es
Feedback
ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ✨ Semien Full Gospel Local Church

ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ✨ Semien Full Gospel Local Church

Ir al canal en Telegram
1 127
Suscriptores
+124 horas
+187 días
+3030 días
Archivo de publicaciones
🗓 26/10/2018 አርብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ          ⏳ቀን 536⏳ መዝሙር ምዕራፍ 61 ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች፤ የዳዊት መዝሙር። 1 አምላክ ሆይ፥ ልመናዬን ስማ፥ ጸሎቴንም አድምጥ። 2 ልቤ ተስፋ በቈረጠ ጊዜ ከምድር ዳርቻ ወደ አንተ እጮኻለሁ፤ በድንጋይ ላይ ከፍ ከፍ አደረግኸኝ። 3 ጽኑ ግንብ በጠላት ፊት ተስፋዬም ሆነኸኛልና መራኸኝ። 4 በድንኳንህ ለዘላለም እኖራለሁ፤ በክንፎችህም ጥላ እጋረዳለሁ፤ 5 አቤቱ፥ አንተ ስእለቴን ሰምተሃልና፤ ስምህንም ለሚፈሩ ርስትህን ሰጠሃቸው። 6 ለንጉሥ ከቀን በላይ ቀን ትጨምራለህ፥ ዓመታቱም ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሆናሉ። 7 በእግዚአብሔር ፊት ለዘላለም ይኖራል፤ ይጠብቁት ዘንድ ምሕረትንና እውነትን አዘጋጅለት። 8 እንዲሁ ለስምህ ለዘላለም እዘምራለሁ ስእለቴን ሁልጊዜ እፈጽም ዘንድ። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook

🗓 25/10/2018 ሀሙስ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 535⏳ መዝሙር ምዕራፍ 60 ለመዘምራን አለቃ አታትፍ የዳዊት ቅኔ 1 አቤቱ፥ ጣልኸን አፈረስኸንም፤ ተቈጣኸን ይቅርም አልኸን። 2 ምድርን አናወጥሃት አወክሃትም፤ ተናውጣለችና ቍስልዋን ፈውስ። 3 ለሕዝብህ ጭንቅን አሳየሃቸው፥ አስደንጋጩንም ወይን አጠጣኸን። 4 ከቀስት ፊት ያመልጡ ዘንድ፥ ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው። 5 ወዳጆችህ እንዲድኑ፡ በቀኝህ አድን፥ አድምጠኝም። 6 እግዚአብሔር በቅድስናው ተናገረ፤ ደስ ይለኛል፥ ሴኬምንም እካፈላለሁ፥ የሱኮትንም ሸለቆ እሰፍራለሁ። 7 ገለዓድ የእኔ ነው፥ ምናሴም የእኔ ነው፤ ኤፍሬም የራሴ መጠጊያ ነው። ይሁዳ ንጉሤ ነው፤ 8 ሞዓብ መታጠቢያዬ ነው፥ በኤዶምያስ ላይ ጫማዬን እዘረጋለሁ፤ ፍልስጥኤም ይገዙልኛል። 9 ወደ ጽኑ ከተማ ማን ይወስደኛል? ማንስ እስከ ኤዶምያስ ይመራኛል? 10 አቤቱ፥ የጣልኸን አንተ አይደለህምን? አምላክ ሆይ፥ ከሠራዊታችን ጋር አትወጣም። 11 በመከራችን ረድኤትን ስጠን፡ የሰውም ማዳን ከንቱ ነው። 12 በእግዚአብሔር ኃይልን እናደርጋለን፡ እርሱ የሚያስጨንቁንን ያዋርዳቸዋልና። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook

🗓 24/10/2018 ዕሮብ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 534⏳ መዝሙር ምዕራፍ 59 ለመዘምራን አለቃ አታትፍ የዳዊት ቅኔ 1 አምላኬ ሆይ፥ ከጠላቶቼ አድነኝ፤ በላዬም ከቆሙት አስጥለኝ። 2 ከግፍ አድራጊዎች ታደገኝ፥ ከደም ሰዎችም አድነኝ። 3 እነሆ፥ ነፍሴን ሸምቀውባታልና፥ ብርቱዎችም በላዬ ተሰበሰቡ፤ አቤቱ፥ በበደሌም አይደለም፥ በኃጢአቴም አይደለም። 4 ያለ በደል ሮጥሁ ተዘጋጀሁም፤ ተነሥ፥ ተቀበለኝ፥ እይም። 5 አንተም አቤቱ፥ የኃያላን አምላክ፥ የእስራኤል አምላክ፥ አሕዛብን ሁሉ ትጐበኛቸው ዘንድ ተነሥ፤ ዓመፅ የሚያደርጉትን ሁሉ አትማራቸው። 6 ማታ ይመለሱ እንደ ውሾችም ይራቡ፥ በከተማም ይዙሩ። 7 እነሆ፥ በአፋቸው አሰምተው ይናገራሉ፤ ሰይፍም በከንፈሮቻቸው አለ፤ ማን ይሰማል? ይላሉ። 8 አንተ ግን አቤቱ፥ ትሥቅባቸዋለህ፥ አሕዛብንም ሁሉ ትንቃቸዋለህ። 9 እግዚአብሔር መጠጊያዬ ነውና፡ ኃይሌን ወደ አንተ አስጠጋለሁ። 10 የአምላኬ ቸርነቱ ይገናኘኛል፡ አምላኬ በጠላቶቼ ላይ ያሳየኛል። 11 ሕግህን እንዳይረሱ አትግደላቸው፤ አቤቱ ጋሻዬ፥ በኃይልህ በትናቸው አውርዳቸውም። 12 ስለ አፋቸው ኃጢአት ስለ ከንፈራቸውም ቃል፥ መርገምንና ሐሰትን ስለሚናገሩ፥ በትዕቢታቸው ይጠመዱ። 13 በቍጣ አጥፋቸው፥ እንዳይኖሩም አጥፋቸው፤ የያዕቆብም አምላክ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ እንዲገዛ ይወቁ። 14 ማታ ይመለሱ እንደ ውሾችም ይራቡ፥ በከተማም ይዙሩ። 15 እነርሱም መብል ለመፈለግ ይበተኑ፤ ያልጠገቡ እንደ ሆነም ያንጐረጕራሉ። 16 እኔ ግን ለኃይልህ እቀኛለሁ፤ በምሕረትህም ማልዶ ደስ ይለኛል፤ በመከራዬ ቀን መጠጊያዬና አምባዬ ሆነኸኛልና። 17 ረዳቴ ሆይ፥ ለአንተ ለአምላኬ እዘምራለሁ፤ አንተ፥ አምላኬ፥ መጠጊያዬ ምሕረቴም ነህና። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook

🗓 23/10/2018 ማክሰኞ🗓 የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን 📖 አንብቦ የመጨረስ  ቻሌንጅ           ⏳ቀን 533⏳ መዝሙር ምዕራፍ 58 ለመዘምራን አለቃ አታትፍ የዳዊት ቅኔ 1 በእውነት ጽድቅን ብትናገሩስ፥ የሰው ልጆች ሆይ፥ በቅን ትፈርዳላችሁ፤ 2 በልባችሁ በምድር ላይ ኃጢአትን ትሠራላችሁና፥ እጆቻችሁም ግፍን ይታታሉና። 3 ኅጥኣን ከማኅፀን ጀምረው ተለዩ፤ ከሆድም ጀምረው ሳቱ፥ ሐሰትንም ተናገሩ። 4 ቍጣቸው እንደ እባብ መርዝ ነው፥ እንደ ምድር አውሬም ጆሮዋ የተደፈነ ነው፥ 5 አዋቂ ሲደግምባት የአስማተኛውን ቃል እንደማትሰማ። 6 እግዚአብሔር ጥርሳቸውን በአፋቸው ውስጥ ይሰብራል፤ እግዚአብሔር የአንበሶቹን መንጋጋቸውን ያደቅቃል። 7 እንደሚፈስስ ውኃ ይቀልጣሉ፤ እስኪያደክማቸው ድረስ ፍላጾቹን ይገትራል። 8 እንደሚቀልጥ ሰም ያልቃሉ፤ እሳት ወደቀች፥ ፀሐይንም አላዩአትም። 9 እሾኻችሁ ሳይታወቅ በትር ሆነ፤ ሕያዋን ሳላችሁ በመዓቱ ይነጥቃችኋል። 10 ጻድቅ በቀልን ባየ ጊዜ ደስ ይለዋል፤ በኃጢአተኛው ደምም እጁን ይታጠባል። 11 ሰውም፡— “በእውነት ለጻድቅ ፍሬ አለው፤ በእውነት በምድር ላይ የሚፈርድ አምላክ አለ፡” ይላል። 🔹🔹🔹🔹♦️♦️♦️🔹🔹🔹🔹 ⛪️ሰሜን ሙሉ ወንጌል አማኞች አጥቢያ ቤተክርስቲያን⛪️ Our Social  Links🔗 Click here to Join 👇 YouTube | Telegram | Instagram | TikTok | Facebook

ሰሜን ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስቲያን ✨ Semien Full Gospel Local Church - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @semienfgbc