cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Daily News Ethiopian 🇪🇹🔵

Daily News Ethiopian 🇪🇹🔵 🇪🇹ኢትዮጵያ አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ ቤተሰብ ይሁኑ Daily News Ethiopian 🇪🇹🔵 @Daily_News_Ethiopian አስተያየትና መልክት ካሎት @Natty19 ምርትና አገልግሎቶን ማስተዋወቅ ከፈለጉ ያናግሩን @Natty19

Mostrar más
Advertising posts
8 714Suscriptores
+124 hours
-57 days
-10830 days

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

💔 6👍 2
የቡድን ሰባት ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ በርካታ አካባቢዎች ይታያሉ ያሏቸው፤ “የማያቋርጡ እና ኃይለኛ ውጥረቶች” እንደሚያሳስቧቸው ገለጹ። በኢንዱስትሪ የበለጸጉት ሰባት አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ይፈጸማሉ የሚባሉ “የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እና በደሎች ሪፖርቶች”፣ “ብርቱ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ” እና “የምግብ ዋስትና እጦት መስፋፋት” እንዳሰጋቸውም አስታውቀዋል። ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቹ በኢትዮጵያ ጉዳይ ስጋታቸውን ያንጸባረቁት፤ በጣልያኗ ካፕሪ ደሴት ያካሄዱትን ስብሰባ ሲያጠናቅቁ ዛሬ አርብ ምሽት ባወጡት  መግለጫ ነው። ሚኒስትሮቹ በዚሁ መግለጫቸው፤ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና በህወሓት መካከል በተፈረመው ግጭት የማቆም ስምምነት አተገባበር ረገድ የተወሰዱ እርምጃዎችን በበጎ እንደሚቀበሉ ገልጸዋል። በሰብዓዊ መብቶች እና በሲቪል ሰዎች ጥበቃ፣ ውጥረቶችን ለመፍታት በሚደረግ ፖለቲካዊ ውይይት፣ በዕርቅ፣ በብሔራዊ ውይይት፣ የሽግግር ፍትህ እና በግጭት ወቅት ወንጀል የፈጸሙ ተጠያቂ ለማድረግ፤ ተጨማሪ እና ዘላቂ እርምጃዎች ተግባራዊ እንዲደረጉ አበረታተዋል። በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች በመካሄድ ላይ በሚገኙ ግጭቶች የሚሳተፉ ወገኖች፤ በንግግር ሰላም ለማውረድ ተመሳሳይ ቁርጠኝነት እንዲኖራቸውም ጥሪ አቅርበዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር )
Mostrar todo...
👍 6
ኢትዮጵያ በታሪኳ ከፍተኛ የተባለ የኮሌራ ወረርሽኝ እያስተናገደች እንደምትገኝ የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ። የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ ለሚያካሂደው ሥራ አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልገውም ገልጿል። የድርጅቱ ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሐኖም ድጋፉ የማይገኝ ከሆነ ድርጅታቸው በሀገሪቷ የሚያከናውነውን ከጤና ጋር የተገናኝ ሥራ ለመቀጠል እንደሚቸገር ተናግረዋል። ዶክተር ቴድሮስ የተስፋፋ ድርቅና በሽታ በሚሊየን የሚቆጠሩ አትዮጵያውያንን ሕይወት አደጋ ላይ መጣሉንም አስረድተዋል። በተለይም በትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያና ሌሎች አካባቢዎች የተፈጠረው ግጭት እና ጦርነት የከፋ ጉዳት አድርሷል ነው ያሉት። በርካታ የጤና ተቋማት እና መሰረተ ልማቶች ላይ ውድመት መከሰቱን አስታውሰው የተለያዩ ወረርሽኞች መከሰታቸውንም ጠቅሰዋል። የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ በሥምንት ክልሎች 41 ሺህ ሰዎች በኮሌራ በሽታ መያዛቸውንም ገልጿል። በሽታው በዚህ ልክ በኢትዮጵያ ሲከሰት በታሪኳ ከፍተኛው እንደሆነም ነው ድርጅቱ የገለጸው። ወባና ኩፍኝም ሌሎቹ ወረርሽኞች መሆናቸውን የጠቀሰው ድርጅቱ፥ በኢትዮጵያ ለሚያከናውነው የበሽታ መከላከልና ጤና አጠባበቅ ሥራ አፋጣኝ የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግለት ጥሪ አቅርቧል።
Mostrar todo...
👍 5👎 1
ቀሲስ በላይ መኮንን በተጠረጠሩበት በሀሰተኛ ሰነድ ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ዝውውር ወንጀል ለምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ ተፈቀደ! የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀሲስ በላይ መኮንን በተጠረጠሩበት በሀሰተኛ ሰነድ የዶላር ዝውውር ወንጀል ለምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ቀጠሮ መፍቀዱ ተሰምቷል፡፡ የፌደራል ፖሊስ መርማሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ከትናንት በስቲያ በአፍሪካ ህብረት ቅጥር ጊቢ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ በአካል ቀርበው ሀሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመያዝ ለ3 ግለሰቦች እና ለአንድ የግል ድርጅት ሒሳብ 6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሊያዘዋውሩ ሲሉ በአፍሪካ ህብረት ሴኪዩሪቲዎች ተይዘው ለፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ተላልፈው መሰጠታቸውን ጠቅሶ የጥርጣሬ መነሻውን ለችሎቱ  ማቅረቡን ዳጉ ጆርናል ከፋና ዘገባ ተመልክቷል። በዚህ መነሻ መሰረትም መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ሥራ ለማከናወን የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።ተጠርጣሪ ቀሲስ በላይ መኮንን ድርጊቱ መፈጸሙን አምነው፤ ይሁን እንጂ ወንጀል አለመፈጸማቸውን አስረድተዋል።ስለሆነም የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።የግራ ቀኝ ክርክሩን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪው ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ በማለፍ ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ፈቅዷል።
Mostrar todo...
👍 4🥰 1
ትላንት ጄኔቫ
Mostrar todo...
ቅዱስ ፓትርያርኩ ለኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛና ዲጂታል ሚዲያ ባለሙያዎች በተዘጋጀው ሥልጠና ማጠናቀቂያ ላይ ቃለ ምእዳንና የሥራ መመሪያ ሰጡ። ዘጋቢ መ/ር አቤል አሰፋ (#EOTCTV ሚያዝያ ፯ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም አዲስ አበባ) +++++++++++++++++++++++++++++++++++ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያ " ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን " በሚል ርዕስ ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ማጠናቀቂያ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አባታዊ ቃለ ምእዳንና መልዕክት አስተላልፉ። የመዝጊያ መርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ የኮንታ ዳውሮ አህጉረ ስብከት ጳጳስ ፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች የሥልጠናው ተሳታፊዎች በተገኙበት ነው የተከናወነው ። በመድረኩ ተሳታፊዎች በሥልጠናው ባገኙተት እውቀትና ግንዛቤ በመነሳት በደረሱበት ስምምነት መሠረት የአቋም መግለጫ አቅርበዋል። በማስከተልም ብፁዕ አቡነ አብርሃም ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሐሰተኛ ወሬ ባለመቀበል እና ለማስተላለፍ የቤተክርስቲያን አጋር በመሆን ለመሥራት ቤተክርስቲያንን ከማይጠቅሙ አጀንዳዎች ራሳቸውን ለማራቅና ሌሎች በአቋም መግለጫቸው በንባብ ያሰሟቸውን ቃል ኪዳኖች መተግበር እንደሚገባቸው ገልጸዋል። ቅዱስ ፓትርያርኩ በሥልጠናው ለተሳተፉ አሰልጣኞችና ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በመድረኩ መዝጊያ ባስተላለፉት መልዕክት የቤተክርስቲያናችን በሚዲያው ዘርፍ ያለውን ክፍተት በማየት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ተፈላጊ የሆነውን ሥራ መሥራቱን በመግለጽ ምስጋና አቅርበዋል። ቅዱስነታቸው እግዚአብሔር ምድርን የሰጠን እርስ በእርስ ተዋደን በሰላም አንድንኖርባት ነው ያሉ ሲሆን ሚዲያዎች እንደሚያስተላልፉት መልዕክት ጎጂም ጠቃሚም ተግባራት እንደሚከናወንባቸው ገልጸዋል። ሚዲያ ከቀና ሁሉም ይቀናል በእዉነት የሚሠሩ ሚዲያዎች ለሀገር ይጠቅማሉ ያሉት ቅዱስነታቸው ሕግና ሥነ ሥርዓትን ተከትለው ካልሠሩ ሚዲያዎች ጎጂ ስለሚሆኑ በጥንቃቄ መሥራት አለባችሁ ብለዋል። #EOTC TV +++++++++++++++++++++++++++++++++++++
Mostrar todo...
👍 8👌 1
💔 4🤬 3
ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በአገልግሎት ላይ ሳሉ ጥቃት ተፈፀመባቸው በተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች በሚዘዋወር ስብከታቸው የሚታወቁት ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በአገልግሎት ላይ ሳሉ ጥቃት እንደተፈፀመባቸው ተገለጸ ! በአሦርያውያን ቤተ ክርስቲያን የአውስትራሊያ ጳጳስ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ማር ማርያም ኢማኑኤል በተለያዩ የማኅበራዊ ትስስር ገጾች በእንግሊዝኛ እና ዐረብኛ ቋንቋዎች በሚያስተላልፉት ስብከት የሚታወቁ ሲሆን በሲድኒ በሚገኝ አንድ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ሳሉ በአንድ ግለሰብ አማካይነት በስለት መወጋታቸው ተገልጿል። የኒው ሳውዝ ዌልስ ፖሊስም ጥቃቱን የፈፀመውን ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ተናግሯል። የኒው ሳውዝ ዌልስ የአምቡላንስ አገልግሎት በዕለቱ ጥቃቱ በደረሰበት ወቅት አራት ሰዎች ቆስለዋል ብሏል። ሊቀ ጳጳሱ የሕክምና እርዳታ ተደርጎላቸው በአሁኑ ወቅት በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙ ተዘግቧል በዕለቱ በሠላሳዎቹ ውስጥ ከሚገኝ ወጣት በተጨማሪ በከባድ ሁኔታ ወደ ሆስፒታል የተወሰደው በሀምሳዎቹ ውስጥ የሚገኝ አንድ ሰው መኖሩንና በርካታ ቦታዎች ላይ ጉዳት እንደደረሰበት ለመገንዘብ ተችሏል። ጥቃቱን የሚያሳየው ቪዲዬ >>>>> https://vm.tiktok.com/ZMMCA7PVT/
Mostrar todo...
👍 3💔 1
በኢትዮጵያ የመረጃና ደኅንነት ዘርፍ እድገት ውስጥ ጉልህ ሚና ያበረከቱት ዶ/ር አምባሳደር አስማማው ቀለሙ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ ********* ከ1956 ዓ.ም ጀምሮ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም እና ደኅንነት በማስጠበቅ ለ60 ዓመታት ያህል በመረጃና ደኅንነት ዘርፍ ሰፊ አበርክቶት ሲያደርጉ የቆዩት ዶ/ር አምባሳደር አስማማው ቀለሙ በተወለዱ በ84 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ዶ/ር አስማማው ቀለሙ በሀገር ዉስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ከማገልገል በተጨማሪ የሀገር ዉስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ሚኒስትር በመሆን አገልግለዋል። ዶ/ር አስማማው ቀለሙ በኢኮኖሚክስ የትምህርት ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ሁለተኛ ድግሪያቸውን ከእስራኤል ሀገር፣ የሦስተኛ ድግሪያቸውን ከቡልጋሪያ ካርል ማርክስ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ኢኮኖሚክስ እንዲሁም ፖስት ዶክትሬታቸውን እንግሊዝ ሀገር ከሚገኘው ለንደን ስኩል ኦፍ ኢኮኖሚክስ አግኝተዋል። ከእነዚህም በተጨማሪ በፖሊስነት ህይወታቸው የ9ኛ ኮርስ አባል የነበሩ ሲሆን በዘርፉ የኮለኔልነት ማዕረግ ላይ ደርሰዋል።
Mostrar todo...
👍 5😭 1
👍 3 2👏 2