ህይወትን በጥበብ
Ir al canal en Telegram
CONTACT ADMIN👦➖ @Eftah12 GROUP :- https://t.me/big_dreamerss
Mostrar más1 085
Suscriptores
+424 horas
+57 días
+3830 días
Archivo de publicaciones
1 085
#አእምሮህ_በችግር_ይደንሳል
አብዛኛው ጭንቀት የሚመጣው ልትቆጣጠረው የማትችለውን ነገር ከመለየት ሳይሆን፣ ልትቆጣጠረው የማትችለው ከሚመስለው ትንሹ ነገር ነው።
ታዲያ አእምሮህ ይህንን የሚፈልገው ለምንድነው?
ባለህ ነገር መደሰትና አመስጋኝ መሆን አትችልም?
የሆነ ደረጃ ድረስ በእርግጠኝነት ትችላለህ።
ነገር ግን አእምሮህ ችግር ይፈልጋል፤ ፊት ለፊትህ ችግር ባይኖር እንኳን በደመ ነፍስ ችግሮችን መፍጠር ይቀጥላል።
የሰው አእምሮ ኢ-ተሰባሪ የሚባል ነው፤ ይህም ማለት ችግር ሲያጋጥመው የበለጠ ይጠነክራል ማለት ነው። ስለዚህ አለት ከፍተኛ ግፊት ሲያጋጥመው አልማዝ እንደሚሆነው ወይም አካል በተደጋጋሚ ለጀርሞች ሲጋለጥ የበሽታ መከላከያ ስርዓቱን እንደሚያጠነክረው ሁሉ፣ አእምሮም ለመነቃቃት ችግር ይፈልጋል።
በሕይወትህ ውስጥ ማንኛውንም አይነት እውነተኛ ፈተና የምትክድና የማትቀበል ከሆነ፣ አእምሮህ የሚያሸንፈው ሌላ ችግር በመፍጠር ሁኔታውን ያካክሰዋል። በመጨረሻ ሽልማት የሚኖረውም ፈተናዎችን ተጋፍጠህ ማለፍ ስትችል ነው፤ ያ ካልሆነ በቀሪው ሕይወትህ ብቻህን ስትዋጋ ትኖራለህ።
አእምሮህን እያሟሸሸው ያለው ደስታን ማሳደድ፣ ትንሽም ቢሆን ፈታኝ ከሆኑ ነገሮች መሸሽና እያጋጠመህ ያለው ፈተና የእጣ ፈንታ ስህተት እንጂ ሕይወት ከመጀመሪያውም ጥሩ ናት ብሎ ከማሰብ ባህል ነው።
@lifeandwisdom
1 085
#ይሄኔ_የት_በደረስኩኝ_ነበር?!
• ሰዎች በእኔ ላይ ምን እንደሚያስቡ ለማወቅ የታገልኩትን ያህል ራሴን ለማወቅ ብሰራ ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!
• በፍጹም የማይፈልጉኝን ሰዎች ስለማመጥና ስከታተል ያሳለፍኩትን ጊዜ ለእኔ ዋጋ ላላቸው ሰዎች ሰጥቸው ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!
• በማያገባኝ የሰዎች ስራና ሃሳብ ላይ በማውራትና በመቃወም ያባከንኩትን ጊዜ የሚደገፍ ሰው ፍልጌ ደግፌ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!
• በየጊዜው ካለእቅድ የማወጣቸውን የገንዘብ መጠኖች በጥንቃቄ ብቆጥባቸው ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!
• ምንም ያህል ብጨነቅ መለወጥ በማልችላቸው ነገሮች ላይ መጨነቄን ትቼ ለመለወጥ አቅም ያለኝ ነገሮች ላይ አተኩሬ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!
• የሚወዱኝ ቤተሰቦቼና ጓደኞቼ ሲመክሩኝ የመስማትና ጥሩውን ምክር የመቀበል ልማድ ኖሮኝ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!
• ለመጀመር ያሰብኳቸውን እነዛን ወሳኝ ነገሮች ጀምሬያቸው ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!
• የማይሆኑ የማሕበራዊ ጎጾች ሳስስ ያመሸሁባቸውን ምሽቶች የቀኑን ውሎየን ለመገምገምና ለነገ በማቀድ ባሳልፋቸው ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!
• ለየእለት ገጠመኞች ምላሽ እየሰጡ ከመሯሯጥ ይልቅ በራእይና በዓላማ ኖሬ ቢሆን ኖሮ . . . ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!
ያም ሆነ ይህ ያለፈው አልፏል! ከጥቂት አመታት በኋላ እንደገና “ይሄኔ የት በደረስኩኝ ነበር?!” የሚል የግምገማ ስሜት እንደሚመለስብኝ ስለማውቅ አሁኑኑ ለውጥን አመጣለሁ።
@lifeandwisdom
1 085
#ራስህን_ፈውስ!
ሰዎች ጠቃሚ ውስጥን የመለወጥ ስራ ከመሥራት የሚቆጠቡበት አንዱ ትልቁ ምክንያት ራሳቸውን መፈወስ ከቻሉ፣ ሕይወታቸው በከፍተኛ ሁኔታ የሚለወጥ መሆኑን በመገንዘባቸው ነው። ምን ያህል ደስተኛ እንዳልሆኑ መረዳት ማለት፣ ሁሉንም ነገር እንደገና መጀመር ማለት በመሆኑ ለጊዜውም ቢሆን የበለጠ ምቾት የማጣት፣ የማፈር ወይም የመፍራት ስሜት እንደሚያጋጥማቸው ያስባሉ።
እዚህ ላይ ስለ አንድ ነገር ግልጽ እንሁን፤ ራስን የማሸማቅቅ ባህሪይህን ማቆም ማለት ለውጥህ ያለው ቅርብ ነው ማለት ነው።
አዲሱ ሕይወትህ አሮጌውን ሕይወትህን ያሳጣሃል፡፡
የምቾት ቀጠናህን እና የጉዞ አቅጣጫህን ያሳጣሃል፡፡
ግንኙነቶችህንና ጓደኞችህን እንዲሁም መወደድህንና መረዳትህን ያሳጣሃል፡፡
ግን ይህ ሁሉ ምንም አይደለም።
ምክንያቱም ለአንተ የተባሉ ሰዎች በሌላ በኩል ሊያገኙህ ነው፤ ወደ ፊት እንድትንቀሳቀስ በሚያደርጉህ ነገሮች ዙሪያ አዲስ የምቾት ቀጠና ልትገነባ ነው። በዚያም ውስጥ ከመወደድ ይልቅ ትፈቀራለህ። ከመረዳት ይልቅ ትታያለህ፣ የምታጣው ነገር ቢኖር ከዚህ በኋላ በማይኖረው የቀድሞ ማንነትህ የተሰራውን ብቻ ነው።
ከአሮጌው ሕይወትህ ጋር ተጣብቆ መቆየት ራስን የማሸማቀቅ የመጀመሪያና የመጨረሻ ድርጊት ነው። ስለዚህ እሱን በመልቀቅ እውነተኛ ለውጥ ለማየት ፈቃደኛ ለመሆን የተዘጋጀህ መሆን ይኖርብሃል።
@lifeandwisdom
1 085
Repost from ሰማያዊ ሕዝብ
የአውሮፓ ፕሮሰስ መጀመር ለምትፈልጉ!!
ከ2-3 ወራት ውስጥ የሚያልቅ የአውሮፓ የስራ እና የትምህርት ፕሮሰስ ወደ ተመረጡ የአውሮፓ ሐገራት እንሰራለን።
ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ የለውም።
DM
👇
@GebrielFox
@GebrielFox
1 085
#እንደገና_ልትወለድ_ነው!
ስራውን ተራራው ስር ለመስራት ፍቃደኛ ከሆንክ፣ ሕይወትህን ሙሉ ስትጠብቀው ወደነበረው ስኬት መግቢያ ሆኖ ታገኘዋለህ።
ይህ ሲሆን አሮጌው ማንነትህ ከዚህ በኋላ ልትመራው እየሞከርክ ያለኸውን ሕይወት ይዞ ማቆየት ስለማይችል፣ እንደገና መፈጠርና እንደገና መወለድ ይኖርብሃል ማለት ነው።
ስለሆነም፣ አሮጌውን ማንነትህን በራዕይህ እሳት በማቃጠል ከዚህ በፊት ሞክረኸው በማታውቀው መንገድ ለማሰብ ፈቃደኛ መሆን ይጠበቅብሃል።
ይህንን ለማድረግ ደግሞ አንተን እስከዚህ ያደረሰህን፣ ነገር ግን ወደፊት ሊያራምድህ በቂ ትጥቅ የሌለውን የቀድሞ ማንነትህን በማጣትህ ማዘንህን ትተህ ከአሁን ጀምሮ የሚመራህን፣ የሕይወትህ ጀግና የሆነውን የወደፊቱን ማንነትህን ማየትና ከእርሱ ጋር አንድ መሆን አለብህ።
ከፊትህ ያለው ተግባር ጸጥ ያለ፣ ቀላልና እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡ ትልቅ ተግባር በመሆኑም ብዙዎቹ ሙከራ ላይ እንኳ አይደርሱም፡፡ ስለዚህ አሁን ቅልጥፍናን፣ ጽናትንና ራስን መረዳትን በመማር ፈጽሞ ከዚህ በፊት የነበርከው አይነት ላለመሆን ሙሉ ለሙሉ መለወጥ አለብህ።
ከፊትህ የቆመው ተራራ የሕይወትህ ጥሪ፣ እዚህ የመሆንህ አላማህና ግልፅ የሆነው መንገድህ ነው። አንድ ቀን፣ ይህ ተራራ ከኋላህ ቀርቶ ታየው ይሆናል፤ በማለፍ ሂደቱ ውስጥ ያገኘኸው ማንነትህ ግን ሁልጊዜ ከአንተ ጋር ይቆያል።
በመጨረሻም ልትቆጣጠረው የሚገባው ተራራውን ሳይሆን ራስህን ነው!
@lifeandwisdom
1 085
"መጀመሪያ የራስህን ድክመትና ጥንካሬ ተቀበል፤ ከዛ ራስህን ውደድ በመጨረሻ ሁሌም ወደፊት ተጓዝ! መብረር የምትፈልግ ከሆነ ወደታች የሚጎትቱህን ነገሮች ሁሉ ማራገፍ አለብህ" ይለናል ሮይ ቲ ቤኔት የተባለ ደራሲ።
በዚህ አለም አስደሳቹ ነገር የራሳችንን እጣ ፋንታ መወሰን የምንችለው ራሳችን ነን። ፈጣሪማ በራሱ አምሳል ፈጥሮ ለማንም ፍጥረት ያልሰጠውን ነፃ ፍቃድ ሰጠን። ምርጫው በእጃችን ነው!
@lifeandwisdom
1 085
"መጀመሪያ የራስህን ድክመትና ጥንካሬ ተቀበል፤ ከዛ ራስህን ውደድ በመጨረሻ ሁሌም ወደፊት ተጓዝ! መብረር የምትፈልግ ከሆነ ወደታች የሚጎትቱህን ነገሮች ሁሉ ማራገፍ አለብህ" ይለናል ሮይ ቲ ቤኔት የተባለ ደራሲ።
በዚህ አለም አስደሳቹ ነገር የራሳችንን እጣ ፋንታ መወሰን የምንችለው ራሳችን ነን። ፈጣሪማ በራሱ አምሳል ፈጥሮ ለማንም ፍጥረት ያልሰጠውን ነፃ ፍቃድ ሰጠን። ምርጫው በእጃችን ነው!
ቆንጆ የረመዳን ቅበላ ተመኘንላችሁ🙏
@factamharic
1 085
Repost from ሰማያዊ ሕዝብ
ኢየሱስ ፈራጅ ነው ወይስ አማላጅ⁉️
.
የማቴዎስ ወንጌል ምን ይላል...?
ያልተገለጠው ሚስጥር‼️
👇👇
ማቴ ፤ 24፥ ... ኢሳ ፤ 33፥ ...
ሉቃ ፤ 12፥ ... ራዕ ፤ 8፥ ...
👇
https://t.me/addlist/k9NjaF5377BkYzQ0
https://t.me/addlist/k9NjaF5377BkYzQ0
1 085
#ሰጠሁ_ብለህ_አታውራ!
❇️ ስለራስህ ማሰብ ያቆምክ ጊዜ... ሌሎችን እንዴት መጥቀም እንዳለብህ ወይም እንደምትችል ታስባለህ።
እመነኝ ለራስህ ሳትሆን ለሌሎች ማሰብ ጀምረሃል ማለት ገና ስሜታዊነቱን ያላሸነፈ፣ ራሱን የሚያታልል አቡሽ ነህ።
❇️ ይህን ስልህ ለማንም አታስብ ማለቴ አይደለም። አንዳንዴም ለሰዎች ያደረግክ ይመስልሃል እንጂ ምስጥ ብለህ ስታስብ አደረግኩለት የምትለው ሰው ያልተናነሰ እያገዘህ ይሆናል።
ብታበላው ወንድምነቱን፣ ብታለብሰው ወዳጅነቱን፣ ብታቀርበው ታማኝነቱን ባለው ለሚያካፍልህ ሰው በቁስ በገንዘብ በልጠህ ብትገኝ ሰጪነት አይሰማህ።
❇️ ሰጠሁ ማለት ያለብህ በህይወትህ ምንም ለማያበረክት ለማታውቀው ሰው ነው።
ሆኖም ለራስህ መሆን ሳትጀምር ካቅምህ በላይ፣ ከሁኔታህ ጋር የማይጣጣም ነገር ለሌሎች ብታደርግ ትርጉም የለሽ ይሆናል።
☑️ ቅድሚያ ለራስህ ስራ። ከዛ ለምታስፈልጋቸው ጊዜ ይኖርሃል።
@lifeandwisdom
1 085
" ስሞት ዘቅዝቃችሁ ቅበሩኝ ራሱን ዝቅ ያደረገ አንድ ቀን ከፍ ማለቱ አይቀርምና "
/ ዲዮጋን /
ተአምረኛው ዲዮጋን እቺን የተናገራት በጊዜው የነበሩት ባላባቶች ሥለ አቀባበራቸው ይጨነቁ እንደነበር ባስተዋለ ጊዜ ነው ። ሕይወትን እንዴት እንደሚኖራት ያላወቀ ሰው ስለሞት እና በክብር ሥለመሞት ሲያስብ እና ሲጨነቅ ማየት አሁን አሁን በእኛም አገር የተለመደ እውነታ ነው ። በውድ የሬሳ ሳጥን መቀበር እና በአበባ መሽቆጥቆጥ በህይወት እያለ አንድ አበባ እንኳን ተክሎ የማያውቅ ሁሉ ሲሞት በአበባ ይከበባል የኛ ሰው በቁሞ ሳይሆን ሞቶ ውድ ነው መሰል...!
፧
በግብፃውያን ዘንድም ፈርኦኖች ሲሞቱ በዛኛው አለም እንዳይፈሩ ተብሎ ሎሌያቸው ከነሕይወቱ በፍቃዱ አብሯቸው ይቀበር እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ይናገራሉ...ዛሬም ከነመኪናቸው የተቀበሩ ዜጎች እንዳሉ መረጃዎችን በየሚዲያው እንሰማለን...የጆሮ ስብአቱ አለመሙላቱ ... ነውና መቻል ነው እንግዲህ
" እንዴት እንደምትኖር ካላወቅህ ሥለሞትህ ልትጨነቅ አይገባም ። "
/ ኮንፊሺየስ /
@lifeandwisdom
1 085
የፈላስፋው ጥመት...
፨፨፨
የጠርጣሪነት ፍልስፍና (scepticism) ጀማሪ እንደሆነ የሚታመንለት የጥንቱ ፈላስፋ ፊሮ አንድ ቀን ጥበብን ያካፍላቸው ዘንድ ወደጋበዙት ሰዎች በማለዳ አመራ። በቦታው ሲደርስ ቁጥሩ እጅግ የበዛ ሰው ተሰብስቦ ሲጠብቀው ተመለከተና ወደተዘጋጀለት የከፍታ ቦታ በዕርጋታ ወጥቶ ቆመ። ፊሮ ትምህርቱን ከመጀመሩ በፊት ጥያቄ ወረወረ፦
<<ዛሬ እዚህ የተሰበሰባችሁት ከእኔ ልትማሩ ነው?>> ተማሪዎቹ በአንድ ድምፅ አዎንታቸውን ገለፁ።
<<እንግዲያውስ ስለምን እንደማስተምር ታውቃላችሁ ማለት ነዋ?>> አለ ፊሮ።
<<ኧረ ምንም አናውቅም>> አሉ ተማሪዎቹ አሁንም በአንድ ድምፅ።
<<ስለምን እንደማስተምር ካላወቃችሁማ ዝም ብዬ ማውራት አልፈልግም>> አለና ከመድረኩ ወርዶ ወደ ቤቱ አመራ።
በነጋታው አሁንም በዚያው ቦታ ህዝቡ ተሰብስቦ ይጠብቀው ጀመር። ፊሮም መጣና በእርጋታ ወደ መድረኩ ወጣ።
<<ዛሬስ ስለምን እንደማስተምር አውቃችኋልና?>> በማለት ጠየቀ።
የተሰበሰበው ህዝብ በአንድ ቃል አዎንታቸውን ገለፁ።
ፊሮም <<ካወቃችሁትማ ወደ ቤቴ ልሂድ....>> በማለት ከከፍታው ላይ ወረደ።
በሚቀጥለው ቀን ወደ ቦታው ሲያመራ አሁንም ህዝቡ ተሰብስቦ እየጠበቀው ነው። የዚያን ቀን ግን ህዝቡ መልሳቸውን አዘጋጅተው ነበር የጠበቁት።
ፊሮም ወደ ከፍታው ከወጣ በኋላ፦<<ዛሬስ ስለምን እንደማስተምር ታውቃላችሁ..?>> አለ።
ህዝቡም፦<<ግማሾቻችን እናውቃለን፤ግማሾቻችን ደግሞ አናውቅም...>> አሉት።
ፊሮም፦<<እንግዲያውስ ግማሾቻችሁ የምታውቁት፤ ለግማሾቹ የማያውቁት ንገሯቸው!..>
፨፨፨
፨ አሁን በእናንተ አረዳድ በፈላስፋው ላይ ነው ወይስ በተከታዮቹ ላይ ነው የሚፈረደው...?
@lifeandwisdom
1 085
#ጣቢያው_እንደተበላሸ_ቴሌቭዥን_አትሁን!
የአንጎል ተመራማሪዎች የአንጎልን እያንዳንዱን ክፍል ከመረመሩ በኋላ አንድ ውጤት ላይ ደረሱ፡-
ከጽሞና በፊት እና በኋላ ያለውን የአንጎል ሁነት ለመግለጽ የቤታን መጠን ከዴልታ ጋር አካፈሉት።
ቤታ ሲካፈል ለዴልታ ያለውን መጠን፤ ከጽሞናው በፊት፣ በጽሞናው ሂደት ላይና ከጽሞና በኋላ ያለውን ለኩት። እያንዳንዱ የጽሞና ሂደት የተለያየ ቢሆንም፣ ውጤቱ እንደሚያሳየው ግን በአብዛኛው ጽሞና የቤታን ሞገድ የሚቀንስ እና የዴልታን ሞገድ የሚጨምር ሆኖ ተገኝቷል።
ይህም ወደ አንድ መዳረሻ ውጤት ያደርሰናል፤ ጽሞና ሁሉንም ይሁን ብለን የምንቀበልበት መንገድ ነው።
የቤታ መብዛት በአእምሮህ ላይ የበዛ ጭንቀት እንዳለ ማሳያ ነው። እናም በየሄድክበት ሁሉ አብዝተህ ትጨነቃለህ።
“ነገ ምን ይሆናል…”
“ሰዎች አፍጥጠው እያዩኝ ነው ስለ እኔ ምን እያሰቡ ይሆን?…”
“ምን አይነት አለባበስ ነው ለብሼ የወጣሁት?”
“ምናለ እንደዚህ ባልላት...” አእምሮ ንዝነዛውን አያቆምም። ጸጥ ማሰኛ የለው፣ ያለማቋረጥ እዥዥዥዥ ይላል- ልክ ጣቢያው እንደተበላሸ ቴሌቭዥን።
@lifeandwisdom
1 085
Repost from ሰማያዊ ሕዝብ
ኢየሱስ ፈራጅ ነው ወይስ አማላጅ⁉️
.
የማቴዎስ ወንጌል ምን ይላል...?
ያልተገለጠው ሚስጥር‼️
👇👇
ማቴ ፤ 24፥ ... ኢሳ ፤ 33፥ ...
ሉቃ ፤ 12፥ ... ራዕ ፤ 8፥ ...
👇
https://t.me/addlist/k9NjaF5377BkYzQ0
https://t.me/addlist/k9NjaF5377BkYzQ0
1 085
#አትሸወድ
ሰዎችን በተግባራቸው መዝናቸው. . .
ቃላቸውም አይሸውድህ!
ይህን ተረዳ፦ ቃላቶች በጣም የተለመዱ እና ምንም የተለየ ዋጋ የሌላቸው ናቸው።
በክርክር ውስጥ ሁላችንም አላማችንን ለመደገፍ ማንኛውንም ነገር ልንናገር እንችላለን። መጽሐፍ ቅዱስን እንጠቅሳለን፣ የማይረጋገጥ ስታቲስቲክስ በመረጃነት እናቀርባለን።
ነገር ግን ከእነዚህ ይልቅ ድርጊት እና ማሳያ የበለጠ ሃያል እና ትርጉም ያላቸው ናቸው። ምክንያቱም እነሱ በዓይናችን ፊት ያሉና ልናያቸው የምንችላቸው ናቸው፤ እነሱን በተመለከተ ምንም አናዳጅ ቃላት የሉም፤ የተሳሳተ ትርጉም የለም። በተረጋገጠ ማስረጃ ማንም ሊከራከር አይችልም።
ባልታሳር ግራሲያን እንደተናገረው፣ "እውነት በአጠቃላይ የሚታይና፣ አልፎ አልፎ የሚሰማ ነው።"
@lifeandwisdom
1 085
#ፉክክራችን_ከራሳችን_ጋር_ይሁን!
እዚህ ምድር ላይ ፈጣሪ ሲያመጣን እጅግ የተለያየ አድርጎ ነው። የጣት አሻራችን፣ የአይን አሻራችን አለም ላይ ያለን የቢሊዮናችንም ሰዎች የተለያየ ነው። የመንትዮች ሳይቀር የተለያየ ነው። ስለዚህ አበርክቷችንም የተለያየ ነው ማለት ነው። ይህ በሆነበት ሁኔታ ራስን ከሌላው ጋር ማነፃፀርና ህይወትን በዛ ቅርፅ መምራት ብዙ ሰው ላይ የሚስተዋል በሽታ ነው።
➢ራሱን ከሌላ ጋር የሚያነፃፅር ሰው ሁሌም ተሸናፊ ነው። ምክያቱም በዛ ሰው የተቀደመ ጊዜ የውስጥ ሰላሙን ያጣል ፤ የቀደመ ጊዜ ደግሞ መጨረሻው ያ መስሎት እንዲቆም እና ከዕድገት እንዲገታ ያደርገዋል። ከሌላ ጋር መወዳደር የጀመርን ጊዜ እዛው ላይ ተሸንፈናል!
ስለዚህ ወዳጆቼ ፉክክራችን ውስጣችን ካለው አቅም ጋር እና ከቀደመ ማንነታችን ጋር ይሁን። "አምና ከነበርኩት እኔ ምን ጨምሬያለሁ?" ብለን ራሳችንን እንጠይቅ።
@lifeandwisdom
