Ethiopian Architecture Construction and Urbanism
It is a platform for information on historical and contemporary architecture, urbanism, landscape, and the construction industry inside Ethiopia. It will also include similar issues from across the world.
Mostrar más12 117
Suscriptores
+3024 horas
+1767 días
+80630 días
Archivo de publicaciones
የሐዘን መግለጫ
በEiABC, አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከ 2005 ዓም ጀምሮ የ ሺዥዋል አርት እና ስኬች መምህር የነበሩት አቶ ግዛው ስዩም ባደረባቸው ሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
የቀብራቸው ስነ ስርዓት የሚካሄደው ነገ 024/9/2016 06:00 ሰዓት ሳህሊተምህረት ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡
ለቤተሰቦቻቸው እና ለስራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።
@ethiopianarchitectureandurbanism
😢 21👍 2
ቢግ ፋይቭ ኮንስትራክት ኢትዮዽያ።
ቢግ ፋይቭ ኮንስትራክት ኢትዮዽያ አውደ ርዕይ በሚሌኒየም አዳራሽ ለሁለተኛ ቀን እየታየ ነው ያለው። የሁሉንም ቀን ትምህርታዊ ንግግሮች መርሀግብር ለማወቅና ለመከታተል የሚከተለውን ማስፈንጠርያ መጠቀም ይችላሉ።
https://www.big5constructethiopia.com/agenda/
@ethiopianarchitectureandurbanism
👍 3
ባህርዳር ዩኒቨርስቲ አርኪቴክቸር ተማሪዎች ማህበር የመጀመርያ ስብሰባ
(Bahir Dar University Architecture Students Association, BASA Launching)
ምንጭ። BASA Linkedin ገጽ
@ethiopianarchitectureandurbanism
👍 12
ቢገ3 ፋይቭ ኮንስትራክት ኢትዮጵያ በክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር በክብርት ጫልቱ ሳኒ በሚሌኒየም አዳራሽ ውስጥ ተመርቋል።
Big 5 Construct Ethiopia's opening ceremony was honored by the presence of H.E. Temesgen Tiruneh - ተመስገን ጥሩነህ, Deputy Prime Minister of Ethiopia and H.E. Chaltu Sani - ጫልቱ ሳኒ Minister, Ministry of Urban and Infrastructure who shared their insights on the construction industry and officially declared the show open.
Visit Big 5 Construct Ethiopia happening now at Millennium Hall, Addis Ababa
ምንጭ። Big 5 Construct Ethiopia
@ethiopianarchitectureandurbanism
👍 4😁 1
ሁለት ባለ 9 ወለል ዘመናዊ ሕንጻዎች እና የስራ ዕድል መፍጠሪያ ማዕከላትን ተመርቀው ለአቅመ ደካሞች ተላለፉ።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ "በጎነት" ተብሎ በተሰየመ የመኖሪያ መንደር የተገነቡ ሁለት ባለ 9 ወለል ዘመናዊ ሕንጻዎችን እና የስራ ዕድል መፍጠሪያ ማዕከላትን መርቀው ለአቅመ ደካሞች እና አካል ጉዳተኞች አስተላልፈዋል።
በመኖሪያ መንደሩ የተገነቡት ሁለት ባለ 9 ወለል ዘመናዊ ሕንጻዎቹ እና የስራ ዕድል መፍጠሪያ ማዕከላቱ ለ140 አቅመ ደካሞች እና አካል ጉዳተኛ ነዋሪዎች ተላልፈዋል።
በልደታ ክፍለ ከተማ ቆርቆሮ ሰፈር በሚባለው የተጎሳቆለ የመኖሪያ መንደር ይኖሩ ለነበሩ አቅመ ደካሞች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ማየት ለተሳናቸው፣ ለተለያየ ማህበራዊ ችግር ለተጋለጡ እና በልማት ለተነሱ ነዋሪዎች የተላለፉት የመኖሪያ ቤቶች፤ ሳሎን፣ መኝታ ቤት፣ የማብሰያ እና የመጸዳጃ እንዲሁም የመኝታ ክፍሎች ያላቸው ቤቶች ናቸው።
በዚህ የ"በጎነት" መንደር ከተላለፉ የመኖሪያ ቤቶች ጋር በማቀናጀት የህጻናት ማቆያ፣ ለእናቶች የስራ ዕድል የሚፈጥር የእንጀራ መጋገሪያ፣ የወንዶችና የሴቶች የውበት ሳሎኖችን እንዲሁም የልብስ ስፌት ማሽኖች ለነዋሪዎቹ የስራ እድል እንዲፈጥሩ ተዘጋጅተዋል።
ማየት ለተሳናቸው ነዋሪዎች ከዘራዎች፣ ለአካል ጉዳተኛ ነዋሪዎች ደግሞ ክራንችና ዊልቸሮችን ሰጥተዋል።
ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመተባበር ቤቶቹን የገነባውን ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በራሳቸውንና በነዋሪዎች ስም አመስግነዋል፡፡
ምንጭ። EBC
@ethiopianarchitectureandurbanism
👍 5❤ 3
መሰረተልማት።
በመጪው ዓመት አጋማሽ ላይ ይጠናቀቃል ተብሎ ለሚጠበቀው ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የዲያስፖራው ድርሻ እስካሁን 0.5 በመቶ መሆኑ ተነግሯል።
ለኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ እስካሁን በጠቅላላ ከዋለው ገንዘብ አኳያ የዲያስፖራው ማህበረሰብ ያበረከተው አስተዋፅዖ ከ1 በመቶ በታች መሆኑ ተሰምቷል።
ግዙፉ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ያለበትን ደረጃ አስመልክተው ገለፃ ያደረጉት የፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ አጠቃላይ ፕሮጀክቱ 96 በመቶ መድረሱንና በመጪው እስከ ጥር ወር 2017 ዓ.ም. ድረስ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነዉ ብለዋል።
ኢንጅነር ክፍሌ አያይዘውም እንደተናገሩት ለግድቡ ግንባታ ድጋፍ ከዲያስፖራው የተደረገዉ ከ 1 በመቶ በታች መሆኑና ይህም ከተጠበቀው አንፃር አነስተኛ ነዉ ብለዋል።
እስከ የካቲት መጨረሻ ድረስ ለኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከዋለው 192 ቢሊዮን ብር ውስጥ የዳያስፖራው ማሕበረሰብ ያበረከተው 1 ቢሊዮን ብር ብቻ መሆኑ ነዉ የተገለፀው ።
ይህ የተነገረዉ ለህዳሴ ግድቡ ግንባታ ገቢ ማሰባሰቢያ ከሁለት ዓመት በፊት ያበለጸገውን መተግበሪያ በአዲስ መልክ አሻሽሎ ማቅረቡን በትላንትናው ዕለት ባሳወቀበት መድረክ ነው።
ምንጭ። Capital
@ethiopianarchitectureandurbanism
👍 3🤔 1
Photo unavailableShow in Telegram
Introducing the sessions of Big 5 Talks: Day-02 at Big 5 Construct Ethiopia.
The Panel discussion will be dedicated to 𝗣𝗿𝗼𝗷𝗲𝗰𝘁 𝗽𝗹𝗮𝗻𝗻𝗶𝗻𝗴, 𝗿𝗶𝘀𝗸 𝗺𝗮𝗻𝗮𝗴𝗲𝗺𝗲𝗻𝘁 𝗮𝗻𝗱 𝗰𝗼𝘀𝘁 𝗮𝗻𝗱 𝗾𝘂𝗮𝗹𝗶𝘁𝘆 𝗺𝗮𝗻𝗮𝗴𝗲𝗺𝗲𝗻𝘁
Participate in these sessions to engage with industry experts and learn about project planning, risk management, and quality management.
Earn free CPD points to further your career and shape the future of the industry.
𝗠𝗲𝗲𝘁 𝗼𝘂𝗿 𝘀𝗽𝗲𝗮𝗸𝗲𝗿𝘀
Endale Shiferaw Engineer, PMI Ethiopia, UNOPS
Kassahun Mamo Wondimu General Manager, K2N Architecture and Engineering Consultancy Plc
Meskerem Tamiru Architect,Meskerem Tamiru Consultants
Sophoniass Deneke Abebe CEO, Amigos Institution
Register now for free to learn from industry thought leaders, earn CPD points, and improve your knowledge and skills.
If you haven't already registered, please register: https://bit.ly/43Rwl1A
Date: 30 May - 01 June 2024
Venue: Millennium Hall, Addis Ababa, Ethiopia
👍 5
አ ር ቱ ሮ መ ዘ ዲ ሚ
[ጁን 19፣ 1922 (ፖጂቦንሲ) – ሜይ 30፣ 2010 (ሲኤና)]
አርቱሮ መዘዲሚ የዛሬ 14 ዓመት በልብ ህመም በሽታ (ስትሮክ) ምክንያት በተወለደ በ81 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
አርቱሮ በኢትዮጵያ የኪነ ህንጻ ታሪክ ውስጥ ያሳረፈው አሻራ እንዲህ በቀላል የሚታይ አይደለም። በደፈናው የአገራችን ትልቅ ባለውለታ ነበር ልንለው እንችላለን። ዘመን ተሻጋሪ ስራዎቹ ዛሬም ድረስ ጎልተው ይታያሉ። ዋና ዋና ሥራዎቹን ብቻ እንደምሳሌ ብንጠቅስ የሚከተሉትን እናገኛለን፦
አፍሪካ አዳራሽ
አዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት
ፊንፊኔ ህንጻ
ዘውዲቱ ህንጻ
በ ጀማል አብዱልአዚዝ በኩል።
@ethiopianarchitectureandurbanism
❤ 8