cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

የኦርቶዶክስ ሥዕሎች

ለኦርቶዶክሳዊያን ብቻ የተከፈተ የመላእክት ፎቶ እና ሌሎችም

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
209
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ወገን ትንቢት እየተፈፀመ ነው🙈። 📣📣📣📢📢ንቃ 📢📢📣📣📣 ግብረ ሰዶማዊነት እየተስፋፋ ነው። ሁላችንም ይህን መልክት እናስተላልፍ ! ወገን ሀገራችን ላይ አለመፈጠሩን እንዴት እናቃለን 🤔 አቃለው የአስራት ሀገር እንደ ሆነች ። ግን አምላካችን የሚምረን ወደሱ ስንመለስ ነው ። እስቲ አንዴ ማረን እንበለው አምላካችን ንፁ ልብ ካገኘ ይምረናል እውነት አይደለም ነው ። አምላካችን ሀገራችንን ሰላም ህዝቧን ደና ዳሮን እሳት መሐሎን ገነት ያድርግልን አሜን። ለማንኛውም አስተያየት @iamrport በዚ
Mostrar todo...
3.03 MB
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞ ❖ ነሐሴ ፲፮ ❖ ✞✞✞ እንኩዋን ለእመቤታችን #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ የትንሳኤና የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞ +"+ ዕርገተ_ድንግል_ማርያም +"+ =>ይሕች ዕለት እጅጉን ታላቅና ክብርት ናት:: ምክንያቱም የድንግል ማርያም ሥጋዋ ተነስቶ ዐርጐባታልና:: ድንግል እመቤታችን ተነሳች: ዐረገች ስንል እንደ እንግዳ ደርሶ: እንደ ውሃ ፈሶ: ወይም በአጋጣሚ የተደረገ አይደለም:: ጥንቱን በአምላክ ልቡና ታስቦ: ሁዋላም ትንቢት ተነግሮለት ነው:: ¤ታሪኩ: ነገሩ: ምሥጢሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅድመ ዓለም በአምላክ ልቡና ታስባ ትኖር ነበር:: ከነገር ሁሉ በፊት #እግዚአብሔር እናቱን ያውቃት ነበር:: ¤ዓለም ተፈጥሮ: አዳምና ሔዋን ስተው: መርገመ ሥጋና መርገመ ነፍስ አግኝቷቸው: በኃዘን ንስሃ ቢገቡ "እትወለድ እም ወለተ ወለትከ - ከ5 ቀን ተኩል (5500 ዘመናት) በሁዋላ ካንተ ባሕርይ ከምትገኝ #ንጽሕት_ዘር ተወልጄ አድንሃለሁ" ብሎ ተስፋ ድኅነት ሰጠው:: ¤ከአዳም አንስቶ ለ5500 ዓመታት አበው: ነቢያትና ካህናት ስለ ድንግል ማርያም ብዙ ሐረገ ትንቢቶችን ተናገሩ:: መዳኛቸውን ሱባኤ ቆጠሩላት:: ምሳሌም መሰሉላት:: ከሩቅ ዘመን ሁነውም ሊያገኟት እየተመኙ እጅ ነሷት:: "እምርሑቅሰ ርእይዋ: ወተአምኅዋ" እንዲል:: +"+ የድንግል ማርያም ሐረገ ትውልድ +"+ *ከአዳም በሴት *ከያሬድ በሔኖክ *ከኖኅ በሴም *ከአብርሃም በይስሐቅ *ከያዕቆብ በይሁዳና በሌዊ *ከይሁዳ በእሴይ: በዳዊት: በሰሎሞንና በሕዝቅያስ ወርዳ ከኢያቄም ትደርሳለች:: ¤ከሌዊ ደግሞ #በአሮን: #አልዓዛር: #ፊንሐስ: #ቴክታና_በጥሪቃ አድርጋ ከሐና ትደርሳለች:: ¤አባታችን #አዳም ከገነት በወጣ በ5,485 ዓመት #ወላዲተ_አምላክ ንጽሕና ሳይጐድልባት: ኃጢአት ሳያገኛት: ጥንተ አብሶ ሳይደርስባት ከደጋጉ #ኢያቄም_ወሐና ትወለዳለች:: (ኢሳ. 1:9, መኃ. 4:7) "ወኢረኩሰት በምንትኒ እምዘፈጠራ" እንዳለ:: (#ቅዱስ_ቴዎዶጦስ_ዘዕንቆራ) ¤ከዚያም ከእናት ከአባቷ ቤት ለ3 ዓመታት ቆይታ ወደ #ቤተ_መቅደስ ትገባለች:: በቤተ መቅደስም ለ12 ዓመታት ፈጣሪዋን እግዚአብሔርን እያመሰገነችና እያገለገለች: እርሷን ደግሞ #መላእክተ_ብርሃን እያገለገሏት: ሕብስት ሰማያዊ: ጽዋዕ ሰማያዊ እየመገቧት ኑራለች:: 15 ዓመት በሞላት ጊዜ ጻድቅ #አረጋዊ_ዮሴፍ ያገለግላት ዘንድ ወደ ቤቱ ወሰዳት:: ¤በዚያም መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ዜና ድኅነትን ነግሯት አካላዊ ቃልን በማሕጸንዋ ጸነሰችው:: ነደ እሳትን ተሸከመችው: ቻለችው:: "ጾርኪ ዘኢይትጸወር: ወአግመርኪ ዘኢይትገመር" እንዳለ:: (#ሊቁ_ቅዱስ_ኤፍሬም #ለብሐዊ) ¤ወልደ እግዚአብሔርን ለ9 ወራት ከ5 ቀናት ጸንሳ: እንበለ ተፈትሆ (በድንግልና) ወለደችው:: (ኢሳ. 7:14) "#ኢየሱስ" ብላ ስም አውጥታለት በናዝሬት ገሊላ ለ2 ዓመታት ቆዩ:: ¤አርዌ ሔሮድስ "እገድላለሁ" ብሎ በተሳበት ወቅትም ልጇን አዝላ በረሃብ እና በጥም: በላበትና በድካም: በዕንባና በኃዘን ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት ከገሊላ እስከ #ኢትዮዽያ ተሰዳለች:: ልጇ ጌታችን 5 ዓመት ከ6 ወር ሲሆነው: ለርሷ ለድንግል ደግሞ 21 ዓመት ከ3 ወር ሲሆናት ወደ ናዝሬት ተመለሱ:: ¤በናዝሬትም ለ24 ዓመታት ከ6 ወራት ልጇን ክርስቶስን እያሳደገች: ነዳያንን እያሰበች ኑራለች:: እርሷ 45 ዓመት: ልጇ 30 ዓመት ሲሆናቸው ጌታችን ተጠምቆ በጉባኤ ትምሕርት: ተአምራት ጀመረ:: ለ3 ዓመታት ከ3 ወራትም ከዋለበት እየዋለች: ካደረበትም እያደረች ትምሕርቱን ሰማች:: ¤የማዳን ቀኑ ደርሶ ልጇ ክርስቶስ ሲሰቀልም የመጨረሻውን ፍጹም ሐዘን አስተናገደች:: አንጀቷ በኃዘን ተቃጠለ:: በነፍሷም ሰይፍ አለፈ:: (ሉቃ. 2:35) ጌታ በተነሳ ጊዜም ከፍጥረት ሁሉ ቀድማ ትንሳኤውን አየች:: ለ40 ቀናትም ሳትለይ ከልጇ ጋር ቆየች:: ¤ከልጇ #ዕርገት በሁዋላ #በጽርሐ_ጽዮን ሐዋርያትን ሰብስባ ለጸጋ መንፈስ ቅዱስ አበቃች:: በጽርሐ ጽዮን ከአደራ ልጇ ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ለ15 ዓመታት ኖረች:: በእነዚህ ዓመታት ሥራ ሳትፈታ ስለ ኃጥአን ስትማልድ: ቃል ኪዳንን ከልጇ ስትቀበል: ሐዋርያትን ስታጽናና: ምሥጢርም ስትገልጽላቸው ኑራለች:: ¤ዕድሜዋ 64 በደረሰ ጊዜ ጥር 21 ቀን #መድኃኒታችን አእላፍ ቅዱሳንን አስከትሎ መጣ:: ኢየሩሳሌምን ጨነቃት:: አካባቢውም በፈውስ ተሞላ:: በዓለም ላይም በጐ መዓዛ ወረደ:: እመ ብርሃን ለፍጡር ከዚያ በፊት ባልተደረገ: ለዘለዓለምም ለማንም በማይደረግ ሞገስ: ክብርና ተአምራት ዐረፈች:: ሞቷ ብዙዎችን አስደንቁአል:: "ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ: ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ" እንዲል:: ¤ከዚህ በሁዋላ መላእክት እየዘመሩ: ሐዋርያቱም እያለቀሱ ወደ ጌቴሴማኒ: በአጐበር ሥጋዋን ጋርደው ወሰዱ:: ይሕንን ሊቃውንት:- "ሐራ ሰማይ ብዙኃን እለ አልቦሙ ሐሳበ: እንዘ ይዜምሩ ቅድሜኪ ወመንገለ ድኅሬኪ ካዕበ: ማርያም ሞትኪ ይመስል ከብካበ" ሲሉ ይገልጡታል:: ¤በወቅቱ ግን አይሁድ በክፋት ሥጋዋን እናቃጥል ስላሉ #ቅዱስ_ገብርኤል (ጠባቂ መልአክ ነው) እነርሱን ቀጥቶ እርሷን ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር ወስዶ በዕጸ ሕይወት ሥር አኑሯታል:: በዚያም #መላእክት እያመሰገኗት ለ205 ቀናት ቆይታለች:: ¤#ቅዱስ_ዮሐንስ መጥቶ ለሐዋርያቱ ክብረ ድንግልን ቢነግራቸው በጐ ቅንአት ቀንተው በነሐሴ 1 ሱባኤ ጀመሩ:: 2ኛው ሱባኤ ሲጠናቀቅም ጌታ የድንግል ማርያምን #ንጹሕ_ሥጋ ሰጣቸው:: እየዘመሩም #በጌሴማኒ ቀብረዋታል:: ¤በ3ኛው ቀን (ነሐሴ 16) እንደ ልጇ ባለ #ትንሳኤ ተነስታ ዐርጋለች:: ትንሳኤዋንና ዕርገቷንም ደጉ ሐዋርያ #ቅዱስ_ቶማስ አይቶ: መግነዟን ተቀብሏል:: ሐዋርያቱም መግነዟን ለበረከት ተካፍለው: እንደ ገና በዓመቱ ነሐሴ 1 ቀን ሱባኤ ገቡ:: ¤ለ2 ሳምንታት ቆይተው: በዚህች ቀንም ሁሉንም ወደ ሰማይ አወጣቸው:: በፍጡር አንደበት ተከናውኖ የማይነገር ተድላ: ደስታና ምሥጢርንም አዩ:: ጌታ ራሱ ቀድሶ ሁሉንም አቆረባቸው:: የበዓሉን ቃል ኪዳን ሰምተው: ከድንግል ተባርከው ወደ #ደብረ_ዘይት ተመልሰዋል:: =>ጽንዕት በድንግልና: ሥርጉት በቅድስና #እመቤታችን: ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሳን ለምኚልን:: አእምሮውን: ለብዎውን: ጥበቡን በልቡናችን ሳይብን አሳድሪብን:: +"+ ቅዱስ_ጊጋር_ሶርያዊ +"+ =>ይሕ ቅዱስ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን የሶርያ መስፍን የነበረ ሲሆን #ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ ሰምቷል:: እመ ብርሃን ለስደት ስትወጣ በመጀመሪያ የሔደችው ወደ #ሊባኖስ ተራሮች ነው:: #መስፍኑ_ጊጋር ነበርና እርሱም የአምላክ እናትነቷን አምኖ አክብሮ አስተናግዷታል:: +ሔሮድስም ይሕንን ሲሰማ ጦር አስከትቶ ወደ ጊጋር ሔደ:: መስፍኑ ጊጋር ሔሮድስን እንደማይችለው ሲረዳ ድንግል ማርያምን ወደ #ግብጽ ሸሽጐ አሸሻት:: ሔሮድስንም ፊት ለፊት ተገናኘው:: ከአቅሙ በላይ ስለነበረም በወታደሮች ተማርኮ ወደ ሔሮድስ ቀረበ:: +እመቤታችንንና ልጇን "አምጣ" ቢለው "አልናገርም" አለው:: በዚህ ምክንያት አካሉን ከብዙ ቆራርጦ ገድሎታል:: በቤተ ክርስቲያን ታሪክም #ስለ_እመ_አምላክ_ፍቅር የተሰዋ የመጀመሪያው ሰው ተብሎ ይታወቃል:: ጌታም ስለ ሃይማኖቱ: ፍቅሩና ሰማዕትነቱ 3 አክሊላትን ሰጥቶታል:: =>አምላከ ቅዱሳን ከድንግል እመ ብርሃን ፍቅር: ከጣዕሟ: ከረድኤቷ
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.