cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

Tibeb Media Ethiopia

ህጋዊ ፍቃድ ያለው የተእማኒ የመረጃ ምንጭ ሙያዊ ስነምግባር መርሃችንነው ።

Mostrar más
Publicaciones publicitarias
43 486
Suscriptores
-5924 horas
-2647 días
-1 06730 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

ዝክረ ነብይ መኮንን ፕሮግራም ተካሄደ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ አዘጋጅነት በሸበሌ ሆቴል ደራሲና ጋዜጠኛ ነብይ መኮንን የሚዘክር ፕሮግራም ተካሄዷል ። በፕሮግራሙ ደራሲያን ጋዜጠኞች እና አድናቂዎች የተገኙ ሲሆን በመድረኩ ደራሲ ዘነበወላ እና ደራሲ አለምአየሁ ገላጋይን ጨሜሮ ከነብይ መኮንን ቅርበት ያላቸው የኪነ ጥበብ ሰዎች ንግግር አድርገዋል ። ነብይ መኮንን በሀገሪቱ ኪነ ጥበብ ትልቅ አሻራ አሰርፎ ያለፈ ታላቅ የኪነጥበብ ፈርጥነው ። በ23 አመቱ ታስሮ በ33 አመቱ የተፈታው ይህ ታላቅ ከያኒ የእስርቤት ቆይታው በኪነጥብ ስራዎቹ ጉልህ ሚና እንደሚጫወት ይነገራል ። በተለይም በእስር ቤት ቆይታ የደረሰበትን ሰቆቃና መከራ አዋዝቶ በስራዎቹ ያቀረበበት መንገድ አድናቆትን አትርፎለታል። አዲስ አድማስ ጋዜጣን በመመስረትና ጋዜጣው ከፍተኛ ተቀባይነት እንዲያገኝ የበረከተው አስተዋፆኦ ከፍተኛ ነው ። በሳለፍነው ሳምንት በኑዛዜው መሰረት በአዳማ ከእናቱ አጠገብ የቀብር ስነስርዓቱ መፈፀሙ ይታወሳል ።
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
👍 1
ኢ/ር ቢጃይ የድርጅታችን ሼሪክ ስለሆነ ደስ ብሎናል- (አክሱማዊት ገ/ሚካኤል) ኢ/ር ቢጃይ ናይከር የ40 በመቶ ሽርክና ከድርጅታቸው መውሰዳቸው ደስ እንዳሰኛቸው የአደይ ውበትና ስፓ ምርቶች አምራችና አቅራቢ ድርጅት ባለቤት አክሱማዊት ገ/ሚካኤል ገለፁ። ኢ/ር ቢዳይ ነሬሽ ናይከር የግሎባል ኢንተርፕርነር ቤጃይ ኢትዮ ኢንዱስትሪያል ኤንድ ኢንጂነሪንግ ሶሉሽን የተሰኘ የሀገር በቀል የማምረቻ ማሽኖች አምራች ድርጅት ባለቤት ሲሆኑ፣ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው "ነጋድራስ" የተሰኘ የሥራ ፈጠራ ውድድር ዳኛም ናቸው። ኢ/ር ቢጃይ በፌስቡክ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው በጥሩ ቁመናና ፈጠራ ላይ የሚገኝ አዋጭነቱ የተረጋገጠ አምራች ድርጅት ካገኙ የ40 በመቶ ወይም (የ20 ሚሊዮን ብር) ሽርክና ለመግባት ማቀዳቸውን በመግለጽ መስፈርት አስቀምጠው የዚህ እድል ተጠቃሚ የሚሆኑ ድርጅቶች እንዲወዳደሩ ባቀረቡት ጥሪ መሰረት አደይ የውበትና ስፓ ምርቶች ማምረቻና አቅርቦት  ድርጅትም መወዳደሩን አክሱማይት ጨምረው ገልጸዋል። እንደ አክሱማዊት ገለጻ ኢ/ር ቢጃይ ነሬሽ ናይከር ለተወዳዳሪዎች ቁልፍ ያሏቸውን መስፈርቶች ያቀረቡ ሲሆን፣ ከነዚህ መስፈርቶች መካከል የሃሳብና ብራንድ ጥራት፣ በኢትዮጵያ መመረት የሚችል የንግድ ሀሳብ፣ በከፊል ኤክስፖርት ተደርጎ ለሀገር የውጭ ምንዛሬ ማምጣት የሚችል 40 በመቶ ሼር ለመስጠት ፈቃደኛ የሆነና የሼሩ ብርም ከ20 ሚሊዮን ያልበለጠ፣ በብራንድ፣ በቢዝነስ ሞዴል፣ በአዋጭነት በቢዝነስ ፓርትነርሽፕ ኤግዚት ስትራቴጅና የስራ ፈጠራ የባለቤትነት መብት ያለው መሆን አለበት የሚሉት ተካትተውበታል። በዚህም መሰረት ነዋሪነቷን በአሜሪካ ያደረገችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ አክሱማዊት ገ/ሚካኤል በአደይ የውበትና ስፓ ማምረቻና አቅርቦት ድርጅቷ ዙሪያ ያቀረበችው ሰፋና ዘርዝር ያለ ሀሳብ የኢ/ር ቤጃይ ነሬሽ ናይከርን ቀልብ መግዛት መቻሉን አክሱማዊት ተናግረዋል። አደይ የውበትና የስፓ ምርቶች ማምረቻና አቅርቦት ድርጅት ዋና ዋና የውበት መጠበቂያ ምርቶቹን በኢትዮጵያ  ብቻ ወራቶችን ጠብቆ ከሚበቅለው አደይ አበባ (Bidens Macroptera) ለማምረት ማቀዳቸው ልዩ እንደሚያደርገው የገለጹት የድርጅቱ መስራችና ባለቤት አክሱማዊት በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ አካባቢ የማምረቻ ቦታ ያላትና ምርቶቹን በዋናነት ለኢትዮጵያ፣ ለአሜሪካ፣ ለመካከለኛው ምስራቅ፣ ለአውሮፓና ለምስራቅ አፍሪካ ለማቅረብ የወጠነችውን እቅድ ለውድድር ማቅረቧን ተናግራለች። በዚሁ መሰረት በርካታ ድርጅቶች ይህንኑ ሽርክና ከኢ/ር ቢጃይ ነሬሽ ናይከር ለማግኘት በውድድሩ የተሳተፉ ሲሆን ኢ/ሩ ካቀረቡት መስፈርቶች አብዛኛውን ያሟላው "አደይ የውበትና የስፓ ምርቶች ማምረቻና አቅርቦት ድርጅት ሆኖ መመረጡን ኢ/ሩ በፌስቡክ ገፃቸው ይፋ አድርገው ተቀብለውናል ሲሉ የድርጅቱ መስራች እና ባለቤት አክሱማዊት ተናግረዋል። በዚህ የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ የገለጹት አክሱማዊት ኢ/ር ቢጃይን በእጅጉ አመስግነው በገቡት ቃልና ባቀረቡት የቢዝነስ ሞዴል መሰረት በከፍተኛ ተነሳሽነት ለመስራት ሞራል ማግታቸውን ተናግረዋል። ከህንዳዊው አለማቀፍ ነጋዴ አባታቸው ያካበቱት ልምድ ቀላል እንዳልሆነ የሚገልጹት ኢ/ር ቢጃይ ነሬሽ ናይከር በአሁኑ ወቅት በኢቢሲ በሚተላለፈው የስራ ፈጠራ ውድድር ዳኛ፣ የአመቱ የበጎ ሰው ሽልማትን ጨምሮ በርካታ እውቅናዎች ያገኙ ሲሆን በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፌስቡክ የትስስር ገፅ አዲስ የሚባል ባህል በመጀመር የንግድ ሀሳብ ኖሯቸው የመነሻ ገንዘብ ላጠራቸው ወጣቶች ሃሳቸውን በማወዳደር "ነፃ ፍሬ ፈንድ" የተሰኘ የ100 ሺህ ብር ሽልማት ለአሸናፊዎች በመሸለም ሀሳባቸውን እውን እንዲያደርጉ ብዙዎችን እያገዙ ሲሆን በርካታ ማህበራዊ ሃላፊነትን እየተወጡ በመሆኑ ለሌሎች ባለሀብቶችም ምሳሌ መሆን የሚችሉና ሊመሰገኑ የሚገባቸው ባለሃብት ናቸው ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
Mostrar todo...
👍 3😁 1
አዲስ የአማራር ለውጥ ማድረጉን ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ አስታወቀ ። @top fans Journalist Abdlwehab Bilall ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ስራውን በአዲስ መልክ ወደላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚያስችለው አዲስ የአመራር ለውጥ አድርጓል ። በዚህ መሰረት ዶ/ር ፍሰሓ እሸቱ የፐርፐዝ ብላክ አለም አቀፍ ስራ አስኪያጅ እንዲሆኑ የተወሰነ ሲሆን ዶ/ር ኤርሚያስ ብርሃኑ አላሮ የፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ስራ አስኪያጅ እንዲሆኑ መወሰኑን ተቋሙ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አስታውቋል። አዲሱ አመራር በቅርቡ ተቋሙ ያጋጠሙትን ችግሮችን ለመቅረፍና የተቋሙን ራኢ ከግብ ለማድረስ እንደሚሰራ አስታውቋል ። ከመንግሥት ጋር ተቀራርቦ እንደሚሰራም የገለፀው ተቋሙ ከዚህ በፊት የባንክ አካውንቱ ታግዶበት እንደነበረ ተገልጾ ስለመለቀቁ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ የተቋቋሙ ስራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ ብርሃኑ አላሮ መንግስት አካወንታችንን ያገደው በጥርጣሬ ነው ለምን ተጠራጠርኩ አይባልም አካውንቱ እንዲከፈት እየተነጋገርን እንገናኛለን ብለዋል ። ከመንግሥት ጋር ምንም ግጭት የለንም የሉት ስራ አስኪጁ የመንግስት ተቋም ውስጥ ካሉ አንዳንድ ግለሰቦች ከተቋሙ ጋር አለመግባባት ውስጥ መግባታቸውን አልሸሸጉም ። የግለሰቦች ጉዳይ ለብቻ ራሱን ችሎ የሚታይ ሲሆን ከመንግሥት ተቋማት ምንም ግጭት የለንም ብለዋል ። ዶክተር ፍሰሃ እሸቱ የድርጅቱን ገንዘብ ይዘው ተሰደዋል በሚል ስለሚወራው ወሬ የተጠየቁት ሀላፊው ገንዘቡ በዝግ አካውንት ውስጥ አንዳለ ገልፀዋል ።
Mostrar todo...
👍 5 1
በሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት የሚገኘውን አቡና ሃረ ድንግል ገዳምን ይዞታ ለማስፋት ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በጌትፋም ሆቴል ተደረገ። @top fans Journalist Abdlwehab Bilall ገደሙ ያረፈበት መሬት ጠባብ በመሆኑ የገዳሙ መነኩሴዎች እና መነኩሴያት በከፍተኛ ችግር ውስጥ በመውደቃቸው በዙሪያው ያሉ የግለሰብ መሬቶችን ካሳ ከፍሎ ወደ ገዳሙ ይዞታ እንዲቀላቅል በፍርድ ቤት የተወሰነ በመሆኑ ለግለሰቦቹ ካሳ ለመክፈል ያለሙ አለም አቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች ሲደረጉ ቆይቷል ። በጌትፋም ሆቴል በተደረገው ፕሮግራም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ሀላፊዎች ። ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ። የገዳሙን ይዞታ ለማስፋት ሁሉም የእምነቱ ተከታዮች የአቅማቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠይቀዋል ። አካውንት ቁጥሮች *ንግድ ባንክ 1000610362463 *አባይ ባንክ 9221111060954312 (10609543) አሃዱ ባንክ 0049269410101 ስልክ የገዳሙ ተወካይ ኣፈ መምህር አባ ገብረ ሥላሴ አለሙ 0918 406967 መልአከ ሰላም ቀሲስ ዘማሪ እንግዳወርቅ በቀለ 0911 636818 ኢንጅነር ግሩም ግዛቸው 0930289273 @tebebmediaethiopia
Mostrar todo...
👍 9
በሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት የሚገኘውን አቡና ሃረ ድንግል ገዳምን ይዞታ ለማስፋት ያለመ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በጌትፋም ሆቴል ተደረገ። @top fans Journalist Abdlwehab Bilall ገደሙ ያረፈበት መሬት ጠባብ በመሆኑ የገዳሙ መነኩሴዎች እና መነኩሴያት በከፍተኛ ችግር ውስጥ በመውደቃቸው በዙሪያው ያሉ የግለሰብ መሬቶችን ካሳ ከፍሎ ወደ ገዳሙ ይዞታ እንዲቀላቅል በፍርድ ቤት የተወሰነ በመሆኑ ለግለሰቦቹ ካሳ ለመክፈል ያለሙ አለም አቀፍ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች ሲደረጉ ቆይቷል ። በጌትፋም ሆቴል በተደረገው ፕሮግራም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ ሀላፊዎች ። ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን ። የገዳሙን ይዞታ ለማስፋት ሁሉም የእምነቱ ተከታዮች የአቅማቸውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠይቀዋል ። አካውንት ቁጥሮች *ንግድ ባንክ 1000610362463 *አባይ ባንክ 9221111060954312 (10609543) አሃ ባንክ 0049269410101 ስልክ የገዳሙ ተወካይ ኣፈ መምህር አባ ገብረ ሥላሴ አለሙ 0918 406967 መልአከ ሰላም ቀሲስ ዘማሪ እንግዳወርቅ በቀለ 0911 636818 ኢንጅነር ግሩም ግዛቸው 0930289273 @tebebmediaethiopia
Mostrar todo...
Tibeb Media Ethiopia

ህጋዊ ፍቃድ ያለው የተእማኒ የመረጃ ምንጭ ሙያዊ ስነምግባር መርሃችንነው ።

ሆራ ትሬዲንግ ከ40-50 በመቶ ቅድመ ክፍያ ብቻ የመኪና ባለቤት የሚሆኑበትን ሁኔታ ማመቻቸቱን አስታዋቀ ። የተለዩ ተሽከርካሪዎችን በመገጣጠም የሚታወቀው ሆራ ትሬዲንግ ከሸገር ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ጋር ባደረጉ ስምምነት መሰረት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ የቤት መኪናዎችን በአምስት አመት ተከፍሎ በሚያልቅ የሀምሳ በመቶ ብድር ለመኪና ፈላጊዎች በስድስት ወራት ውስጥ እንደሚያስረክብ ገልጿል ። ከ40 - 50 በመቶ የሚሆነውን ቅድመ ክፊያ በአምስት ወራት ውስጥ ቀስበቀስ የሚከፍሉ ሲሆን ቀሪው ሀምሳ በመቶ በሸገር ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም በብድር የሚሸፈን በመሆኑ በአምስት አመት ውስጥ  በመኪናው ሰርተው እንዲከፍሉ መመቻቸቱን ነው የሆራ ትሬዲን ስራ አስኪያጅና ባለቤት አቶ አደም ከዲር የገለፁት ። መኪናዎች ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ወጪቆጣቢና አየር ንበረት የማይበክሉ ናቸውም ብለዋል በአሁኑ በብድር ለሽያጭ የቀረቡት BYD የቤተ መኪናዎች የመሸጫ ዋጋቸው 2.2 ሚሊዮን ሲሆን ገዢዎች በአምስት ወራት ውስጥ 1.1 ሚሊዮን ብቻ ከፍለው የመኪና ባለቤት መሆን ይችላሉ የተባለው በዛሬው እለት ሸገር ማይክሮ ተቋም እና ሆራ ትሬዲንግ የመግባቢያ ሰነድ በተፈራረሙትበት ወቅት ነው። ሆራ ትሬዲንግ እስካሁን ከመቶ ሺህ በላይ ባጃጆችን  በመገጣጠም ለደምበኞቹ ማቅረቡን በፕሮግራሙ ላይ አስታውቋል ።
Mostrar todo...
👍 7 2🥴 1
የኢቢኤስ ቴሌቨዥን ጋዜጠኛ መቅደስ ደበሳይ የቅንጡ ሞልና አፖርታማ ባለቤት ከሆነው ዋርካ ታወር ጋር በስካይላይት ሆቴል በአብሮነት ለመስራት የሚያስችላትን የብራንድ አምባሳደርነት ስምምነት በከፍተኛ ሚሊየን ብሮች ተፈራረመች ቅንጡው ዋርካ ታወር ከግራውንድ እስከ 2ኛ ፎቁ የተለያዩ የህፃናትና የአዋቂዎች ብራንድ አልባሳትን የፎቶ ስቱዲዮና ኮስሞቲክስ መሸጫዎችን ያካተተ ሲሆን 3ኛ ፎቁ ላይ የተንጣለለ ሬስቶራንትን የያዘ ነው። ከ4ኛ እስከ 12ኛ ወለሉ ደግሞ በስተቀኝ ባለው የህንፃው ክፍል የንግድ ተቋማት ቢሮዎችን በስተግራ ደግሞ ቅንጡ የመኖሪያ ቤቶችን የያዘ አዲሱ የቦሌ ውበት ነው። 54 አይነት አለማቀፍ ብራንዶችን የያዙ የንግድ ቤቶች እንዲሁም 34 ቪአይፒ አፖርታማዎችን አካቶ ከያዘው ከዚህ ግዙፍና ዘመናዊ ተቋም ጋር በአምባሳደርነት መስራት መጀመሬን በአክብሮት ለማሳወቅ እወዳለሁ። በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ተወዳጅ እና ተደናቂ የመዝናኛ ዝግጅቶቻችን ላይ ያላት አበርክቶ ለምሳሌ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ዙረት የተሰኝ በከተማችን ምን አዲስ አለ በሆቴል በሪልስቴት በጤና ወዘተ ከተለያዩ ሀገሩስ ያሉ አለማቀፍ ተቋማት ትን የሚያስተዋውቅ ፕሮግራም አዘጋጅ እና አቅራቢ ስለጤናዎ ከከባድ እስከ ውስብስብ ቀዶጥገና አብሮ በመግባት የሚዘጋጅ ፕሮግራም አዘጋጅ እና አቅራቢያ የቡና ሰአት በሀገራችን ያሉ የተከበሩ ሙሁራን የሚጠየቁበት ዝግጅት በብቃት የምጠይቅ የምትናገር ጋዜጠኛ በመዝናኛ እንዲሁም በቁምነገር ይሄ ቀረሽ የማትባል ጋዜጠኛ ነች የማስተዋቀቅ ብቃት እና ሁለገብ መሆኗ ደግሞ ለዚህ የብራንድ አምባሳደርነት ተቀዳሚ ምርጫ እንድሆን ትልቁን ድርሻ የወሰደ ነው ከዚህም በተጨማሪ ከሌሎች ትልልቅ ተቋማት ጋር በብራንድ አምባሳደርነት እና ማስታወቂያዎች ላይ አብሮ ለመስራት ድርድር ላይ መሆኟን ከቅርብ ሰው በሚስጥር ሰምተናል።
Mostrar todo...
👍 8👏 1
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.