cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

ፍቅር እና ቃል

. ለሰዎች ማንነት ብለህ የራስህን ማንነት አታበላሽ ለሰዎች አላማ ብለህ የራስህን አላማ አትዘንጋ አንተ ራቆትህ ሆነህ ሌሎችን አታልብስ መጀመራ ለራስህ ቁም ለራስህ ጠበቃ ሁን ለራስህ በቂ ስትሆን ለሰዎች አስብ ምክንያቱም እራስህን ስታተርፍነው ሌሎችን ማትረፍ የምትችለው። ከእብዶች መኃል የምኖር አንድ እብድ ነኝ,,, Creator @nuyaan for any comments @nuyaan

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
184
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

⛵️ህመም ያዘለ ፍቅር #ክፍል_ሰላሳ_አራት ...ፍፁም ለማምለጥ እየሞከረ ነዉ ቤዛዊት በተቀመጠችበት ቦታ በሀሳብ እሩቅ ተጉዛ ስለ ፍፁም መቅረት ትብከነከናለች "ምን ሆኖ ቀረ?" በአይምሮዋ የሚመላለስ ጥያቄ ነዉ። ሀሳቧ ሁለት ፅንፍ ይዞ ይጋጫል "ይመጣል አይቀርም" የሚል የመፅናኛ እና የጤነኝነት ሀስብ በተቃራኒዉ "አይመጣም ቀርቷል" የሚል በህመም የገነነ ዉጥረት ባላቸዉ ጥያቄወች ተዉጣ በቀኝ እጇ አገጯን ደገፍ አርጋ አይኖቿን አሁንም ፊት ለፊቷ አሻግራ ተስፋ ባለነቁረጥ የፍፁምን መምጣት በጉጉት ስትጠባበቅ ቆይታ አሉታዊዉ ሀሳቧ የፍፁምን መቅረት አሳምኗት ከተቀመጠችበት በፍጥነት ዘላ ተነስታ እንደወታደራዊ አቋቋም በተጠንቀቅ ከቆመች በኋላ ለመራመድ መንቀሳቀስ ስትጀምር በርቀት ሁኔታዋን ሲታዘቡት የነበሩት እማማ ስንቅነሽ ፈጠን እያሉ ተራምደዉ አስቆሟት "የት ልትሄጂ ነዉ ልጄ?" በእድሜ ብዛት የደከመ በሚመስል አሳዛኝ የእናትነት ድምፅ የቤዛዊትን እጆች ለመያዝ እጃቸዉን እየሰደዱ "ቀረ በቃ አይመጣም" ቆጣ ብላ እጆቿን እያወናጨፈች ሊይዟት የቀረቡትን የእማማ ስንቅነሽን እጅ እየገፋች "ማን ..." ካሉ በኋላ እማማ ስቅነሽ ይመጣል እየጠበኩት ነው ያለቻቸዉን አስታዉሰዉ "ፍፁምን ነዉ ምን አለ ትንሽ ብትጠብቂዉ ታድያ ልጄ ወዴት ልትሄጂ ነው የተነሳሽዉ.." ከጎናቸዉ እንዳትርቅ እየፈለጉ ቤዛዊትን ማባበል ጀመሩ የት እንደምትሄድ ያላረጋገጠችዉ ቤዛዊት ግን የእማማን ተማፅኖ ከቁብ ሳትቆጥር ሂጂ ሂጂ የሚላትን ስሜት እየተከተለች እማማን "እመለሳለሁ እመለሳለሁ እሺ" እያለች በእርጅናና በህይወት የጎበጠ ትከሻቸዉን በእጇ ዳበስ አርጋ እማማ ስንቅነሽን ወደ ኋላ ትታ እስዋ ወደ ፊት መራመድ ጀመረች። ፍፁም ፍቃዱን አመልጣለሁ ብሎ ዘዉ ብሎ የገባበት ቤት መኖርያ ቤት መስሎት እየተሳቀቀ የያዝኩትን ክራንች ማነከሴንም አይተዉ ያዝኑልኛል ብሎ ሰተት እንዳለ ቤቱ ዉስጥ በቁጥር የሚቆጠሩ ሰወች ሰብሰብ ብለዉ ስላየ በፍርሀት እና ተመልሼ ልዉጣ አልዉጣ እያለ በቆመበት ሲያስብ አንዲት ደርባባ ሴትዮ ከቤቱ ዉስጠኛ ክፍል መጋረጃ ገልጣ ስትወጣ ፊት ለፊት ሲገጣጠሙ ፍፁም እንደምንም ብሎ "ሰላም ዋልሽ" አንገቱን ለሰላምታ ያክል ዝቅ እያረገ ሴትየዋ ፊት ለፊቷ አይታዉ የማታዉቀዉ ሰዉ በማየቷ ጥቂት ተገርማ ክራንቹን አቋቋሙን ፊቱን በገረፍታ አይታዉ ፊቷ ላይ ፈገግታ እየተነበበ "እንዴ ምን አስቆመህ አረፍ በል እነጂ..." በአይኖቿ ሰወቹ ከተቀመጡበት አግዳሚ ወንበር ክፍት ቦታ እያሳየችዉ መቀመጡን ስታይ ተመልሳ ወደ ጓዳዋ ፈጠን እያለች ገባች ፍፁም የተቀመጡትን ሰወች ቃኛቸዉ የራሳቸዉ ጨዋታ ላይ ናቸዉ ሁሉም እግራቸዉ ስር ንኬል ተቀምጧል መሀል ላይ ጆግ ሙሉ ጠላ መኖሩን አስተዋለ ወድያዉ ሴትየዋ በጣሳ ዉሉ ጠላ ይዛ መጥታ ፊት ለፊቱ አስቀመጠች ጠላ ቤት መግባቱ ስለገባዉ ፈገግ እያለ አመስግኖ ተቀብሎ መጠጣት ጀመረ። ቤዛዊት የመንገዱን ጠርዝ ይዛ በለሆሳስ እያወራች ከንፈሮቿ እየተንቀሳቀሱ አንዴ ቆም ብላ እያሰበች ሲላት ፈጠን ፈጠን እያለች እየተራመደች ነዉ "ቀረ !!" አንገቷን ከግራ ወደ ቀኝ እያንቀሳቀሰች "ቤቱ ለምን አልሄድም እንደዉም እሄዳለሁ" እጇን ከንፈሯ ላይ ጣል አርጋ ትንፋሽ እየሳበች አሰበች "ይሄኔ ከእህቴ ጋር ይሆናል" ንዴቷ እየጨመረ ሄዶ እጆቿን ለቡጢ በሚመስል አኩዋሀን ጨበጠቻቸዉ ወደ ፍፁም ቤት ሄዳ ፍፁም እና እህቷን አብረዉ ሆነዉ ስታገኛቸዉ ምን ልታረግ እንደምትችል እያሰበች "ኪኪኪኪኪ ኪኪኪኪ ኪኪኪኪኪ" እየተንከተከተች ስትስቅ መንገደኛ ሰዉ አይቷት እጆቹን ለማማተብ አንዴ ግንባሩን ቀጥሎ ወደ ሆዱ በስተመጨረሻ ሁለቱን ትከሻወቹን አስነክቶ እየዞረ እያያት ሲያልፍ ሳቋን አቁማ ኮስተር ለማለት እየሞከረች ወደ ፍፁም ቤት አመራች። ፍቃዱ በንዴት ብዛት ተበሳጭቷ ባዶ ሜዳ ላይ ቆሞ ይዉረገረጋል "እንዴት ይሄ ያመልጠኛል የት ሊገባ ይችላል" እያለ በቆመጠት ዙርያዉን ይቃኛል ነገር ግን ፍፁምን ማየት ስላልቻለ እና ፀሀይዋም አቅም አሳጥታዉ ስለደከመዉ ለመመለስ እያሰበ ጥቂት ወደ ኋላ ሲራመድ አንድ ጎልማሳ ሰዉዬ የጣሳ ምልክት ከተሰቀለበት ቤት በመጠኑ ገድገድ እያለ ሲወጣ ተመልክቶ ቆመ። ይቀጥላል... የዚህ ምህራፍ የመጨረሻ ክፍል ማታ ይለቀቃል!!! @fikrenakal @fikrenakal
Mostrar todo...
በጉልበት ያሸነፍከው ቀን ጠብቆ ይጥልሀል በፍቅር ያሸነፍከው እድሜ ልኩን ሲወድህ ይኖራል
Mostrar todo...
⛵️ህመም ያዘለ ፍቅር #ክፍል_ሰላሳ_ሶስት #ምዕራፍ አንድ ሊጠናቀቅ ሁለት ክፍል ቀረው ...ወረቀቱን ፍለጋ ወደ ዉስጥ ተመለሰ ፍቃዱ ወረቀቱን እያነሳ ድል እንዳረገ ሰው ኮራ እና ጀነን እያለ "አገኘኋችሁ" ሲል አጉተምትሞ የወረቀቱን አቅጣጫ ተከትሎ መሄድ ጀመረ። እማማ ስንቅነሽ ቁርስ ሰራርተዉ ዉጪ ተገትራ የቆመችዉን ቤዛዊትን ወደ ቤት ዉስጥ ገብታ እንድትበላ ጠሯት አልሰማቻቸዉም ልቧ ከአሁን አሁን መጣ አልመጣም ብላ የምትጠብቀዉ ፍፁም ላይ ነዉ። ቀረብ ብለዉ እየነኳት "ልጄ የምትጠብቂዉ ሰዉ አለ እንዴ" እማማ ስንቅነሽ በሁኔታዋ ተጠራጥረዉ ጠየቋት "አዎ ግን አሁን አልነግሮትም" ፈጠን ፈጠን እያለች እያወራች የእማማን ልብ ለማንጠልጠል አስባ ነገር ግን እማማ ስንቅነሽ ምንም አልመሰላቸዉም እንደሚያማት ስለሚያዉቁ አብዳ ለይቶላት ጨርቋን ጥላ ሳይፀየፉ ሰዉ ናት ብለዉ ስላቀረቧት አሁን አሟት ቢሆን እንኳ ሰዉ የምትጠብቀዉ ሊጫኗት አልፈለጉም። እዉነተኛ ወዳጅም እንደዚህ ነዉ ጥፋትህን ስህተትህን ካወቀ በስህተት በጥፋትህ ተጠቅሞ ሊጎዳህ አይሞክርም ያግዝሀል ያበረታሀል እንጂ እማማ ስንቅነሽም የቤዛዊትን እጅ በፍቅር ይዘዉ ሳብ እያረጉዋት "በይ ነይና ቁርስሽን በልተሽ ትጠብቂዋለሽ" ለእሳቸዉ የእሷ ቁርስ መብላት እንጂ ታማ ዉጪ መገተሯ ወይ በጤነኛ አይምሮዋ ሰዉ ቀጥራ እየጠበቀች መሆኑ ብዙም ትኩረት አይሰጣቸዉም ቤዛዊት የቀጠረችዉ ሰዓት ሳይደርስ መጨነቋ እየገረማት እና ፍፁምን ምን ያክል እንደምትወደዉ እያሰበች ወደ ቤቱ ዉስጥ ከእማማ ስንቅነሽ ጋር ተከታትለዉ ገቡ። እጇ ላይ ያሰረችዉ ሰዓት ይቆጥራል እርግጠኛ ስላልመሰላትም በእማማ ስንቅነሽ በር በኩል የሚያልፉ እና የሚያገድሙ ሰወችን "ይቅርታ ሰዓት ስንት ነዉ?" በሚያሳዝን አስተያየት ትጠይቃለች "ሶስት ተኩል፣አራት ስዓት .." እያሉዋት የጠየቀቻቸዉ ሰወች ያልፉሉ እሷም ያሰረችዉ ሰዓት ግን ትክክል ነበር የሚሰራዉ። ቤዛዊት ስልኳን ይዛ ባለመዉጣቷ ተበሳጨች ይዛዉ ብትጠፋ ቤተሰቦቿ እየደወሉ የሚጨቀጭቋት ስለመሰላት ነበር ትታዉ የወጣችዉ አሁን ግን ብይዘዉ ኖሮ ስትል ተመኘች የፍፁም መዘግየት እያሳሰባት ስድስት ስዓት ሊሆን ተቃርቧል። እማማ ስንቅነሽ በጠራራ ፀሐይ ዉጪ የቆመችዉን ቤዛዊትን ቤት እንድትገባ ለመለመን ከጉዋዳቸዉ ወጡ "አይ ልጄ ፀሀዩ በረታብሽ እንዳያምሽ ወይ ወደ ቤት ግቢ አልያም በረንዳ ላይ ጥላ ቦታ ተቀመጪ" "ቀረብኝ እኮ ሶስት ሰዓት ተባብለን ስድስት ሰዓት ሞላ" "እኮ ይመጣል ብቻ ከፀሐይዋ ራቅ በይ" እንደዚህ ሲልዋት ቤዛዊት በደስታ ፈገግ እያለች "የሚመጣዉ ማን እንደሆነ ልንገሮት?" በእሺታ እማማ ስንቅነሽ ጭንቅላታቸውን ነቀነቁ "ጉዋደኛዬ ፍቅረኛዬ ባሌ" ቀጠል አድርጋም "ፍፁም ይባላል ሲመጣ አስተዋዉቃችሁዋለሁ" እማማ በእሷ ደስተኛ መሆን እየተደሰቱ እና እያዋሩ ቤዛዊትን ከፀሀዩ ወደ ጥላ ወስደዋት ነበር። (ከሰዓታት በፊት) ፍፁም ሁለት ስዓት ተኩል አካባቢ ከተባለዉ አድራሻ በታክሲ ተሳፍሮ እንደወረደ እና ባለችዉ አቅጣጫ ጥቂት ከተራመደ በኋላ ቦታዉን ለማረጋገጥ ፈልጎ ቤዛዊት የሰጠችዉን ወረቀት ኪሶቹ ዉስጥ ሲፈልግ ስላጣዉ እየተበሳጨ የት ሊጥለዉ እንደቻለ ማሰብ ጀመረ። ቤቱ እየወጣ ለአከራዩ ብር ሲሰጥ ሊሆን እንደሚችል ገምቶ የቦታዉን እርግጠኝነትን ለማረጋገጥ ጭንቅላቱን መጠየቅ ተያያዘ አልተሳሳተም ያለችዉ ቦታ ላይ ደርሷል ነገር ግን እሱ ከቆመበት መንገድ ተሻግሮ ነበር አንገቱን ቀና አርጎ ለማየት ሞከረ ቤዛዊትን በርቀት አያት በእድሜ ገፋ ካሉ ሴትዮ ጋር ቆማ ታወራለች ስላያት እየተደሰተ ግዜ ሳያጠፋ መንገዱን ሊሻገር ሲል በቅርብ እርቀት ከቅድም ጀምሮ ከጀርባዉ የነበረ የመሰለዉ ሰዉ ስላየ መሻገሩን ተቶ የሰዉየዉን ፊት ለማየት በቀስታ ዞሮ በጨረፍታ አይቶት መሻገሩን ወደ ቤዛዊት መቅረቡን ትቶ ቀጥታዉን መንገድ ይዞ እየተናደደ እያጉተመተመ መራመድ ጀመረ። "ከቤት ጀምሮ ሲከተለኝ ነበር ወይስ እንዴት እዚህ ድረስ ሊመጣ ቻለ" ፍፁም እራሱን እየጠየቀ ከኋላዉ የሚከተለዉን ሰዉዬ ለማምለጥ እየሞከረ ነዉ "አይ ፍቃዱ ምን አርግ ነዉ ግን የሚለኝ ምን በደልኩት ምን አሰቀየምኩት ይሄን ያህል የጎን ዉጋት የሆነብኝ" ፍፁም ከፊት ሲራመድ ፍቃዱ አድፍጦ ከኋላው እየተከተለዉ ነዉ ፍፁም እሮጦ ማምለጥ ተመኘ ነገር ግን እግሮቹ ለመሮጥ ብቁ አደሉም ፍፁም እያነከሰ ፍቃዱን ለማምለጥ ክራንቹን ተጠቅሞ ፈጠን ፈጠን ለማለት እየታገለ ነዉ ከጀርባዉ ያለዉ ፍቃዱ ግን ዘና ብሎ እየተራመደ በፍፁም አረማመድ አነካከስ እየሳቀ እየተከተለዉ ነበር። አንዳንዴ በህይወት መስመራችን ዉስጥም ከእኛ በብዙ እጥፍ የሚበልጡን በብዙ እጥፍ የተሻሉ ሰወች አሉ ነገር ግን አብዛኞቹ ስለበለጡን የሚኮፈሱ ስላነስን የሚንቁን ናቸዉ ህየወትንም ከባድ የመያረጋት መሮጥ የሚችል ሰዉን በታመመ እግር በክራንች ታግዘዉ ማምለጥ መቻል ነዉ። ይቀጥላል... @fikrenakal @fikrenakal
Mostrar todo...
⛵️ህመም ያዘለ ፍቅር #ክፍል_ሰላሳ_ሁለት በነፋሻዉ አየር በንፋሱ ዉልብታ ቅርንጫፎቹን ከወዲህ ወድያ የሚዉረገርገዉን የባህርዛፉን ግንድ ተደግፋ ቤዛዊት የቀጠረችዉን ፍቅረኛዋን በጉጉት አይኖቿ አሻግረዉ እያዩ ትጠብቃለች። እማማ ስንቅነሽ ትመጣለች ብለዉ ያልጠበቋትን የበፊትዋን እብድ ጤነኛ ሆና በመምጣቷ እየተደሰቱ እና አምላካቸዉን እያመሰገኑ በጠዋት መጥታ እንግዳ ስለሆነችባቸዉ ቁርስ ቢጤ ሊሰሩላት ደፋ ቀና እያሉ ነዉ። በእርግጥ ከህልማቸዉ ጠፍታ አታዉቅም እርቃኗን ሆና በብርድ ስትንሰፈሰፍ አይናቸዉ ላይ ስለተቀረፀች ድቅን ትልባቸዋለች በወለደ አንጀታቸዉ አፈር አልብሰዉ የቀበሯት ልጃቸዉን ያዩ ይመስል ቤዛዊትን ሲያዩ ስፍስፍ ብለዉ ያዝኑላታል። ፍፁም ነግቶ ልቡም በጭንቀት እንደተወጠረ ቤዛዊት ካለችዉ ቦታ ለመሄድ ለባብሶ ጨርሶ የአንድ እጁን ክራንች ትቶ በአንዱ ብቻ እየተጠቀመ በሩን ቆልፎ ከወጣ በኋላ የፃፈችለት ወረቀትን ከኪሱ አዉጥቶ በድጋሜ ተመልክቶ ኪሱ ዉስጥ መልሶ ሊከተዉ እየሞከረ ከጀርባዉ አከራዩ ጉሮሮአቸውን እየጠረጉ "እህህ እንዴት አድረሀል አቶ ፍፁም?" ፍፁም ሳያስበዉ ስለጠሩት ደንገጥ እያለ እና የቤት ኪራይ ቀን መድረሱም ትዝ እያለዉ ኪሱ ዉስጥ ከያዘዉ ዳጎስ ያለ ገንዘብ መሀል ቆጥሮ እያወጣ ለአከራዩ እየሰጣቸዉ "ይመስገን" አላቸውና ስዓት እንዳያረፍድ እና ቤዛዊትን እንዳያጣት አስቦ እየተቻኮለ ወጣ። የቤዛዊት አባት ቤዛዊት ቦርሳ አንግባ እንደወጣች ከእንቅልፋቸዉ እንደነቁ ሰራተኛቸዉ ስለነገረቻቸዉ ተናደዉ "እዚች ልጅ ላይ ያለዉ ሴጣን መች ይሆን እረፍት የሚሰጠን" እያሉ እያጉተመተሙ ወደ ቤዛዊት መኝታ ክፍል ደርሰዉ እንደገቡ መጀመርያ አይናቸዉ ጠረጴዛ ላይ የተቀመጠ ወረቀት ላይ ስለሆነ በእጃቸዉ ሳይነኩት በእርቀት ቆመዉ ለማንበብ አንገታቸዉን ሰገግ አርገዉ አይኖቻቸውን ሰደዱ "አትፈልጉኝ በፈጠራችሁ አምላክ ተዉኝ" የሚሉ ቃላቶችን ሲያነቡ ወረቀቱን አንስተዉ ጨምድደዉ እየወረወሩት "ጥርግ በያ ለኔ ስትይ ገደል ለምን አትገቢም" እየጮሁ ተናግረዉ በሀሳብ እና በንዴት እየተዉረገረጉ ወደ ሳሎን አምርተዉ ተለቅ ያለዉ ሶፋ ላይ ዘፍ ብለዉ ተቀምጠዉ ቤዛዊትን ማማረር እና መራገም ጀመሩ "የእራሷ ጉዳይ" አሉና ስለ ቤዛዊት ላለማሰብ ፂማቸዉን በእጇቻቸዉ ሲነካኩ ቆይተዉ አይናቸዉ ከሳሎኑ ግድግዳ ላይ ከተሰቀለዉ የቤተሰብ ፎቶ ላይ ተተክሎ ቀረ እሳቸዉ ባለቤታቸዉን አቅፈዉ ፎቶዉ ላይ ይታያሉ የቤዛዊት ታላቅ እህት እናቷን ተደግፋ ከጀርባ ቆማለች ፊቷ ላይ ፈገግታ ይነበባል ቤዛዊት ከረሜላ አልገዛልህም እንደተባለ ህፃን አኩርፋ አባቷን ተደግፋ ትታያለች የቤዛዊት አባት ፎቶዉን እያዩ ቆይተዉ ቤዛዊት ላይ መጨከን እና መተዉ አላስችል ስላላቸዉ በሀዘን ተዉጠዉ ለአቶ ፍቃዱ እርዳኝ ለማለት ስልካቸዉን አዉጥተዉ መደወል ጀመሩ። ተንኮለኛ እና ሞኝ ሰዉ አይጥመድህ ከህይወትህ ለማሶጣት በጣርክ ቁጥር የጠራከዉ ይመስለዋል ስለዚህ ሁሌም ሲከተልህ ይኖራል ፍቃዱ እየተጣደፈ ስራዉን ትቶ የፍፁምን እና የቤዛዊትን ህይወት ለማመሰቃቀል ወደ ፍፁም የተከራየበት ቤት አመራ ወደ ግቢዉ ሲደርስ ቤዛዊት ኖራ እንዳትመታዉ እራሱን ለመጠበቅ እየተንሿከከ ወደ ግቢዉ ዉስጥ ዘለቀ። የፍፁም በር ጋር ሲደርስ ከጀርባዉ ሰዉ መኖር እና አለመኖሩን ለማረጋገጥ ዙርያዉን ቃኝቶ ጆሮዉን የፍፁም በር ላይ ለጥፎ ሲያዳምጥ ድምፅ በማጣቱ እየተገረመ በሩን ሲያንኳኳ እና ቆይቶም ለመክፈት ሲታገል ማንም አለመኖሩን ሲያዉቅ እየተበሳጨ ወደ መጣበት ሊመለስ ሲል መሬት ላይ የወደቀ ወረቀት አይቶ ጎንበስ ብሎ ካነሳዉ በኋላ ለማንበብ ሞከረ የቦታ አድራሻ የቀጠሮ ሰአት መልሶ መሬት ላይ ጥሎት ሹክክ ብሎ ወደ ዉጪ ወጣ " የት ሄደዉ ይሆን " ሲል ብዙ ካሰበ በኋላ ወረቀቱ መልስ ያለዉ ስለመሰለዉ ወረቀቱን ፍለጋ ወደ ፍፁም ግቢ ፈገግ እያለ ተመለሰ። ይቀጥላል... @fikrenakal @fikrenakal
Mostrar todo...
⛵️ህመም ያዘለ ፍቅር #ክፍል_ሰላሳ_አንድ ...ያንቺ ነዉ ሲል አፋጠጣት ቤዛዊት አንዴ ፍፁምን አንዴ አባቷን አፈራርቃ እያየች የተረገመ ፍቃዱን በዉስጧ እየረገመች መሬት ላይ የወደቀዉን ጡት ማስያዣ አንስታ እና ንዴቷ እየተቀሰቀሰ አይኗን እያጉረጠረጠች "ያንተ ነዉ ልስጥህ ...አንተ ሴታሴት ወረኛ" ጥፍሮቿን አሹላ ወደ ፍቃዱ ተጠጋችዉ ፍቃዱ አዋረድኳቸዉ ብሎ መዋረዱ እየታየዉ አመጣጧ እያስፈራዉ ወደ አባቷ ቀስ እያለ መጠጋት ጀመረ "አረ ተረጋጊ ሴትዮ" አፉ ላይ የመጣለትን ቃል እያወራ ፍፁም ለመገላገልም አልተነሳም አልጋዉ ጠርዝ ላይ ተቀምጦ የጥፋተኝነት እና ደግ አረኩ በሚል ሁለት የተቃረኑ ሀሳቦች ተዉጦ ከሀሳቡ ያነቃዉ ብርጭቆ ከግድግዳ ጋር ሲጋጭ የሚያሰማዉ ድምፅ ነበር "ኳኳ ከሽሽሽሽሽ" ፍቃዱ በሩን በርግዶ እየተንደፋደፈ ወጣ አባቷ በድንጋጤ ተዉጠዉ አንገታቸዉን አቀርቅረዉ እና ፍጥርጣሪዉን ፈርተዉ። አይናቸዉን ጨፍነዉ ቆይተዉ ልጃቸዉን በልመና አስተያየት እያዩዋት "ተረጋጊ ልጄ በቃ" እያሉ መለመን ጀመሩ መታመሟ እየመሰላቸዉ እየፈሩ በንዴት የጦፈችዉ ቤዛዊት የወረወረችዉ ብርጭቆ ፍቃዱን ስላላገኘዉ እና እልኋ ስላሎወጣላት ግላ "ሁለተኛ ይሄን የተረገመ ሰዉ ማየት አልፈልግም" እጆቿ እየተንቀጠቀጡ እና የታችኛዉን ከንፈሯን ወደ አፍዋ ዉስጥ ስባ በጥርሶቿ ነክሳ። በትክክለኛዉ ስዓት አንዳንዴ ጥፋትን ለመሸፈን ሌላ ጥፋት ማጥፋት የመጀመርያዉ ጥፋትን ያደበዝዝልናል ሰዓቱን ካልጠበቀ ደሞ በሁለት ስህተት ቅጣት ያስጠይቀናል መልካም ነገርም እንደዚህ ነዉ በትክክለኛዉ ስዓት ጥሩ ነገር ላይ ሌላ ጥሩ ነገር ማስራት እና ድጋሜ ጥሩ ማሰብ የመጀመርያ ደስታችንን አስረስቶ ወደ እጥፍ ድርብ ወደ ሆነ ደስታ ዉስጥ ይከተናል። አባቷ ልጃቸዉ ቤዛዊትን እየለመኗት ይዘዋት እየወጡ ነዉ ዞራ ፍፁምን ተመለከተችዉ ምን ማረግ ይችላል ከአባቷ ነጥቆ ማስቀረት አይችል እየከፋዉ እና እያዘነ ለመሰናበት እጆቹን አየር ላይ አነሳ እስዋም በአይኖቿ እንባ እየቀረሩ እያየችዉ አባቷ አቅፈዉ እንደያዟት ወደ ዉጪ ወጣች የቤዛዊት አባት እግሬ አዉጭን ብሎ የሮጠዉን ፍቃዱን በአይናቸዉ እየፈለጉት ነበር ቤዛዊት የአባቷ መኪና ዉስጥ ገብታ ስትቀመጥ ወረቀት እና እስኪርቢቶ ስላገኘች ፊቷ ፈገግ እያለ የሆነ ነገር ሞነጫጭራ ፅፋ ኪሷ ዉስጥ አባቷ እንዳያዩዋት ከከተተች በኋላ "የረሳሁት እቃ አለ መጣሁ.." አባቷን ብላቸዉ ከመኪናዉ ወርዳ ወደ ፍፁም ቤት መሮጥ ጀመረች። ፍፁም ቤዛዊት እንደወጣች ብቸኝነት ቀንድ አዉጥቶ መልክ ኖሮት ሰፈረበት ከፋዉ ወራቶች እያለፉ ስለሆነ በዚህ ወቅት የትም ትምህርት ቤት ተቀጥሮ ማስተማር እንደማይችል ሲያስበዉ ከአልጋ ወደ አልጋ ቦታ እየቀያየረ እየመሰለዉ አዘነ ቤዛዊትም የእሱ ትሁን አትሁን ግራ በገባዉ ሁኔታ ስትታመም ሲሻላት አብሯት ከጎኗ እንዳይሆን መሰናክል ሲበዛበት ይባስ ብለዉ ቤተሰቦቿ ጣልቃ እየገቡ እረፍት እና ደስታ ስለነሱት ተስፋ ወደ መቁረጥ እየሄደ እየተጨነቀ ሲያስብ በሩ ተበርግዶ ተከፍቶ ቤዛዊት እየፈጠነች ገብታ ሀይሏን በሙሉ ትከሻዉ ላይ ጥላበት ካቀፈችዉ በኋላ እና ከንፈሩን በፍጥነት ለኮፍ አርጋ ስማዉ እንደለመደችዉ ከኪሷ የተጣጠፈ ወረቀት አዉጥታ ሰጥታዉ በገባችበት እየፈጠነች ወጣች። ከወጣች በኋላ ወረቀቱን ገልጦ አነበበዉ የቦታ ስም ተፅፎበታል አቅጣጫዉን እና ነገ ሶስት ሰአት እንገናኝ ይላል አንብቦት ሲጨርስ ደስ እያለዉ በጀርባዉ ጋደም አለ። ቤዛዊት ቤቷ ስትደርስ መሳቅ መጫወት አበዛች ቤተሰቦቿ ደስ እያላቸዉ መሽቷ ለእንቅልፍ ወደየአልጋቸዉ ተለያዩ እስዋ ግን ስለነገዉ እያብሰለሰለች የባንክ ደብተሯን ኪሶ ዉስጥ ከትታዉ በለበሰችዉ ሱሪ አልጋዋ ላይ ወጣች። ነፋሻማ አየር ከአዲስ አበባ ወደ ክፍለ ሀገር መዉጫ መስመር በአካባቢዉ የበቀሉት ዛፎች በንፋስ ይወዛወዛሉ ዛፎቹ ላይ ያሉት የወፍ ዝርያወች ቢንጫጩም ዜማ አላቸዉ እማማ ስንቅነሽ ቤዛዊትን በራቸዉ ላይ ቆማ ሲያገኟት የሞተች ልጃቸዉ መቃብር ፈንቅላ እንደወጣች ተደስተዉ እያዩዋት "ልጄ ልጄ የምትመጪ አልመሰለኝም የኔ የዋህ የኔ ምስኪን" እያሉ አቀፏት ይቀጥላል... @fikrenakal @fikrenakal
Mostrar todo...
​​⛵️ህመም ያዘለ ፍቅር #ክፍል_ሰላሳ ....ሁለቱም ተያዩ ሁለቱም ከተኙበት ቀና እያሉ ተያዩ በሁለቱም ሀሳብ ዉስጥ የቤዛዊት ቤተሰቦች እሳት ጎርሰዉ በር ላይ የቆሙ ስለመሰላቸዉ እየተደናገጡ አልጋዉ ጠርዝላይ የተበታተኑ ልብሷቻቸዉን ማሰስ ጀመሩ ስላጧቸዉ ከአልጋ ሁለቱም ወርደዉ ብርድ ልብሱን መነቃቀሩት ከአልጋዉ ግርጌ መሬት ላይ ልብሷቻቸዉ ወድቀዉ ስላገኙ እየተቻኳሉ ለባብሰዉ ድጋሜ ተያዩ በሩ መንኳኳቱን ግን አላቆመም ነበር። የፍፁም በር ላይ ምግብ ይዘዉ የቆሙት አከራዩ በልባቸዉ "ሞተዋል እንዴ እነዚህ ሰወች" እያሉ ለመመለስ እያሰብ ፍፁም በሩን ከፍተላቸዉ "እንዴት አደራችሁ ምግብ ይዤ ብመጣ ደጅ አስጠናችሁኝ እኮ..." አከራዩ መበሳጨታቸዉ ፊታቸዉ ላይ እየተነበበ ቤዛዊት ጆሮዎቿን ቀስራ እያዳመጠች ነዉ የአባቷ ድምፅ እየመሰላት ዉስጧ እየተረበሸ ፍፁም አከራዩ በመሆናቸዉ እፎይታ እየተሰማዉ እና ለመዋሸት እየተንተባተበ "ስላልሰማን ነዉ ይግቡ" እያለ እንዲገቡ በሩን ከፈት አረገላቸዉ "አይ ምኑን ገባሁት ይቺን ቅመሱ እስቲ" አሉና በዳንቴል የተሸፈነ ትሪ አቀብለዉት "እግርህንም እንደማይህ እያገገምክ ነዉ ወደ ኋላ መጥቼ እናወራለን" እያሉት ወደ ቤታቸዉ ተመለሱ። ፍፁም የተሸፋፋነዉን ትሪ ሳይገልጠዉ ገና የምግቡ ሽታ ስላወደዉ በመጠኑ እያነከሰ አልጋዉ ላይ እየተቀመጠ ቤዛዊትም ትላንት የበላች ስለሆነች ከተቀመጠችበት ተነስታ ከተጣጠበች በኋላ ፍፁምም እንዲታጠብ እረድታዉ አከራዩን እያመሰገኑ መመገብ ጀመሩ። የቤዛዊት አባት የዶክተር መለሰን ስልክ አዉርተዉ ከጨረሱ በኋላ እና ፍፁም ቤዛዊትን ፈልጓ መጥቶ ነበር የሚለዉን ስለሰሙ ከሱ ቤት ዉጪ ልጃቸዉ ወዴትም እንደማትሄድ አስበዉ ወደ ታላቋ ልጃቸዉ የፍፁምን ቤት እንድታሳያቸዉ ደወሉ "ሄሎ ልጄ እንዴት ነሽ" "ደህና ነኝ አባ" መለሰችላቸዉ "የአሰተማሪዉን ቤት የምታዉቂዉ መሰለኝ አሁን እንገናኝ እና ታሳይኛለሽ" የቤዛዊት ታላቅ እህት ቤዛዊትን መጥላት ሳይሆን እየፈራቻት ነዉ ልታረጋት የነበረዉ ነገር አይምሮዋ ዉስጥ ስለተቀረፀ ብቻ ቤዛዊትን ላለማየት የፍፁምን ቤት ብታዉቀዉም ደብቃ "ዉይ አላዉቀዉም ቤቱን " "እኔም ሰዉ ነሽ ብዬ አንቺ ጋር መደወሌ" አባቷ እየተናደዱ ስልኩን ዘግተዉ ወደ መምህር ፍቃዱ መደወል ጀመሩ። ፍፁም እና ቤዛዊት ደስታ በደስታ ሆነዋል ከባዱን ጊዜ እንዳለፉት ቆጥረዉ ጠባቧ የፍፁም ክፍል ዉስጥ አልጋዉ ላይ ጋደም ብለዉ ስላሳለፉት ነገር ከተያዩበት ቀን ጀምሮ እስካሁን ስላሳለፉት ነገር በነፃነት እየተያዩ እየተሳሳቁ እያወሩ ተቃቅፈዉ እየተላፉ እየተሳሳሙ አስደሳች ጊዜ አያሳለፉ ነዉ ፍፁም ቤዛዊትን መላ አካሏን እየተመለከተ ቆይቶ ከቤዛዊት ጋር አይን ለአይን ተጋጩ ፈገግ አለች ፊቷ ፍክት ብሏል የዉስጥ ስሜትን በአብዛኛዉ የሰዉ ፊት ላይ ማየት ይቻላል በዚህ ሰአት ህመም ያለባት ቀርቶ ታማ የምታዉቅ እንኳን አትመስልም ክትክት እያለች ትስቃለች ፈገግታዋ ዉስጥ ንፁህነት የዋህነት ምስኪንነት ይነበባል ተጠጋግተዉ ተቃቅፈዉ እየተያዩ ቤዛዊት ሳያስበዉ ከአይኖቿ የእንባ ዘለላወች እየወረዱ "እወድሃለሁ እንዳትርቀኝ ላጣህ አልፈልግም" አለችዉ ከአይኖቿ የሚፈሱትን እንባወች ለማስቆም እየሞከረች "አልተዉሽም ቤዚ ከልቤ ነዉ" እያለ ፍፁም በከንፈሮቹ ከንፈሮቿን ሳማት። ሁለቱም ደክሟቸዉ በጀርባቸዉ ተኝተዉ እጇቻቸዉን ብቻ አየር ላይ ዘርጋተዉ በጣቶቻቸዉ እየተቆላለፉ የፍፁም በር በድጋሜ ተንኳኳ ፍፁም ለመክፈት ቀስ እያለ ተነሳ። የቤዛዊት አባት እና መምህር ፍቃዱ ተከታትለዉ በፍፁም ጋባዥነት ወደ ዉስጥ ገቡ የቤዛዊት አባት ልጃቸዉን ስላዩዋት እየተደሰቱ ከፍፁም ጋር ማደሯን በልባቸዉ ጠርጥረዉ አንጀታቸዉ እየጨሰ ልጃቸዉን "ተነሽና ወደ ቤት እንሂድ" አዘዙ መምህር ፍቃዱ አይኖቹን ከወድህ ወድያ እያንቀዋለለ ቆይቶ የቤዛዊትን ጡት ማስያዥያ ስላየና ለአባቷ አሳይቶ ነገሮችን ለማክረር ስላሰበ ቤዛዊትን በፌዝ አስተያየት እያያት "ያ ነገር ያንቺ ነዉ " ሲል አፋጠጣት ይቀጥላል... @fikrenakal @fikrenakal
Mostrar todo...
አንዳድን እዜ እንጠንቀቅ ብዙ "ብልጥ ልሁን" የሚሉ ሰዎች ሊከቡን ይችላሉ አለ አደል እነሱ ብስል እኛ ጥሬ የሆኑ እና የሆንን አይነት የመሰላቸው.... እና ያው ይቅርባችሁ ለማለት ነው አስተውሉ የዝምተኛ ሰው ደጀኑ ትዝብቱ ነው...ሁሉ ነገራችሁን ያስተውላል...ያያል..ያያል...ይታዘባል በዚህ ውስጥ ቶሉ እናይሄድ በልመና ሚያቆየው እሱ ያዳመጠው በናንተ ማንነት ውስጥ ያለውን የትንሽ #መልካምነት የአድነኝ ጥሪን ነው። ስለዚ እራሳችሁን ለማየት ሞክሩ። #እውነት #ላንተ_ነው #ላንቺም
Mostrar todo...
⛵️ህመም ያዘለ ፍቅር #ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ ...ተኝታ አገኛት የፍፁምን መምጣት በመስኮታቸዉ በኩል አጮልቀዉ ያዩት አከራዩ ከቤታቸዉ በፍጥነት እየወጡ በር ላይ ቆሞ የቤዛዊትን ቤቱ መጥታት ያስገረመዉን ፍፁም አቅፈዉ ለመሳም እየዳዳቸዉ እና የያዘዉን ክራንች በአይናቸው በሀዘኔታ እየተመለከቱ "ፈጣሪ እንኩዋን አተረፈህ ልጄ ፈፅሞ ይማርህ" የሀበዛ ልማድ የሆነዉን ከንፈራቸዉ በጥቂቱ ገርበብ አርገዉ "ምፅ" የሚልድ ድምፅ እየፈጠሩ ፍፁም ከልባቸዉ መሆኑ ስለገባዉ እና ሀዘናቸዉ ተሰምቶት "አሜን አሜን" ብሎ እያወራ አከራዩ ወደ ጆሮዉ ጠጋ ብለዉ "እንኳን ለቤትህ አበቃህ ቤትህን እስከዛሬ ስንጠብቅ ነበረ" አጮልቀዉ አይናቸዉን ከቆሙበት በረንዳ ወደ ፍፁም ቤት እያማተሩና እየጠቆሙት "ደፈርከኝ አትበለኝና እጮኛህን ከፍቼ ያስገባኋት እኔ ነኝ" "ጥሩ አርገዋል አመሰግናለሁ" በቆመበት እያስቸገሩት ስለሆነ ቀኑም እየመሸ ስለሆነ "ሰላም እደሩ እሺ" አላቸዉና ወደ ቤቱ ዉስጥ ሰተት አለ። ወደ አልጋዉ ተጠግቶ የተኛችዉን ቤዛዊትን በፍቅር እየተመለከታት ህልም እራሱ የምታይ አትመስልም ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ስለወሰዳት ቀስቅሶ ለማዋራት ያሰበዉን ሀሳብ ትቶ አልጋዉ ጠርዝ ላይ ተቀመጠ። የዶክተር መለሰ ሀኪም ቤት ጥበቃ ዞር ሲሉ የጠፋችባቸዉን ሴት አስደንገጣቸዉ ወደ አለቃቸዉ መለሰ ቢሮ እየተበሰጫጩ አምርተዉ "በስመአብ ጋሼ ምን ሴጣን እንደሰፈረባት አላዉቅም ልጅቷ ላይ በር ላይ አላስወጣሽም ብያት ወደ እርሶ ጋር ተከተይኝ ብያት እየመጣን ለአፍታ ዞሬ ብመለከት እንደ ንፋስ ተበተነሽ" ግራ የተጋባዉ ዶክተር መለሰ "ምን.." ሲላቸዉ "ጠፋች እያልኳ ጋሼ" "ማን?የቷ?" "ያቺ በቀደም ከእርሷ ጋር የመጣችዋ ወጣት ልጅ" አሉት ጥበቃዉ እንዴት እርሶን አልፋ ወጣች እንዳይላቸዉ እየሰጉ ዶክተር መለሰ ከወንበሩ ተነስቶ ጥበቃዉን አልፏቸዉ ወደ ቤዛዊት ክፍል አምርቶ በሩን ከፍቶት ገባ የተገላለጠ አልጋ ትንሽ እንደመተከዝ ብሎ ወደ መሬት ሲያቀረቅር መሬት ላይ የተጣለ መድሀኒት ተመለከተ ለእንቅልፍ ብሎ የሰጣት ነበር አየተናደደ እና እየተበሳጨ ወደ አባቷ መደወል ጀመረ። ስዓቱ ከመሸ ቆየ ፍፁም ከተቀመጠበት ተነስቶ በሩን ቀርቅሮት ወደ አልጋዉ ተመልሶ ቤዛዊትን እንዳይቀሰቅሳት እየተሳቀቀ ከጎኗ ጋደም አለ ሳያስበዉ በክንዱ ክርን ስለነካት ቤዛዊት እያኮረፈች ከነቃች በኋላ ወድያዉ ከጎኗ የተኛዉን ፍፁምን ስታየዉ ፈገግ እያለች በተኛችበት በደረቷ ተስባ የፍፁምን ጉንጭ ሳመችዉ "እንዴት ነክልኝ ፍፄ" "ደህና ነኝ አንቺስ" ከንፈርዋ ለከንፈሩ ተጠግተዉ የትንፋሽዋ ሙቀት እየተሰማዉ ነዉ "እንዴት እንደናፈቀኝ.." አለችና የተኝጨባረረዉን ፀጉሩዋን በስርአቱ ሰብስባዉ ካስያዘችዉ በኋላ ፍፁም እንዲያቅፋት እጁን ከደረቱ ላይ አንስታ ከአንገቷ ዙርያ ካሳረፈችዉ በኋላ ተመቻችታ ተንተራሰችዉ ፍፁም የሚያወራዉ የሚናገረዉ ነገር ጠፍቶበት እና ቀጥሎ ሊፈጠር የሚችለዉ ነገር እያሳሰበዉ ጣራ ጣራዉን እያየ ቤዛዊት ከንፈሮቿን ከንፈሩ ላይ አሳረፈቻቸዉ በቀስታ ባለመስማማት አንገቷን ቀና አድርጎ አያት የድሮዋ ቆንጆዋ ሳቂታዋ ቤዛዊት ናት አይኗቿ ፍቅርን ተርበዉ በለሆሳስ ገርበብ ብለዉ ተከፍተዋል ከንፈሮቿም ደግመዉ ሊስሙት አኮብኩበዋል ስሜቱን ማሸነፍ ስላቃተዉ እሱም እየሳማት የብርድ ልብስ ሙቀት ሳያስፈልጋቸዉ የፍቅራቸዉን የመጀመርያ ፅዋ አብረዉ ተጓነጩ። ጠዋት አልጋዉ ላይ ቤዛዊት እና ፍፁም እርቃናቸውን ተኝተዉ የፍፁም ቤት በር በሀይል ሲደበደብ ሁለቱም በድንጋጤ ነቅተዉ ተያዩ። ይቀጥላል... @fikrenakal @fikrenakal
Mostrar todo...
አንዳንድ ህመሞችን በቀላሉ በትዝታ ታክማቸዋለህ ግን አይድኑም:: በጉም ህልም ብጥስጣሽ ተስፋዎች ፈላልገህ የሮም ሀውልቶችን በሚያስንቅ ፅናት አንድ ቦታ ቆመህ ትጠብቃለህ:: ለተበደልከው ሁሉ ተስማሚ ሰበብ የሚሰጥህ ልጏም የለሽ ስሜት አለህ:: ከቁብ አለመቆጠርህን ረስተህ ፈገግ የምትልበት ፍለጋ ትማስናለህ ፤ ለህመምህ እንዲመችህ አርገህ አጋጣሚው ላይ ደንቅረህ ሀሴት ታደርጋለህ:: የምታወጣው ቃል ተቀባይ አጥቶ ካንተው ቢጋጭም ያንን ገደል-ማሚቶ አታምንም አዳማጬ ቃል አጣች ስትል ትደሰታለህ:: እምነት እየቀደድክ ተስፋህ መፍሰሱን ታውቃለህ ..... መጉደልህ ይሰማሀል ግን ምንም አታረግም:: አንዱ እንጂ ብቸኛው አለመሆንህን ታውቃለህ ግን ለአይንህ አማራጭ አትሰጠውም:: ትናደዳለህ ..... ታዝናለህ ..... ይከፋሀል ..... ከህልሞችህ ሳትደርስ ተጠልፈህ ትወድቃለህ .... አይሆነትን ትሆናለህ ኗሪ ነህና ይሄ ሁሉ ህይወትህ ነው:: በዛ ሰአት እስትፋስ ሁሉ ድምፅ ነው:: ድምፅ ሁሉ የልብ ቃል ነው:: ቃልም ግዙፍ ፀጥታ ይሆናል:: ፀጥታ ደግሞ ትልቁ መግባቢያ! ስታፈቅር ተሰብረሀል ግን ደህና ነህ:: Maki✍(that girl)🖤
Mostrar todo...
⛵️ህመም ያዘለ ፍቅር #ክፍል_ሀያ_ስምንት ...ከሆስፒታል ወጣ የገጪዉ ሚስት የተወሰነ ገንዘብ ሰጥታዋለች እያነከሰ በክራንች ተጠቅሞ ለመራመድ ቢሞክርም ሁሉም ነገር ልምድ ስለሚጠይቅ እና በክራንቹ ታግዞ መራመድ ስላልቻለ ኮንትራት ታክሲ ለመያዝ አስፓልት ዳር ቆሞ መጠበቅ ጀመረ መኪና ማግኘት ሳይችል ቀርቶ ጥቂት ስለቆመ ብቻ እግሮቹ ብርክ ብርክ አሉበት በቆመበት ላለመዉደቅ ሲታገል ከጎኑ የሰዉ እጅ ስለደገፈዉ ተመልሶ በመከራ ለመቆም ቻለ "ምን እየጠበቅክ ነዉ ወንድሜ አሞሀል መሰለኝ " ጥቁር በጥቁር የለበሰች ሴት ደገፍ አርጋ ይዛዉ በሀዘኔታ እግሮቹን እያየች "ምን ባክሽ ትራንስፗርት አጥቼ እኮ ነዉ " ክራንቹን ጠበቅ አረጎ እየያዘ ጠበቅ አርጋ የያዘችዉ የልጅቷ እጅ ከድጋፍ አልፎ ሰዉነቱን ጨምድዳ ስለያዘችዉ እየጨነቀዉ ልጅቷ የፊቱን ሁኔታ ስታይ እና እራሱን ችሎ መቆሙን ስታስተዉል ለቀቅ እያረገችዉ ፊት ለፊታቸዉ የቆመችዉን ቀይ ቀለም የተቀባች መኪና እየጠቆመችዉ "የምትፈልግበት ላደርስህ እችላለሁ" እንዲከተላት ምልክት እየሰጠችዉ የመኪናዉን በር በቀስታ ከፍታ እንዲገባ ጋበዘችዉ ፍፁም ጥቂት ካንገራገረ በኋላ እያመነታ ወደ መኪናዉ ዉስጥ ገብቶ ተቀመጠ ክራንቾቹን በእጆቹ አቅፎ እንደያዘ ልጅቷ የፍፁምን መግባት ስታስተዉል በሩን መዘጋቱን አረጋግጣ ወደ ሹፌር መግቢያ በር ዞራ ገብታ ከተቀመጠች በኋላ የት መሄድ እንደፈለገ ጠይቃዉ ስለነገራት የመኪናዉን ሞተር አስነስታ በነገራት አቅጣጫ መንዳት ጀመረች ፍፁም የልጅቷን መልካምነት እያስተዋለ በዚህ ዘመን ማን ሰዉ ያግዛል?ሲል እራሱን እየጠየቀ እና በልቡ እያመሰገናት በቀስታ አንገቱን አዙሮ መንገዷ ላይ ትኩረት አርጋ የምትነዳዉን ሴት አያት ከለበሰችዉ ጥቁር ልብስ እንዳለቀሰች ከሚያስታዉቁት አይኖቿ እና ከቀሉት ጉንጮቿ የሆነ ነገር ተረድቶ "ሀዘን ላይ ነሽ መሰለኝ" ሲል ለስለስ ባለ ድምፅ ጠየቃት "አዎ" የሚል አጭር መልስ ሰጥታዉ ፍፁም መጠየቅ እና ማፅናናት እየፈለገ ነገር ግን የነቤዛዊት ሰፈር ስለደረሱ እና መዉረድ ስላለበት እየተፀፀተ "በጣም አመሰግናለሁ አንቻንም ፈጣሪ ያፅናሽ" የሚል ቃል ከአፉ ወጥተዉ ከመኪናዋ ወርዶ ወደ እነቤዛዊት በር ጋር ቆሞ ማንኳኳት ሲጀምር ያደረሰችዉ መልካም ሴት መኪናዋን እያስጓራች አልፋዉ ከአይኑ እራቀች። ቤዛዊት እህቷ ላይ የመግደል ሙከራ ካረገች በኋላ ዶክተር መለሰ አባብሎ እና የህክምና ጥበብ ተጠቅሞ እሱ የከፈተዉ የግል ሆስፒታል ተኝታ እንድትታከም ከቤተሰቦቿ ጋር ተማክሮ ሁሉም ስለተስማሙ መታከም ጀምራለች። ብቻዋን በሆነች ቁጥር ግን ዶክተሩም አልተረዳላትም እንጂ ህመሟ ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ ነበር። ዶክተር መለሰ አብሯት ጥቂት ካዋራት እና መድሀኒት ዉጣ እንድትተኛ ካረጋት በኋላ መሻሻል እና ለዉጥ ስላላየባት ምን አይነት የተለየ ህክምና ሊሰጣት እና ልትድን እንደምትችል እያሰበ ቤዛዊት የተኛችበትን ክፍል ለቆ ወጣ ቤዛዊት የዶክተር መለሰን መዉጣት ስትመለከት አፍዋ ዉስጥ ሳትዉጠዉ የደበቀችዉን ኪኒን በእጇ ከአፏ እያወጣችዉ እና መሬት ላይ ወርዉራ ጥላዉ ብቻዋን ማዉራት እና መበሳጨት ጀመረች ፍፁምን ካየችዉ ሁለት ቀን እንዳለፋት አስታዉሳ ከአልጋዋ ዘላ ወርዳ በቀስታ እየተራመደች የክፍሏን በር ከፍታዉ አንገቷን አጮልቃ ተመለከተች ዶክተር መለሰ ከታማሚ ጋር ፊት ለፊቷ ቆሞ ያወራል እስዋን ታማሚዉ እያያት ቢሆንም ዶክተር መለሰ ጀርባዉን ሰጥቷት ስለቆመ ሊያያት አይችልም ያረገችዉ ነጠላ ጫማ ድምፅ እንዳይፈጥር እየተጠነቀቀች እና የግድግዳዉን ጠርዝ እየታከከች እያወራ የቆመዉን ዶክተር መለሰን አልፋዉ ወደ በሩ ከወጣች በኋላ መጠንቀቆን ትታ ስላመለጠችዉ እና በብልጠቷ እየተደሰተች ከግቢዉ በር ጨርሳ ልትወጣ ስትል የሀኪም ቤቱ ጥበቃ ፊቷ ቆሟ "አንቺ ባለፈዉ ከጋሼ መለሰ ጋር የመጣሽዉ ልጅ አደለሽ?" ብሎ ሲያፋጥጣት እየተናደደች እና ዘበኛዉን እንዴት ሊተዋት እንደሚችል ካሰበች በኋላ ሀሳብ ስለመጣላት እጆቿን ወደ ኪሷቿ ከታ "እቃ ልገዛ ነበር" አለችና ከኪሷ ያወጣችዉን የብር ኖቶች እያሳየችዉ ጥበቃዉ በጥርጣሬ እያያት "ጋሼ አንቺ እንድትወጪ የሚፈቅዱ አይመስለኝም ተከተይኝ እንጠይቃቸዉ እንጂማ አላሷጣሽም" እያለ ፊት ፊቷ እየተራመደ ተደብቃ ወደወጣችበት ሊያስገባት ሲሞክር ሀሳቧ እንዳልተሳካ ያወቀችዉ ቤዛዊት እያወራ የሚሄደዉን ጥበቃ ሳትከተል ክፍት ወደሆነዉ በር በቀስታ ሄዳ ከወጣች በኋላ ከአካባቢዉ እስክትርቅ መሮጧን ቀጠለች። ፍፁም ቤዛዊት ቤት ዉስጥ እንደሌለች እና የዶክተር መለሰ ሀኪም ቤት እንደሄደች ስለነገሩት ምን ሆና ይሆን በሚል ሀሳብ ተዉጦ እና ለመራመድ እንኳን እየታገለ ወደ ነገሩት ሀኪም ቤት ሄዶም ስላጣት እያዘነ ከተዘጋ ሳምንታት ወዳለፉት ወደ ተከራየዉ ቤት በሀሳብ ተዉጦ በቀስታ እየተራመደ ቤዛዊት የት ልትጠፋ እንደምትችል እያሰበ ቤቱ ደርሶ የበሩን መከፈት አይቶ እየተገረመ እና እየተደናገጠ ወደ ዉስጥ ሲዘልቅ መሄጃ ያጣችዉ ግራ የተጋባችዉ ቤዛዊት አልጋዉ ላይ ድብን ያለ እንቅልፍ ወስዷት ተኝታ አገኛት (ከሰዓታት በፊት) ቤዛዊት እሩጫዋን ገታ አርጋ የምትሄድበትን አሰበች ቤተሰቦቿ እንደማይፈልጓት ስለተሰማት ፍፁምን ፍለጋ ወደ ተኛበት ሆስፒታል ብታመራም ዛሬ እንደወጣ ስለነገሯት ወደ ቤቱ ሄዶ ይሆናል በማለት ነበር ወደ ፍፁም ቤት እንዳታጣዉ እየፀለየች የሄደችዉ ስትደርስ ቤቱ ዝግ ሆኖ አለመኖሩን ስታስተዉል ይመጣል በሚል ተስፉ በረንዳዉ ላይ ተቀምጣ ብዙ ስዓት ስለቆየች የፍፁም አከራይ ታዝበዋት እና ስለፍፁም መጥፋት አሳስቧቸዉ ከጠየቋት እና የሆነዉን ሁሉ ስትነግራቸዉ እና እጮኛዉ ነኝ ብላ ስለነገረቻቸዉ በእምነት ቤቱን ከፍተዉ ያስገቧት። ይቀጥላል... @fikrenakal @fikrenakal
Mostrar todo...
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.