cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegaciĂłn. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Anel_muslim

Ishek 🙏🙏🙏 Hadis 📘📗📘📗 Sira 📓📓📓 https://t.me/joinchat/AAAAAE5YFEE0qbPPzoWqPQ

Mostrar mĂĄs
Publicaciones publicitarias
569
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 dĂ­as
Sin datos30 dĂ­as

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

እንካን ለ 1498 ለታላቁ ነብዩ ሙሀመድ መዉሊድ በሰላም አደረሳቹ እያልን በአንዋር መስጅድ ነገ ጁመዐ የመዉሊድ መቀበያ ሰለዋት ይቀራል 🤗 ✦✦ قُلْ بِفَضْلِ اللَّهِ وَبِرَحْمَتِهِ فَبِذَٰلِكَ فَلْيَفْرَحُوا هُوَ خَيْرٌ مِّمَّا يَجْمَعُونَ «በአላህ ችሮታና በእዝነቱ (ይደሰቱ)፡፡በዚህም ምክንያት ይደሰቱ፡፡ እርሱ ከሚሰበስቡት ሀብት በላጭ ነው» በላቸው፡፡ ✦✦✦ "በእዝነቱ" የሚለው የተፈለገበት የአለሙን እዝነት ረሱሉላህን ስለመሆኑ አንዳች ሸክ የለውም።ታላቁ የቁርአን ተንታኝ ኢብኑ ዓባስ "ወቢራሕመቲሂ" የሚለው ነብዩን ነው ብለዋል። ✦✦ አዎን! በሚገባ ነው እንጂ ደስ የሚለን።ሙስሊም ሆኖ በነብዩ መምጣት የማይደሰት ማን አለና!? عليك الصلاة والسلام. ሁላቹንም ተጋብዛቹሀል የታላቁ አንዋር መስጂድ ወጣት ጀማዓ
Mostrar todo...
ነቢ ሰዐወ 12 ሚስቶች የነበሯቸው ሲሆን አስራ ሁለቱም የመላው ሙስሊሞች እናት በመባል ይታወቃሉ። እነሱም 1፦ ከዲጃ ቢንቱ ኹወይሊድ 2፦ ሰውዳ ቢንቱ ዘምዓ 3፦ ዓኢሻ ቢንቱ አቢ በክር 4፦ ሓፍሳ ቢንቱ ዑመር 5፦ ዘይነብ ቢንት ኩዘይማ 6፦ ሂንድ ቢንቱ አቢ አመያ 7፦ ዘይነብ ቢንቱ ጃሕሽ 8፦ ጁወይሪያ ቢንቱል ሓሪስ 9፦ ማሪያ ቢንቱ ሸምዑን (አልቂብጢያ) 10፦ ረምላ ቢንቱ አቢ ሱፍያን 11፦ሰፊያ ቢንቱ ሑየይ 12፦ መይሙና ቢንቱል ሓሪስ ነቢ ሰዐወ ከነዚህ እናቶቻችን መካከል ከከዲጃ እና ከማሪያ ብቻ ልጅ ያገኙ ሲሆን ከዲጃ የሚከተሉትን ልጆች ወልዳላቸዋለች። 1፦ ዐብዱላህ 2፦ ቃሲም 3፦ ዘይነብ 4፦ ሩቀያ 5፦ ኡሙ ኩልሱም 6፦ ፋጢማ ማሪየቱል ቂብጢያ ደግሞ የሚከተለውን ወልዳለች። 1፦ ኢብራሂም ነቢ 8 የልጅ ልጆች የነበሯቸው ሲሆን አምስቱ የፋጢማ ሁለቱ የዘይነብ እና አንዱ የሩቀያ ነው። የፋጢማዎቹ፦ 1፦ ሀሰን 2፦ ሁሰይን 3፦ ሙህሲን 4፦ ኡሙ ኩልሱም 5፦ ዘይነብ የዘይነብ ልጆች፦ 1፦ ዐሊይ 2፦ ኡማማ የሩቀያ ልጅ፦ 1፦ ዐብዱላህ አብዝኃኛዎቹ የልጅ ልጆቻቸው በጨቅላ እድሜያቸው የሞቱ ሲሆን የነቢ ሰዐወ ዝርያዎች በፋጢማ (ፅጌረዳችን) ረዐ ልጆች በኩል ሊስፋፋ ችሏል። አላህ በጀነት ከነርሱ ጋር ይሰብስበን። Sefwan Sheik Ahmedin 🌹اللهم صل وسلم وبinارك على سيدنا وحبيبنا وقدوتنا وشفيعنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين🌹 🌹አሏሁማ ሰሊ ዓላ ሙሀመድ ወዓላ ዓሊ ሰይዲና ሙሀመድ🌹
Mostrar todo...
لَّقَدْ كَانَ لَكُمْ فِي رَسُولِ اللَّهِ أُسْوَةٌ حَسَنَةٌ لِّمَن كَانَ يَرْجُو اللَّهَ وَالْيَوْمَ الْآخِرَ وَذَكَرَ اللَّهَ كَثِيرًا ❤️❤️❤️اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وآله وصحبه أجمعين ❤️❤️
Mostrar todo...
🥀 #ያማረ_መገርገበያ 🥀 #ዐመቱን_ሙሉ_ከህመም_መጠበቅ_ይፈልጋሉ? 💚 ሙሀረም 10ኛው ቀን ላይ(አሹራ), ለቤተሠቡ በጣም የሚጣፍጥ ምግብ ካዘጋጀ ቤተሠቡን ካንበሻበሸ (ካስደሠተ) ቤቱ አመቱን ሙሉ በበረካ ይሞላል(አላህዬ ያንበሸብሸዋል) ኪቺራ የተባለውን የአረብ ምግብ መስራትም ይወዳል፤ እኛ ምን አለፋን ለቤተሰባችን የቀለልን ጣዕም ያለው ምግብ ሠርተን ማቅረብና ቤተሰብ ማስደሰት። #ኪቺራ:- የምግብ አይነት የሚዘጋጀው በሚያምር ሁኔታ ከስጋ፣ ከቅባት እህል፣ ገብስ፣ ስንዴ፣ አንዲሁም ሩዝ ተመሳሳይ ይዘት እስኪኖራቸው ድረስ ማብሠል። 💚 #ፋቲሃ ለሠይዱና ዒማም ሁሰይን( ረዲየላሁ ዐንሁ) መቅራትም በጣም የተወደደ ተግባር ነው። 💚 በዚሁ ቀን ማለትም ዐሹራ (ሙሀረም 10 ) አንድ ሠው ገላውን ከታጠበ ከምንም አይነት በሽታ ዐመቱን ሙሉ ይጠበቃል። ምክንያቱም በዚህ በተባረከ ቀን #ዘምዘም_ውሃ አለም ላይ ያሉትን ሁሉንም ውሃዎች ያካልላል(ይደርሳል)። አላህዬ ካገራልን የዘንድሮ ረቡዕ ስለዋለ #ነገ_እንታጠባለን። 👇👇👇 #ዐሽረፈል_ኸልቅ_ሠይዱል_ሙርሠሊን_ሠይዳችን (ሠለላሁ ዐለይሒ ወሠለም ) እንዲህ ብለዋል፦ " #በአሹራ_ቀን_ዐይኑን_ኩል_የተካለ 🖊ሠው ዐይኑን በፍፁም በሽታ አይነካውም "የነብዩላህ ኑህ (ዐለይሂ ሰላም) ህዝቦች ኩል ተኩለው🖊 ነው መርከቡ ላይ የወጡት።
Mostrar todo...
اللَّهُمَّ صَلِّ عَلى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ الفاتِحِ لِمَا أُغْلِقَ و الخاتِمِ لِمَا سَبَقَ نَاصِرِ الحَقِّ بَالحَقَّ و الهَادِي إلى.صِرَاطِكَ المُسْتَقِيمِ و عَلَى آلِهِ حَقَّ قَدْرِهِ و
Mostrar todo...
ጦለዓል በድሩ ዓለይና የተባለለት ኑር ጨረቃ ዛቱ ለመዲና ነዋሪዎች ብቻ አይደለም የወጣው። ለዓለሙ ቢገለጥ ይበቃል። ወቀመሩላሂ፣ ሸምሱ ሸምሱላሂ፣ ኑሩ ኑሪላሂ! ምድር ምጥ በተያዘችበት፣ በቀትር በጨለመችበት ኑር ሆኖ መጣና ከውኑን አበራው! ሲራጀን ሙኒር! ያ ፊቱ ከጨረቃ የሚያበራው የሁለት ሐገር ነጋሴ ወደ መዲና ዘለቀ። ሰማይ እና መሬቱን በብርሃን ሞልቶ ደመቀ። በመዲና ያንን ክስተት ያስተዋለ የአስር ዓመት ልጅ "መዲና በሙሉ ብርሃን ተሞልታ ዋለች" ሲል ተናገረ። ከዓይኖቻቸው ይልቅ ልቦቻቸው ተመለከቱ። በሩህ ሰለሉ። ውስጠታቸው ያንን ውበት አስተዋለ። ባላሰቡት ባልተዘጋጁበት የድንገቴ "ጦለዓ" እያሉ ተቀኙ። ወጣት አዛውንቱ፣ ሴቱ ወንዱ ከቴምሩ ዛፍ እኩል እየተወዘወዘ አዜመለት። ያንን "የቁድሲያ" ብርሃን ተመልክተው ሁሉም ሰለሙ። قد جأكم من الله نور እንዳለው ብርሃኑ ፈነጠቀ። በመካ ሐረም ተረግዘው በመዲና ሐረም ተምጠው እንደተወለዱ ሆነ። ኑሩ ጀለጀላሉሁ ከመዲና ሰዎች ዓይን እና ልብ ላይ የአጝያሩን ሒጃብ ገልጦ የአቅማሩን አንዋር አፈሰሰባቸው። ተመልክተው እንዲጠግቡ አወጀበባቸው። አይተው እንዲረኩ ፈቀደላቸው። አስተውለው እንዲብሰከሰኩ ወሰነባቸው። ጀማላው እንደ ጦር ተወርውሮ በእያንዳንዱ ቀልብ ላይ ተሰካ። ያማ ሶሀብይ رآيت الهلال ووجه النبي وكان هلالين عند النظر فلولا التورد في الوجنتين وما لاح لي سواد من الشعار لكنت اظن الهلال وجه النبي ووجه اللنبي القمر እያለ የፈይዱን ቡን አፈላው። ደንግጦ ኖሯል። በስካር ብዛት ጥቁሩ ፀጉሩ ሊነጣ ደረሰ። ዓይኑ እየተጥበረበረ ሁለት ጨረቃ ያያል። እንዲያው ነቢ ባያዝኑለትማ ኖሮ ዓይኑ በነቢ ኑር ተይዞ ይቀር ነበረ። ሐድረተል ጀላላው ገለጥ ያለ ጊዜ ለነፍስ ፋታ አይሰጥም። ወጀላሉላሂ፣ ወጀማሉላሂ፣ ወከማሉላሂ፣ ወሒጃቡላሂ አሏቸው‘ኮ አቦ። በገላጣዋ የፀሀይ ብርሃን ውስጥ ሩሖች ያንን የጨረቃ ብርሀን ያስተውሉ ዘንድ አላህ ልዩ ተአምር አድርጎ ሠራቸው። ሙሐመድዩን ኑራኒዩን የፈጠራቸው ጊዜ ኑሩ ተወርውሮ ይህቺን ከውን ደበሰቃት። ለዛም "ከጌታችሁ ዘንድ ብርሃን መጣችሁ" ተሰኙ። ዓይኑ የተገለጠለት ሰው እየሰለለ እስከ ሩሑ ይዘልቅበታል ያን የጀማል ኑር። ሰይድ ዑመር ኑሩ ተንቧልቆባቸው ነበረ። ያንን የተቅዋ ኑር ይዘው "ጦለዓ" ያሰኘውን፣ ነብዬ ከሲዲቁ ጋር የሃብሉላህን ገመድ አጥብቀው ያሰሩበትን፣ "ዓልይም በቦታው ተኛለት ሊሞት" ያስባለውን የሒጅራ ቀን ይዘው የኢስላምን ቀን መቁጠሪያ አድርገው ቀመቀሙት። ከቃፍ እስከ ቃፍ ሙስሊሙ በዚህ የኑር ቁጥር ይቆጥራል። ያ ኑር መዲና የዘለቀበት ቀን የሰው ልጅ ሕይወት የተቀየረበት፣ የሙስሊም ሐገራት አመራር የተቃናበት፣ የኢስላም ጁንድ የተበራታበት ቀን ሆነ። ያ ብርሃን ልብን እና ሰውነትን፣ ህግን እና አስተዳደርን አዳረሰ። ቤት እና ቤተ መንግስት፣ መስጂድ እና ገበያን አጣጥሞ አፀና። የትልቁ ሠው ስደት በፈትሕ፣ ሀዘኑ በሳቅ ነው የተደመደመው። ለኛም የጭንቅ መፍፈረጃ የኸይራቱ ሁላ መከፈቻ ዓመት ያድርግልን። ቀልባችንም ዳኢም ወደ መዲና ተጓዥ ይሁንልን። አሚን እንኳን አደረሰን!💚💚💚
Mostrar todo...