cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

طالب العلم

በአላህ ፍቃድ በዚህ ነፃ መድረክ ማንኛውም ሰው ከዲናችን ጋር ተያያዥ ጉዳዮችን መማርና ማስተማር ይችላል።የምናውቀውን በማሳወቅና የማናውቀውን በመማር ሁላችንም የበኩላችንን እንወጣ።በዋናነትም የሰለፊያ መሻይኾች ትምህርቶችንን እናስተላልፋለን። جزاكم الله خير ወደ ግሩፑ መቀላቀል የሚፈልግ @ebnumuslim01

Mostrar más
El país no está especificadoEl idioma no está especificadoLa categoría no está especificada
Publicaciones publicitarias
179
Suscriptores
Sin datos24 horas
Sin datos7 días
Sin datos30 días

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

የዙልሒጃ አስር ቀናቶች 〰〰〰〰〰〰〰〰 ♦️አዲስ ወቅታዊ ምክር 📝በነዚህ ውድ ቀናቶች፦ ▪️የሰዎች መዘናጋት ▪️ግንዛቤን ማስፋት ▪️ከረመዷን ይበልጣሉን? 【ክፍል፦ ①】 🏷 ኢንሻአላህ ይቀጥላል…… http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru
Mostrar todo...
① የዙልሂጃ 10 ውድ ቀናቶች.mp34.64 MB
Photo unavailableShow in Telegram
🍁አንድ ቀን ከምትወዷቸው ሰዎችጋ ጓደኝነታችሁ ካበቃ ፍቅራቸውን በልባቹህ ውስጥ አኑሩት! #ሚስጥራቸውንም,ታሪካቸውንም.. ደብቁላቸው! 🌸#ምክኒያቱም፦ ጓደኝነት ማለት #መልካም_ስነ_ምግባር ማለት ነው:: ✔️መልካምነት አብሮ በመኖር ውስጥ ብቻ ሳይሆን አብሮ ባለመኖር ውስጥም መልካም መሆን! ርቀውም ቀርበውም ያው መልካሞች'መልካም ናቸውና!! ↷⇣🌹⇣↷ https://t.me/Alselfiy
Mostrar todo...
📌ድብልቅልቁ የትምህርት ዓለም ዋይታ በእውነተኛው የኢስላም ብርሃን ሲፈታ📌 📝 ተከታታይ ፅሁፍ 👉ክፍል አንድ👈 بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيم ብዙ ወገኖች እንዲህ በማለት ይጠይቃሉ ፦ ግን እንዴት የወንድና የሴት መደባለቅ ወንጀል ሊሆን ይችላል❓❗ በመጀመሪያ ወንድም እህቶቼ አላህ ሐቅን የምናይበትና የምንቀበልበት ልባዊ ብርሃን ይስጠን !!! በማስከተልም አላህ ልዕለ ሃያሉ አምላክ ይህንን አስከፊ ድርጊት በመከልከል እንዲህ ይለናል ፦ {{ "وَإِذَا سَأَلْتُمُوهُنَّ مَتَاعًا فَاسْأَلُوهُنَّ مِنْ وَرَاءِ حِجَاب" }} { "ዕቃ (መዋስን) በጠየቃችኋቸው ጊዜ ከሒጃብ (ከግርዶሽ) ኋላ ሆናችሁ ጠይቋቸው።" } ውዱ የአላህ ነብይም ( ﷺ ) እንዲህ በማለት ያስጠነቅቁናል ፦ (( "عَنْ عُقْبَةَ بْنِ عَامِرٍ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ قَالَ إِيَّاكُمْ وَالدُّخُولَ عَلَى النِّسَاءِ فَقَالَ رَجُلٌ مِنْ الْأَنْصَارِ يَا رَسُولَ اللَّهِ أَفَرَأَيْتَ الْحَمْوَ قَالَ الْحَمْوُ الْمَوْتُ " )) (( " አደራችሁን "አጂነቢይ" (ለትዳር የተፈቀዱ ሴቶች) ባሉበት መግባትን ተጠንቀቁ። " )) በዚህም ጊዜ አንድ የመዲና ሰው " የባል ቅርብ ዘመድ ቢሆንስ? " በማለት ጠየቃቸው። እርሳቸውም :– (( " የባል ቅርብ ዘመድማ የባሰውን ሞት ነው። " )) በማለት የሴትና ወንድ መደባለቅ አስከፊ መዘዝ እንዳለው አመላከቱ። አሁንም ግልፅ አልሆነልንም አላህና መልዕክተኛው ለምንድን ነው❓ እንዲህ በከባዱ የከለከሉት ? የሚሉ ወገኖች አሉ❗ በመጀመሪያ ደረጃ ግልፅ ያልሆነልን ነገር ሁሉ ትክክል አይደለም ማለት አይደለም። ምክንያቱም ፦ አላህና መልዕክተኛው አንድን ፍርድ ወይም ውሳኔ ሲያሳልፉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የመተግበር ግዴታ አለብንና። ታላቁ አምላክ አላህም እንዲህ ይለናል፦ {{ " وَمَا كَانَ لِمُؤْمِنٍ وَلَا مُؤْمِنَةٍ إِذَا قَضَى اللَّهُ وَرَسُولُهُ أَمْرًا أَنْ يَكُونَ لَهُمُ الْخِيَرَةُ مِنْ أَمْرِهِمْ وَمَنْ يَعْصِ اللَّهَ وَرَسُولَهُ فَقَدْ ضَلَّ ضَلَالًا مُبِينًا" }} 【(الأحزاب (36)】 (( " አላህና መልዕክተኛው የሆነ ነገርን በፈረዱ ጊዜ ለወንድና ለሴት አማኞች በጉዳያቸው ላይ ምርጫ ሊኖራቸው አይገባም። አላህንና መልህክተኛውን የሚያምፅ በርግጥም ግልፅ የሆነ ጥመትን ጠሟል" )) 【አል– አሕዛብ (36)】 የአላህና የመልዕክተኛው ውሳኔ ውስጥ ጥልቅ የሆነ ጥበብ አለው። ስለዚህም ብዙ ጊዜ ለመቀበል እንቸገርና ስንልፈሰፈስ እንታያለን። ለዚህም ነው አላህ እንዲህ በማለት የእውቀትን ሚስጥር የነገረን ፦ {{ " وَمَا يَعْلَمُ تَأْوِيلَهُ إِلَّا اللَّهُ وَالرَّاسِخُونَ فِي الْعِلْمِ يَقُولُونَ آَمَنَّا بِهِ كُلٌّ مِنْ عِنْدِ رَبِّنَا وَمَا يَذَّكَّرُ إِلَّا أُولُو الْأَلْبَاب} 【 آل عمران (7) 】 (( " ትክክለኛውን ትርጉም አላህ ብቻ እንጂ ሌላ ማንም አያውቀውም። በዕውቀትም የጠለቁት በርሱ አምነናል ሁሉም ከጌታችን ዘንድ ነው ይላሉ። የአእምሮ ባልተቤቶች እንጂ ሌላው አይገሰጽም " )) አላህ ከተገሳጮች ያድርገን❗ ስለዚህም ነው፤ አላህ በወሰነው ውሳኔ ውስጥ ጥልቅ ጥበብ አለ የምንለው ፤ ስለሆነም አላህን ለመፍራት ቁርጠኛ እንሁን የቻልነውን ያህል ሁሉ ስለ እውነተኛው ‼ እደግመዋለሁ❗ ስለ እውነተኛው "ኢስላም" እንወቅ በማስከተልም እንደድንቆቹ ሰሐባዎች ሰምተናል እንታዘዛለን እንበል ! አላህ ይርዳን !!! እንግዲህ ወንድም እህቶቼ ከዚህም በበለጠ ምክንያቱ በተሰወረብንና ባላወቅነውም ጉዳይ ላይ አላህና መልክተኛውን መታዘዝ ግድ ከሆነብን ምነው ታዲያ❓ ምክንያቱ እጅግ በጣም ተብራርቶ በተነገረን የኢኽቲላጥ እና የአመፅ አይነቶች አይነት በአይነቱ በተለያዩ ማማለያዎች ቀርበውልን ቀን በቀን እየተጋትናቸው "ሰብር" ማድረጋችን ?! ሳንጎዳስ ቀርተን ይሆን ?! ወይስ እስልምናን ጠቅመንበት ነው ?! ወይንስ እንደኩፋሮች የማይቻለውን የአላህ ቅጣት አይመጣብንም ብለን ተማምነን ነው ❓❗ 👉 በትንሹም ቢሆን ነካ ላደረገን እንኳን ብርክ ብርክ ብሎን ፣ ድንፋታችን ቀዝቅዞ ፣ መላው ጠፍቶንና ግር ብሎን ገና ከዓዚዙ ሳንታረቅ ??? አሁንስ መቼ ተማርን❓ መቼ ተመከርን❓መቼስ ተቀጣን❓ እንደውም ይባስ ብለን ለዚህ ሁሉ ቅጣቱና ማስፈራሪያው ትልቁ መንስኤ የሆነውን የኢኽቲላጥ ትምህርት መቼ እንደ ሚጀምር በመጠባበቅ ጭንቀት ውጦናል። ብዙ ነገር እየሰማን ነዉ። የኛ ነገር ያሳዝናል መጨረሻችን ምን ይሆን? የአዛኞች ሁሉ አዛኝ የሆንከው አምላክ ሆይ እዘንልን ! ግን ይህ ሁሉ ሲሆን መካሪ ፣ ገሳጭ ፣ አስጠንቃቂ ጠፍቶ ነዉን ? እሱንስ ተውት ሆድ ይፍጀው ብለን ግን አንተወውም። ስለ እውነተኛና አስመሳይ መካሪዎች ልዩነት ከሆነ ደግሞ በአላህ ፈቃድ በቀጣይ በምናቀርበው ተከታታይ ጽሁፍ አላህ ግልፅ አድርጎ እንዲያሳየን በማለት እየለመንኩት… 👉 እስቲ እኔስ ለዚህ ፅሁፍ ምን አነሳሳኝ? 1ኛ· አላህ ጥራት የተገባው አምላክ (( " ከናንተ ውስጥ ወደ መልካም ነገር የሚጣሩና ከመጥፎ ነገር የሚከለክሉ ይኑሩ" )) በማለቱ እና ከስጋትም ለመዳን ስል … {{ " وَلْتَكُنْ مِنْكُمْ أُمَّةٌ يَدْعُونَ إِلَى الْخَيْرِ وَيَأْمُرُونَ بِالْمَعْرُوفِ وَيَنْهَوْنَ عَنِ الْمُنْكَرِ وَأُولَئِكَ هُمُ الْمُفْلِحُون " }} 【(آل عمران (104)】 (( " ከናንተ ወደ በጎ ነገር የሚጣሩ ከመጥፎ ነገር የሚከለክሉ ህዝቦች ይኑሩ የሚድኑ ህዝቦች እነኚህ ናቸው። " )) 【አል–ዒምራን (104)】 2ኛ· በተጨማሪም በመልካም ባለማዘዛቸውና ከመጥፎ ባለመከልከላቸው የተነሳ በነብያቶች አንደበት የተረገሙ በመሆናቸው … {{ " لُعِنَ الَّذِينَ كَفَرُوا مِنْ بَنِي إِسْرَائِيلَ عَلَى لِسَانِ دَاوُودَ وَعِيسَى ابْنِ مَرْيَمَ ذَلِكَ بِمَا عَصَوْا وَكَانُوا يَعْتَدُونَ} 【 (المائدة (78)】 (( " ከእስራኤል ልጆች እነዚያ የካዱት በዳውድና በመርየም ልጅ በዒሳ አንደበት ተረገሙ። ይህም ትዕዛዝን በመጣሳቸውና ወሰንን የሚያልፉ በመሆናቸው ነው። " )) 【አል ማኢዳ (78)】 3ኛ· የሰው ልጆች ከመልካም ነገር ርቀው በመጥፎ ነገር ላይ ሲዘወትሩ ለጥፋት የተዘጋጁ ህዝቦች እንደሚሆኑና አስከፊ ለሆኑ አደጋዎችም ተጋላጭ ስለሚሆኑ … አላህ ካለ በቀጣዩ የምናየው ይሆናል ፦ እኔም ለናሙና ያህል እንደ መግቢያ ይህን ካልኳችሁ ወደ ዋናው መልዕክቴ ልመለስና አንድ ብዬ ስጀምር ፦ 👉 የኢኽትላጥ ትምህርት የእውነት ጉዳት የለውምን ??? 👈 በአላህ ፍቃድ ክፍል ሁለት ይቀጥላል ፦ ✍Umu_teymiyah
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
🍁#ድቅድቅ ባለ ጨለማ ውስጥ ትልቅ ብርሃን አለ። ጨለማው ወንጀላችን ሲሆን ብርሃኑ ኢስቲግፋር ከልብ ተፀፅቶ መመለስ ከዛም #የአል_ረህማንን እዝነት ማግኘት ነው። 🍁አል_ረህማንም ወደ ብርሃን ሲጠራን #እዲህ_ይላል፦‹ባሪያዎቼ ሆይ! በየእለቱ በቀንና በሌሊት ወንጀል ትፈጽማላችሁ እኔ ሁሉንም ወንጀል እምራለሁ። እናም ወንጀላችንን ማረን በሉኝ እምራችኋለሁ።›› ↷⇣🌹⇣↷ https://t.me/Alselfiy
Mostrar todo...
ሱረቱል ካህፍ ቃሪዕ ኻሊድ አል-ጀሊል 👇👇👇👇👇 https://t.me/Alselfiy
Mostrar todo...
018.mp324.11 MB
Photo unavailableShow in Telegram
اللهم صل وسلم على نبينا وحبيبنا ورسولنا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين وسلم تسليما كثيرا صل الله عليه وسلم
Mostrar todo...
Photo unavailableShow in Telegram
ሰላምሽ እየናፈቀን ቀናቶች ሳምንቶች ወራቶቹ ወድመው አመቻቶች እየቆጠርን ዛሬም ነገም ተስፋ አለን ትድኛለሽ ብለን! ተስፋችንም ሁሉን አስተዳዳሪና አስተናባሪ ሁሉን ፈጣሪ የሰላም ባለቤት የሆነው የላቀው ጌታች አሏህ ነው። ያረብ....ታመና በጥና...! እንባችንም ደርቆ ሆዳችንም ነፍሮ ለብችኖም ደምቶ ቁስልን በቁስል ይዘን ይሄው ባንተው እዝነት ዛሬ ላይ ደረስን....ያረብ....ያሰላም.....ሰላምህን ያአሏህ እኛ በዳዮችን ይክሳል ብለንምንጮህበት አካል አይንረንም ሊኖረንም አይችልም إلا انت! አጥፊዎችን አጥፍተህ ለተበዲዮች ፍርድህን ሰላምህን ፍትህህን አውርድልን! ጌታችን ሆይ..! እንደ ሰው ልጅ ክፋትማ አንዳችም በምድእ ላይ ምትንቀሳቀስ ነገር ባችኖረች ነበር ....አንተ ግን ቻይ አዛኝ ነህና....እዘንልን!
Mostrar todo...
🚫ከሚሰግድ ሰው አጠገብ ሆነን አናውራ!🚫 አሏህን ከማክበር አንዱ የዲን ህግጋትን ማክበር ነው በተለይም አሏህን ከሰው ልጆች ጋር የሚያገናኝ የሆነውን ሰላትን ማክበር ለአሏህና ለዲኑ ያለንን ክብር ከሚያሳዩ ነገሮች መሃል አንዱ ነው‼️ ሰላት ከሚሰግድ ሰው አጠገብ ሆነን ድምጽን ጮኽ አድርጎ ማውራት የሰጋጁን ሃሳብ የሚሰርቅ ነገር ማድረግ ጌታውን ከሚያከብር ሰው የማይጠበቅ ተግባር ነው። ብዙዎቻችን እናውቃለን ግን እንተገብረውም! ብዙዎቻችን አዛን ሲባል ማለትና ማድረግ የሚኖርብንን እናውቃለን ግን. አናደርገውም። (إلا من رحيم ربي) አሏህ ይዘንልን ቀልባችንን የተገራች ቀልብ ያድርግልን አሚን! ↷⇣🌹⇣↷ https://t.me/Alselfiy https://t.me/Alselfiy
Mostrar todo...
በሰለፎች መንገድ

💎«رَبَّنَا آتِنَا مِن لَّدُنكَ رَحْمَةً وَهَيِّئْ لَنَا مِنْ أَمْرِنَا رَشَدًا ♻️« ጌታችን ሆይ! ከአንተ ዘንድ እዝነትን ስጠን፤ ለእኛም ከነገራችን ቅንን አዘጋጅልን‼️ ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ

https://t.me/Alselefiy

ለአስተያየትዎ

https://t.me/Alselefiygoldenislamicgroup

እንደ ታዘዝከው ቀጥ በል/በይ ! የሰው ልጂ እንደፈለገው ልቅና ገደብ አልባ መሆን የለበትም የታዘዘውን መታዘዝ የተከለከለውን መከልከል ያስፈልጋል ፡፡ በአንድ ነገር ላይ ከታዘዝን ወይም ከተከለከልን አሚን ብሎ መቀበልና ቀጥ ብሎ መተግበር ግዴታ ነው ፡፡ አላህ በተከበረው ቃሉ ምን ይለናል ፡ فَاسْتَقِمْ كَمَا أُمِرْتَ وَمَن تَابَ مَعَكَ وَلَا تَطْغَوْا ۚ إِنَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ እንደ ታዘዝከውም ቀጥ በል፡፡ ከአንተ ጋር ያመኑትም (ቀጥ ይበሉ)፡፡ ወሰንንም አትለፉ፤ እርሱ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነውና፡፡ ♻ ♻ ♻ https://t.me/Alselfiy
Mostrar todo...
በሰለፎች መንገድ

💎«رَبَّنَا آتِنَا مِن لَّدُنكَ رَحْمَةً وَهَيِّئْ لَنَا مِنْ أَمْرِنَا رَشَدًا ♻️« ጌታችን ሆይ! ከአንተ ዘንድ እዝነትን ስጠን፤ ለእኛም ከነገራችን ቅንን አዘጋጅልን‼️ ወደ ቻናላችን ይቀላቀሉ

https://t.me/Alselefiy

ለአስተያየትዎ

https://t.me/Alselefiygoldenislamicgroup

ክፍል 2 የሀጅ ና ኡምራ ት/ት ደርሶች👂👆https://t.me/ustazAbdalmajid
Mostrar todo...
AUD-20150906-WA0084.mp37.69 MB
AUD-20150908-WA0034.mp37.68 MB
Elige un Plan Diferente

Tu plan actual sólo permite el análisis de 5 canales. Para obtener más, elige otro plan.