cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

የእርቅ-ይሁን ማዕድ® 💌

◈ አንዳች ወሰንና ገደብም ከሌለው...ካላንዳች መድሎ እኩል ከሚለግሰው ሰላምን ከፍቅርን...አንድነትን አበርክቶ መለያየትን ጠልቶ...አይቻልም መንፈስን ከይቻላል የሚያቆራኝ...አብሮነት ከሚሻው እርቅ-ይሁን ሲል ዘወትር ይቅርታን ከሚሰብከው ከእርቅ ማዕድ እንቋደስ...! : : : #Join And #Share ..... @Erk_yehun @Erk_yehun For any comment... @Erk1236

Mostrar más
Advertising posts
282Suscriptores
Sin datos24 hours
Sin datos7 days
Sin datos30 days

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

Keep your thought positive Because your thoughts becomes YOUR WORDS Keep your words positive Your words become YOUR BEHAVIOUR Keep your behavior positive Your behavior becomes YOUR HABIT Keep your habit positive Your habit becomes YOUR VALUES Keep your values positive Your values becomes YOUR DESTINY #At_any_means, #anytime, #any_where, #to_anyone stay positive መልካም ቀን
Mostrar todo...
የጊዜ ጉዳይ ነው! አንተ ነገህን መወሰን አትችልም፤ አንተ የምትችለው ደጋግመህ የምታደርገውን ልማድ መወሰን ነው፤ ከዛ ያ ልማድህ ግን ነገህን መወሰን ይችላል! የጊዜ ጉዳይ ነው ምርጥ ልማድ ካለህ ምርጥ ቦታ ያደርስሀል! ውብ ምሽት ተመኘንላችሁ🙏 @manyazewaleshetu!
Mostrar todo...
ትንሽ ፈገግታ ! መልካም ስትሆን ለሰዎች ምን እየሰጠኃቸው አንዳለህ አታውቅም ፈገግ ብለህ በማየትህ ብቻ ትልቅ ተስፋ የሰጠኃቸው ብዙዎች አንዳሉ ገምተህስ ታውቃለህ? ስለዚህ ወዳጄ ምንም ማድረግ ባትችል እንኳን ከልብህ ፈገግ ብለህ ለሰዎች ሰው እንዳላቸው እንዲሰማቸው አድርግ ውጤቱ ብዙ ነዉ! ደስ የሚል ሰኞ ተመኘን 🙏 @manyazewaleshetu 😊
Mostrar todo...
ሰው ሁን....! ሰው ነኝ ባዮች ሰው ያልሆኑ ስንቶች የተከበረውን የእርሱን ስራ ተሸክመው እየተዘዋወሩ በህይወት እንዲያ እየተመላለሱ....ኸረ ስንቶች አሉ የሰውነት ትርጉሙ ቅሉ ላፍታ ያላወቀላቸው...። ሰውነት ትርጉሙ እና ዋጋው እጅጉን ረቂቅ ነው።ግና ላላወቀው በስሜት ፈረስ ለሚጋልብ...በሰሞነኛ ሰረገላ እራሱን አንግሶ ለሚጓዝ....ማስተዋል ለራቀው ፤ሰክኖ ማሰብ ለተሳነው፤የሰሜት ፈረስ ለሆነ አላፊዎች ለሚጋልቡት፤ወረተኛ ለሆነ፤የይቅርታን ዋጋ ሲሶዋን ላልተረዳ፤ዝምታዎች ፍራቻ፤እንክረም ሞኝነት ለመሰለው፤እውነትን አርክሶ ሀሰትን አንግሶ ለሚጓዝ፤ከመናገር በቀር መኖርን ለማይችል፤በቃላት ስንጠቃ የማወቅን ጥግ የተረዳ የሚመስለው፤ሳይጀምረው የጨረሰ ለሚመስለው፤ማወቅን በቅጡ ያልተረዳ በእውቀት በቃሁኝ ለሚል.....እስኪ ወዳጄ ለዚህ አይነቱ ፍጡር ምኑጋነው ሰው??? ሰው ነኝ ብለን ካልን እስኪ ድርጊቶቻችንን ቆም ብለን እናስተውል? ምኑጋነኝ እንበል...በፈጠረን ፊት ለአፍታ ብንቀርብ ምን ምላሽ ይኖረን ይሆን ብለን ትዕዛዛቱን ከተግባራችን እናመሳክር...!!! ሰውነት መሆን የራቀህ ወዳጄ እስኪ ሰው ሁን! ለራስህም የማታፍርበትን ተግባር ተግብር....ይመስለናል ግን ከሰውነት የራቅን ብዙዎች ነን ይባስ ብሎ የተሳሳተው ጉዟችን እያወቅነው ሳለ ትክክል እንደሆን እንኩራራበታለን....ይህ ግን እስከመች? ሰው እንሁን....ወዳጄ እስኪ የተከበረውን አታርክሰው በድርጊትህ ሲጠሉህ በድርጊትህ ሲዘልፉና ሲያንቋሽሹህ የፈጣሪን ስራ እያስወቀስክ እንደሆነ አድርገህ ተረዳው....ከዛም ማስተዋልን ተላበሰው መንገድህን ምረጥ አመሻሽ ላይ መግቢያህን ሊያሳምርልህ የሚችለውን ንፁሑን እና ምቹውን ምረጥ...ጊዜያዊነት ጊዜያዊ ነው፤በሀሰት የተገነባ ይፈርሳል ውሸት ምንም ለጊዜው ያማረች ቢመስልም የቆይታ እድሜዋ አጭር ነው ማብቂያዋ ገደብ የተበጀለት...የሚሻልህን ታውቃለህ ብቻ ግን ሰው ሁን....! ✍:በ እርቅ-ይሁን🔔 @Erk1236
Mostrar todo...
#ሕይወት_እንደ_ነጭ_ወረቀት! ዛሬ የማጋራችሁን ሃሳብና የማቀርብላችሁን Challenge በቁም ነገር በመውሰድ ወረቀትና እስኪሪፕቶ በመያዝና በመጻፍ (ወይም በስልካችሁ ላይ Note በመያዝ) ራሳችሁን ለለውጥ እንድታቀርቡ ላነሳሳችሁ፡፡ Challenge #1 እስከዛሬ የኖራችሁትን የሕይወት ልምምድ፣ እውቀት፣ ጥበብ፣ ከስህተታችሁ የመማር ሁኔታና የመሳሰሉትን ነገሮች እንደያዛችሁና ሳይወሰዱባችሁ ዛሬ የሕይወታችሁ የመጀመሪያ ቀን ቢሆን ምን አይነት የወደፊታችሁን በምን መልኩ ታዩት ነበር? ምን አይነት የሕይወት እቅድ ታወጡ ነበር? ምንስ አዲስ ነገር ትጀምሩ ነበር? ከላይ ለጠየኳችሁ ጥያቄ መልስ ካሰባችሁና መልስን ከሰጣች በኋላ የሚቀጥለውን ጥያቄዬን አንብቡና ለራሳችሁ መልስ ስጡ፡፡ Challenge #2 እስከዛሬ የነበራችሁን ስኬትም ሆነ ስህተት የማሰብና ግምገማ የማድረግ ጊዜ ቢሰጣችሁና ዛሬ የሕይወታችሁ የመጨረሻ ቀን ነች ብትባሉ “ምነው አቁሜው በነበረ የምትሉት አጉል ተግባርና ልማድ … ምነው ተለይቼው በነበረ የምትሉት አስቸጋሪ ሰው …” እና የመሳሰሉት ሁኔታዎች ምን ምን ናቸው? አሁን ለመጀመሪያው ጥያቄ (Challenge #1) የሰጣችሁትን መልስ ተመልከቱት፡፡ በሉ ዛሬውኑ እቅዱን አውጡት፣ በትንሹም ቢሆን ውጡና ጀምሩት፡፡ ሕይወታቸውን ለተሸለ ነገር የለወጡ ሰዎች ያንን ያደረጉት በዚህ መልኩ ነው፡፡ በመቀጠል ለሁለተኛው ጥያቄ (Challenge #2) የሰጣችሁትን መልስ ተመልከቱት፡፡ በሉ ዛሬውኑ ማቆም የሚገባችሁን አጉል ልምምድ አቁም፣ መለየት የሚገባችሁን አደገኛ የሰው-ለሰው ግንኙነት አቁሙ፡፡ ሕይወታቸውን ከጤና ቢስ ልምምድና ግንኙነት ያዳኑ ሰዎች ያንን ያደረጉት በዚህ መልኩ ነው፡፡ ሕይወት ማለት እንደ ነጭ ወረቀት ንጹህ ሆና የተጀመረችና በጉዞው ሂደት ግን በብዙ ልምምዶች የቆሸሸች የፈጣሪ ስጦታችን ነች፡፡ እንደ አዲስ መጀመር የማይቻል ነገር የለም፡፡ የማይታረም ነገር ግን የለም፡፡ የማይለወጥም ነገር የለም፡፡ የለውጡ ቀን ግን ዛሬ ነው፡፡ ይህ የለውጥ እድል ነገ የመኖሩን ጉዳይ ማንም ቃል አልገባለንም፡፡ መጀመር ያለበት ዛሬ ይጀመር!!! መቆም ያለበት ዛሬ ይቁም!!! በ......ዶ/ር ኢዮብ ማሞ
Mostrar todo...
ወዳጄ.... ደስተኛ መሆን ትፈልጋለህን ? በርግጥ ቀንን እንዴት ማሳለፍ እንደሚገባህ ማወቅ ትሽለህን? አንድ መንፈሳዊ መጠጥ እሰጥህለሁ ። ይህ መጠጥ ሰካራም ሰዎች እንደሚጠጡት ንግግርን የሚያጠፋው ዓይነት መጠጥ አይደለም ። ይህ መጠጥ አንደበታችነ እንዲኮላተፍ የሚያደረግ አይደለም ። ይህ መጠጥ ዓይናችን በአግባቡ ማየት እንዲሳነው የሚያደርግ አይደለም ። መዝሙር መዘመር ተማር ! ያን ጊዜ ደስታን በእርግጥ ታየዋለህ ። #ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ
Mostrar todo...
#ዕለት....ዕለት ልባዊ ምስጋና ማቆረብ...! 1ኛ . ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነሳ ፈጣሪህን አመስግን ለሊቱን በዙሪያ ባደሩ መናፍስት በሞት ልትወሰድ ስለነበር 2ኛ ሙሉ አካል ስላለህ አካልህ ሙሉ ባይሆን እንኳን በጤና አልያም በህይወት ያቆየህ ፈጣሪ ምክንያት ስላለው ነው ለዚህም አመስግነው 3ኛ ቢያንስ በቀን አንዴ እንኳን አፍህን ትሽራለህ ቢኖር መርጠህ በልተህ ባይኖርህ ውሀ እንኳን ጠጥተህ ትውላለህ ለዚህ የፍጥረታት ጌታን አመስግን 4 . በመንገድህ ሁሉ ስትሄድ ሠላምታ እና ትህትና ከአንደበትህ አይራቅ 5. ለሚገጥምህ መጥፎ ነገር ሁሉ ምላሽህ ደግ እና መልካም ነገር ይሁን ክፉ ተነጋግረህ ክፉ ሰርተህ ከሰውም ከእንስሳውም ከሁሉ ፍጥረት ከምትጣላ ይልቅ ሁሉን እንዳመጣጡ በፍቅር ሸኘው 6. ባረፍክበት ሁሉ እርዳታህን ለሚሻ ሁሉ ደግ ልቦናህን እና ቀኝ እጅህን አትከልክል የዛሬ ቸርነትህ የነገ እረፍትህን ያበጃጃል እና 7. ከማንም ጋር በማይረባ ጊዜያዊ ጥቅም አትጣላ አትጋጭ ችኩል አትሁን ለሚያልፍ ቀን ብለህ ፍፁም አትማረር ይልቅ ይቅር ማለትን ቅድሚ መስጠትን ለልብህ አስተምር ላንተ ያለው እንጀራ ሳይሻግት ሳይደርቅ በለምለምነቱ በጊዜው ከነሌማቱ ቤትህ ይገባልና 8. ህፃናትን ሁሉ በአንድ ልብ ውደድ ሠው ማፍቀርን ሀቀኝነትን እና ደግነትን አስተምራቸው ነገ በድካምህ ጊዜ ሮጠው የሚደርሱልህ እነሱ ስለሆኑ ወጣት እኩዮችህን አትናቅ አንተ የደረስክበት እንዲደርሱ እርዳቸው ከአንተ የበለጡም ስለሚኖሩ ራስህን ለማሻሻልም የሚረዳህ ቸር ማድረግ ነውና ከፍ ለማለት የሌሎችን ጫንቃ አትስበር እንዲያው እጅ ለእጅ ተያይዞ መለወጥን አስብ አዛውንቶችን አተጨቁን ምርቃታቸው ርግማናቸውም ከአፋቸው ጠብ አይለምና ከፈጣሪ እንዳትጣላ ''የሚያድግ ህፃን አይጥላህ የሚሞት ሽማግሌ አይርገምህ'' 9. ስላለህም ስላጣኸውም ሁሉ አመስግን ስላሣለፍከው መከራም ስላየኸውም ተድላ በምክንያተ አመስግን የሚሆነው ሁሉ በምክንያት ባንተ ላይ ስለተከናወነ አመስግን ማማረር ከቶ ስለማይበጅ 10. ስላሣለፍከው ቀን ሁሉ ምሽት በቤትህ ለፈጠረህ አምላክ ምስጋናን አቅርብ ብዙዎች አንተ ያየኸውን ቀን ሳያዮ ብዙ እየተመኙ በህይወት ወደማይቀረው አለም አልፈዋልና ።።።።።።።።።።።።።።።።።። ክፉ እንድናስብ እንድንፈፅም ከዚያም በራሳችን እንድናዝን እንድንፀፀት የሚያረገን የክፋት አባት እሱ ሠይጣን ነውና እሱን በቸርነት በመልካም ስራና በየእምነታችን በፈጣሪ ምስጋና እንበቀለው እንጉዳው ከዚህ በላይ ጉዳትና በቀል የለም ሰው ሳይሆን ሠይጣን ነውና ጠላታችን በሱ ላይ ነው በቀለኝነታችን ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
Mostrar todo...
#በየቀኑ_የምትሰማቸው_5_ውሸቶች #1_ሕልምህን_አሁን_ተወው_ወደፊት_አንድ_ቀን_ታልመዋለህ። አንድ ቀን? አንድ ቀን መቼ ነው? በእርግጠኝነት ያለህ ብቸኛ ቀን ዛሬ ነው፡፡ በሕይወትህ ውስጥ ለውጥ ማምጣት የምትችልበት ብቸኛው ቀን ዛሬ ነው፡፡ ዛሬን፣ የተቀረው አዲስ ሕይወትህ የመጀመሪያ ቀን አድርጋት፡፡ #2_ካልተሳካልህ_አለቀልህ። ስህተት! ይሄ ፍጹም ውሸት የሆነ ረብ የለሽ አባባል ነው፡፡ የመውደቅ አጠገቡም ሆነ ሕይወትህ የመመሰቃቀል ጫፍ እንኳ አልተቃረበም፡፡ በእርግጥ የከፋ ነገር ቢገጥምህ እንኳ አለቀልህ ማለት አይደለም። #3_ሕልም_የምትለውን_ትተህ_አርፈህ_ስራህን_ስራ። መኝታ ክፍልህ ውስጥ ራስህ ላይ ቆልፈህ ሁለተኛ ፈጽሞ ከክፍልህ አለመውጣት፡፡ ልክ እንደዚህ አድርገህ መላው ሕይወትህን እና ሕልምህን ሽንት ቤት ውስጥ ጥለህ፣ በላዩ ላይ በውኃ ማውረድ፡፡ ይህን ነው እየመከሩህ ያሉት። አትስማቸው #4_እሱማ_ሊሆን_አይችልም። አንዳንድ ነገሮች የማይቻሉ የሚመስሉበት ምክንያት ማንም ሰው ገና ስላላሳካቸው ነው፡፡ ይህ ማለት ግን በአንተ እርዳታ እነዚህ ነገሮች ወደፊት አይሳኩም ወይም አይቻሉም ማለት አይደለም፡፡ ለመጨረሻው ውጤት እራስህን የእውነት እስከሰጠህ ድረስ ማንኛውም ነገር የመሆን እድል አለው፡፡ ከአንተ የሚጠበቀው ከልብህ መፈለግ ብቻ ነው፡፡ #5_እድለኛ_ከሆንክ_ብቻ_ነው_የሚሳካልህ። እነዚህ እድለኞች እንዳንተ ያሉትን አሉታዊ ሰዎች አያዳምጡም፡፡ አንድ ነገር ለማሳካት ቆራጥነት፣ ፍቃደኛነት እና ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግ ያውቃሉ፡፡ ቀላልና ፈጣን እንደማይሆንም ያውቃሉ፡፡ ስኬታቸው የሚወሰነው በእነርሱ ብቻ መሆኑንም የሚያውቁ ናቸው፡፡ ከእነሱ መሀል አንዱ መሆን ትችላለህ፡፡ #ልብ_በል እነዚህን ሁሌም የሚደሰኮሩ ሀሳቦች አትቀበላቸው፤ አትመናቸው፤ ፈጽሞ እድል ፈንታ አትስጣቸው፡፡ ወዳጄ- ለማሸነፍ ተፈጥረሀል!! #በራስ_መተማመን_መጽሐፍ 5ተኛው ዕትም በቡክላንድ አሳታሚ ታትሞ በገበያ ላይ ውሏል። በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛል፡፡ 📗📒📕
Mostrar todo...