NeoGenia Educational Consultancy ኒዮጂኒያ ኤጁኬሽናል ኮንሰልታንሲ
Ir al canal en Telegram
WE offer individual and small group tutoring to all grade level students. Students can get help with assignments, concepts, or essays, as well as help with general study strategies. Come in and see what tutoring can do for you! +251911 72 86 11
Mostrar más231
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días
Archivo de publicaciones
🙏ውድ የኒዮጂኒያ ኤጁኬሽናል ኮንሰልታንሲ ወላጆች🙏
👉የአዲሱ ካሪኩለም የተማሪዎች መማሪያ መፅሐፍት ሙሉ በሙሉ በመንግስት በኩል ተባዝተው እስኪሰራጩ ድረስ በወላጆች ጥያቄ መሠረት ልጆቻችሁን ማገዝ እንድትችሉ የመንግስት መጽሐፎችን በሶፍት ኮፒ ከዚህ በታች ባሉ የየክፍሎች የቴሌግራም ቻናሎች ያያያዝን መሆኑን እየገለጽን መጽሐፍቶቹ ታትመው ሲመጡ የምናሳውቃችሁ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
ማሳሰቢያ:- ወላጆች መጽሐፎቹን አውረደው ለልጆች ከመስጠት ባለፈ ልጆች ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በስልክ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚ በመሆን ከትምህርታቸው እንዳይርቁ በጥብቅ እንዲከታተሏቸው እናሳስባለን።
CLICK ON THE LINKS FOR THE NEW CURRICULUM BOOKS.
👇👇👇
ለ1ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 1: Resources
ለ2ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 2: Resources
ለ3ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 3: Resources
ለ4ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 4: Resources
ለ5ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 5: Resources
ለ6ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 6: Resources
ለ7ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 7: Resources
ለ8ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 8: Resources
ለ9ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 9: Resources
ለ10ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 10: Resources
ለ11ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 11: Resources
ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች | Grade 12: Resources
የ2016 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ግንቦት ወር ላይ እንዲሰጥ ከወዲሁ ዝግጅቶች እየተደረጉ ይገኛል።
የአሁኑ ፈተና ድብልቅ / ሃይብሪድ መሆኑን ከቀናት በፊት መግለጫ የሰጡት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።
ድብልቅ ፈተና ማለት ግማሹ ኦንላይን (የኢንተርኔት ችግር የሌለባቸው አካባቢዎች) ፤ የኢንተርኔት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ደግሞ ከዚህ ቀደም ሲሰጥ በነበረበት አካሄድ በወረቀት ነው የሚሰጠው።
ይህ የፈተና አሰጣጥ አካሄድ በዩኒቨርሲቲዎች ላይ ፣ በመንግሥት በጀት ፣ በትምህርት ቢሮዎች ላይ ጫናውን እንደሚቀንስ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ምንም እንኳን የመግዛት አቅም ባይኖረውም ለፈተናው የሚሆኑ #ታብሌቶችን ከመንግሥት ተቋማት ጋር በመነጋገር ለፈተናው ጊዜ በመውሰድ ፈተናውን በድብልቅ እንደሚሰጥ አመልክቷል።
የ2016 ዓ/ም ፈተና ድብልቅ በሆነ መንገድ እንዲሰጥ ከወዲሁ ዝግጅቶቹ እየተደረጉ ሲሆን የሶፍትዌር ስራው ከወዲሁ መጠናቀቁ ተገልጿል።
የዘንድሮውም ምዝገባ በኦንላይን ሲሆን፣ ተፈታኞች በአካል ተገኝተው ፎቶ እንዲነሱ ይደረጋል ፤ በዚህ ረገድ ቁጥጥሩ ጠበቅ እያለ ይሄዳል ተብሏል።
የተሻሉ የፈተና አዘጋጆች፣ ፈተናዎች እንዳይሰረቁ የሳይበር ጥበቃ፣ የደህንነት ካሜራዎች ፣ የተቋማት ትብብር (ኢንሳ፣ ፈተናዎች አገልግሎት) ፣ ጥንቃቄ የተሞላበት የፈተና ህትመት ዝግጅት ከዚህ ቀደሙም በተሻለ መልኩ ጠንካራ ስራ በጋራ እንደሚሰራ ትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።
የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች ከወዲሁ እራሳቸውን ለመመዘኛ ፈተናው ብቁ እና ዝግጁ እያደረጉ መሄድ ያለባቸው ሲሆን መምህራን፣ ወላጆች፣ መላው የትምህርት ማህበረሰብ ተማሪዎችን እያገዙ ለፈተናው እንዲዘጋጁ ማደርግ አለባቸው።
በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ገብተው ባለፉት ሁለት ብሄራዊ ፈተናዎች ማለትም በ2014 እና 2015 ከተፈተኑት አጠቃላይ ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዛ በላይ አምጥተው ያለፉት እጅግ ጥቂት ናቸው።
በ2014 ፈተና 896,520 ተማሪዎች ተፈትነው ያለፉት 30,034 ወይም 3.3 በመቶ ብቻ ሲሆኑ በ2015 ፈተና 845,099 ተማሪዎች ተፈትነው ማለፍ የቻሉት 27,267 ወይም 3.2 በመቶ ብቻ ናቸው።
በተለይ ፈተናው በየአካባቢው ካሉ ትምህርት ቤቶች ግቢ ውስጥ ወጥቶ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ መሰጠት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የተመዘገበው ውጤት ብዙሃኑን ያስዳነገጠ እንዲሁም የትምህርት ስርዓቱ ያለበትን አሳሳቢ የሚባል ደረጃ ያመላከተ ሆኗል።
ቀን 18/5/2015 ዓ.ም
ለ2014 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ውጤት ከሌሊቱ 5 ሰዓት ከ30 ጀምሮ ይፋ ይሆናል።
ለ2014 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ውጤት ሌሊቱ 5 ሰዓት ከ30 ጀምሮ ይፋ እንደሚሆን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ።
በዚህም ተፈታኞች ከዛሬ ሌሊቱ 5 ሰዓት ከ30 ጀምሮ በዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ፣ በ6284 አጭር የጽሑፍ መልዕክት መላኪያ ላይ የምዝግባ ቁጥራቸውን (Registration Number) ብቻ በመላክ ወይም በቴሌግራም https://t.me/eaesbot ማየት የሚችሉ መሆኑን ተገልጿል።
ማሳሰቢያ፡-
• ማንኛውም ቅሬታ ያላቸው ተፈታኞች በአካል መምጣት ሳያስፈልግ እስከ ጥር 26/2015 ዓ.ም ድረስ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዌብ ሳይት https://eaes.edu.et/ ላይ Compliant የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ማቅረብ ይችላሉ፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
You Tube: https://www.youtube.com/watch?v=TWkBGoeYCNQ...
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
