🥰 🥰በደብረ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን🥰 🥰ከቀኑ 9:00 እንገናኝ።🥰 🤝Share 👇join👇 👇group👇                👇channel👇 @bdebremhret      @yedebremhret @bdebremhret        @yedebremhret
1 136
19
ቤተክርስቲያን ቀን ከሌት ለምትናፍቃችሁ ወጣቶች ነው። &lt;&lt;ኑ በብርሀኑ ተመላለሱ&gt;&gt; ሼር በማድረግ አድርሱልን🙏 🥰ታህሣስ 11/2017🥰 🥰በደብረ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክር
ቤተክርስቲያን ቀን ከሌት ለምትናፍቃችሁ ወጣቶች ነው። <<ኑ በብርሀኑ ተመላለሱ>> ሼር በማድረግ አድርሱልን🙏 🥰ታህሣስ 11/2017🥰 🥰በደብረ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን🥰 🥰ከቀኑ 9:00 እንገናኝ።🥰 አምላካችን ጠብቆን ለዕለቱ ያድርሰን፤ በቤቱ ያቁመን🙏 👇join👇 👇group👇 👇channel👇 @bdebremhret @yedebremhret @bdebremhret @yedebremhret
747
20
Sin texto...
645