ዛዱል ኸይር Zadul Kheir
(መልካም ስራ ከክፉ አወዳደቅ ይጠብቃል) صنائع المعروف تقي مصارع السوء
Mostrar más207
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
- Suscriptores
- Cobertura postal
- ER - ratio de compromiso
Carga de datos en curso...
Tasa de crecimiento de suscriptores
Carga de datos en curso...
በግና ፍየል በረከት ናቸው
አሏህ በበግና ፍየል በረከት አድርጓል። በአመት አንድ ጊዜ ሲወልዱ ትመለከታለህ ፤ አሏህ የሻው ያክል ከስጋቸው ይበላል ፤ ከአራዊቶች በተቃራኒ በነርሱ ምድር ትጥለቀለቃለች ፤ አራዊቶች በአንድ ጊዜ ስድስት ወይም ሰባት ልጅ ይወልዳሉ ፤ የምድር ጥግ ላይ እንጂ አይታዩም። በግና ፍየል ተወዳጅ የተባረኩ ገንዘቦች ናቸው።¹
ከሚገርመው ተፈጥሯቸው ሰውነታቸው ግዙፍ የሆኑትን ዝሆን እና ጎሽ ተመልክተው አይፈሩም። ተኩላ ሲመለከቱ ግን በብርቱ ይፈራሉ። ይህም አሏህ በተፈጥሯቸው የፈጠረው ነገር ስላለ ነው።²
በግና ፍየል በዋነኝነት የስጋ ፥ የወተት እና የሱፍ ምንጭ ሁነው ለሰው ልጅ ሲያገለግሉ ቆይተዋል። ፍየል በወተት ብዛት እና በቆዳ ውፍረት ከበግ ይበልጣሉ። በጎች ደግሞ ከፍየል የበለጠ የብዙ ፀጉር ባለቤት(ሱፍ) ናቸው።
ሑመይድ ብኒ ማሊክ ብኒ ኹሰይሚ እንዲህ አለ፦ ❝ከአቡ ሁረይራ ጋር ''ዐቂቅ'' በሚባል ቦታ ተቀምጠን ሳለ የመዲና ሰዎች በግመል ላይ ሁነው ወደ እኛ መጡ ፤ ከግመላቸው ላይ ወረዱ። አቡ ሁረይራ «ወደ እናቴ ሂድና ልጅሽ ሰላምታ ያቀርብልሻል ፤ የሆነ ነገር መግቢን ይልሻል» በላት አለኝ። (ሂጄ ስነግራት) በትሪ የተወሰነ ዘይትና ጨው አድርጋ ከገብስ የሆነ ሶስት ዳቦ ጋር አቀረበች። ተሸክሜ ወደነርሱ ይዤ በመሄድ ፊትለፊታቸው አስቀመጥኩት። ያኔ አቡ ሁረይራ «አሏሁ አክበር»አለ። በመቀጠል «ለአሏህ ምስጋና ይግባው ! ምግባችን ተምርና ዉሃ ሆኖ ሳለ ዳቦ ለመገበን ጌታ» አለ። ሰዎቹ (እንግዶቹ) ከምግቡ ምንም አልቀመሱም። እነርሱም በሄዱ ጊዜ እንዲህ አለኝ፦«የወንድሜ ልጅ ! ለበጎችህ መልካም ሁን ፤ ንፍጣቸውን ጥረግ ፤ በረታቸውን (ማደሪያቸውን) አሳምር ፤ በዙሪያቸው ስገድ ፤ እነርሱ የጀነት እንስሳ ናቸው። ነፍሴ በእጁ በሆነችው አሏህ እምላለሁ ወደ ፊት በሰዎች ላይ የተወሰኑ በጎች ያሉት ሰው እርሱ ዘንድ ከመርዋን መኖሪያ ቤት የበለጠ ተወዳጅ የሚሆኑበት ዘመን መምጣቱ በጣም ቅርብ ነው።»❞ [ማሊክ “ሙወጠእ” (2/933) ፤ አል አደቡል ሙፍረድ 572]
ይቀጥላል...
የካቲት 06/2015
https://t.me/ZadulKheir
ከአንቀፆች ጋር ⓶⓶⓻
قَالَ هَلْ ءَامَنُكُمْ عَلَيْهِ إِلَّا كَمَآ أَمِنتُكُمْ عَلَىٰٓ أَخِيهِ مِن قَبْلُ
«ከአሁን በፊት በወንድሙ ላይ እንዳመንኳችሁ እንጂ በእርሱ ላይ አምናችኋለሁን። [ዩሱፍ 64]
«ሙእሚን በአንድ ጉድጓድ ሁለት ጊዜ አይነደፍም።» (لا يلدغ المؤمن من جحر مرتين) የሚለውን ይጠቁመናል።
#ከተረሱ ሱናዎች ⓵⓶
ለይለተል ጁሙዓ ሶለዋት ማብዛት
***
ነብዩ(ﷺ) እንዲህ ብለዋል:- «የጁሙዓ ቀንና ሌሊት ሲመጣ በኔ ላይ ሶለዋት አብዙ»
አልባኒ ሐሰን ብለውታል
"اختر من تزرعهم في أرض قلبك بدقة، اختيار البذور أسهل من اقتلاع الأشجار.